Learning

Learning Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Learning, Digital creator, Bahir dar, Bahir Dar.

29/05/2025

አምሀራ
አም=ነፃ
ሀራ=ህዝብ
አምሀራ =ነፃ ህዝብ

ቅኔ የሆነ ታላቅ ህዝብ !!!
አማራ እኔም(individualistic)
እኛም(collectivist) ስነልቦና ያለው ማኅበረሰብ ነው፡፡ ይህ ሲባል የእኛ ስነልቦና በአብዛኛው የተላበስ ቢሆንም ሁል ጊዜ መጨፍለቅና በደቦ መወሰን አይስማማውም፡፡
እኔነትና እኛነት አይጣሉበትም፡፡ ይህም የሆነው ራስን ከማወቅና (self-awareness) ራሰን ከመግዛት (self-regulation) የመጣ ነው፡፡ ፈረንጆቹ self-actualization የሚሉት አይነት ትዎሪ አይደለም፡፡ ምናልባት ራስን ማወቅና (self-awareness) ራሰን ከመግዛት (self-regulation) ከዚያም በላይ ነው፡፡ በስልቦና ራስን ከማወቅ የበለጠ ምንም ትልቅ ነገር የለም፡፡ አማራ የእኔ (individualistic) ስነልቦና የተላበሰ መሆኑ ብዙ ጀግኖች ጎልተው እንዲወጡ ረድቶታል፡፡ አደንና ጦርናት ላይ በግለሰብ ደረጃ ጀብድ መስራት የተለመደ ነው፡፡ አጤ ቴዎድሮስ ውስጥ እኔ (individualistic) ስነልቦና መኖሩ አሸናፊ እንዲሆኑ ረድቶአቸዋል፡፡ ከሽፍትነት እስከ ታላቅ መሪነት 💪፡፡ አማራ የጠነከረ የእኛ (collectivist) ስነልቦና የተላበሰ በመሆኑ ደግሞ survive ከማድረግም አልፎ ሰፊ አገር ገንብቶ እንዲኖር ረድቶታል፡፡ አማራ collectivist ስለሆነ the Amhara concept of family is very broad, encompassing parents, children, grandparents, aunts, uncles, and cousins. እንዲያውም በአማርኛ cousins የሚባል ቃል የለም፤የእህት ልጅ፣ የወንድም ልጅ፤ ነው የሚባለው፡፡ እየሰፋ ሲሄድ አንድ የወሎ አማራ ሌላውን የወሎ አማራ የወንዜ ልጅ ወንድሜ ነው የሚለው፡፡ ጎንደር፤ ጎጃም፤ ሸዋም እንዲሁ ነው፡፡ ለምሳሌ የጎንደር አማራ ሌላውን የጎንደር አማራ ለሌላ ሰው ሲያስተዋውቀው የእኛ አገር ሰው ከማለት ይልቅ ወንድሜ ነው ይላል፡፡
…..
አማራ የኅልውና ጥያቄዎቹን (existential questions) የመለሰ ማኅበረሰብ በመሆኑ ጤነኛ ስነልቦና የተላበሰ ነው፡፡ ይህ ማለት ከየት መጣሁ፤ ዘሬ፣ ርስቴ (አገሬ) ወዴት ነው? ማን ፈጠረኝ? ምንድን ነኝ? የሚሉት ሁሉ በልቡ የተፃፉለት በመሆኑ አንድም ቀን አወዛግበውት አያውቁም፡፡ አማራ ፈጣሪውን ያወቀው በትምህርት አይደለም፤ በልቦናው እንጂ፡፡ የልቦና ጸንሰ ሐሳብ ፈረንጅ ውስጥ የለም፡፡ mind ልቦናን አይወክልም፡፡ ልቦና ረቂቅ ነው፡፡ አስተሳሰብን ደመነፍስን ኅሊናን ፍርድን ሁሉ ይመለከታል፡፡ አማራ ለኅሊናዊ የማይበጅ ወይንም ኅሊናው ያልፈቀደውን ነገር አድርግ ሲባል ‹‹ብሞት ይሻለኛል›› ይላል፡፡ ይህ በexistential ስነልቦና የጤንነት ምልክት ነው፡፡ ለኑሮውም ለሞቱም ምክንያት ያለው ሰው እጅግ ጤነኛ ነው፡፡
…..
አማራ ኃይሉ መንፈሳዊነቱ ላይ ነው (external agency) ፡፡ አጤ ቴዎድሮስ እኔ የክርስቶስ ባሪያ ይል ነበር፡፡ አማራ ለስኬቱ ክሬዲቱን በአብዛኛው ለፈጣሪው ነው የሚሰጠው፡፡ ለአማራ መንፈሳዊነቱንና ዓለማዊነቱን መለየት ከባድ ነው፡፡ ዓለማዊና መንፈሳዊ የሚባል ስብዕና የለም፡፡ አማራ መንፈሳዊም ዓለማዊም ነው፤አይጣሉበትም፡፡ መንፈሳዊነቱ ለኑሮው ለአመራር ጠቅሞታል እንጂ፡፡
…….
አማራ ወንድነት የባህሪው ነው፡፡ ወንድነት ፆታ የለውም፡፡ በእርግጥ በአብዛኛው ለወንዶች ጋር ያለ ስነልቦና ነው፡፡ ወንድነት brave, courage, warrior ማለት ነው፡፡ የአማራ ልጅ ከተወለደ ጀምሮ ወንድነትን እንዲላበስ socialize ይደረጋል፡፡ እናም እግዚአብሔር ሰውን ነፃ ይሆን ዘንድ ፈርዶበታል፤አማራ ደግሞ ልጁን ወንድ (brave, courage, warrior) ይሆን ዘንድ ይፈርድበታል፡፡
….
አማራ ሥልጡንነትና ዘመናይነት ስነልቦና የተላበሰ ነው፡፡ በትንሹ አንድም ቤቱ ውስጥ ያሉት እቃዎች አሰራር አጊያጊያጥ የልብሱ ጥልፍ(ዲዛይን) ማየት ይቻላል በትልቁ ደግሞ ይሉኝታውና በአንተና በእኔ መካከል ያለውን ድንበር የመለየት ችሎታው ትልቅ ያደርገዋል፡፡ አማራ ሥልጡንነት ስነልቦና የተላበሰ ነው ማለት ሥርዓት ያለውና በኑሮው ሁሉ ሥርዓትን የሰራ ማኅበረሰብ ነው ፡፡ አመጋገብ አለባበስ አረማመድ አነጋገር ልጅ አስተዳደግ ሕዝብ አስተዳደር ሁሉም ሥርዓት አለው፡፡ አንድን ማኅበረሰብ ሥልጡን ነው ዘመናዊ ነው ለማለት ትልቁና ዋናው መስፈርት ሥርዓት ነው፡፡ አደለም እንዴ? ነው፡፡ ሕንፃ መንገድ ቴክኖሎጂ ሕክምና እዚያ በኋላ ነው፡፡ ደግሞም አማራ እነዚህም አሉት፤አንዳንድ ደብተራዎቹና መሻሂዎች ዘመናዊ ሐኪምን ያስንቃሉ፡፡ ብዙ ማኅበረሰቦች እንደቀላል የሚያዩት የአማራን ይሉኝታ ነው፡፡ ይሉኝታ በስነልቦና- ይሉኝታ is the development of community –mindedness. አስምሩበት፡፡ ይሉኝታ የሰውነት የውኃ ልክ ነው ፡፡ (yilougnta is the absolute essential to the concept of personhood. It is the internalization of social rules and values that determine personhood.)
….
አማራ ማኅበረሰብ ውስጥ መማርና አለመማር በብሰለት ደረጃ ልዩነቱ አጨቃጫቂ ነው፡፤ ገበሬውም ሊቅነት አለው፡፡ ዋናው ሊቅነት የቃል ነው፡፡ አማራ ንግግሩ በጣም ሰምና ወርቅ ነው፡፡ ኃዘኑንም ደስታውንም በአሽሙር በቅኔ ይናገራል፡፡ አማራ ሌላው ኃይሉ የንግግር ችሎታው ላይ ነው፡፡ የአውሮፓ የintelligence theory ለአማራ አይሰራም፡፡ ለምሳሌ የሼህ ሁሴን ጅብሪልና አለቃ ገብረሃናን ሊቅነት ትዎራው አቃፊ አይደለም :: ሼህ ሁሴን ጅብሪል መፍረድ የጀመሩት ገና በሰባት ዓመታቸው እንደነበርና የሚናገሩትም መሬት ጠብ የማይል እንደነበር ይነገርላቸዋል። ወደር የማይገኝላቸው ትንቢት ተናጋሪ ነበሩ፡፡ በአውሮፓ አስተምሮ ግን ትንቢት መናገር የሊቅነት የአዋቂነት ማሳያ አይደለም፤እንዳውም የአዕምሮ መታወክ ነው፡፡
…..
አማራ ውስጥ ኃቀኝነት ትኅትናም አለ፡፡ እውነቱን ተናግሮ ከመሸበት ማደር ወይንም የተናገርኩት ከሚጠፋ የወለድሁት ይጥፍ እንዲል፡፡ አማራ ጥጋብን ይፈራል፡፡ ጥጋብ ሲባል በድንቁርና በማን አለብኝነት የሚመጣውን ነው፡፡
….
በአማራ ድኃና ኃብታም አንድም የተለያዩም ናቸው፡፡ አንድነታቸው ሁለቱም ኩሩነታቸው ነው፡፡ ኃብታምና ባለሥልጣን እንዲሁም ቄስና ሼህ በማኅበረሰቡ ውስጥ ትልቅ ቦታ አላቸው፡፡ በአብዛኛው አዎንታዊ የሄኑ የስነልቦና መገለጫዎች ይነገርላቸዋል፡፡ ድኃም ግን በማንነቱ ከኃብታም አያንስም፤በድኅነቱ የሚመጣበት አይወድም፤ከደረስህበት ‹‹እኔ ድኅነቴን ይዤ ለተቀመጥሁት ምን ሆነኝ ብለህ ነው አንተው›› ይልሃል፡፡ ኃብታም የድኃን ጉለበት ይበዘብዛል እንጂ ስነልቦናውን እንዲበዘብዘው ግን ብዙም አይፈቅድም፡፡
…………
አማራን ማጥናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ አንደኛ ብዙ ነገሮቹ ሲምቦሊክ (symbolic) ናቸው፡፡ ለምሳሌ፡- በማተቤ የመጣ ሲል በኃይማኖቱ ይመስልህና ግን እርሱን ብቻ አደለም ፡፡ ላመነበት ሁሉ ሟች መሆኑን ለማሳዬት ነው፡፡ ለምሳሌ፡- እናት የብዙ ነገሮች symbol ነች፡፡ በተለይ የአገርና የኃይማኖት፡፡ እናት መሬት ናት፡፡ መሬት እህል አብቃይ ናት፡፡ በአማራ ስነልቦና እናትንና የልጅን የስነልቦና ትስስር በቋንቋ መግለፅ ከባድ ነው፡፡ አማራ ‹‹እናትማ እናት ናት›› ነው የሚልህ ወይንም ‹‹የእናት ሞትና የድንጋይ መቀመጫ እያደር ይቆረቁራል›› ይልሃል፤ እናትን ማጣት ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ለመግለጽ፡፡
…………
አማራ ባለ ብዙ ታሪክ ሕዝብ ነው፡፡ ታሪክ ደግሞ ትናንት ብቻ አይደለም ተስፋም ነው፡፡ በስነልቦና ሁላችንም የትውስታ (የታሪክ) ውጤቶች ነን፡፡ ስንሞትም አንዳች የሚረባ ነገር ጥለን የምናልፈው ትውስታን ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ አንድ ማኅበረሰብ ታሪካም ከሆነ እውቀትን ከትናንት ከታሪኩ ይቀዳል፤ነገን ተስፋ ያደርጋል፡፡ ይህ አፍሪካውነትም ነው፤ሳንኮፋ( Sankofa) ይባላል፡፡ Sankofa is a Ghanaian symbol for remembering, to learn from the past. ስለሳንኮፋ ሌላ ጊዜ እመለስበታለው፡፡ ግን ብቸኛ መዳኛችንም ይመሰላኛል፡፡ Sankofa ነፃነትንም ያላብሳል፡፡ Sankofa = return to the past and fetch-ለሁሉም ለስነልቦናም ለፖለቲካም ይበጃል፡፡
………
በአማራ ስነልቦና ሰው አንዴ ተሰርቶ የሚያልቅ አይደለም፤እንዲያው ሙሉ ሰው የማይባልም ሰው አለ፡፡ ሰው ሙሉ ይሆን ዘንድ ስም ያስፈልገዋል፡፡ ይገረዛል፤ኃይማኖት ይኖረዋል፤ከዚያ ያገባል.፤…እያለ ሂደቱ ይቀጥላል፡፡ self-actualization በአማራ ስነልቦና እንደአብርሀም ማስሎው ትርክት አይደለም፡፡ አማራ ክብሩን ከኅልውናው፤ከአገሩ ሊያስቀድም ይችላል፡፡
መች ጀመርኩና እቀጥላለሁ።

26/05/2025

#በግዴታ ይሁንባችሁ ሳታነቡ እንዳታልፉ ።
#ቤተሰብ ሁናችሁ #በውርስ ገንዘብ #ለማትግባቡ ይሄን የሁለቱ ወንድማማቾች ታሪክ አንቡት!!
የእርሻ መሬት ወርሰው በጋራ የሚሰሩ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ!
አንድኛው ትዳር መስርቶ ትልቅ ቤተሰብ ሲኖረው ሁለተኛው ግን ብቻውን ነበር የሚኖረው፡!
ከዕለታት አንድ ቀን ወንድማማቾቹ ከቤተሰባቸው የወረሱትን ሀብትና ንብረት በመከፋፈል በየግላቸው ለመስራት
ይስማማሉ! ከዚያም ያለውንም ሀብት እኩል ተከፋፍለው የየግላቸው ኑሮ ይጀምራሉ፡፡
ወድያውኑ ግን ብቻውን የሚኖረው ወንድሙ ከራሱ ጋር መነጋገር ይጀምራል ያለውን #ሀብትና ትርፍ እኩል መከፋፈላችን አግባብ አልነበረም ብሎ ያስብ እና እኔ ብቻየን ነው የምኖረው የሚያስፈልገኝ ነገር በጣም ትንሽ ነው እርሱ ግን ብዙ የቤተሰብ ሀላፊነት አለበት በማለት ያስባል፡፡
እናም በጎተራው ካለው እህል አንድ ጆንያ የሚሆነውን ሁል ግዜ ማታ ማታ እየተደበቀ ወንድሙ ጎተራ ውስጥ ማስገባት ይጀምራል፡፡
በተመሳሳይ ግዜ ሚስትና ልጆች ያሉት ወንድምም በተመሳሳይ ሁኔታ ያስባል “ይህንን ሀብት እኩል መካፈል አልነበረብንም፡፡ እኔኮ
ትዳር አለኝ፡፡ ሚስቴና ልጆቼ ሁል ግዜ ከጎኔ በመሆናቸው ወደፊት በደንብ ይንከባከቡኛል፡፡ወንድሜ ግን ብቸኛ ነው፡፡ ወደፊት አጠገቡ ሆኖ የሚንከባከበው እንኳ የለውም” ሲል ያስባል፡፡
እርሱም እንደዚያኘው ወንድም በጎተራ ካለው እህል አንድ ጆንያ የሚሆነውን ሁል ግዜ ማታ ማታ እየተደበቀ ወንድሙ ጎተራ ውስጥ ማስገባት ይጀምራል፡፡ ወንድማማቾቹ በዚህ ሁኔታ ለብዙ ግዜ ኖሩ፡፡
ከብዙ ግዜ ብኋላ ግን ሁለቱንም አንድ ነገር ያስገርማቸው ጀመር፡፡ በጎተራቸው ውስጥ ያለው እህል መጠን እየቀነሰ አለመሄዱ ግራ ያጋባቸዋል፡፡ ሁለቱም የገጠማቸውን ያልተለመደ ነገር ለመመርመር በየግላቸው
እየጣሩ ሳለ ከእለታት አንድ ቀን ሌሊት ላይ የተለመደውን ተግባራቸውን ለመፈጸም እህል የተሞላበት ከረጢት እንደተሸከሙ
በድንገት ተገናኙ ። ምንም አይነት ቃላት ሳይለዋወጡ ሸክማቸውን መሬት ላይ በመጣል በፍቅር ተቃቅፈው አለቀሱ።
የመተሳሰብ ፍቅር በአይምሮህ አስበህ በአንደበትህ የምታወጣው ቃል ሳይሆን፣ በልብህ የሚንፈራገጥ የማይወለድ ፅንስ ነው።
የአንድ አባት ልጆች ነን!!
ምንጭ:- FACEBOOK

20/05/2025

ኢሳያስ አፈወርቂ ስለ አማራ


የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ

19/04/2025

ሊረዷችሁ የሚችሉ ያልተፃፉ 22 ማህበራዊ ህጎች፡

1. አንድን ሰው በተከታታይ ከሁለት ጊዜ በላይ አይደውሉ። ጥሪዎን ካላነሱ፣ የሚያከናውኑት አስፈላጊ ነገር እንዳለ ያስቡ፤

2. የተበደራችሁትን ገንዘብ፣ የተበደራችሁት ሰው ከማስታወሱ ወይም ከመጠየቁ በፊት መልሱ። ይህ ታማኝነትዎንና ባህሪዎን ያሳያል። ይህ በዣንጥላ፣ እስክሪብቶና የምሳ ዕቃ ላይም በተመሳሳይ መልኩ ይሠራል።

3. አንድ ሰው ምሳ/እራት ሲጋብዝዎት፣ በሜኑው ላይ ያለውን ውድ ምግብ በጭራሽ አይዘዙ።

4. ‘ኦህ፣ ገና አላገባህም/ሽም?’ ወይም ‘ልጆች የሉህም/ሽም’ ወይም ‘ለምን ቤት አልገዛህም/ሽም?’ ወይም ‘ለምን መኪና አትገዛም/ዢም?’ አይነት አግባብ ያልሆኑ ጥያቄዎችን አይጠይቁ። በፈጣሪያችሁ! ይህ የእናንተ ችግር አይደለም፤

5. ከኋላችሁ ለሚመጣው ሰው ሁል ጊዜ በሩን ክፈቱ። ወንድም ይሁን ሴት፣ ትልቅም ይሁን ትንሽ ለውጥ የለውም። በህዝብ ፊት ሰውን በአግባቡ በመያዝ ትንሽ አትሆኑም፤

6. ከጓደኛ ጋር ታክሲ ከወሰዱና እሱ/እሷ አሁን ከከፈለ/ች፣ በሚቀጥለው ጊዜ ለመክፈል ይሞክሩ፤

7. የተለያዩ አስተያየቶችን አክብሩ። ለእናንተ 6 የሆነው ነገር በተቃራኒ ላለ ሰው 9 ሆኖ እንደሚታይ አስታውሱ። በተጨማሪም፣ ሁለተኛ አስተያየት ለአማራጭ ጥሩ ነው፤

8. ሰዎች ሲያወሩ በጭራሽ አያቋርጧቸው። ሀሳባቸውን ገልጸው እንዲጨርሱ ፍቀዱላቸው። 'ሁሉን ስማ፣ ሁሉን አጣራ' እንደሚባለው፤

9 . አንድን ሰው ብትቀልዱበትና እሱ በቀልዱ እየተደሰተበት ካልሆነ ወዲያውኑ አቁሙ፤ ዳግመኛም አታድርጉት። ይህን መቀጠል ግዴለሽ መሆንዎን ያሳያል፤

10 . አንድ ሰው ሲረዳችሁ “አመሰግናለሁ” ይበሉ።

11. በአደባባይ አመስግኑ። በግል ተቹ፤

12. በአንድ ሰው የሰውነት ክብደት ላይ አስተያየት ለመስጠት የሚያበቃ ምንም ምክንያት የለም ማለት ይቻላል። ዝም ብለው፣ “በጣም ታምራለህ/ያምርብሻል” ይበሉ። ስለ ክብደት መቀነስ ማውራት ከፈለጉ፣ እነሱ ራሳቸው ያነሱታል፤

13. አንድ ሰው በስልካቸው ላይ ፎቶ ሲያሳያችሁ፣ ወደ ግራ ወይም ወደ ቀኝ አታንሸራትቱ። ቀጥሎ ምን ሊኖር እንደሚችል አታውቁም፤

14. የስራ ባልደረባችሁ የዶክተር ቀጠሮ እንዳለው/ላት ከነገረዎት/ች፣ ለምን እንደሆነ አይጠይቁ፣ ዝም ብለው "ደህና እንደምትሆን/ኚ ተስፋ አደርጋለሁ" ይበሉ። የግል ህመማቸውን እንዲነግሯችሁ በሚያስገድድ አላስፈላጊ ሁኔታ ውስጥ አታስገቧቸው። እንዲያውቁ ከፈለጉ፣ ያለ የእርስዎ ጠያቂነት ያደርጉታል፤

15. የጽዳት ሰራተኛውን እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው (CEO) በተመሳሳይ አክብሮት ይያዙ። ከእናንተ በታች ላለ ሰው ምን ያህል ባለጌ መሆን እንደምትችሉ በማሳየት ማንንም አታስደንቁም፤ ነገር ግን በአክብሮት የምትይዟቸው ከሆነ ሰዎች ያስተውላሉ፤

16. አንድ ሰው በቀጥታ እያናገረዎት ከሆነ፣ ስልክዎን ማፍጠጥ የትህትና የጎደለው ነው፤

17. እስካልተጠየቁ ድረስ በጭራሽ ምክር አይስጡ፤

18. ከረጅም ጊዜ በኋላ ከአንድ ሰው ጋር ሲገናኙ፣ እነሱ ስለእሱ ማውራት ካልፈለጉ በስተቀር፣ ስለ እድሜያቸውና ደሞዛቸው አይጠይቋቸው፤

19. ነገሩ በቀጥታ የማይመለከታችሁ ከሆነ በራሳችሁ ጉዳይ ላይ አተኩሩ - ዝም ብላችሁ ጣልቃ አትግቡ፤

20. መንገድ ላይ ከየትኛውም ሰው ጋር እያወሩ ከሆነ የፀሀይ መነፅርዎን ያውልቁ። ይህ የአክብሮት ምልክት ነው። ከዚህም በላይ፣ የአይን ለአይን ግንኙነት እንደ ንግግራችሁ ሁሉ አስፈላጊ ነው፤

21 . በድሆች መካከል ስለ ሀብታችሁ በጭራሽ አታውሩ። በተመሳሳይ፣ ልጅ በሌላቸው ሰዎች መካከል ስለ ልጆቻችሁ አታውሩ።

22 . ጥሩ መልዕክት ካነበቡ በኋላ "ስለመልዕክቱ አመሰግናለሁ" ለማለት ይሞክሩ።

ማድነቅ/ማመስገን የሌላችሁን ነገር ለማግኘት በጣም ቀላሉ መንገድ ነው።

እወዳችኋለሁ !

ተዋነይ - Tewanay

19/04/2025

“ሰውን በገንዘብ የሚሸጥ ትውልድ ይሁዳን ማማት አይችልም” ብጹዕ አቡነ አብርሃም

የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ስቅለት በባሕር ዳር ከተማ ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ታስቦ ውሏል፡፡

በበዓሉ ላይ ትምህርተ ወንጌል የሰጡት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ አብርሃም በዓለ ስቅለት የማይሞተው የሞተበት፤ በሞቱ ሞትን የገደለበት፤ ለሰው ልጆች ነጻነትን ያወጀበት፤ የታሰሩት የተፈቱበት፤ የራቁ የቀረቡበት፤ የሰው ልጅ ጥንተ ጠላት ዲያቢሎስ የታሰረበት እና የወደቀበት ነው ብለዋል፡፡

ሰዎች ለገንዘብ ሲገዙ የማያደርጉት የለም ያሉት ብጹዕነታቸው ጻድቁን ያስገድላሉ፤ ንጹሕ ደምም ያፈሳሉ ነው ያሉት፡፡ ሰዎች ለእግዚአብሔር ሲገዙ ፍቅርን እና ርህራሄን ገንዘባቸው ያደረጋሉ ብለዋል፡፡

ባላቸው የተቸገረን ይረዱበታል፤ የሌላ አይመኙም፤ በተሰጣቸው እና ባላቸው ይጠቀሙበታል፤ የተራበውን ይመግቡበታል፤ የተራቆተውን ያለብሱበታል ነው ያሉት፡፡ ይሁዳ ከገንዘብ ፍቅሩ የተነሳ ጌታውን አሳልፎ መስጠቱን ገልጸዋል፡፡

ይሁዳ ጌታውን አሳልፎ ከሰጠ በኋላ ተጸጽቶ፤ ንፁሑን አሳልፌ ሰጥቻለሁ፤ በድያለሁ ብሏል ያሉት ብጹዕነታቸው ጊዜ ካለፈበት በኋላ ጸጸት መልካም አይደለም ብለዋል፡፡

ንስሐ ጊዜው ሳያልፍ ነው፤ የንስሐ ጊዜ ዛሬ ነው፤ የጸጸት ሰዓት ዛሬ ነው፤ ሁሉ ነገር ካፈ በኋላ ጸጸት ትርጉም የለሽ ነው፤ በጊዜው ካልተጸጸቱ ዋጋ የለውም ነው ያሉት፡፡

ጻድቅን አሳልፎ መሰጥተን ለምንም እንደማይጠቅም የይሁዳ ድርጊት ያስተምራል ብለዋል፡፡ በአላስፈላጊ ምኞት ሰክሮ የሚሮጥን፤ በንጹሐን ደም ተሸጋግሮ ባለሀብት ለመኾን የሚጥር ሰው ቢኖር እርባና እንደሌለው ከይሁዳ ይማር ነው ያሉት፡፡

ሁላችንም በድለናል፤ አጥፍተናል፣ በድያለሁ ብለን መጸጸት፤ ንስሐ መግባት አለብን ብለዋል በመልዕክታቸው፡፡

እንደ ይሁዳ ሁሉ ዛሬም የንፁሕ ደም የሚያፈስሱ፤ ንጹሕን አሳልፈው የሚሰጡ፤ እውነተኛውን ጻድቁን የሚያስገደሉትን ኢትዮጵያ መታቀፏን ገልጸዋል፡፡

ንጹሕ ደም ማፍሰስ፤ ጻድቁን አሳልፎ መስጠት ምንም እንደማይጠቅም ከይሁዳ እንማር፤ በደላችንን አምነን አምለካችን ኾይ ማረን እንበለው ብለዋል፡፡

ይሁዳ ለራሱ ቢጎዳም ለእኛ ግን አስተምሮናል ነው ያሉት፡፡ እኛ ከይሁዳ መሻል አለብን፤ ዛሬ ላይ እንደ ይሁዳ ሰው የሚሸጥበት ዘመን ደርሰናል፤ "ሰውን በገንዘብ የሚሸጥ ትውልድ ይሁዳን ማማት አይችልም" ብለዋል። ከይሁዳ የተሻለ ትውልድ አልተገኘም፤ ከልብ ጸጸት የሌለበት፤ የከንፈር ብቻ ጽድቅ ያለበት ዘመን ነው ብለዋል፡፡

ሕሊናቸውን ለእግዚአብሔር የተሰጡ፤ ከዓለም የተገለሉ፣ ደጋግ ሰዎች ስላሉ በቸርነቱ እንኖራለን ነው ያሉት፡፡

በድያለሁ የሚለውን እንመን ያሉት ብጹዕነታቸው አምላክ በድለነው ሳለ ለእኛ መከራ ተቀብሏል፤ እኛ ግን በድለንም በድለናል አንልም ብለዋል፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ግርጌ እናት ሰጥቶናል፤ ያለ እናት አልተወንም ነው ያሉት፡፡ ስለ ሰላም እንጸልይ፤ ስለ ሀገራችን እንጸልይ፤ ክርስቲያን ስለ ዓለም ሁሉ ይጸልያልና ስለ ዓለም ሁሉ እንጸልይ፤ የተፈናቀሉትን እንዲመለሱ፤ ሰላም እንዲነግስ፤ ንጹሕ ደም መፍሰስ በቃ እንዲለን ተግተን እንጸልይ ብለዋል በመልዕክታቸው፡፡

Via: አሚኮ

01/04/2025
09/11/2020

happy

Address

Bahir Dar
Bahir Dar
BDU

Telephone

+251921430163

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Learning posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share