አልጀዚራ All jezira

  • Home
  • አልጀዚራ All jezira

አልጀዚራ All jezira አለማቀፋዊ እና የተመረጡ ሀገራዊ መረጃዎች ይቀርቡበታል።

ዮርዳኖስ ለፍልስጤማውያን እርዳታን መላኳ ተሰማ።   ➯➯➯➯➯አልጀዢራዮርዳኖስ በጋዛ የረሃብ አደጋ እየጨመረ ወደመጣበት የጋዛ ሰርጥ አካባቢ የነብስ አድን እርዳታ በመላክና ለፍልስጤማዉያን ፈጥ...
25/07/2025

ዮርዳኖስ ለፍልስጤማውያን እርዳታን መላኳ ተሰማ።

➯➯➯➯➯አልጀዢራ

ዮርዳኖስ በጋዛ የረሃብ አደጋ እየጨመረ ወደመጣበት የጋዛ ሰርጥ አካባቢ የነብስ አድን እርዳታ በመላክና ለፍልስጤማዉያን ፈጥኖ በመድረስ ቀዳሚዋ ሀገር መሆኗ ተሰማ ።

በጆርዳን ሃሽሚት በጎ አድራጎት ድርጅት (JHCO) ከአለም ሴንትራል ኩሽና እና ከአለም የምግብ ፕሮግራም ጋር በመተባበር የተላከው የእርዳታ ኮንቮይ ሃሙስ እለት ከአማን ተነስቶ ወደስፍራው መላኩን የመንግስት ቃል አቀባይ መሀመድ ሞማኒ ተናግረዋል።

ሞማኒ ለዮርዳኖስ ሮያ የዜና ጣቢያ በሰጠው መግለጫ ምንም እንኳን መሰናክሎች እና ተግዳሮቶች ቢኖሩም ዮርዳኖስ "እርዳታን በማስጀመር እና በመላክ ከመጀመሪያዎቹ መካከል በመሆኗ ኩራት ይሰማታል" ብሏል።
ባለፉት 10 ቀናት ውስጥ 147 የጭነት መኪናዎች የተውጣጡ አምስት ኮንቮይዎች ወደ ጋዛ መላካቸውን የገለፁት ሚኒስተሩ በዚህ ዙር 50 የጭነት መኪና ኮንቮይ ዱቄት፣ እህል፣ ዘይት እና የህጻናት ፎርሙላዎችን ጨምሮ አስፈላጊ የምግብ ምርቶችን መያዙን ገልፀዋል ።
የዮርዳኖስ የዜና ወኪል እንደገለጸው እርዳታን ለማድረስ የሚደረገው ጥረት በእስራኤል ድንበር ላይ ረጅም መጓተት እንደገጠመው እና እርዳታውን ለመቀበል ወደ መሻገሪያ በሚመጡት ተስፋ የቆረጡ ሲቪሎች ላይ የእስራኤል ወታደሮች በቀጥታ ጥይቶች ይተኩሳሉ ብሏል።

የዮርዳኖስ መንግሥቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተጨማሪ የእርዳታ መኪናዎችን ወደ ጋዛ ለመላክ ዝግጁ ብትሆንም ነገር ግን እስራኤል ፍቃደኛ አለመሆኗን የገለፁ ሲሆን “የእስራኤል መሰናክሎች ጋዛ ላይ ለመድረስ ቀዳሚ እንቅፋት ሆነው ቀጥለዋል” በማለት የበጎ አድራጎት ድርጅቱ ለተጨማሪ እርዳታ ግፊት ለማድረግ “ሁሉንም እድሎች ” እንደሚጠቀም ተናግሯል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በጋዛ ያለው ሰብአዊ ቀዉስ መቀጠሉን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ገልጿል ደ
እንደ ተቋሙ ገለፃ ከሆነ በግንቦት ወር በዩናይትድ ስቴትስ እና በእስራኤል የሚደገፈው የጋዛ ሰብአዊ ፋውንዴሽን ኦፕሬሽንን ከተቆጣጠረ በኋላ የእስራኤል ወታደሮች ምግብ ለማግኘት ሲሉ ከ1,000 በላይ ፍልስጤማውያንን መግደላቸውን በዚህ ሳምንት ተናግሯል።

➯አልጀዚራ

ቱርክ አዲስ ቴክኖሎጂ ለአለም አስተዋወቀች !    ➯➯➯➯➯አል ጀዚራ ቱርክ በጦር ሜዳ ላይ የሚደርሰውን የድሮን ስጋቶችን ለመዋጋት ለመከላከልና ለማክሸፍ የሚያስችል አልካ-ካፕላን የተባለውን ...
24/07/2025

ቱርክ አዲስ ቴክኖሎጂ ለአለም አስተዋወቀች !

➯➯➯➯➯አል ጀዚራ

ቱርክ በጦር ሜዳ ላይ የሚደርሰውን የድሮን ስጋቶችን ለመዋጋት ለመከላከልና ለማክሸፍ የሚያስችል አልካ-ካፕላን የተባለውን በቴክኖሎጂ የረቀቀ ተሽከርካሪ አስተዋወቀች ።

ይህ በአይነቱ የመጀመሪያው የተባለው ከአየር፣ ከመንገድ ዳር የሚደርሱ ቦምቦች፣ ፈንጂዎች፣ እና ያልተፈነዱ ቦምቦች በውጊያ ዞኖች የሚመጡ ስጋቶችን ለማስወገድ ይረዳል የተባለው ተሽከርካሪ አንካራ ዘመናዊ ቴክኖሎጅዎችን የደረሰችበትን ልህቀት ያሳያል ተብሏል ።

አለም አሁን እየተጠቀመባቸዉ ካለዉ የአየር መከላከያ ዘዴዎች ይልቅ ድሮኖችን፣ ሄሊኮፕተሮችን እና ሌሎች የበረራ መሳሪያዎችን ለማጥቃት ኤሌክትሮማግኔቲክ መጨናነቅ እና ጠንካራ ሌዘርን ይጠቀማል የተባለው ይህ ተሽከርካሪ የአየር ላይ ስጋቶችን ለማስወገድ እንደሚያስችል ተነግሯል ።

በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ ክትትል እና የጠላት ማስጠንቀቂያዎችን መለየትን እንደሚችል የተነገረለት መኪና የላቀ መመሪያ ቴክኖሎጂዎችን የሚጠቀሙ ከራዳር ዉጭ የሆኑ ሰዉ አልባ ድሮኖች ፈንጂዎችን በፍጥነት ለማወቅ እና ለማስወገድ የሚያስችሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙለት ሲሆን የከተማ ቦታዎችን፣ ክፍት ቦታዎችን እና ኮንቮይዎችን ለመጠበቅ ሁለገብ በሆነ መንገድ ሊሰማራ ተገልጿል ።

ራስን መከላከል የሚያስችሉ የኃይል ስርዓቶች ፍላጎት በአለም አቀፍ ደረጃ እያደገ ሲሄድ፣ ቱርክ ራሷን በዚህ የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ለመወዳደር እያዘጋጀች ነው።

➯አል ጀዚራ

ኢራን ከእስራኤል ጋር ለሚደረግ ጦርነት ዝግጁ ነች፤ የኒውክሌር ፕሮግራሟንም አታቆምም ሲሉ ፕሬዝዳንት ፔዜሽኪያን ተናገሩ፡፡የኢራኑ ፕሬዝዳንት ከአልጀዚራ ጋር በነበራቸው ቆይታ ቴህራን የዩራኒየ...
23/07/2025

ኢራን ከእስራኤል ጋር ለሚደረግ ጦርነት ዝግጁ ነች፤ የኒውክሌር ፕሮግራሟንም አታቆምም ሲሉ ፕሬዝዳንት ፔዜሽኪያን ተናገሩ፡፡

የኢራኑ ፕሬዝዳንት ከአልጀዚራ ጋር በነበራቸው ቆይታ ቴህራን የዩራኒየም ማበልፀግ ፕሮግራሟን እንደምትቀጥል አስታውቀዋል፡፡

የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ሀገራቸው እስራኤል ለምትከፍትባት ማንኛውም ጦርነት ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል፡፡

በሀገራቱ መካከል በተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ብዙም ተስፋ እንደሌላቸው በመግለጽ፤ቴህራን ለሰላማዊ ዓላማ የጀመረችውን የኒውክሌር ፕሮግራም ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል፡፡

ይህ አስተያየት የመጣው ምዕራባውያን ሀገራት ከግጭቱ በኋላ ስለ ኢራን የኒውክሌር ምኞት መፍትሄ እንፈልጋለን ባሉበት ወቅት ሲሆን፤ በኒውክሌር ተቋማት ላይ የደረሰው ጥቃት ዋሽንግተን ከምትለው ያነሰ ጉዳት ማድረሱ እየተዘገበ ባለበት ወቅት ነው፡፡

➯➯➯➯➯አል ጀዚራ

ፔዜሽኪያን ለአልጀዚራ እንደተናገሩት ለማንኛውም አዲስ የእስራኤል ወታደራዊ እርምጃ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነን፤ የጦር ኃይላችንም በድጋሚ ወደ እስራኤል ለመግባት ዝግጁ ነው ብለዋል፡፡

ኢራን የ12 ቀኑን ጦርነት ያስቆመው የተኩስ አቁም ስምምነት ይዘልቃል ብላ እንደማታምንም ተናግረዋል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ‹‹በጣም ብሩህ ተስፋ የለንም››ያሉት ፔዜሽኪያን ለዚህ ነው ለማንኛውም ሊከሰት ለሚችል ሁኔታ እና ለማንኛውም ምላሽ ራሳችንን ያዘጋጀነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

እስራኤል ጎድታናለች፤ እኛም ጎድተናታል፡፡ ከባድ ድብደባ አድርሳብናለች፤ እኛም በጥልቅ መትተናታል፤ ነገር ግን ኪሳራዋን እየደበቀች ነው ብለዋል፡፡

የእስራኤል ጥቃቶች ግንባር ቀደም ወታደራዊ ሰዎችን እና የኒውክሌር ሳይንቲስቶችን ከመግደል እና የኒውክሌር ተቋማትን ከማውደም ባለፈ የኢራንን የሥልጣን ተዋረድ ለማጥፋት ያለመ ነበር ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ነገር ግን ሙሉ በሙሉ ይህን የማድረግ ዕቅዳቸዉ ከሽፏል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በሰኔ 24 ከተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት በፊት በኢራን አብዛኞቹ ሰላማዊ የሆኑ ከ9መቶ በላይ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ፤ በእስራኤል በኩል ደግሞ ቢያንስ 28 ሰዎች ተገድለዋል።

➯አልጀዚራ

በአውሮፓ የሚገኙ 25 ሀገራት በጋዛ ያለው ጦርነት እንዲያበቃ ጥሪ አቀረቡ➯➯➯➯➯አል ጀዚራ ብሪታንያና ፈረንሳይን ጨምሮ 25 የአውሮፓ ሀገራት ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ በጋዛ ያለው ጦርነት እን...
22/07/2025

በአውሮፓ የሚገኙ 25 ሀገራት በጋዛ ያለው ጦርነት እንዲያበቃ ጥሪ አቀረቡ

➯➯➯➯➯አል ጀዚራ

ብሪታንያና ፈረንሳይን ጨምሮ 25 የአውሮፓ ሀገራት ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ በጋዛ ያለው ጦርነት እንዲያበቃና እስራኤልም ዓለም አቀፍ ህግን ማክበር አንዳለባት አሳስበዋል።

የአውስትራሊያ፣ የካናዳና የጃፓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች “በጋዛ በንጹሐን ላይ የሚደርሰው ስቃይና ለዜጎች የሚደርሰው የሰብአዊ ርዳታም ተገቢነት የጎደለው ነው፣ ንጹሀን ዜጎች መገደላቸውን በመግለጫቸው አውግዘዋል።

እስራኤል ለህዝብ የሚደረገውን አስፈላጊ የሆነውን ሰብአዊ እርዳታ መከልከሏ ተቀባይነት የለውም፣ በአለም አቀፍ የሰብአዊ ህግ መሰረት ግዴታዋን መወጣት አለባት” ሲሉ አመላክተዋል።

መግለጫው “የእስራኤል የእርዳታ አሰጣጥ የጋዛን ህዝብ ሰብአዊ ክብራቸውን የሚነጥቅ ነው” ብሏል።

መግለጫውን የፈረሙት የ20 የአውሮፓ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እንዲሁም ካናዳ፣ አውስትራሊያና ኒውዚላንድ፣ የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽነር ናቸው።አሜሪካና ጀርመን በመግለጫው ላይ አልፈረሙም ተብሏል።

መግለጫውን የፈረሙት ሀገራት በአስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል። ለዘላቂ ሰላም እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

ሩሲያ እና ኢራን በካስፒያን ባህር ላይ ለ3 ቀናት የጋራ ልምምድ ሊያደርጉ ነው እንደሆነ ተነገረCASAREX 2025 በሚል የኮድ ስም በሚደረገው በዚህ ልምምድ የኢራን ባህር ሃይል፣የ IRGC ...
22/07/2025

ሩሲያ እና ኢራን በካስፒያን ባህር ላይ ለ3 ቀናት የጋራ ልምምድ ሊያደርጉ ነው እንደሆነ ተነገረ

CASAREX 2025 በሚል የኮድ ስም በሚደረገው በዚህ ልምምድ የኢራን ባህር ሃይል፣የ IRGC ባህር ሃይል፣የኢራን ኮማንዶዎች እና የሩሲያ ባህር ሃይል የሚሳተፉ ሲሆን የቀጠናው ሃገራትም በተመልካችነት ይታደማሉ ተብሏል።

➯አልጀዚራ

ኢራን በሁለት ሳምንት ውስጥ ኒውክሌር መታጠቅ ትችላለች ➯➯➯➯➯የኢራን መሪ አያቶላ አሊኻሚኔ ፈቃድ ከሰጡ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ መታጠቅ እንደምትችል የዋይት ሀ...
22/07/2025

ኢራን በሁለት ሳምንት ውስጥ ኒውክሌር መታጠቅ ትችላለች

➯➯➯➯➯

የኢራን መሪ አያቶላ አሊኻሚኔ ፈቃድ ከሰጡ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ መታጠቅ እንደምትችል የዋይት ሀውስ የፕሬስ ሴክሬታሪያት ካሮሊን ሌቪት አስታወቀ፡፡

የዋይት ሀውስ የፕሬስ ሴክሬታሪ ካሮሊን ሌቪት እንደገለጹት፣ "በጣም ግልፅ እንሁን፣ ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያን ለማግኘት የሚያስፈልጋት ሁሉ አላት" ይህንን ለማድረግ የጠቅላይ መሪው ውሳኔ ብቻ ነው የሚያስፈልጋቸው ብለዋል።

"የኒኩሌር መሳሪያ ለመታጠቅ ሁለት ሳምንታት ይወስዳል ያሉት ካሮሊን፣ ይህም ጉዳይ በእስራኤል ላይ ብቻ ሳይሆን በአሜሪካና በመላው አለም ላይ ስጋት ይፈጥራል" ብለዋል።

የቀድሞው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ኢራንን ለኒውክሌር ጦር መሳሪያ አስፈላጊ የሆነውን የፋይሲሌል ቁስ ለማግኘት 90 በመቶ ንፁህ የሆነ በቂ ዩራኒየም ለማበልጸግ ከአንድ እስከ ሁለት ሳምንታት እንደሚፈጅ መናገራቸው አይዘነጋ ሲል ኤቢሲ ዘግቧል።

በመጋቢት ወር የብሄራዊ መረጃ ዳይሬክተር ቱልሲ ጋባርድ የኢራናውያን የኒውክሌር ቦምብ "አይገነቡም" የሚል መደምደሚያ ላይ እንደደረሱና የበላይ መሪው እስካሁን አንድ እንዲገነባ አልፈቀደም ሲሉ መስክረዋል ብሏል።

➯አልጀዚራ

20/07/2025

የጋዛ ዜጎች በረሀብ እያለቁ ነው።
➯➯➯➯➯
በጋዛ በዛሬው ዕለት ከ80 በላይ ህጻናት በምግብ እጥረት ምክንያት ሞተዋል።

➯አል ጀዚራ

ኢራን ለቀጣዩ ፍልሚያ ዝግጅት ለማድረግ ከሩሲያ ጋር ውይይት እያደረገች ነው።     ➯አልጀዚራ
20/07/2025

ኢራን ለቀጣዩ ፍልሚያ ዝግጅት ለማድረግ ከሩሲያ ጋር ውይይት እያደረገች ነው።

➯አልጀዚራ

የወንድ የዘር ፍሬ ስለ ወንዶች ጤና ምን ይነግረናል?ከሰሞኑ መቀመጫውን ዴንማርክ የደረገ አንድ የጥናት ተቋም የወንዶች የዘር ፍሬ ጤና እና ከአጠቃላይ ጤና ጋር ባለው ዝምድና ዙሪያ ያተኮረ የ...
14/07/2025

የወንድ የዘር ፍሬ ስለ ወንዶች ጤና ምን ይነግረናል?

ከሰሞኑ መቀመጫውን ዴንማርክ የደረገ አንድ የጥናት ተቋም የወንዶች የዘር ፍሬ ጤና እና ከአጠቃላይ ጤና ጋር ባለው ዝምድና ዙሪያ ያተኮረ የጥናት ውጤት ይፋ ሆኗል፡፡

በሰው ልጆች ስነ ተዋልዶ ጤና ላይ ያተኮሩ የጥናት ውጤቶች በሚወጡበት በዚህ አምድ ላይ የወጣው ጥናት እንደሚለው ከሆነ የወንዴ የዘር ፍሬ ጥራት ከወንዶች ጤና ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው፡፡

ከ80 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል በተባለው በዚህ ጥናት ላይ እንደተገለጸው የተሻለ ጥራት ያለው የዘር ፍሬ ያላቸው ወንዶች ጤነኛ እና ረጅም እድሜ የመኖር እድላቸው ሰፊ ነው ተብሏል፡፡

➯አልጀዚራ

"የፒኬኬ አሸባሪ ቡድን ትጥቅ መፍታት ለታላቋ ተርክዬ ጎህ የቀደደ  ነውሲሉ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ገለፁ።➯➯➯➯➯አል ጀዚራ የፒኬኬ አሸባሪ ቡድን ትጥቅ መፍታት ለታላቋ ተርክዬ አዲስ ምዕራፍ የ...
13/07/2025

"የፒኬኬ አሸባሪ ቡድን ትጥቅ መፍታት ለታላቋ ተርክዬ ጎህ የቀደደ ነውሲሉ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ገለፁ።

➯➯➯➯➯አል ጀዚራ

የፒኬኬ አሸባሪ ቡድን ትጥቅ መፍታት ለታላቋ ተርክዬ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ጎህ ነው ሲሉ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ገለፁ።

የተርክዬ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን የፒኬኬ አሸባሪ ቡድን ትጥቅ መፍታቱ ታሪካዊ የለውጥ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም የ86 ሚሊየን ዜጎች ድል መሆኑን ጠቅሰው፤ ተርኪዬ ወደ አዲስ የአንድነት እና የጥንካሬ ምዕራፍ እየገባች መሆኑን አስታውቀዋል።

ኤርዶጋን በአንካራ የፍትህ እና ልማት (ኤኬ) ፓርቲ 32ኛ የምክክር ስብሰባ ላይ ይህ የታሪክ አዲስ ምዕራፍ መሆኑን ገልፀው፤ ለታላቅና ጠንካራ ተርኪዬ በሮች ሙሉ በሙሉ ተከፍተዋል ብለዋል።

የሽብር ቡድኑ ጦር መሳሪያ ለመጣል መወሰኑ ለተርኪዬ ድል ከመሆኑ በላይ ቱርኮች፣ ኩርዶች እና አረቦች ያሉ ሁሉም አሸናፊዎች መሆናቸውን ገልፀዋል ሲል የዘገበው አናዶሉ ነው።

ቡድኑ በትናንትናው ዕለት ትጥቅ ትግሉን ማቆሙን በማስታወቅ የታጠቃቸውን መሣሪያዎች ማቃጠል መጀመሩ ይታወሳል።

➯አልጀዚራ

Address


Telephone

+251918398494

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አልጀዚራ All jezira posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share