Admas Media አድማስ ሚዲያ

Admas Media አድማስ ሚዲያ Abol

13/08/2024

አውቀን እንታረም!

ወልቃይት ጠገዴ ላይ 1972ዓ.ም ላይ የተሰራ ስህተት 2016ዓ.ም ላይ አይደገምም!

የ1966ቱን አብዮት ተከትሎ የዘር ጥላቻን መሰረቱ ያደረገ የትግል ትርክት ሲተከል፤ አማራን በመዋቅር የሚያጠቃ ኃይል ወደፊት ተስፈንጥሮ ለመውጣት እርሾ እየያዘ ነበር፡፡ የወቅቱ ሴረኛ ኃይሎች ትግል ሁለት መልክ ነበረው፡፡ በአንድ በኩል ቀጥተኛ ፍረጃ ውስጥ የገቡ እንደወያኔ ያሉ አማራ-ጠል ኃይሎች፤ በሌላ በኩል ደግሞ በአማራ ሕዝብ በተለይም ልሂቃኑ ላይ ውስጣዊ ድብቅ ዓላማ ኑሯቸው ነገር ግን ውስጣቸውን ሳይገልጡ ‹ለጋራ የትግል ዓላማ እንታገላለን› የሚሉ ‹መደባዊ መሳይ› ኃይሎች ነበሩ፡፡

በሁለተኛው ጎራ ከሚመደቡ ኃይሎች አንዱ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኀብረት (EDU) ነው፡፡ ይህ ኃይል ዋና መሪዎቹ መሠረታቸው ትግራይ፤ የጀርባ መደባቸው መሳፍንቶች ሆነው ወታደራዊ አቅሙን ደግሞ በቀድሞው አጠራር የጎንደር ክፍለ-ሃገር ላይ ያደረገ ነበር፡፡

የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኀብረት (EDU) የትግል መነሻው ወታደራዊውን የደርግ ሥርዓት ለመታገል ነው ቢባልም፣ ይህ ኃይል በሂደቱና በፍጻሜው የዋናው ጠላት በር ከፋች ነበር፡፡

‹ኢዲዩ›ን በውጤት ብቻ ሳይሆን በውስጣዊ የድርጅት ታሪኩ ሲታይ፣ በትግል ስም ያቀፋቸውን የአማራ ተወላጅ አርበኞች ያስፈጀና ቀጥተኛ ፍረጃ ውስጥ ለገባው አማራን በ‹‹ጨቋኝነት›› ፈርጆ ለተነሳው ወያኔ መንገድ ጠራጊ ሆኖ ያገለገለ ኃይል ነው፡፡

በተለይም በትግራይ ከመጀመሪያው የወያኔ ኃይል ጋር ተጋጭቶ ከወጣ በኋላ በትግል አካሄድ የተለያየ ቢመስልም፤ በተግባር ግን ለወያኔ መንገድ መጥረግን ያለመ ትግል ያደርግ እንደነበር ታሪኩ ይመሰክራል፡፡ ዘግይቶም ቢሆን ዛሬን እንድንማርበት ያን ታሪክ መመርመር አስፈላጊ ሆኖ ተገንቷል፡፡

የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኀብረት (EDU) ከትግራይ ወጥቶ ወልቃይት-ጠገዴን የትኩረት ማዕከሉ በማድረግ ሲንቀሳቀስ ትግሉ እውነት መስሏቸው ይህን ኃይል የተቀላቀሉ የጎንደር አማራዎች በርካታ ነበሩ፡፡

ጣሊያንን ያንቀጠቀጡ ታላላቅ አርበኞች፣ ባላባቶች፣ ባለፀጋዎች፣… የጎንደር መልክ፤ የአማራ ኩራት፤ የኢትዮጵያ ዳር ድንበር አስከባሪ የሆኑ ትልልቅ ሰዎቻችን ይህን ኃይል ተቀላቅለው ያደረጉት ትግል ከውስጣቸው ባሉ ሴረኛ የትግራይ መሳፍንቶች ተጠልፎ፤ አንድ በአንድ ከትግል ሜዳው ተለቀሙ፡፡ ሞት ለአማራ ብቻ የሆነ እስኪመስል ድረስ ኢዲዩ ውስጥ ያሉ የጎንደር ክፍለ ሃገር ተወላጅ ታጋዮች በየአውደ ውጊያው ወደቁ፡፡

ይህ የ1972 የወያኔ ወረራ መግቢያ ምዕራፍ መንገድ ጠረጋ እንደሆነ ለማወቅ የወቅቱ አባቶቻችን አልታደሉም ነበር፡፡ በርግጥም ሁኔታው ነቢይነትን ይጠይቅ ነበር፡፡

የትግራይ መሳፍንቶች ልብ ግን ቢቆፍሩት አይገኝምና በኢዲዩ ትግል ሥም እንቁ የአማራ ታጋዩችን አስፈጅተው፤ ወያኔ ቀድሞ በተጠረገለት መንገድ (የወልቃይት-ጠገዴ አርበኞች ሞትና መበታተን) ነገር ቀሎለት ተከዜን ተሻግሮ እግሩን ተከለ፡፡

በኢዲዩ፣ ኢሕአፓ፣ ኢሰፓ፣… ትግል የተበታተነው የአማራ ልሂቅ፣ ወልቃይት ጠገዴ ላይ የፀረ ቅኝ-ግዛት ትግሉን በተደራጀ መንገድ ለመጀመር አልታደለም ነበር፡፡ የብሔር ንቃትም አልነበረውም፡፡
ጥቂቶች ‹እጅ አንሰጥም› ያሉ የከፋኝ አርበኞች የፀረ ቅኝ-ግዛት ትግሉን ቢጀምሩትም በኢዲዩ ትግል ሥም በርካታ ጀግኖች ወድቀው ነበርና ወያኔ ወልቃይት ጠገዴን በሽፍትነት ወረራ ይዞ፤ በእጁ በገባው ኮሪደር ራሱን በማጠናከር፣ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ድጋፎችን አግንቶ ወደዋናው ሥልጣን ለመንጠላጠያ ተጠቅሞበታል፡፡

ከ40 ዓመታት በኋላ ታሪክ ራሱን ሊደግም…?

ያለፈው ሃምሳ ዓመት የትግል ታሪካችን

05/08/2024
05/08/2024

በወላይታ ዞን በተከሰተ የመሬት ናዳ የ12 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት ናዳ የ11 ሰዎች እንዲሁም በማንአራ ቀበሌ የአንድ ሰው ሕይወት አልፏል።

ዛሬ ረፋድ 5 ሰዓት አካባቢ በጤፓ ቀበሌ በድጋሚ በተከሰተው የመሬት ናዳ አደጋ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል።

በወላይታ ዞን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ የሕዝብ እና ሚዲያ ግንኙነት ዳይሬክተር ዘለቀ ቦሎሎ በተከሰተው አደጋ እስካሁን በተደረገ ፍለጋ የ11 ሰዎች አስከሬን መገኘቱን እና የአደጋው አስከፊነት እየጨመረ በመምጣቱ በአደጋው ቀጣና ያሉ ነዋሪዎችን የማዳን ሥራ መጀመሩን ለአዲስ ዋልታ ዲጂታል ሚዲያ ገልጸዋል።

በተያያዘ በዞኑ ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ ማንአራ ቀበሌ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።

በአደጋው የአንድ ሰው ሕይወት ያለፈ ሲሆን በአንድ ሰው ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት እንደደረሰ ተገልጿል።

የአካባቢው ነዋሪዎችም ከቤት ንብረታቸው እንደተፈናቀሉ የገለጹት ዳይሬክተሩ ዘለቀ ቦሎሎ የተጎዱ ወገኖችን የመደገፍ ተግባር እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

የአርበኛ ዘመነ ካሴ አስገራሚ ንግግሮች •  ከተደራጀህ፣ ከነቃህ፣ ከታጠቅህ ትተርፋለህ፤ ያለዚያ ትጠፋለህ፡፡•  በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆነን መተባበር ያቃተን ለምንድን ነው?•  ይህ የመከራ ዘመ...
30/06/2023

የአርበኛ ዘመነ ካሴ አስገራሚ ንግግሮች
• ከተደራጀህ፣ ከነቃህ፣ ከታጠቅህ ትተርፋለህ፤ ያለዚያ ትጠፋለህ፡፡
• በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆነን መተባበር ያቃተን ለምንድን ነው?
• ይህ የመከራ ዘመን መቼ ነው የሚያበቃው? እንዴት ነው የሚያበቃው? ማን ነው
የሚያቆመው?
• ይህ ዘመን መብቃት አለበት፣ መቆም አለበት፡፡
• ስንደራጅ የነገ ጀንበራችን አይጠልቅም!!
አቦል ሚዲያ /Abol media

Abol Media is a media that provide entertainment and fact information's for the audience!

☪ ዒድ አል አድሃ ሙባረክ ☪ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1ሺህ 444ኛው ዓመተ ሒጅራ የኢድ አል አደሃ (አረፋ)በዓል በስላም አደረሳቹ ፣አደረስን!!በዓሉ የሰላም፣ የፍ...
28/06/2023

☪ ዒድ አል አድሃ ሙባረክ ☪

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1ሺህ 444ኛው ዓመተ ሒጅራ የኢድ አል አደሃ (አረፋ)በዓል በስላም አደረሳቹ ፣አደረስን!!

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር ፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ ይሆንልን ዘንድ አቦል ሚዲያ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን🙏

🕌*

20/10/15

29/04/2023

🔥 ‼️

"…የብርሃኑ ጁላ መከላከያ የምሥራቅ ዐማራ ፋኖ የምሬ ወዳጆን ቤተሰብ ሳያፍኑ እንዳልቀረ ተነገረ። መከላለያው መብራት አጥፍቶ ካፈናቸው ቤተሰቦቹ መካከል፦

"…የ8 ወር ነፍሰጡት ባለቤቱን ወ/ሮ ደርብን፣ እህቱ አንጉታ፣ አያቶቿ ወይም የአባቷ እና የእናቷ አባት እናቶች፣ አዛውንት መነኮሳት እና ከዚህም በላይ ከ15 የበለጠ ቤተሰብ አው ያለው 6 ህፃናት ናቸው።

"…ዛሬ ምሽት 2:00 ማታ ሲሆን ቅድሚያ የከተማውን ሙሉ መብራት አጥፍተው 1 ሻለቃ ጦር ሙሉ መንደሩን ወርሮ በኮማንድ ፖስት በለችው ከታማ ውስጥ ያሉ ቤተሰቦቹን ይዘው መሄዳቸው ተነግሯል። የዓይን ምስክሮች እንደተናገሩት ከሆነ ወደቤቱ በዙ መኪና እየተመላለሰ የነበረ ሲሆን 2 ጊዜ የጥይት ተኩስም መስማታቸውን ተናግረዋል። መብራት በመጥፋቱ እና መንቀሳቀስ ስለማይቻል በትክክል በእርግጠኝነት የወሰዱት የሰው ብዛት ለጊዜው አለመታወቁም ተነግሯል።

"…ሁኔታውን ለማጣራት ወደ አርበኛ የዋርካው የምሬ ወዳጆ ዘንድ ተደጋጋሚ የስልክ ሙከራ ያደረግኩ ሲሆን መስመሩ ከአገልግሎት መስጫ ክልል በመሆኑ ከምሬ ላረጋግጥ አልቻልኩም።

"…አይደለም እስር ጭፍጨፋም የዐማራን የነፃነት ጉዞ አያስቆመውም። አለቀ።

15/04/2023

የካርቱም በረከት በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ይደር 🙏🏻

‹‹በሚዲያ የአማራ ሕዝብ ግፍ ደርሶበታል ብለህ ሕዝቡን አነሳስተሀል›› ሲል ፖሊስ ወነጀለ!ሚያዝያ 07 ቀን 2015 ዓ.ምአቦል ሚዲያጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ...
15/04/2023

‹‹በሚዲያ የአማራ ሕዝብ ግፍ ደርሶበታል ብለህ ሕዝቡን አነሳስተሀል›› ሲል ፖሊስ ወነጀለ!

ሚያዝያ 07 ቀን 2015 ዓ.ም
አቦል ሚዲያ

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርቧል። ጋዜጠኛው የአማራ ሕዝብ ግፍ ደርሶበታል በማለት መንግስትን አስገድዶ ከስልጣን ለማውረድ በሚዲያ ሲንቀሳቀስ ነበር። ተከባብሮ የሚኖርን ሕዝብ ለመለያት ሲሰራ ነበር የሚል ክስ የቀረበበት ሲሆን፤ ለተጨማሪ ማጣራት 14 የምርመራ ቀን ታስሮ ይቆይልን ሲል ፖሊስ ጠይቋል።

የጋዜጠኛው ጠበቆች በበኩላቸው ፤ የሚዲያ ባለሙያ ታስሮ የሚጣራበት የሕግ አግባብ የለም ስለዚህ የዋስትና መብቱ ተከብሮ በዋስ ይለቀቅ›› ሲሉ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል። አክለውም -ደንበኛችን ከሕግ አግባብ ውጪ ፍርድ ቤት ሳይቀርብ 48 ሰዓት አልፎታል፤ የመብት ጥሰት ተከናውኖበታል ሲሉ ፖሊስን ከሰዋል። ፖሊስም ‹‹ከባህርዳር መከላከያ ነው የያዘው፤ ከእነሱ እስክንረከብ ነው ጊዜ የሄደብን›› የሚል ምላሽ ለፍርድ ቤቱ ሰጥተዋል።

በመጨረሻ፣ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ በጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ላይ የ10 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በተያያዘ ዜና የኢትዮ ሰላም ሚዲያ ባለቤት የሆነውና ከጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ጋር በአንድ መዝገብ የተከሰሰው ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው፤ በተመሳሳይ ክስ የተከሰሰ ሲሆን፤ የአስር ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶበታል። ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በአሁኑ ሰዓት ከሌሎች ጋዜጠኞች ጋር በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ጊዜያዊ እስረኛ ማቆያ በእስር ላይ ይገኛል ሲል የዘገበው ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር ነው።

ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች አቦል ሚዲያን ይወዳጁ

አልገባኝም ‼️አልገባኝም። በእውነት አልገባኝም። የአማራ ክልል አመራሮች ምን እየሆኑ ነው? ህወሀት ሃይሉን አጠናክሮ ወደ ወልቃይትና ራያ ተጠግቷል። ባለፉት ሁለት ቀናት ይበልጥ ወደፊት በመም...
14/04/2023

አልገባኝም ‼️

አልገባኝም። በእውነት አልገባኝም። የአማራ ክልል አመራሮች ምን እየሆኑ ነው? ህወሀት ሃይሉን አጠናክሮ ወደ ወልቃይትና ራያ ተጠግቷል። ባለፉት ሁለት ቀናት ይበልጥ ወደፊት በመምጣት ምሽጎችን በኮንክሪት እየሰራ ነው። ህወሀት ወደ ቀደመው ቁመናው እየተመለሰ ይገኛል። በወለጋ ከትላንት ሌሊት ጀምሮ ማንነትን መሰረት ያደረገ ግድያ ዳግም አገርሽቷል። በተለይ አንገርጉትን በተባለችው ከተማ በርካታ ዜጎች መገደላቸውን ሌሊቱን በስልክ መረጃ ስቀበል ነው ያነጋሁት። ያነጋገርኳቸው ሰዎች ግድያውን የሚፈጽመው መከላከያ ሰራዊት ነው ይላሉ። ለማመን ተቸገርኩ። መለዮና ዩኒፎርም ተቀይሮ ካልሆነ በቀር መከላከያ በዚህ ደረጃ ግድያ ውስጥ ይገባል የሚል እምነት የለኝም። ከሆነ እጅግ አደገኛና አሳሳቢ ነው። ምናልባት የኦሮሚያ ልዩ ሃይል ከስምሪት ውጪ ነው እያሉ የሚነግሩን የክልሉ ባለስልጣናት በሌላ ዩኒፎርም ልዩ ሃይላቸውን አሰማርተው ከሆነስ? ያነጋገርኳቸው ሰዎች የሸኔን ስም ተሳስተው እንኳን አልጠሩም። ምንድን ነው ነገሩ?

ትላንት አመሻሽ ላይ ከደሴ ወደ ሸዋ ሮቢት ያመሩ የነበሩ የአማራ ልዩ ሃይል አባላት በኦነግ ሸኔ ተፈጸመ በተባለ ጥቃት በርካታዎቹ እዚያው ረገፉ። የተረፉት ወዴት እንደደረሱም አልታወቀም። መሳሪያ ተነጥቀው ባዶ እጃቸውን ነበር የተሸኙት። እጅና እግራቸውን ብቻ ይዘው እንዲሄዱ ተፈረደባቸው። አረ በህግ አምላክ?! ምን እየሆነ ነው? እስቲ የትኛው ክልል ልዩ ሃይል ነው በዚህ ደረጃ ትጥቁን የፈታው? የምን መደንዘዝ ነው? አቶ ግርማ የሺጥላ ስለዚህ ጉዳይ ምን አፍ ኖሮት የቴሌቪዥን መስኮት ላይ ይደቀናል? ዶ/ር ሰማ ጥሩነህ ይሄን ያህል ባርነት እንዴት ቻሉት? ተበልቶ ማስበላት። እንዴት ያሉ ጉዶች ናቸው የአማራን ክልል የሚመሩት ጎበዝ?!

ህወሀት ፈርጥሟል። ትጥቅ መፍታት የሚሉት የጅሎች ጨዋታ ነው ብሎናል። የኦሮሚያ ልዩ ሃይል መለዮ ይቀይር ይሆናል እንጂ ጫፉም የሚነካ አይደለም። የሌሎችም እንደዚያው። የአማራ ክልል ላይ የሆነው ግን ፍጹም ግራ የሚያጋባ፡ ወዴት እያመራን እንደሆነ አዛዦቹም፡ ተላላኪዎቹም፡ ሰለባዎቹም እርግጠኛ መሆን የማይችሉት አደገኛ አዝማሚያ ነው። እንዴት አንድ ስጋት ያለበት ክልል ባርነትን በገዛ ፍቃዳቸው የተቀበሉ ሰዎች ስልጣኑን ይዘው ለጌቶቻቸው ህዝብን እንደመስዋዕት በግ ያቀርባሉ? ይኸው ውጤቱን እያየነው ነው። የኤፍራታ ግድም ወረዳ አንድ አመራር እንደነገሩኝ ልዩ ሃይሉ ትጥቅ መፍታቱን ተከትሎ ሸኔ መሳሪያውን እየወለወለ ነው። መከላከያ አጠገባችን ሆኖ ትዕዛዝ አልተሰጠኝም ብሎ የልዩ ሃይል አባላቱን አስጨፍጭፏል ነው የሚሉኝ። በማይጠብሪ የልዩ ሃይሉን መውጣት እግር ተከትሎ ህወሀት ዘንባባ እያነጠፈ ሊገባ ተዘጋጅቷል። በራያ የልዩ ሃይሉ መውጣት ለህወሀት ሰዎች ጮቤ ያስረገጣቸው ዜና የሆነው ያለምክንያት አይደለም። ጎበዝ! ምን እየሆነ ነው ?

Mesay mekonnen (Anchor Media)

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Admas Media አድማስ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share