Ethio ኢትዮ

Ethio ኢትዮ Followed By 205,000 peoples

እስራኤል ያጋጠማትን ሰደድ እሳት ተከትሎ የዓለምአቀፉን ማህበረሰብ ድጋፍ ጠየቀች*********************እስራኤል በእየሩሳሌም ከተማ አቅራቢያ ያጋጠማትን ከባድ ሰደድ እሳት ተከትሎ የ...
01/05/2025

እስራኤል ያጋጠማትን ሰደድ እሳት ተከትሎ የዓለምአቀፉን ማህበረሰብ ድጋፍ ጠየቀች
*********************

እስራኤል በእየሩሳሌም ከተማ አቅራቢያ ያጋጠማትን ከባድ ሰደድ እሳት ተከትሎ የዓለምአቀፉን ማህበረሰብ ድጋፍ ጠይቃለች፡፡

ከእየሩሳሌም በቅርብ ርቀት ላይ የተከሰተው ከባድ ሰደድ እሳት መዛመቱን ተከትሎ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ መደረጉ ተገልጿል፡፡

እንዲሁም በሰደድ እሳቱ የተነሳ በርካታ መንገዶች እንዲዘጉ መደረጉም ተነግሯል፡፡

ባለው ከባድ የአየር ጠባይ እና በኃይለኛ ንፋስ ታግዞ እየተዛመተ የሚገኘውን የሰደድ እሳት ለመቆጣጠር የእሳት አደጋ ሰራተኞች ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸውን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ሃገሪቱ ብሄራዊ የአደጋ ጊዜ ላይ መሆኗን ገልፆ፤ የሰደድ እሳቱን ለመከላከል የዓለምአቀፉን ማህበረሰብ ድጋፍ ጠይቋል፡፡

የተከሰተው የሰደድ እሳት ምናልባትም በታሪክ ትልቅ የሚባል መሆኑን የገለጹት የእየሩሳሌም ግዛት የእሳት አደጋ ድፓርትመንት ኮማንደር ሽሙሊክ ፍሬይድማን፤ የሰደድ እሳቱ በሰዓት 60 ማይል ፍጥነት የሚጓዝ በመሆኑ የበለጠ እንዳይዛመት አስጊ አድርጎታል ብለዋል፡፡

የሰደድ እሳቱ በኃይል መዛመቱን ተከትሎ ባለስልጣናቱ ቴላቭቭን ከእየሩሳሌም የሚያገናኘውን መንገድ ለመዝጋት መወሰናቸውንም ነው የተገለጸው፡፡

በእስራኤል እሮብ እለት የተከሰተውን የሰደድ እሳት ለመከላከል ሃገሪቱ ባቀረበችው የድጋፍ ጥያቄ 3 የእሳት መከላከያ አውሮፕላኖችን ከጣሊያን ማግኘቷም ተነግሯል፡፡

በተበጠሰ የኤሌክትሪክ ገመድ ምክንያት የባልና ሚስት ህይወት አለፈበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ 01ቀበሌ የኤሌክትሪክ አደጋ የጥንዶችን ህይወት ቀጥፏል።ሟቾቹ አቶ አሸናፊ ...
23/10/2024

በተበጠሰ የኤሌክትሪክ ገመድ ምክንያት የባልና ሚስት ህይወት አለፈ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ 01ቀበሌ የኤሌክትሪክ አደጋ የጥንዶችን ህይወት ቀጥፏል።

ሟቾቹ አቶ አሸናፊ አበበና ወይዘሮ ሻለኔ ታሪኩ የተባሉ ሲሆን መተዳደርያቸዉ የእርሻ ስራ ስለነበረ የበቆሎ ማሳቸዉን በማረስ ከቆዩ በኋላ ወደ መኖርያ ቤታቸው ሲመለሱ በአካባቢያቸው የሚያልፍ የኤሌክትሪክ ገመድ ተበጥሶ መዉደቁን ያላዩት አቶ አሸናፊ ገመዱን በመርገጥ በኤሌክትሪክ ይያዛሉ።

ይህንን ያዩት ባለቤታቸው ወይዘሮ ሻለኔ የትዳር አጋራቸዉን ነብስ ለማትረፋ በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ ከግንዛቤ እጥረት የተነሳ የኤሌክትሪክ ገመዱን በመያዛቸዉ የሁለቱም ህይወት ማለፉን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ኢንስፔክተር አሸናፊ ኃይሌ ተናግረዋል ።

ህይወታቸው ያለፈው ጥንዶቹ በትዳር ህይወታቸው ስድስት ልጆችን አፍርተዋል።
(ብስራት ሬዲዮ ቴሌቪዥን)

Loading...HAMSTER ጥቂት ደቂቃዎች ቀሩት። 2 ኛ ዙር ስለጀመረ
26/09/2024

Loading...
HAMSTER ጥቂት ደቂቃዎች ቀሩት። 2 ኛ ዙር ስለጀመረ

how many you got? mine is in  the comment
22/09/2024

how many you got? mine is in the comment

የሚገርም ምስል❤ ይመልሱ
14/09/2024

የሚገርም ምስል❤ ይመልሱ

ሞባይል ስልክ አብዝቶ መጠቀም ለጭንቅላት ካንሰር ያጋልጣል?የዓለም ጤና ድርጅት የሞባይል ስክ እና ጭንቅላት ካንሰር ያላቸውን ዝምድና አሳውቋል250 ሺህ በጎ ፈቃደኞች እና መራማሪዎች የተሳተፉ...
05/09/2024

ሞባይል ስልክ አብዝቶ መጠቀም ለጭንቅላት ካንሰር ያጋልጣል?

የዓለም ጤና ድርጅት የሞባይል ስክ እና ጭንቅላት ካንሰር ያላቸውን ዝምድና አሳውቋል
250 ሺህ በጎ ፈቃደኞች እና መራማሪዎች የተሳተፉበት ጥናት ውጤት ሞባይል ስልክ እና የጭንቅላት ካንሰርን ግንኙነት ይፋ አድርጓል

ሞባይል ስልክ አብዝቶ መጠቀም ለጭንቅላት ካንሰር ያጋልጣል?

የሰው ልጅ ተንቀሳቃሽ ስልክን ወይም ሞባይልን ከፈረንጆቹ ከ1990ዎቹ ጀምሮ መጠቀም መጠቀም ጀምሯል፡፡

ሞባይል ቴክኖሎጂ የሰው ልጆችን ህይወት ካቀለሉ ዘመን አመጣሽ ምርቶች መካከል ዋነኛው ሲሆን ቀስ በቀስ የሰው ልጅ እጅግ አስፈላጊ ምርት ወደ መሆን ተሸጋግሯል፡፡

ይህ በዚህ እንዳለ ግን ሞባይል ስልክ የራሱ ጥቅም እንዳለ ሆኖ የጎንዮሽ ጉዳቶች እንዳሉትም አያጠያይቅም፡፡

በርካታ ተመራማሪዎች በተለያዩ ጊዜያት ይፋ ያደረጓቸው የጥናት ውጤቶች በሞባይል ስልክ ላይ ያለው ጨረር ወይም ራዲየሽን የራሱ የሆነ የጎንዮሽ ጉዳቶች አሉት ሲሉ ቆይተዋል፡፡
ሰዎች በብዛት ሞባይል ስልክን ሲጠቀሙ ከስልኩ ላይ የሚለቀቁት ጨረሮች አዕምሮን በመጉዳት ለጭንቅላት ካንሰር ያጋልጣሉ የሚሉ ያልተረጋገጡ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር ተብሏል፡፡

ከዓለም የጤና ድርጅት ጋር በቅንጅት የተሰራ አንድ ጥናት እንዳስታወቀው ሞባይል ስልክ የጭንቅላት ካንሰርን አያስከትም ተብሏል፡፡

ከ250 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞች የተሳተፉበት ህ ጥናት የጭንቅላት ካንሰር እና ሞባይል ስልክ ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌላቸውም ዩሮ ኒውስ ጥናቱን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡

ለሰባት ዓመታት ተደርጓል የተባለው ይህ ጥናት ሞባይል ስልክ አብዝተው የሚጠቀሙ እና አልፎ አልፎ የሚጠቀሙ ሰዎች ላይ ምንም አይነት ልዩነት እንደሌለ ተገልጿል፡፡

Al Ain Amharic

አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ከሀገረ ህንድ ያስተላለፈው መልዕክት "ለሁላችሁም መልካም የጤና ምኞት አመሰግናለሁ የሰው ሁሉ ክብር አይጉደልባችሁ ። ወሬውን አንዳንዶች አጋነውታል እንደውም አንዱ ...
14/07/2024

አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ከሀገረ ህንድ ያስተላለፈው መልዕክት

"ለሁላችሁም መልካም የጤና ምኞት አመሰግናለሁ የሰው ሁሉ ክብር አይጉደልባችሁ ። ወሬውን አንዳንዶች አጋነውታል እንደውም አንዱ ትራንፕን የጨረፈው ጥይት ነጺንም ጨርፎታል አሉ አለኝ እንዲህ የሚመኝ አይጥፋ ። ሌላው ደሞ ልጅ ሆኜ ዑራኤል መቃብር ሲቆፍር የማውቀው ደውሎ ላንተ ግንባር ቦታ አለኝ ብሎ ዘመደ ብዙ መሆኔን አሳውቆኛል ። በጣም ደህና ነኝ በቅርብ ቀን እመለሳለሁ ። "

የማይነበብ ፊርማ

ነጻነት ወርቅነህ

ይህ ማዳበሪያ ለጠየቀ አርሶ አደር ከመንግሥት የተሰጠ ምላሽ ነው!😥በዛሬው እለት ማዳበሪያ ሳናገኝ የዘር ወቅት እያለፈብን ነው፣ መሬታችን ጦሙን ሊያድር ነው ብሎ አቤቱታ ለማቅረብ ወደ ሀድያ ...
24/07/2023

ይህ ማዳበሪያ ለጠየቀ አርሶ አደር ከመንግሥት የተሰጠ ምላሽ ነው!😥

በዛሬው እለት ማዳበሪያ ሳናገኝ የዘር ወቅት እያለፈብን ነው፣ መሬታችን ጦሙን ሊያድር ነው ብሎ አቤቱታ ለማቅረብ ወደ ሀድያ ዞን አስተዳደር የመጡ አርሶ አደሮች ተደብድበው በጥይት ከተበተኑ በኋላ ታስረዋል።

ያሳዝናል። ቆስሏል 😱
24/07/2023

ያሳዝናል። ቆስሏል 😱

«ሞት አልፈራም፣ስፈጠርም እንደምሞት አውቃለሁ።» -ከማንዶ ፍቅሩ ሙሉዬ
24/07/2023

«ሞት አልፈራም፣ስፈጠርም እንደምሞት አውቃለሁ።» -ከማንዶ ፍቅሩ ሙሉዬ

አሳዛኝ ክስተት❗😭🇪🇹ምእራብ ሀረርጌ  ቡርቃ dhintuu ወረዳ ኩርፋ በተባለች የገጠር መንደር በ ሀምሌ 12/11/2015 ከምሽቱ 12:30 ላይ ሰፈር ውስጥ እየተጫወቱ የነበሩ አምስት ህጻናት...
23/07/2023

አሳዛኝ ክስተት❗😭🇪🇹

ምእራብ ሀረርጌ ቡርቃ dhintuu ወረዳ ኩርፋ በተባለች የገጠር መንደር በ ሀምሌ 12/11/2015 ከምሽቱ 12:30 ላይ ሰፈር ውስጥ እየተጫወቱ የነበሩ አምስት ህጻናትን ጅብ ጠልፎ በመውሰድ በላቸው።

በዚህ እጅግ ልቡ የተሰበረው ማህበረሰብ ወዲያው ተሰባስቦ ክትትል በማድረግ ጅቦቹን በማደን ከዚህ በምስል የምንመለከተውን ጅብ ገድለው ሆድቃውን በመቅደድ ከሆዱ ውስጥ ያገኟቸውን የተወሰኑ የልጆቻቸውን እጇች ቀበሩ😢😢😢

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio ኢትዮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share