08/05/2026
ቢቢሲ በአማራ ክልል እየተካሄደ ባለው ጦርነት የተፈጸሙ ወሲባዊ ጥቃቶችን በሚመለከት በሠራው ጥልቅ የምርመራ ዘገባ የአምንስቲ ኢንተርናሽናል ዩኬ የመገናኛ ብዙኃን ሽልማት (ሚዲያ አዋርድ) አሸነፈ። ሽልማቱ በምርጥ የፊቸር ዘገባ (Best Written Feature) ምድብ የተሠጠ ሲሆን፣ "ቢገድሉኝ ይሻል ነበር"፡ የሴቶችን ሕይወት እያበላሸ ያለው የተዘነጋው የአማራ ክልል ጦርነት በሚል ርዕስ የቀረበ ነው። ዘገባውን ለመሥራት ለስድስት ወር ያህል ጥልቅ ምርመራ ማድረግ፣ የጥቃት ሰለባዎችን በማነጋገር እማኝነት መቀበል፣ እንዲሁም የሕክምና ማስረጃዎች መመልከት ጠይቋል።
https://bbc.in/4topHuV