
08/06/2025
የባቲ ወረዳ ሰላምና ህዝብ ደህንነት ጽ/ቤት በUNDP PSF ፕሮጀክት ድጋፍ ከወረዳው ከሁሉም ቀበሌዎች ለተውጣጡ ወጣቶች ሴቶች በግጭት መከላከልና አፈታት እንዲሁም በቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ዙሪያ ለወጣቶች ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ተገለፀ።
#ባቲ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን
ሰኔ 30 /2017 ዓ.ም
በባቲ ወረዳ ከ26 ቱም ቀበሌዎች ለተውጣጡ ለወጣቶች ና ሴቶች በግጭት መከላከል አፈታት ና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዙሪያ ከUNDP PSF በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ለ3 ተከታታይ ቀናት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በወረዳው አፈጉባኤ አዳራሽ እየሰጠ ይገኛል።
በስልጠናው መርሃ ግብር ላይ የዞን የሰላምና ህዝብ ደህንነት መምሪያ ም/ሃላፊ አቶ አወል እንድሪስ የባቲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ አብዱ የባቲ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሰይድ ዘይኑ ን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።
የስልጠና መርሃግብሩን በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት አቶ ሰይድ ዘይኑ እንደተናገሩት ወጣቱ
የህብረተሰብ ክፍል ነገን በአዲስና በተሻለ ሁኔታ ለመገንባት ሁከት ና ግጭቶችን ቀድሞ የመከላከልና የሰላም ግንባታ ላይ ትኩረት በመስጠት ከመቼውም ጊዜ በላይ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
ሰላምን ለማስፈን ግጭቶችን ለማስወገድ ሁሉም ሰው ድርሻ ያለው ቢሆንም የሀገር ተረካቢ የሆኑ ወጣቶች ዋነኛ የሰላም ባለቤት መሆናቸውን በመገንዘብ ግጭቶችን ቀድሞ በመከላከል ና በመፍታት ሰላምን በማስፈን ውስጥ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አክለው ተናግረዋል።
በወረዳው በሁሉም ቀበሌያት በአሁኑ ዘመናዊ ዓለም የግጭት መነሻ ምክንያቶች፣የግጭትና የሰላም ምንነት፣የተዛቡ የትርክት ግንዛቤዎች ምልከታዎች እና የግጭት አፈታት ዘዴዎች ላይ በተዘጋጀው ሰነድ በዞን ባለሙያ ቀርቦ በስልጠና ተሳታፊዎች በስፋትና በጥልቀት የጋራ ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል ::
በሰልጣኝ ተሳታፊዎች በተነሳው ሃሳብ ወጣቱ ትውልድ ሃገር ተረካቢ እደመሆናችን መጠን በ አከባቢያችን የግጭት መፍቻ እሴቶችን በማጎልበት ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት በግንባር ቀደምትነት በባለቤትነት ይዘን ልንሰራ ይገባል ብለዋል።
የሚዲያ ይዘት ማበልጸግ ዝግጅትና ስርጭት