Kominikeeshinii Mootummaa Aanaa Baateeባቲ ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Bati
  • Kominikeeshinii Mootummaa Aanaa Baateeባቲ ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን

Kominikeeshinii Mootummaa Aanaa Baateeባቲ ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን Odeeffannoo sochii misoomaa aanaa keenyaa fi ta'iinsoota adda addaa ittiin isiniif tamsaasna. Like f

የባቲ ወረዳ ሰላምና ህዝብ ደህንነት ጽ/ቤት በUNDP PSF ፕሮጀክት ድጋፍ ከወረዳው ከሁሉም ቀበሌዎች  ለተውጣጡ ወጣቶች ሴቶች በግጭት መከላከልና አፈታት እንዲሁም በቅድሚያ ማስጠንቀቂያ  ዙ...
08/06/2025

የባቲ ወረዳ ሰላምና ህዝብ ደህንነት ጽ/ቤት በUNDP PSF ፕሮጀክት ድጋፍ ከወረዳው ከሁሉም ቀበሌዎች ለተውጣጡ ወጣቶች ሴቶች በግጭት መከላከልና አፈታት እንዲሁም በቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ዙሪያ ለወጣቶች ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ተገለፀ።

#ባቲ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን
ሰኔ 30 /2017 ዓ.ም

በባቲ ወረዳ ከ26 ቱም ቀበሌዎች ለተውጣጡ ለወጣቶች ና ሴቶች በግጭት መከላከል አፈታት ና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዙሪያ ከUNDP PSF በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ለ3 ተከታታይ ቀናት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በወረዳው አፈጉባኤ አዳራሽ እየሰጠ ይገኛል።

በስልጠናው መርሃ ግብር ላይ የዞን የሰላምና ህዝብ ደህንነት መምሪያ ም/ሃላፊ አቶ አወል እንድሪስ የባቲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ አብዱ የባቲ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሰይድ ዘይኑ ን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።

የስልጠና መርሃግብሩን በመክፈቻ ንግግር የከፈቱት አቶ ሰይድ ዘይኑ እንደተናገሩት ወጣቱ
የህብረተሰብ ክፍል ነገን በአዲስና በተሻለ ሁኔታ ለመገንባት ሁከት ና ግጭቶችን ቀድሞ የመከላከልና የሰላም ግንባታ ላይ ትኩረት በመስጠት ከመቼውም ጊዜ በላይ ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

ሰላምን ለማስፈን ግጭቶችን ለማስወገድ ሁሉም ሰው ድርሻ ያለው ቢሆንም የሀገር ተረካቢ የሆኑ ወጣቶች ዋነኛ የሰላም ባለቤት መሆናቸውን በመገንዘብ ግጭቶችን ቀድሞ በመከላከል ና በመፍታት ሰላምን በማስፈን ውስጥ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አክለው ተናግረዋል።

በወረዳው በሁሉም ቀበሌያት በአሁኑ ዘመናዊ ዓለም የግጭት መነሻ ምክንያቶች፣የግጭትና የሰላም ምንነት፣የተዛቡ የትርክት ግንዛቤዎች ምልከታዎች እና የግጭት አፈታት ዘዴዎች ላይ በተዘጋጀው ሰነድ በዞን ባለሙያ ቀርቦ በስልጠና ተሳታፊዎች በስፋትና በጥልቀት የጋራ ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል ::

በሰልጣኝ ተሳታፊዎች በተነሳው ሃሳብ ወጣቱ ትውልድ ሃገር ተረካቢ እደመሆናችን መጠን በ አከባቢያችን የግጭት መፍቻ እሴቶችን በማጎልበት ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት በግንባር ቀደምትነት በባለቤትነት ይዘን ልንሰራ ይገባል ብለዋል።

የሚዲያ ይዘት ማበልጸግ ዝግጅትና ስርጭት

Aanaa Baateetti Orrenteeshiniin Qorumsa kutaa 8ffaa ,6ffaa fi 12ffaa kan bara 2017  kennamaa jira. Caamsaa 30 /2017 Komu...
07/06/2025

Aanaa Baateetti Orrenteeshiniin Qorumsa kutaa 8ffaa ,6ffaa fi 12ffaa kan bara 2017 kennamaa jira.

Caamsaa 30 /2017 Komunikeeshinii A/Baatee

MBNA Bulchiinsa Saba Oromoo Aanaa Baateetti, Orrenteeshiniin Qorumsa kutaa 8ffaafi kutaa 6ffaa Kan bara 2017 gaggeessitoota Aanaa, supparvaayizaroota manneen barnootaa, Barsiisota qormaata Qoraniifi Qaamolee nageenyaatiif kenname.

Sanada Orrenteeshinii kanaa kan dhiheessan I/A Waajjira Barnootaa Aanaa Baatee Obbo Umar Mahammad " bara kana barattoota kutaa 8ffaa 1072 fi barattoota kutaa 6ffaa 1462 haala seera qabeessaan qorumsa kennuuf qophii xumurreerra jedhaniiru.

Waltajjii kana Kan dursan Obbo Mahammad Abduu bulchaa Aanaa Baateefi Obbo Sayid Zeynuu I/G Paartii Badhaadhinaa damee aanaa Baatee yeroo tahan milkii Firii barattootaa kanaaf xiyyeeffannoo kennamee hojjetamuu akka qabu kallattii kennaniiru.

Orrenteeshinii irratti Ciminaa fi hanqina qorumsa bara 2016 akka ka'umsaatti gamaggamuun qormaata bara kanaa haala kamiin milkeessina? isa jedhu irratti sirriitti marihatameera. haaluma kanaan qorumsi kutaa 8 Waxabajjii 3-4 kan kennamu yeroo tahu kan kutaa 6ffaa itti fufee waxabajjii 5-6 kan kennamu tahuun ibsameera.

"Qormaata Gaarii Barattoota Keenyaaf"

ከባቲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ አብዱ የተላለፈ የኢደል አል አድሃ የአረፋ በአል  የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት !!ለመላው የወረዳችን ና የሀገራችን የእስልምና እምነት ተከታዩች እን...
05/06/2025

ከባቲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ አብዱ የተላለፈ የኢደል አል አድሃ የአረፋ በአል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት !!

ለመላው የወረዳችን ና የሀገራችን የእስልምና እምነት ተከታዩች እንኳን 1446ኛዉ የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ፡

የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል የተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ ስርአቶች የሚከናወኑበት ሲሆን፤ በዚህም ሕዝበ ሙስሊሙ እርድ በመፈጸም ና ለሌሎች ለተቸገሩ ወንድሞቹ በማካፈል፣ በጋራ በመጸለይ እና ከፈጣሪ ምህረትን የሚያስገኙ በጎ ተግባራትን በማከናወን የሚያሳልፉበት ታላቅ በዓል ነው ብለዋል።

ይህንን የወንድማማችነት፣ የመረዳዳትና የመተዛዘን ድንቅ እሴት በማስቀጠል ለተቸገሩና የኢኮኖሚ አቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ያለንን በማካፈል በዓሉን አንድ ሆነን በደስታና በፍቅር ልናከብር ይገባል ሲሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸው ለህዝበ ሙስሊሙ አስተላልፈዋል።

ኢድ ሙባረክ ኢድ ሙባረክ ኢድ ሙባረክ

04/06/2025

#ዜና በባቲ ወረዳ በሚገኙ የተለያዩ ቀበሌዎች ላይ ከዩኒሴፍ በተገኘ ድጋፍ የሚሰሩ የመፀዳጃ ቤት ግንባታ በተመለከተ ゚viralシfypシ゚viralシalシ

Harki Araaraaf Diriire Eebbifamaa jira!*************************************Caamsaa 27/2017 Komunikeeshinii A/Baatee.Bul...
04/06/2025

Harki Araaraaf Diriire Eebbifamaa jira!
*************************************
Caamsaa 27/2017 Komunikeeshinii A/Baatee.

Bulchiinsa Saba Oromoo Aanaa Baatee Kilaastara Eelaatti, Gaggeessaan ABO Shanee tokko jalee miseensota jaha qabachuun gara araaraatti dhufuun ibsame.

Jaarsoliin Lagaa maatii shanee walitti qabuun sirriitti erga mariissisnee booda, miseensota shanee argachuun araarri mootummaan dhiheesse, araara dhugaa tahuufi obboleessi obboleessa waliin warra harkaa walitti godhee qabsoon qabsaahamu waan hin jirreef Abbagaarota irratti araraara gochuuf qindoominaan hojjenneerra jedhaniiru.

Gaggeessaa waraanaa damee tokkoo kan ture Huseen Ahimad Xolahaa Nuti nutti fakkaateee miseensa taanee turre, qabsoon karaarraa maquu arginaan fedhii keenyaan galuuf erga murteessinee turreerra, garuu araara dhugaa eegaa turre, amma araara mootummaan keenyaafi Maanguddoonni keenya nuuf dhiheessan fudhannee dhufneerra. kana booda waan akkisii irraa fagaachuuf balee seenneerra jedheera.

Araarichis bakka Olomaayiin, Jaarsoliin, gaggeessitootni aanaa, gaggeessitootni gandaa argamanitti Abbagaarotaan magaalaa Eelaatti raawwateera. dhuma irratti jaarsoliin siingeen keenya akkuma ciistetti jirti, ijoolleen keenya kabaja Hawaasa keessaniitiif jecha gara araaraatti akka dhuftan jechuun waamicha erga dhiheessanii booda. warra gale eebbisuun goolabameera.

Araarri fala;Nageenyi mo'ataadha.!

"ህብረተሰቡ የጤና ፓኬጅን ተግባራዊ  በማድረግ ራሱንና አካባቢውን ከተለያዩ ተላላፊ ሽታዎች መጠበቅ እንዳለበት ተጠየቀ"የባቲ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር በግልና አከባቢ ንፅህ...
04/06/2025

"ህብረተሰቡ የጤና ፓኬጅን ተግባራዊ በማድረግ ራሱንና አካባቢውን ከተለያዩ ተላላፊ ሽታዎች መጠበቅ እንዳለበት ተጠየቀ"

የባቲ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር በግልና አከባቢ ንፅህና ብሎም ከአር የፀዳ ቀበሌ(መንደር) መፍጠር ላይ የተዘጋጀ ስልጠና ለወረዳው የቀበሌ አመራሮችና ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱ ተገለፀ።

ባቲ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

የባቲ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር በግልና አከባቢ ንፅህና ብሎም ከአር የፀዳ ቀበሌ(መንደር) ለመፍጠር በዩኒሴፍ ድጋፍ በየቀበሌዎቹ ለሚገነቡ መፀዳጃ ቤቶች ጉዳይ ላይ የተዘጋጀ ስልጠና በወረዳው ለሚገኙ የቀበሌ አመራር ፣ጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ና ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የንቅናቄ ማስጀመሪያ ስልጠና በወረዳው አፈጉባኤ አዳራሽ አካሂዷል ።

በስልጠናዉ ላይ ተገኝተዉ ንግግር ያደረጉት
የወረዳው ግብርና ልማት ጽ/ቤት ዋና ሃላፊና ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ይማም
ከ60-80% የሚሆኑ ተተላላፊ በሽታዎች ከግልና ከአካባቢ ንፅህና ጉድለት ጋር ተያያዥነት ያላቸዉ ችግሮች በመሆናቸዉ፤ በዘንድሮ ዓመት በዩኒሴፍ ድጋፍ በወረዳችን በሚገኙ ቀበሌዎች መፀዳጃ ቤት ቆፍሮ መገንባት ብቻ ሳይሆን አጠቃቀም ላይ ትኩረት ሰጥተን መሥራት እና የሚተላለፉ በሽታዎች ላይ ተጨማሪ ግንዛቤ ለመፍጠር ነዉ ብለዋል።

ስልጠናዉ በጤና ጽ/ቤት የሃይጅን እና ሳኒቴሽን ባለሙያ አቶ አብደላ መሀመድ ተግባራቱ የሚፈፀምበትን አግባብ የሚያመላክት ሰነድ ቀርቦ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት በዩኒሴፍ ፕሮጀክት ለቀበሌወቻችን የመጣውን የመፀዳጃ ቤት ግንባታ ለተለያዩ በሽታዎች ተጋላጭ የሚያደርገንን ጉዳይ የሚቀርፍልን በመሆኑ የጤና ባለሙያውን ምክ ረሃሳብ በመተግበር በተቀመጠው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ቀበሌዎቻችን ሞዴል እናደርጋለን ብለዋል።

የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ አምሳሉ ጌታቸው በሰጡት አስተያየት የቀበሌ አመራሩ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያውና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ና ተናቦ በመስራት በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ርብርብ መደረግ እዳለበት አፅእኖት ሰጥተው አሳስበዋል ።

የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ዋና ሃላፊ አቶ አህመድ እንደተናገሩት የቀበሌ አመራሮች ሁለገብ የስራ ተሳታፊዎች እንደመሆናችሁ መጠን ይህን እድል በመጠቀም በየቀበሌያችሁ ተልዕኮውን በማስፈጸም ቀበሌዉን ግንባር ቀደም አደርጎ፤ ከአር የፀዳ መንደር (ሞዴል ቀበሌ) ተፈጥሮ ማየትና ንፅህናው የተጠበቀ፣ ቆሻሻን የሚጠየፍ ትዉልድ ና ማህበረሰብ የመፍጠር ሥራ በቁርጠኝነት መሥራት ከሁላችንም ይጠበቃል ሲሉ ተናግረዋል ።

የጤና ጽ/ቤቱ የሃይጅን እና ሳኒቴሽን ባለሙያ አቶ አብደላ መሀመድ ተግባራቱ ለማስፈፀም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገው ውይይት በአንድ ወር ጊዜ ለመፈፀምና ለማጠናቀቅ ከሁሉም አካላት ጋር ከመግባባት ላይ የተደረሰበት መድረክ መሆኑን ተናግረዋል ።

የሚዲያ ይዘት ማበልጸግ ዝግጅትና ስርጭት

"የአካባቢያችን ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ ፣ ፅንፈኞችንም አምርረን ለመታገል ና ልማታችንን ለማስቀጠል  የምንቆጥበው አንዳችም ጉልበት  የለም "አሉ የባቲ ወረዳ የተአ ክላስተር ነዋሪ...
01/06/2025

"የአካባቢያችን ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ ፣ ፅንፈኞችንም አምርረን ለመታገል ና ልማታችንን ለማስቀጠል የምንቆጥበው አንዳችም ጉልበት የለም "አሉ የባቲ ወረዳ የተአ ክላስተር ነዋሪዎች !!

በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር በባቲ ወረዳ የተአ ፣የቦፋ ፣የጨለለቃ፣ የዳመቶ ና ቡርቃ ቀበሌ ነዋሪዎች የተሳተፉበት የህዝብ የውይይት መድረክ በተአ መልካ ማዕከል መካሄዱ ተገለፀ ።

የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ተቀዳሚ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ አባፍሮ ባደረጉት ንግግር የተአ መልካ ክላስተር ህዝብ የሰላምን ፋይዳ በቅጡ የተረዳ የአንድነት የውንድማማች ባለቤት የሰላም አንባሳደር መሆናችሁን በአካባቢያችሁ ባረጋገጣችሁት ሰላም ማስመስከር ችላችኋል ብለዋል።

ይህን በመደማመጥ በአንድነት ሰርታችሁ ያረጋገጣችሁትን ሰላም ለወረዳው አንዳንድ ቀበሌዎች ና ለዞናችንም ጭምር ትምህርት የሚወሰድበት አቅም በመሆኑ ተሞክሮአችሁን ለሌሎች በማጋራት መስራት ይገባል ብለዋል።

የተአ መልካ ክላስተር የረጂም ጊዜ የህዝቡ ጥያቄ የነበረውን የኒቶርክ ጥያቄ ባረጋገጣችሁት አስተማማኝ ሰላም መልስ መስጠት የተቻለው በአንድነት ሆናችሁ በአካባቢያችሁ ባረጋገጣችሁት አስተማማኝ ሰላም በመሆኑ ሰላማችሁን ጠብቃችሁ የበለጠ በማስቀጠል እደ መንግስት የህብረተሰባችንን አንገብጋቢ ጥያቄ መልስ ለመስጠት በቁጭት ና በትግታት ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።

የባቲ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ መሀመድ አብዱ የህዝብን አንገብጋቢ የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ህዝቡ የአካባቢውን ሠላም በዘላቂነት ማረጋገጥ ተቀዳሚ ተግባሩ መሆን አለበት ብለዋል።

ዛሬ የምናካሂደው ህዝባዊ ውይይት አንድነቱን እና ወንድማማችነትን በማጠናከር የሰላም አንባሳደር በሆነው በተአ ክላስተር ላይ ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ህዝቡ የአካባቢውን ዘላቂ ሠላምን ከመንግስት ጋር ተባብሮ ከጽንፈኞች መጠበቅ ከቻለ የልማት ጥያቄዎችን በአጭር ጊዜ ማሳካትና መመለስ እንደሚቻል የተኣ ክላስተር ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።

የተኣ ክላስተር የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት "ሰላም ካለ ሁሉም ነገር አለ እኛ የምንፈልገው ሠላምና ልማት ነው፤ ልማታችንን የሚያደናቅፍ ለማናቸውም ፀረ ሰላም ሀይል ቦታ የለንም"።

አካባቢያችን ብሎም ወረዳችንን ወደ አስተማማኝ ሠላም ለመመለስ በሚደረገው ጥረት ከመንግሥት ጎን በመቆም የሚጠበቅብንን ሁሉ ለማድረግ የምንቆጥበው አንዳችም ጉልበት የለሞ ሲሉ ተናግረዋል።

አሁን ላይ በወረዳችን በርካታ የልማት ስራዎች ተሰርተው እንዲጠናቀቁና ለወረዳው አርሶ አደርም ተገቢውን ግልጋሎት እንዲሰጡ ሁሉም በአንድነት የአካባቢውን ሰላም ሌት ተቀን በመጠበቅ የዜግነት ግዴታውን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ፤የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አላምር ተሻለ፤የአማራ ክልል መሬት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ እብሬ ከበደ፤ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ተቀዳሚ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ አባፍሮ የዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ሀላፊ አቶ አህመድ ሁሴን ፤የባቲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ አብዱ ፤ የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ፖሊስ መምሪያ ም/ኢ/ር ኡመር መሀመድ የሀይማኖት አባቶች አባ ገዳወች የተአ ክላስተር ኖሪወችና ባለ ድርሻ አካላት ተገኝተዋ።

የሚዲያ ይዘት ማበልጸግ ዝግጅትና ስርጭት

30/05/2025
"ትልልቅ ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስ የዚህ ዘመን አመራር ና የህዝባችን ድምር ውጤት መገለጫ ነው። "የአማራ ክልል መሬት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ እብሬ ከበደበባቲ ወረዳ ከ181 ...
30/05/2025

"ትልልቅ ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስ የዚህ ዘመን አመራር ና የህዝባችን ድምር ውጤት መገለጫ ነው። "
የአማራ ክልል መሬት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ እብሬ ከበደ

በባቲ ወረዳ ከ181 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ በክልልሉ ባጀት እየተሰራ የሚገኝ የመንገድ ልማት ፕሮጀክት ስራ ና በአዋሬ ቀበሌ በሀርቡ ወንዝ ላይ በ 38 ሚሊየን ብር ወጭ ግንባታው በፍጥነትና በጥራት እየተሰራ የሚገኛውን የድልድይ ግንባታ ፕሮጀክት መጎብኘቱ ተገለፀ።

የአማራ ክልል መሬት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ እብሬ ከበደ፤ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ሀላፊ አቶ አህመድ ሁሴን ፤የባቲ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ አብዱና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዛሬው እለት የመስክ ምልከታ ተደርጓል።

በጉብኝቱ ወቅት በወረዳው የሚገኙ ሁሉም ፕሮጀክቶች በተቀመጠላቸው የእቅድ ጊዜ መሰረት አጠናቆ ለማስመረቅ ስራዎቹ በፍጥነት ና በጥራት እየተከናወኑ መሆኑን በመስክ ጉብኝቱ ለመረዳት እንደተቻለ ተገልጿል ።

በመስክ ጉብኝቱ የተሳተፉ የክልል እና የዞን ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እንደገለፁት የወረዳው አስተዳደር ፕሮጀክቶቹ በአጭር ጊዜ በጥራትና በፍጥነት እንዲያጠናቀቅ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አድንቀዋል ።

አሁንም ቀሪ የፕሮጀክቱ ስራዎች በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ ከስካሁኑ በበለጠ አስፈላጊውን ድጋፍ ትብብር በ ማድረግና ለሚያጋጥሙ ችግሮች የጋራ መፍትሄ በመስጠት ሥራው ከተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ሲሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።

የሚዲያ ይዘት ማበልጸግ ዝግጅትና ስርጭት

"ባገኘነው የሙያ ስልጠና ታግዘን በመረጥነው የስራ መስክ በመሰማራት ራሳችንን እና ቤተሰባችንን ለመለወጥ ተዘጋጅተናል።"UNDP P S F ፕሮጀክት የታቀፉ ሰልጣኝ ተሳታፊዎች!! የባቲ ወረዳ ስ...
30/05/2025

"ባገኘነው የሙያ ስልጠና ታግዘን በመረጥነው የስራ መስክ በመሰማራት ራሳችንን እና ቤተሰባችንን ለመለወጥ ተዘጋጅተናል።"

UNDP P S F ፕሮጀክት የታቀፉ ሰልጣኝ ተሳታፊዎች!!

የባቲ ወረዳ ስራና ስልጠና ጽ/ቤት በUNDP P S F ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ስራ ለሚሰማሩ አካላት እየሰጠው ያለው የ 3 ቀን ስልጠና በዛሬው እለት መጠናቀቁ ተገለፀ።

የወረዳው ስራና ስልጠና ጽ/ቤት ባለሙያ ና የፕሮጀክቱ ፎካል ፐርሰን አቶ ሃይለማርያም በላይ እንደገለፁት ከ17 ቱም የወረዳው ቀበሌዎች የተመለመሉ 43 ት ሰልጣኞች ለ3 ተከታታይ ቀናት በኮሌጁ ብቁ መምህራን በሂወት ክህሎት ፣ በኢንተር ፕነረር ሽብ ፣ ና በቢዝነስ ሽብ ስልጠናውን በቦታው ተገኝተው በትኩረት ና በንቃት ተከታትትለው ማጠናቀቃቸውን ተናግረዋል ።

በዛሬው እለትም ሁሉም ሰልጣኝ ሰርቼ እለወጥበታለሁ ብሎ በመረጠው የስራ ዘርፍ ወደ ስራ እንዲገባ ከፕሮጀክቱ ለእያንዳንዳቸው የተመደበላቸውን የ 500$ ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ባወጡት በእያንዳንዳቸው የባንክ አካውንት ገቢ ይደረጋል ብለዋል።

በቀጣይም ሰልጣኞቹን የስራ ውል በማስገባት በተዋቀረ ኮሚቴ አማካኝነት የመረጡትን የስራ አማራጭ ታሳቢ ባደረገ መልኩ የግዥ ሂደቱ እደሚፈፀም ተናግረዋል ።
ጽ/ቤቱም አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ በመስጠት በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ውጤታ እንዲሆኑ በ ባለሙያዎች ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር ያደርጋል ሲሉ ተናግረዋል ።

ስልጠናውን በባቲ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ የተከታተሉ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት ያገኙት ስልጠና በሚሰማሩበት የስራ ዘርፍ ላይ እንዴት ውጤታማ ና ተጠቃሚ እንደምሆን በቂ እውቀትና ግንዛቤ ያገኘንበት በመሆኑ ተደስተናል ብለዋል።

በቀጣይ በተደረገልን ድጋፍ አማካኝነት በተሰጠን ስልጠና መሠረት ጠንክረን በመስራት ከራሳችን አልፈን ቤተሰባችንንም ለመጥቀም ተዘጋጅተናል ብለዋል።

በመጨረሻም የUNDP PSF ፕሮጀክት በዚህ አይነቱ የስራ መስክ እንድንሰማራ ና ሰርተን እንድንለወጥ ላደረገልንን ሁለንተናዊ ድጋፍ እናመሰግናለን ሲሉ ተናግረዋል ።

የሚዲያ ይዘት ማበልጸግ ዝግጅትና ስርጭት

የባቲ ወረዳ ና የባቲ ከተማ አስተዳደር የአለም አካባቢ ቀንን ምክንያት በማድረግ የጋራ የፅዳት ዘመቻ ና የፓናል ውይይት ማካሄዳቸው ተገለፀ።ግንቦት፣ 22/2017 ዓ.ም (ባቲ ወረዳ መንግስት ...
30/05/2025

የባቲ ወረዳ ና የባቲ ከተማ አስተዳደር የአለም አካባቢ ቀንን ምክንያት በማድረግ የጋራ የፅዳት ዘመቻ ና የፓናል ውይይት ማካሄዳቸው ተገለፀ።

ግንቦት፣ 22/2017 ዓ.ም (ባቲ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን):

በኦሮሞ ብ/ዞን የባቲ ወረዳ አስተዳደር ከ ባቲ ከተማ አስተዳደር የአካባቢና ደን ጥበቃ ተጠሪ ጽ/ቤት ጋር በመሆን "የፕላስቲክ ብክለት እንግታ" በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ52ኛ ጊዜ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ32ኛ ጊዜ የአለም አካባቢ ቀንን አስመልክቶ በጽዳት ዘመቻና በፓናል ውይይት በጋራ እክብረዋል።

በፓናል ውይይቱ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን መሬት መምሪያ ሀላፊ አቶ ዘሪሁን በቀለ አካባቢያችንን ከብክለት መከላከልና በጋራ በማፅዳት ንፁህ እና ውብ ለነዋሪዎቿ ምቹ ና ተስማሚ አካባቢን ፣ከተማን የመፍጠር ተግባር የአንድ ሰሞን ሳይሆን የዘወትር ተግባራችን መሆን አለበት ብለዋል።

የአለም የአካባቢ ቀንን አስመልክቶ የውይይት መነሻ ሰነድ በባቲ ወረዳ ግብርና ጽ /ቤት ባለሙያ በአቶ ወንድሜነህ አሰፋ የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይም ከተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ምክክር ተደርጓል።

በውይይቱም ላይ ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ አለማስወገድ የሚያስከትለውን ጉዳት ደረቅ ቆሻሻን በተመለከተ በኢትዮጵያ ያለውን ህግና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በፓናል ውይይት ተሳታፊዎች ሰፋ ያለ ሃሳብና አስተያየት ተሰጥቶበት የፓናል ውይይቱ ተጠናቋል ።

የሚዲያ ይዘት ማበልጸግ ዝግጅትና ስርጭት

Qopheessummaa Aanaa Baateefi Magaalaa Baateetiin  Guyyaan Ayyaana Naannoo Addunyaa  dhaadannoo "Faalama Pilaastikii Haa ...
30/05/2025

Qopheessummaa Aanaa Baateefi Magaalaa Baateetiin Guyyaan Ayyaana Naannoo Addunyaa dhaadannoo "Faalama Pilaastikii Haa Ittisnuu" jedhuun kabajamaa jira.

Caamsaa 22/2017 Komunikeeshinii A/Baatee

MBNA Bulchiinsa Saba Oromootti Waajjirri Eegumsa Naannoo fi Kunuunsa Bosonaa Aanaa Baateefi Magaalaa Baatee kabaja guyyaa Ayyaana Naannoo Addunyaa bara 2017 Galma bulchiinsa magaalaa Baateetti kabajaa jira.

Ayyaana kana irratti obbo Zarihun Baqqalee I/G Qajeelcha Lafaa Bulchiinsa Saba Oromoo, obbo Abduu Ahimad kantiibaa magaalaa Baatee, gaggeessitoonni aanaafi magaalaa Baatee akkasumas gahee qabeessonni irratti argamaniiru.

Waltajjicha irratti haasaa baniinsaa kan godhan obbo Zaruhun Baqqalee I/G Qajeelcha Lafaa Bulchiinsa Saba Oromoo" Qulqullummaan Qaroomina waan taheef naannoo keenya faalama irraa bilisa goonee biyya qulqulluu haa uumnuu" jedhaniiru.

Sanada marii dhiyaateen faalamaan wal qabatee haala addunyaan irra jirtu dhiyaateera. haa tahuu malee biyyi keenyaa itti fayyadama wallaaluun faalama pilaastikiiitiin miidhamaa jiraachuun ibsameera. pilaastikiin bakka hundatti harca'u akka salphaatti qilleensaafi bishaaniin fudhatamuun naannoo hunda kan fasalan akkasumas biyyeen kan hin nyaattamne waan tahaniif bakka arginetti darbuu osoo hin taane, dhabamsiisuu ykn walitti qabuun bakka deebisnee itti fayyadamuu qabnutti erguu qabna jedhameera. kana malees seera dhabamsiisa faalamaa hordofuu akka qabnu ibsameera.

Waltajjii kana kan dursan Aadde Zaharaa Saanii I/Gtuu Waajjira Eegumsa Naannoofi Kunuunsa Bosonaa Aanaa Baateefi Obbo Habiib Mahammad I/G Afa Yaa'ii Magaalaa Baatee yeroo tahan Aadaa dhamamsiisa faalamaa naannoo keenyaa ilaalchisee hirmaattota waliin marii bal'aa gochaa jiru.

"Faalama pilaastikaa ittisuun naannoo qulqulluu haa uumnuu"!

Address

Bati

Opening Hours

09:00 - 17:00

Telephone

+251335530079

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kominikeeshinii Mootummaa Aanaa Baateeባቲ ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share