Henok Zegabiwe - ሄኖክ ዘጋቢው

Henok Zegabiwe - ሄኖክ ዘጋቢው Content Creator Reliable News Source

የሮማው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ❗️የሮማው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ቫቲካን አስታውቋል። የሮማው ጳጳስ እና የካ...
21/04/2025

የሮማው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ❗️

የሮማው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ቫቲካን አስታውቋል።

የሮማው ጳጳስ እና የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን መሪ ፖፕ ፍራንሲስ በ2013 የፈረንጆቹ ዓመት ነበረ በነዲክቶስ 16ኛን በመተካት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት፡፡

በዚህ ወር መጨረሻ አከባቢ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ሊኖር እንደሚችል ሲነገር ነበረ፣ ሆኖም መንግስት ይህን ጭማሪ በወሩ አጋማሽ ላይ ድንገት ዱብ አድርጎታል፡፡የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ለመጨረሻ ...
23/03/2025

በዚህ ወር መጨረሻ አከባቢ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ሊኖር እንደሚችል ሲነገር ነበረ፣ ሆኖም መንግስት ይህን ጭማሪ በወሩ አጋማሽ ላይ ድንገት ዱብ አድርጎታል፡፡

የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ለመጨረሻ ገለዜ ተግባራዊ የሆነው ባለው ታህሳስ ወር በገና በዓል ዕለት ነበር፡፡

እነሆ ይህ ጭማሮ ሶስት ወራትን ገደማ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል፡፡

ጭማሪው ገና የሚቀጥል ሲሆን ልክ እንደ አሁኑ ሁሉ ሰኔ ላይም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ጭማሪ እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡

በዛሬዉ የዋጋ ጭማሪ አንድ ሊትር ቤንዚን የ 10 ብር ጭማሪ ተደርጎበት በታህሳስ ወር ሲሸጥበት ከነበረው 101.47 ብር ወደ 112 ብር ገብቷል፡፡

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ከዛሬ መጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ይፋ አድርጓል።

በዚሁ መሰረት አንድ ሊትር ቤንዚን ሲሸጥበት ከነበረው 101.47 ብር የ10 ብር ገደማ ጭማሪ ተደርጎበት በ-112.67 ብር እንዲሸጥ ወስኗል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ፣ ኬሮሲን 107.93 ብር ፣ ነጭ ናፍጣ 107.93 ብር፣ ቀላል ጥቁር ናፍጣ 109.22 ብር እንዲሁም ከባድ ጥቁር ናፍጣ 106.75 ብር በሊትር የሚሸጥ ይሆናል።

በሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬዲዮ በጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ በሚቀርበው ሸገር ካፌ መሰናዶ ላይ ሙሁራዊ ትንታኔ በመስጠት የሚታወቁት የዩኒቨርሲቲ መምህርት ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር) ለስራ ጉዳ...
17/03/2025

በሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬዲዮ በጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ በሚቀርበው ሸገር ካፌ መሰናዶ ላይ ሙሁራዊ ትንታኔ በመስጠት የሚታወቁት የዩኒቨርሲቲ መምህርት ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር) ለስራ ጉዳይ ባመሩበት ሀገር በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርትነትና የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር በመሆን ያገለገሉት ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ(ዶ/ር) ከዚህ አለም በሞት መለየታቸው ሸገር ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው ዜና ዕረፍት አስነብቧል፡፡

በኮኔል ዩኒቨርሲቲ እና በኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ትምህርታቸውን የተከታተሉት ዶ/ር ኤልሳቤጥ በሸገር ሬዲዮ በ ሸገር ካፌ ፕሮግራም በሥነ ጥበብና ታሪክ ጉዳዮች ላይ በተደጋጋሚ በመቅረብ እውቀታቸውን አካፍለዋል፡፡

ዶ/ር ኤልሳቤጥ ለስራ ጉዳይ ባመሩበት በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ሻርጃ ከተማ ማረፋቸውንና አስከሬናቸውን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ሸገር ዘግቧል፡፡

ለዶ/ር ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ ወዳጅ እና ዘመዶች የዝግጅት ክፍላችን መፅናናትን ይመኛል፡፡

አመሻሹን መጠነኛ የዝናብ ካፊያ በማስተናገድ ላይ የምትገኘው አዲስበባ ከበድ ያለ የመሬት ንዝረት ጎብኝቷታል፡፡ዛሬ ከምሽቱ 3 ሰዓት ከ55 ገደማ አዋሽ አከባቢ ከበድ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ ያ...
16/03/2025

አመሻሹን መጠነኛ የዝናብ ካፊያ በማስተናገድ ላይ የምትገኘው አዲስበባ ከበድ ያለ የመሬት ንዝረት ጎብኝቷታል፡፡

ዛሬ ከምሽቱ 3 ሰዓት ከ55 ገደማ አዋሽ አከባቢ ከበድ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ ያጋጠመ ሲሆን ንዝረቱም አዲስአበባን ጨምሮ በበርካታ የኢትዮጵያ አከባቢዎች ተሰምቷል፡፡

የመሬት ንቅናቄው በተለይ በአዲስአበባ በተለያዩ አከባቢዎች ከሌላው ጊዜ በተለየ ጠንከር ብሎ ለተወሰኑ ሰከንዶች ያህል መሰማቱን ለዝግጅት ክፍላችን ከደረሱ ጥቆማዎችና ዘጋቢዎቻችን ካላኩልን መረጃ ተረድተናል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአፋር ክልል በሬክተር ስኬል 5.1 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ዛሬ እሁድ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ/ም ምሽቱን መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤትን ጠቅሶ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘገባ አስነብቧል፡፡

ንዝረቱ በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የተሰማው ርዕደ መሬት፤ ከአዋሽ ከተማ በስተሰሜን 50 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተከሰተ መሆኑን ተቋሙ አስታውቋል።

በመጨረሻም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዘደንት በመሆን ላለፉት ሁለት ዓመታት ገደማ በስልጣን ላይ የቆዩት አቶ ጌታቸው ረዳ ከስልጣን ሊነሱ ስለመሆናቸው ተሰምቷል፡፡ከወደ ትግራይ በኩል ያሉ...
15/03/2025

በመጨረሻም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዘደንት በመሆን ላለፉት ሁለት ዓመታት ገደማ በስልጣን ላይ የቆዩት አቶ ጌታቸው ረዳ ከስልጣን ሊነሱ ስለመሆናቸው ተሰምቷል፡፡

ከወደ ትግራይ በኩል ያሉ አክቲቪስቶች እና ጋዜጠኞች አቶ ጌታቸው ረዳ ከሀላፊነት ተነስተው በምትካቸው ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ሊሾሙ እንደሆነ በመፃፍ ላይ ይገኛሉ፡፡

ባለፈው ማክሰኞ የአቶ ጌታቸው ረዳ ምክትል፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዘደንት እና የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ከመቀለ ወደ አዲስአበባ በማምራት ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር መክረው መመለሳቸውን ሪፖርተር የእንግሊዘኛው ዕትም ጋዜጣ ዘግቧል፡፡

ሌ/ጀነራሉ የእነደ/ፅዮንን ቡድን እና የፌደራሉን መንግስት ለማስማማት ከመቀለ ይዘውት የመጡትን አጀንዳ በማቅረብ ሰፊ ምክክር ያደረጉ ሲሆን በመጨረሻም ሌ/ጀነራሉ በአቶ ጌታቸው ረዳ ምትክ እንዲሾሙ የጋራ መግባባት ላይ ስለመደረሱ ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ምንጮች የተሰማው፡፡

ከወራት በፊት ደ/ፅዮን ገ/ሚካኤል እና አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ እና ጀነራል ፃድቃን በተገኙበት በጠ/ሚር ዐቢይ አህመድ ፅ/ቤት ጥብቅ የተባለ ምክክር በተደረገበት ወቅት እነደ/ፅዮን የአቶ ጌታቸውን ከስልጣን መነሳት እና በሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ የመተካት ሀሳብ አቅርበው በጠቅላዩ ውድቅ ተደርጎባቸው እንደነበረ በወቅቱ ተዘግቦ ነበር፡፡

ታዲያ አሁን የፌደራሉን መንግስት እና ህወሀትን በሚያስማማ መንገድ አቶ ጌታቸው ከስልጣን ተነስተው በምትካቸው ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ እንደሚሾሙ እየተነገረ ነው፡፡

ይህ አዲስ ሹም ሽር የትግራይን ፖለቲካ ያረጋጋል በሚል ተስፋ የተደረገበት ሲሆን በዚሁ መሰረት ጀነራሉ በቀናት ጊዜ ውስጥ የሹመት ደብዳቤ ይሰጣቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

አዲሱ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዘደንት ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ገና በታዳጊነት ዕድሜያቸው የህወሀትን ትጥቅ ትግል ተቀላቅለው ደርግን የተዋጉ ከዚያም ከ1983 ዓ/ም አንስቶ በመከላከያ ውስጥ በከፍተኛ አመራርነት ያገለገሉ የጦር መሪ ናቸው፡፡

ከመከላከያ በጡረታ ሊገለሉ በተቃረቡባቸው የመጨረሻዎቹ ሶስት ዓመታት በመንግስታቱ ድርጅት ሰላም አስከባሪ ጦር ውስጥ ወደ ሱዳን በመዝመት ተልዕኮአቸውን ተወጥተዋል፡፡

ከሱዳን መልስ ጡረታ የወጡት ጀነራሉ ኋላ የትግራዩ ጦርነት በተቀሰቀሰበት ወቅት የትግራይ ሰራዊት በመባል የሚታወቀውን ጦር በመምራት አዋግተዋል፡፡

ጦርነቱ በፕሪቶሪያው የዘላቂ ግጭት ማቆም ስምምነት ካበቃበት ጊዜ አንስቶም በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ የአቶ ጌታቸው ምክትልና የፀጥታው ዘርፍ መሪ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡

በፕሪቶሪያው ስምምነት ላይ እንደተመላከተው የጊዜያዊ አስተዳደሩን መሪ የመምረጥ ስልጣን የጠ/ሚሩ እንደመሆኑ ጠ/ሚር ዐቢይ ከዚህ ቀደም ከአቶ ጌታቸው ረዳ በፊት ለአስተዳደሩ ሀላፊነት ደ/ፅዮን እጩ ሆነው በቀረቡ ጊዜ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጋቸውና አቶ ጌታቸውን መሾማቸው ይታወሳል፣ አሁን ደግሞ አቶ ጌታቸውን በማንሳት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደን በእርሳቸው ፈንታ ለመሾም ተሰናድተዋል ተብሏል፡፡

Address

Bole
ADDISABEBA,KOTEBE

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Henok Zegabiwe - ሄኖክ ዘጋቢው posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share