Ethio News

Ethio News ለተሻለ መረጃ ስለመረጡን እናመሰግናለን

አሜሪካ የኢራን የኒውክሌር ተቋማትን በቦምብ ደበደበችአዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጥቃቱ በሶስት የኒውክለር ተቋማት ላይ የተፈጸመ ነው ።       በተራሮች መካከል የሚገኝ...
22/06/2025

አሜሪካ የኢራን የኒውክሌር ተቋማትን በቦምብ ደበደበች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጥቃቱ በሶስት የኒውክለር ተቋማት ላይ የተፈጸመ ነው ።

በተራሮች መካከል የሚገኝውና ግዙፉ ፎርዶው የኒውክሌር ተቋም ደግሞ ዋነኛው ሰለባ ነው።

የቦንብ ድብደባው በተሳካ ሁኔታ መፈጸሙን የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አረጋግጠዋል።

ኢራን የሰላም አማራጭ የማትከተል ከሆነ ጥቃቱ ይቀጥላል ሲሉም ትራምፕ ዝተዋል።

አሜሪካ በእስራኤል እና ኢራን ግጭት በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ አቋሜን አሳውቃለሁ ካለች ዛሬ ሶስተኛ ቀኗ ነበር።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

ከአሰቃቂው የአውሮፕላን አደጋ የተረፈችው ነፍስአዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017  ቪሽቫሽ ኩማር ራሜሽ ትውልደ ህንዳዊና የእንግሊዝ ዜግነት ያለው ግለሰብ ነው። ግለሰቡ ቀደም ብሎ ከእንግሊዝ ዘመ...
12/06/2025

ከአሰቃቂው የአውሮፕላን አደጋ የተረፈችው ነፍስ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 ቪሽቫሽ ኩማር ራሜሽ ትውልደ ህንዳዊና የእንግሊዝ ዜግነት ያለው ግለሰብ ነው።

ግለሰቡ ቀደም ብሎ ከእንግሊዝ ዘመዶቹን ለመጠየቅ ወደ ህንድ ያቀና ሲሆን÷ በዛሬው ዕለት በህንድ ከተከሰተው አሰቃቂ የአውሮፕላን አደጋ መትረፉ እያነጋገረ ይገኛል፡፡

ቪሽቫሽ ኩማር ራሜሽ ከህንድ ወደ ለንደን እየተመለሰ በነበረበት ወቅት በተሳፈረበትና ቦይንግ 787-8 የሚል ስያሜ ባለው አውሮፕላን አሰቃቂ አደጋ ተከስቷል።

ይሁን እንጂ ቪሽቫሽ በአውሮፕላኑ መስኮት በኩል መቀመጡ ከአደጋው ህይወቱ እንዲተርፍ ምክንያት መሆኑን ተናግሯል፡፡

ግለሰቡ ከአሕመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያ አውሮፕላኑ ከተነሳ 30 ሴኮንድ በኋላ ከፍተኛ ድምፅ ማሰማት መጀመሩን እና ወዲያው በሴኮንዶች ልዩነት መከስከሱን ለሂንዱስታን ታይምስ ገልጿል፡፡

ከአውሮፕላኑ መከስከስ በኋላ ራሴን ስቼ ነበር፤ ነገር ግን ስነቃ የሞቱ ሰዎች አስከሬን አጠገቤ ነበር፤ የሞቱ ሰዎችን አስከሬን ሳይ ተነስቼ ሮጥኩኝ ሲልም አክሏል፡፡

በአደጋው ሰውነቱ ላይ መጠነኛ ጉዳት ደርሶበት የነበረው ግለሰቡ÷ ሰዎች ደርሰው ወዲያ ወደ ሆስፒታል እንደወሰዱት እና ህክመናውን እየተከታተለ እንደሚገኝ ተናግሯል፡፡

ግለሰቡ በእግሩ፣ በደረቱ እና በዓይኖቹ ላይ መጠነኛ ጉዳት እንደደረሰበት የኤ ኤን አይ ዘገባ አመላክቷል፡፡

በህንድ በተከሰተው የአውሮፕላን አደጋ እስካሁን የ204 ሰዎች አስከሬን የተገኘ ሲሆን÷ ቀሪ ሰዎችን የመፈለግ ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

በሚኪያስ አየለ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

!

ነገሌ ቦረና፤ ሰኔ 4/2017በነገሌ ቦረና ሆስፒታል ከአንዲት የ70 ዓመት አዛውንት 14 ኪሎ ግራም የማህጸን እጢ በቀዶ ህክማና ተወገደ፡፡በሆስፒታሉ ከፍተኛ የህክምና ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ...
12/06/2025

ነገሌ ቦረና፤ ሰኔ 4/2017

በነገሌ ቦረና ሆስፒታል ከአንዲት የ70 ዓመት አዛውንት 14 ኪሎ ግራም የማህጸን እጢ በቀዶ ህክማና ተወገደ፡፡

በሆስፒታሉ ከፍተኛ የህክምና ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ታሪኩ ገልዳ ለኢዜአ እንደገለጹት ሁለት ሰዓታት በፈጀው ቀዶ ህክምና እሳቸውን ጨምሮ ሰባት የህክምና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

ይህም በሆስፒታሉ የህክምና ታሪክ ከ70 አመት አዛውንት ማህጸን 14 ኪሎ ግራም መጠን ያለው እጢ በቀዶ ህክምና ሲወጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ብለዋል፡፡

በነገሌ ቦረና ሆስፒታል ደረጃ ከመለስተኛ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ በስተቀር የዚህን ያክል ቀዶ ህክምና ተደርጎ እንደማይታወቅም ገልጸዋል፡፡

ከአዛውንቷ ማህጸን በቀዶ ህክምና የተወገደው እጢ ለ16 አመታት ያክል አብሯቸው እንደኖረ በምርመራ መረጋገጡንም ተናግረዋል።

ዜጎች የጤና ችግር ሲገጥማቸው በባህላዊ መንገድ ለማስወገድ ከመንቀሳቀስ ይልቅ ወደ ህክምና ተቋም ቢመጡ በአጭር ጊዜ መፍትሄ እንደሚያገኙም መክረዋል፡፡

በምስራቅ ቦረና ዞን ሊበን ወረዳ የቀርሳማሊ ቀበሌ ነዋሪዋ ወይዘሮ ሀቢባ አሬሮ፤ በሽታው ምግብ ስለከለከላቸው ውሀና ወተት ብቻ በመጠጣት ለዓመታት እንዳሳለፉ ተናግረዋል፡፡

በባህላዊ መድኃኒትና በጤና ተቋማት ህክምና ለመዳን ባደረጉት ክትትል በብዙ ሺህ የሚቆጠር ገንዘብ ወጪ ማድረጋቸውን አስታውሰዋል፡፡

የጉበት በሽታ ነው በሚል በየ6 ወሩ ከውስጣቸው በመርፌ ውሀ ይቀዳ እንደነበር የተናገሩት አዛውንቷ ወደ ነገሌ ቦረና ሆስፒታል በመምጣት ባገኙት ህክምና እፎይታ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡

ወይዘሮ ሀቢባ፤ ከእንስሳት እርባታ ጎን ለጎን በሰብል ልማት የሚተዳደሩ የዘጠኝ ልጆች እናት መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡

" ከስህተታቸው የማይማሩ ጥቂት የቀድሞ የህወሓት ሀይሎች ለስልጣን ሲሉ ወደ ግጭት ለመግባት ፍላጎት እንዳላቸው እየገለጹ ነው " - አቶ ጌታቸው ረዳየጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች...
24/05/2025

" ከስህተታቸው የማይማሩ ጥቂት የቀድሞ የህወሓት ሀይሎች ለስልጣን ሲሉ ወደ ግጭት ለመግባት ፍላጎት እንዳላቸው እየገለጹ ነው " - አቶ ጌታቸው ረዳ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ?

አቶ ጌታቸው ረዳ እና አብርሃም በላይ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ከሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ጋር በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ውይይት እያደረጉ ነው።

አቶ ጌታቸው በዚሁ ወቅት " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መፈረሙ ትግራይን የጦርነት አውድማ የማድረግ ፍላጎት ያላቸው አካላትን ምኞት ያስቀረ ነው " ብለዋል፡፡

" የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ በህገ-መንግስቱና በፕሪቶሪያው ስምምነት ተፈናቃዮችን በሚፈለገው ልክ ወደ ቀያቸው መመለስ አልተቻለም " ሲሉ ገልጸዋል።

" ለዚህም በትግራይ ክልል በስልጣን ላይ ያለው ኃይል የሕዝቡን አጀንዳ ከማስቀደም ይልቅ ስልጣንና ስልጣን ብቻ በማለቱና እዚህ ግባ የሚባል ስራ ባለመስራቱ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

አቶ ጌታቸው በትግራይ ክልል አሁን የተፈጠረው ችግር የትግራይ ፖለቲከኞች የፈጠሩት መሆኑን ገልጸዋል። አመራሩ የያዘው ግትር አቋም ትግራይን ከአደጋ ስጋት እንዳትወጣ እያደረጋት ተናግረዋል።

" የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ዓላማው ችግሮች በህገ-መንግሥታዊ አውድ እንዲፈቱ ማድረግ ቢሆንም፤ ከስህተታቸው የማይማሩት ጥቂት የቀድሞ የህወሓት ሀይሎች ለስልጣን ሲሉ ወደ ግጭት ለመግባት ፍላጎት እንዳላቸው እየገለጹ ነው " ብለዋል።

" ከአሁን ቀደሞ የተፈጠረው ግጭት የትግራይን ህዝብ ዋጋ አስከፍሏል። አሁንም የትግራይ ህዝብ ተመሳሳይ ነገር እንዳይገጥመው የእነዚህን ሀይሎች እኩይ ፍላጎት እንዲያውቅ እያጋለጥን ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" በስልጣን መቀጠል የሚፈልጉ ጥቂት የአመራር ቡድኖች ልጆቻቸውን አስቀምጠው የደሀ ልጆችን ለእሳት እንደማገዱ በተግባር ያሳዩ ናቸው " ያሉ ሲሆን " ይህ ኃይል ' የእኔ ስልጣን ካልተረጋገጠ ሁሉም ነገር ገደል ይግባ ' የሚል ነው ዓላማውም ከተጠያቂነት ለማምለጥ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

የትግራይ ህዝብ ሰላም ፈላጊ መሆኑን ገልጸው " ከተጠያቂነት ለማምለጥ ዳግም የትግራይ ህዝብን ወደ ግጭት ለማስገባት የሚያደርገውን ጥረት ማጋለጥ ይገባል " ብለዋል።

" የትግራይ ክልል ግንኙነት ከፌዴራል መንግስት ጋር መሆኑ ግድ ነው ' ከእከሌ ጋር ሆኜ ማጥቃት እችላለሁ ' የሚለውን ማጋለጥ አለብን " ሲሉ ተናግረዋል።

" የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነትን በትክክል ገቢራዊ ለማድረግ ከፌዴራል መንግስት ጋር ያለው ግንኙነት መጠናከር አለበት የትግራይ ህዝብ ለተወሰኑ ሰዎች የስልጣን ጥም መሞት የለበትም " ብለዋል።

" በአሁኑ ወቅት 99 በመቶ የሚሆነው አመራር ሰላም ፈላጊ ነው ፤ ጥቂት የግጭት ጠማቂዎች በጋራ ልንታገላቸው ይገባል "ሲሉ ገልጸዋል።

መረጃው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ነው።

" በላያችን ላይ ያንዣበበው የደህንነት ስጋት መፍትሄ እስኪበጅለት ድረስ ለጊዜው ማንኛውም የዳኝነት አገልግሎት መስጠት አቁመናል " - ፍርድ ቤትዛሬ ግንቦት 12 /2017 ዓ.ም በመቐለ ማእከ...
21/05/2025

" በላያችን ላይ ያንዣበበው የደህንነት ስጋት መፍትሄ እስኪበጅለት ድረስ ለጊዜው ማንኛውም የዳኝነት አገልግሎት መስጠት አቁመናል " - ፍርድ ቤት

ዛሬ ግንቦት 12 /2017 ዓ.ም በመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት ደጃፍ የተለጠፈው ማስታወቂያ፥ " በላያችን ላይ ያንዣበበው የደህንነት ስጋት መፍትሄ እስኪበጅለት ድረስ የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት ጨምሮ በሰባቱ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ዳኞችና ፍርድ ቤቶች ለጊዜው ማንኛውም የዳኝነት አገልግሎት መስጠት አቁመዋል " ይላል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የማስታወቂያውን ትክክለኝነት ለማረጋገጥ ሐውልት ፣ ዓይደር ፣ ቀዳማይ ወያነ ወደ ተባሉ ክፍለ ከተሞች ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

በዚህም ማንኛውም አይነት አገልግሎት መቆሙን አረጋግጧል።

ዛሬ ከሰዓት በኋላ ደግሞ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፍርድ ቤቶቹ መዘጋታቸው አረጋግጦ ለመዝጋታቸው ምክንያት የሆነ ችግር አጣርቶ እርምጃ እንደሚወስድ ቃል ገብቶ ዳኞቹ ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ ተማፅኗል።

ለመሆኑ ፍርድ ቤቶቹ እስከ ስራ ማቆም እርምጃ እንዲወስዱ የገፋፋቸው ምክንያት ምንድን ነው ?

ባለፈው አርብ ግንቦት 8/2017 ዓ.ም በመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት ዘውዱ የተባለች ሟች ላይ የተፈፀመ ወንጀል ለመዳኘት በተጠራው ችሎት ላይ የበዳይ ተጠርጣሪ ቤተሰቦች ችሎቱ ከመረበሽ በዘለለ በዳኞችና አቃቤ ህግ ላይ መጥፎ ቃላት በመጠቀም ዝተዋል።

በረብሻው ምክንያትም በዛው ቀን በተጠርጣሪዎች ላይ ሊሰጥ የነበረው የመጨረሻ ውሳኔ ተሰርዞ ለግንቦት 18/2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቆጠሮ ተይዘዋል።

ይህንንና ሌሎች ስጋቶች " አላሰራ ብለውኛል " ያለው የትግራይ ዳኞች ማህበር በፍትህ አረጋጋጭ ዳኞች ላይ የሚታዩ ችግሮች ካልተፈቱ እስከ ስራ ማቆም የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስድ ግንቦት 9/2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አሳውቆ ነበር።

ይህንን ተከትሎ ዛሬ ግንቦት 12/2017 ዓ.ም የስራ ማቆም እርምጃ ወስዷል። እርምጃው የጀመረበት እንጂ የሚቆምበት ቀን አልተገለፀም።

ዳኞችና ፍርድ ቤት ለጠሩት ስራ የማቆም አድማ ምክንያት የሆነው ችግር ትኩረት ሰጥቶ እንደሚፈታ የገለፀው የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ዳኞች የህዝባዊ አገልግሎታቸውን እንዲቀጥሉ በማመፀን የተፈጠረው ችግር በአስቸኳይ አጣርቶ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።

EthiopiaFamilyMekelle

19/05/2025
" የጤና ባለሙያዎች ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ደርሷል " - ማኅበሩየኢትዮስፕየ ነርሶች ማህበር ፥ የጤና ባለሙያዎች ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ መድረሱን ገለጸ። ጥያቄ ስለጠየቁ የታሰሩ ባለሙያዎች እንዲፈ...
19/05/2025

" የጤና ባለሙያዎች ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ደርሷል " - ማኅበሩ

የኢትዮስፕየ ነርሶች ማህበር ፥ የጤና ባለሙያዎች ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ መድረሱን ገለጸ። ጥያቄ ስለጠየቁ የታሰሩ ባለሙያዎች እንዲፈቱ እንዲሁም ዛቻና ማስፈራሪያዎች እንዲቆሙ ጠይቋል።

ማህበሩ ይህን ያለው በተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች እየተካሄደ ባለዉ የጤና ባለሙያዎች ወቅታዊ እንቅስቃሴ ዙሪያ በላከው መግለጫ ነው።

ማህበሩ ፤ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ለደረሰው የጤና ባለሙያዎች ጉዳይ መንግስት ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቋል።

ማህበሩ ምን አለ ?

- በአሁኑ ሰዓት እየተነሱ ያሉት የባለሙዎቹ እና የማህበሩ አባላት ጥያቄዎች ማለትም፦
• የተቋማት ግብዓት እጥረት መኖር
• የደመወዝ ማነስ
• የጥቅማጥቅም አለመኖር
• የትምህርት እድል እና የደረጃ እድገት አለማግኘት
• የስራ ቦታ ደህንነት አለማግኘት ... ለረዥም ጊዜያት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ለውይይት ሲቀርቡ እና አጀንዳ ሆነው የቆዩ መሆናቸውን ገልጿል። ጉዳዩ አሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሰ በመሆኑም ሁኔታው የመንግስትን ትኩረት እንዲያገኝ ጠይቋል።

- " የህክምና አገልግሎት ተቋርጦ ወይንም ተስተጓጉሎ ጥያቄ ማቅረብ የጤና ተቋማቱም ሆነ ጤና ሙያተኛው ማዕከል የሆኑትን ታካሚዎች ለሞት ለእንግልት የሚዳርግ በመሆኑ የምንቀበለው አይደለም " ያለው ማህበሩ " ስራዎቹ በአስቸኳይ ወደነበሩበት እንዲመለሱ ሙያተኞቹ፣ የተቋማት ሃላፊዎችም ሆነ ጤና ሚኒስቴርና ባለድርሻ አካላት አፋጣኝ ውይይት እና የመፍትሄ አቅጣጫ በማስቀመጥ የመፍትሄ አካል እንዲሆኑ " ሲል ጠይቋል።

- " ጥያቄ ጠይቃችኋል " ወይም " አስተባብራችኋል " በሚል ምክንያት በእስር ላይ የሚገኙ ጤና ባለሙያዎች እንዲፈቱ ፤ በተቋማትም ሆነ በሌሎች አካላት የሚደረጉ ዛቻና ማስፈራሪያዎችም እንዲቀሙ ጠይቋል።

- ጥያቄ ያላቸው ነርሶችም ሆነ ሌሎች ሙያተኞች ለውይይት በሚዘጋጁ መድረኮች በመገኘት ጥያቄአቸውን እንዲያቀርቡ እና ለመፍትሄ ተባባሪ እንዲሆኑ ጠይቋል።

" በአደጋው ሕይወታቸዉን ያጡ ሰዎች ትክክለኛ ቁጥር 19 ሲሆን 13 ከባድ ጉዳት ደርሷል " - የግልግል በለስ ከተማ ፖሊስበበንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ግልግል በለስ ከተማ ዛሬ ረፋድ...
18/05/2025

" በአደጋው ሕይወታቸዉን ያጡ ሰዎች ትክክለኛ ቁጥር 19 ሲሆን 13 ከባድ ጉዳት ደርሷል " - የግልግል በለስ ከተማ ፖሊስ

በበንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ግልግል በለስ ከተማ ዛሬ ረፋድ በደረሰው የትራፊክ አደጋ የሟቾች ቁጥር 19 መድረሱን የከተማው ፖሊስ አዛዠ ኮማንደር ታዬ ጉርሜሳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ስካቫተር (ማሽን) ጭኖ መነሻዉን ቻግኒ ከተማ በማድረግ ወደ ዐባይ ግድብ አቅጣጫ ሲጓዝ የነበረው ተሳቢ ተሽከርካሪ ፍሬን በጥሶ መንገድ በመሳት የሕዝብ መዝናኛ ሆቴል ላይ በመውጣቱ ነው አደጋው የደረሰው።

በአደጋዉ እስካሁን የ19 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ 13 ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል።

" በአደጋው 30 ሰዎች ሞተዋል " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ትክክል እንዳልሆነ አዛዡ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ከዚሁ አደጋ ጋር በተያያዘ የክልሉ ፓሊስና የከተማው ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል የሟቾች ቁጥር 19 መሆኑን ገልጸዋል።

የክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን ከ19 ሟቾቹ መካከል 17 ወንዶች ሁለቱ ደግሞ ሴቶች እንደሆኑ አመልክቷል።

13 ሰዎች ደግሞ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ከነዚችም ውስጥ 11ዱ ወንዶች ሁለቱ ሴቶች እንደሆኑ አብራርቷል።

ፖሊስ " መኪናው መንገድ ስቶ ቤት ውስጥ ገብቶ ነው አደጋው የደረሰው ሹፌሩ መሪ እምቢ ብሎት ነው " ብሏል።

የከተማው ኮሚዩኒኬሽን መምሪያም በአደጋው የ19 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ 13ቱ ሰዎች ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ምን ያክል ሰዎች እንደሆኑ ገና ቁጥራዊ መረጃው እንዳልተለየ ገልጾ፣ " ገና አሁን ነው ሰው እየወጣ ያለው " ብሏል።

የአደጋውን መንስኤ ስንጠይቀውም፣ " የቴክኒክ ችግር ነው፤ ከኬላ ጀምሮ ፍሬን እምቢ ብሎት ነው የመጣው " የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

Via ቲክቫህ ኢትዮጵያ

ጤና ሚኒስቴር ምን አለ ?" የጤና ሞያ የሥራ ማቆም አድማ ከማይደረጉባቸው የሥራ ዘርፎች መካከል አንዱ መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል " - ጤና ሚኒስቴርዛሬ ምሽት ጤና ሚኒስቴር በወቅታዊ የጤና አ...
15/05/2025

ጤና ሚኒስቴር ምን አለ ?

" የጤና ሞያ የሥራ ማቆም አድማ ከማይደረጉባቸው የሥራ ዘርፎች መካከል አንዱ መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል " - ጤና ሚኒስቴር

ዛሬ ምሽት ጤና ሚኒስቴር በወቅታዊ የጤና አገልግሎት ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል።

ሚኒስቴሩ " መቼምና በምንም ሁኔታ መቋረጥ ከሌለባቸው ማኅበራዊ አገልግሎቶች አንዱ የጤና አገልግሎት ነው " ያለ ሲሆን " ዛሬን ጨምሮ ባለፉት ቀናት በመላ ሀገራችን በሚገኙ የጤና ተቋማት እንደ ወትሮው ሁሉ መደበኛ የጤና አገልግሎቶች ለማኅበረሰባችን ያለምንም መቆራረጥና መስተጓጎል እየተሰጡ ይገኛሉ " ብሏል።

" ይሄንን የተረዳው የጤና ባለሞያ በማኅበራዊ ሚዲያ በሚሠራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች ጫና ሳይገፋ የገባውን የሞያ ቃል ኪዳን እና መሐላ ጠብቆ ማኅበረሰቡን እያገለገለ በመሆኑ ምስጋና ይገባዋል " ሲል ገልጿል።

ሚኒስቴሩ " በጥቂት የማስተማሪያ የጤና ኮሌጆች/ተቋማት በመደበኛ የሥራ ገበታቸው ላይ ያልተገኙ የተወሰኑ ባለሞያዎች እንዳሉ መረጃዎች ደርሰውናል " ያለ ሲሆን " ከእነዚህ የጤና ባለሞያዎች መካከል ብዙዎቹ በሐሰተኛ መረጃ የተወናበዱ ሲሆኑ ጥቂቶቹ ደግሞ ጥፋትን ዓላማቸው ያደረጉ ናቸው " ብሏል።

" ድርጊቱ የራስን ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ወገን እና መላውን ማኅበረሰብ ከመጉዳት ባለፈ ከሞያ ሥነ ምግባር፣ ከሰብአዊነት አኳያ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው " ሲል ገልጿል።

" ከሕግ አኳያም የጤና ሞያ የሥራ ማቆም አድማ ከማይደረጉባቸው የሥራ ዘርፎች መካከል አንዱ መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል። የጤና ባለሞያዎች ጥያቄ እንኳን ቢኖራቸው በሥራ ገበታቸው ተገኝተው መደበኛ ሥራቸውን እያከናወኑ ጉዳያቸውን ለሚመለከተው አካል ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል " ብሏል።

" እነዚህ የጤና ባለሞያዎች ወደ ሥራ ገበታቸው ተመልሰው ማኅበረሰባቸውን እንዲያገለግሉ በየተቋማቸው ጥሪ ተደርጓል " ያለው ጤና ሚኒስቴር " መንግሥት የጤና ባለሞያውን ዘላቂ ተጠቃሚነት ባረጋገጠ መልኩ በጥናት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ለመስጠት ቀደም ብሎ የጤና አገልግሎት አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ 1362 /2017 አጸድቆ ደንብና መመሪያዎችን በማውጣት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል " ሲል ገልጿል።

" በጎ ኅሊና ያላቸው የጤና ባለሞያዎች ይህንን በመገንዘብ ሥራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ ጥሪ እናቀርባለን " ብሏል ሚኒስቴሩ።

" በሌላ በኩል ኅብረተሰቡ በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች በሚሠራጩ የሐሰት መረጃዎች ሳይረበሽ የሚፈልገውን የጤና አገልግሎት በተለመደው መልኩ በጤና ተቋማት ማግኘት እንደሚችል እናሳውቃለን " ብሏል።

" መንግሥት በሆደ ሰፊነት ችግሩን ለመፍታት ያሳየውን ትዕግሥት ወደጎን በመተው በሥራ ገበታቸው ላይ ባልተገኙ እንዲሁም በጤና ተቋሙም ሆነ ከጤና ተቋሙ ውጭ ሆነው ሁከትና ብጥብጥ በሚፈጥሩት ላይ አስፈላጊ የሆነ ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ቀድመን እናሳውቃለን " ሲል አስጠንቅቋል።

ከሰሞኑን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የጤና ባለሙያዎች " መኖር ከብዶናል የጤና ስርዓቱ መለወጥ አለበት ለዚህም ያቀረብናቸው ጥያቄዎች አሉ የጊዜ ገደብ ብናስቀምጥም ምላሽ አልተሰጣቸውም " በማለት ከፊል የስራ ማቆም አድማ እያደረጉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበርም የባለሙያዎቹን ጥያቄዎች ትክክል እንደሆነና ሊመለሱ እንደሚገባቸው በተደጋጋሚ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል አቋሙን ገልጿል።

ከትላንት በስቲያ በሰጠው ቃል ደግሞ " ለጤና ባለሙያዎች ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት አረፈደም፤ እልህ በመጋባት የጸጥታ ኃይል በማሰማራት የጤና ባለሙያዎችን ማፈኑ ቁሞ ፤ ለጥያቄዎቹ ምላሽ ለመስጠት ትኩረት ይደረግ " ብሎ ነበር።

ከጤና ባለሙያዎቹ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ለእስር እየተዳረጉ በርካታ ባለሙያዎች እንዳሉ በርካቶችም ማስፈራሪያና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሆነ ማኅበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

ምንጭ:- ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

Address

Bole
Bole

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00
Sunday 09:00 - 17:00

Telephone

+251916817972

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio News:

Share