Cheta Woreda Communication

Cheta Woreda Communication Cheta woreda communication

ምርጫው ተዓማኒ ፣ዲሞክራሲያዊና ፍትሀዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት ተባለ ይህ የተባለው በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ሰራተኞች ፐብሊክ ግንባር ማህበራዊ ዘርፍ ህ...
25/05/2026

ምርጫው ተዓማኒ ፣ዲሞክራሲያዊና ፍትሀዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት ተባለ

ይህ የተባለው በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ሰራተኞች ፐብሊክ ግንባር ማህበራዊ ዘርፍ ህብረት "ቡና ጠጡ" ፕሮግራም ላይ ነው።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የጨታ ወረዳ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና የመንግስ ረዳት ተጠር አቶ አክሊሉ አለማዬሁ እንዳሉት ምርጫው ተዓማኒ ፣ዲሞክራሲያዊና ፍትሀዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት ብሏል።

በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያለውን መንግስት ለመመስረት ምርጫ ወሳኝ መሆኑን ገልፀው እንደሀገር ለ7ኛ ዙር እየተካሄደ ያለው ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ ሁሉም አካባቢውን በነቂስ መከታተል አለበት ብሏል።

የብልጽግና ፓርቲ እሳቤዎችንና ግቦችን ለማሳካት የህብረቱ አባላት በምርጫ ወቅት በግዜ ወጥቶ ብልጽግና ፓርቲን ከመምረጥ ባለፈ ሌሎችም በአደረጃጀታቸው በግዜ ወጥቶ እንዲመረጡ ማድረግ አለብን ብሏል።

በቡና ጠጡ ፕሮግራሙ ላይ የዞን ደጋፊና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የማህበራዊ ዘርፍ ህብረት አመራርና አባላት ተሳትፈዋል።

በወጋዬሁ ወንድሙ

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

ወታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR

"373 መምህራን የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ወስደዋል" :- የካፋ ዞን መምህራን ማህበር የካፋ ዞን መምህራን ማህበር የመምህራንን መብት እና ጥቅማ-ጥቅም የማስጠበቅ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደ...
24/05/2026

"373 መምህራን የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ወስደዋል" :- የካፋ ዞን መምህራን ማህበር

የካፋ ዞን መምህራን ማህበር የመምህራንን መብት እና ጥቅማ-ጥቅም የማስጠበቅ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ገለጸ፡፡

የማህበሩ ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ወንድሙ፣ ማህበሩ ከ13 ሺህ በላይ አባላትን ያቀፈ አንጋፋ ማህበር ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ማህበሩ ከተቋቋመለት አላማ አንፃር የመምህራንን መብት እና ጥቅማ-ጥቅም የማስጠበቅ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል የትምህርት ጥራትን የማረጋገጥ ሥራዎች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም ነው የገለጹት፡፡

የመምህራን የደረጃ ዕድገት፣ የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ እንዲሁም ሌሎች የትምህርት ማሻሻያ ላይ ማህበሩ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ በዞኑ 373 መምህራን ተደራጅተው የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ እየተሰጣቸው እንደሆነም ገልፀዋል።

በቀጣይ ተደራጅተው እየጠበቁ ያሉ መምህራን የመሬት ባለቤት እንዲሆኑ ማህበሩ የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡

ከማዘጋጃ ከተሞች ውጭ ያሉ መምህራንን በሚመለከትም የአከባቢው አስተዳደር እና ህዝብ ምቹ መኖሪያ እንዲያዘጋጁላቸው ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡

ማህበሩ ከዞኑ አስተዳደር ጋር ባለው መልካም ግኑኝነት ችግሮችን በውይይት የመፍታት ልምድ እየዳበረ መጥቷል ብለዋል፡፡

የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የበርካታ አካላትን ተሳትፎ የሚጠይቅ ነው ያሉት አቶ ተመስገን "የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው መምህር ነው" ብለዋል፡፡

በዚህም መሠረት መምህራን የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ የበኩላቸውን ጥረት እያደረጉ እንደሚገኙም ነው የገለጹት፡፡

በቀጣይ ቀናት ለክልላዊና ብሔራዊ ፈተናዎች ተማሪዎችን የማዘጋጀት ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

.4

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

ወታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ለሚደረገው የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ ለሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች የሥራ ስምሪት ተሰጠ::በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች...
23/05/2026

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ለሚደረገው የብልጽግና ፓርቲ የድጋፍ ሰልፍ ለሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች የሥራ ስምሪት ተሰጠ::

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የአስተዳደርና ፖለቲካ መቀመጫ እንዲሁም የካፋ ዞን ርዕሰ ከተማ በሆነቹ ቦንጋ በቀን 18 ለሚደረገው ክልል አቀፍ የብልጽግና ፓርቲ ማጠቃለያ ድጋፍ ሰልፍ ለሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች የመጀመሪያ ዙር የሥራ ስምሪት ተሰጠ::

የድጋፍ ሰለፉ በብልጽግና ፓርቲ የተመዘገቡ ስኬቶችና ድሎችን አስመልክቶ የሚደረግ ሀገራዊ ይዘት ያለውና የዞኑ ህዝብ ለብልጽግና ፓርቲ ያለውን ፍቅር የሚገልጽበት ልዩ ኩነት በመሆኑ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሙያዊ ስነምግባር አክብሮ ጥራት ያለውን መረጃ ለህዝቡ ማድረስ እንዳለባቸው የካፋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢኖቨሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ተፈሪ ታደሰ ተናግሯል::

አቶ ተፈሪ እንዳሉት ሁሉም ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት የሚሰሩት ትክክለኛ ተዓማኒና ጥራት ያለውን መረጃ ለህዝብ ለማድረስ በመሆኑ በሰልፉ ዕለት ተግባራትን በቁርጠኝነት መፈፀም የሚያስችል ዝግጅት ማድረግ እንዳለባቸው አቶ ተፈሪ አመላክተዋል::

የካፋ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮ ጽ/ቤት ኃላፊው አቶ አዳሙ እሸቱ በበኩላቸው ከፊታችን ግንቦት 18 በቦንጋ ከተማ የሚደረገው የብልጽግና ፓርቲ ማጠቃለያ የድጋፍ ሰልፍ ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ሁሉም የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በመረዳት ይህንን የሚመጥን የሚዲያ ሽፋን መስጠት እንዳለባቸው ገለፀዋል::

በተለይ በድጋፍ ሰልፉ ወቅት ህዝቡ ለፓርቲ ያለውን ስሜትና ፍቅር በአደባባይ የሚገልጽበት ታላቅ ቀን በመሆኑ ይህንን ድባብና ኩነቶችን በተገቢው በመከታተል ጥራት ያለውን እና በትክክለኛ መረጃ ላይ የተደገፈ በ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሽፋን መስጠት ከሁሉም እንደሚጠበቅ አቶ አዳሙ እሸቱ አሳስቧል::

በመድረኩ የተገኙት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች በሰጡት አስተያየት የድጋፍ ሰልፉ ለሀገረ መንግስት ግንባታው ሂደት ያለው ሚና ጉልህ በመሆኑ የተሰጣቸውን የሥራ ሃላፍነት ሙያዊ ስነምግባር አክብረው ጥራት ያለውን እና ተገቢ መረጃ ለህዝቡ ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አመላክተዋል::

በቀጣይ ተጨማሪ የሥራ ሥምሪት የሚሰጣቸው የሚዲያ ባለሙያዎች እንዳሉ ማወቅ የተቻለ ሲሆን በድጋፍ ሰልፉ ላይ መላው ህዝብ ተሳታፊ እንዲሁን የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኮሚቴ አሳስቧል ሲል የዘገበው የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

ወታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR

የጋዜጠኛ ፍቅሩ በላይ የቀብር ስነ-ስርዓት በቦንጋ ደብረ-ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተፈፀመበደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የቦንጋ ቅርንጫፍ ጣቢያ ባልደረባ የነበረው ጋዜጠኞ ፍቅሩ በ...
23/05/2026

የጋዜጠኛ ፍቅሩ በላይ የቀብር ስነ-ስርዓት በቦንጋ ደብረ-ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተፈፀመ

በደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የቦንጋ ቅርንጫፍ ጣቢያ ባልደረባ የነበረው ጋዜጠኞ ፍቅሩ በላይ የቀብር ስነ-ስርዓት ቤተሰቦቹ፤ ወዳጅ ዘመዶቹ እና የስራ ባልደረቦቹ በተገኙበት በቦንጋ ደብረ-ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።

ዝግጅት ክፍላችን በጋዜጠኛ ፍቅሩ በላይ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቹ፤ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለስራ ባልደረቦቹ መጽናናትን ይመኛል።

It is the Prosperity Party that brought the country out of the economic and political crisis it entered፦ Mrs Solomon Hai...
22/05/2026

It is the Prosperity Party that brought the country out of the economic and political crisis it entered፦ Mrs Solomon Haile

A public discussion forum was held on the 7th national general election and other issues in Arara Kebele of Cheta district.

The Chief Administrator of Cheta District, Mrs Solomon Haile, said that the government will step by step solve the questions of good governance and development raised by the people.

He said that it was the Prosperity Party that brought the country out of the economic and political crisis it was in. He said that the Prosperity Party is working hard to benefit the society in economic, social and political as well as security and others.

The South West People Regional State Transport and Road Development Office Deputy Head, and representing the Prosperity Party in the State Council, "feleke Salam" Constituency Engineer Zemede Andarge, who is said that he will work diligently to complete the infrastructure works that have been started and not completed, and said that all sections of the society should cooperate with the government.

Zemede, who pointed out that he will work to establish good governance in the area and ensure the benefit of the people, said that in the 7th national general election that will be held after a few days, all the parties who took a card should continue the development works started by electing Prosperity Party.

Thr District prosperity Party branch office, Mrs Alemu zewude, said that as a country, the results of the Prosperity Party are being recognized by the world governments and he said that we should continue to elect the Prosperity Party in the upcoming elections so that the results that are still being recorded continue.

He said that the people should be on the side of the government and the party in order to get the ideas of the party to the brink and speed up the remaining development works.

He said that our party and the government will continue to consult with various sections of the society and provide joint solutions to common problems.

A consensus has been reached to solve the problems of the people step by step by consulting and cooperating with the people.

By Wondimu

Cheta District Government Communications Affairs Office.

Follow our Facebook Telegram and Tiktok pages to get up-to-date, reliable, fresh and fast information, like them 👇👇👇👇👇????

On Facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

Via Telegram፦https://t.me/C12g6/1057?single

On Tiktok፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnV

ሀገሪቱ ከገባችበት ከኢኮኖሚና ከፖለቲካ ቀውስ ያወጣው ብልጽግና ፓርቲ ነው፦ አቶ ሰለሞን ኃይሌ በጨታ ወረዳ አራራ ቀበሌ 7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ላይ የህዝብ ውይይ...
22/05/2026

ሀገሪቱ ከገባችበት ከኢኮኖሚና ከፖለቲካ ቀውስ ያወጣው ብልጽግና ፓርቲ ነው፦ አቶ ሰለሞን ኃይሌ

በጨታ ወረዳ አራራ ቀበሌ 7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ላይ የህዝብ ውይይት መድረክ ተካሂዷል።

በህዝብ ዘንድ የሚነሱ የመልካም አስተዳደርና የልማት ጥያቄዎችን መንግስት ደረጃ በደረጃ እየፈታ ይሄዳል ያሉት የጨታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ ፓርቲው ያመጣቸውን ነፃነትና ሌሎች መልካም ዕድሎችን በተገቢው ተጠቅሞ የአካባቢውን ዕድገት ማረጋገጥ ከእኛ ይጠበቃል ብሏል።

ሀገሪቱ ከገባችበት ከኢኮኖሚና ከፖለቲካ ቀውስ ያወጣው ብልጽግና ፓርቲ መሆኑን ገልፀው ብልጽግና ፓርቲ በኢኮኖሚ ፣በማህበራዊና በፖለቲካ እንዲሁም በደህንነትና በሌሎች ዘርፎች ማህበረሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን አበክረው እየሰራበት እንደሚገኝ ተናግሯል።

የደ/ም/ኢ/ህ/ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ እንዲሁም በክልል ምክር ቤት ብልጽግና ፓርቲን ወክሎ ፈለገ ሠላም ምርጫ ክልል እየተወዳደሩ የሚገኙ ዘመዴ አንዳርጌ (ኢ/ር) ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ የመሠረተ ልማት ስራዎችን ለማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግሮ ሁሉም ማህበረሰብ ክፍሎችም ከመንግስት ጎን በመሆን በትብብር መስራት አለባቸው ብሏል።

ቀጣይ በአካባቢው መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራ የጠቆሙት ዘመዴ ከቀናቶች በኃላ በሚደረገው 7ተኛ ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ላይ ሁሉም ካርድ የወሰዱ አካላቶች ብልጽግና ፓርቲን በመምረጥ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማስቀጠል አለባቸው ብሏል።

የወረዳ ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ዘውዴ በበኩላቸው እንደ ሀገር በብልጽግና ፓርቲ የመጡ ውጤቶች በዓለም መንግስታት ዕውቅና እያስገኙ መሆኑን ተናግሮ አሁንም እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ቀጣይነት እንዲኖራቸው በመጪው ምርጫ ብልጽግና ፓርቲን በመምረጥ ማስቀጠል አለብን ብሏል።

የፓርቲውን ዕሳቤ ከዳር ለማድረስና የቀሩ የልማት ስራዎችን ለማፋጠን ህዝቡ ከመንግስትና ከፓርቲ ጎን መሆን እንዳለበት አንስቶ የሚሰሩ የልማት ስራዎችን ለማሳካት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንደሚገባ ተናግሯል።

በቀጣይም ፓርቲያችንና መንግስት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በዘላቂነት እየመከረ ለጋራ ችግሮች የጋራ መፍትሔ እየሰጠ ይሄዳል ብሏል።

የህዝቡን ችግር ከህዝቡ ጋር በመመካከርና በመተባበር ደረጃ በደረጃ እየፈቱ ለመሄድ የሚያስችል የጋራ መግባባት ተፈጥሯል።

በወጋዬሁ ወንድሙ

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

ወታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR

የፀናችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የወጣቶች ሚና የጎላ ነው ስሉ የወረዳ ምክትል አስተዳደርና ሥራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ከተማ ከፍያለው ተናገሩ።በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ በባሺ ቀይ ...
22/05/2026

የፀናችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የወጣቶች ሚና የጎላ ነው ስሉ የወረዳ ምክትል አስተዳደርና ሥራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ከተማ ከፍያለው ተናገሩ።

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ በባሺ ቀይ ማዘጋጃ የ7ኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫን አስመልክቶ በወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት የብልፅግና ፓርቲ የይምረጡኝና የቡና ጠጡ መርሃግብር ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የወረዳ ምክትል አስተዳደርና ሥራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ከተማ ከፍያለው በሀገር ደረጃ ከፍተኛውን ቁጥር የያዘው የወጣቱ ኃይል ነው በማለት የፀናችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የወጣቶች ሚና የጎላ እንደሆነ ተናግረዋል።

የለውጡ መንግስት ብልፅግና ወደስልጣን ከመጣበት ማግስት ጀምሮ ዘርፈ ብዙ ትሩፋቶችን አስመዝግቧል በማለት በቅርበት የመገልገል መሻትን በመቀበል በክልል የመደራጀት ጥያቄን መልስ የተሰጠበት ነው ብልዋል።

የወረዳ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታረቀኝ መስፍን በበኩላቸው ፓርቲያችን ብልፅግና በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ሁኖ በርካታ ድሎች ያስመዘገበ ነው በማለት በወረዳ ደረጃም የዘመናት ጥያቄ የነበሩ የባንክ አገልግሎት፣ የንፁህ መጠጥ ውኃና የመብራት አገልግሎትን ጨምሮ የህዝብ ጥያቄዎችን እየፈታ መጥቷል በቀጣይም አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ወጣቱ ኃይል የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማዘመን ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ይጠበቅበታል ያሉት ኃላፊው በዲጂታል መረብ የዘመነች ኢትዮጵያን ለመገንባት የብልፅግና ፓርቲ አስቻይ ሁኔታዎችን እየፈጠረ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ እንዲሆን የወጣቱ ሚና የጎላ ነው ያሉት አቶ ታረቀኝ ወጣቱ የአካባቢውን ሰላም በማስጠበቅ እረገድ የበኩላን መወጣት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

ወጣቶች የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የሆነውን የስንዴ ነዶ ለይቶ የማወቅ፣ የማስተዋወቅና የመምረጥ ኃላፊነታቸው በአግባቡ በመወጣት ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር እንዲያሻግሩ ጠይቀዋል።

ምክትል አስተዳደር አቶ ከተማ አክለው የዛሬ ፍሬዎች የነገ ሀገር ተረካቢ ወጣቶችን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ የማድረግ ስራ በወረዳ ደረጃ ባለፉት 8 ዓመታት ውስጥ በሰፊው መሰራቱን አስታውሰዋል።

በኢኮኖሚ ዘርፍ እንደወረዳ የተሻለ እምርታ ተመዝግቧል ያሉት አቶ ከተማ በ2013 ዓ/ም 17ሚልዮን ብር ብቻ መሰብሰቡን በማስታወስ በ2018 ዓ/ም እስካሁን ከ92 ሚልዮን ብር በላይ መሰብሰቡን በመናገር የተመዘገበው ለውጥ የብልፅግና ፓርቲ ትሩፋት ነው ብለዋል።

በመጨረሻም ወጣቱ ኃይል በስንዴ ነዶ የተወከለውን የብልፅግና ፓርቲን እንዲመረጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ወጣቶችም በተለያዩ የድጋፍ ኩኔቶች የብልፅግና ፓርቲ ወገንተኝነታቸውን እና ከፓርቲ ጎን መሆናቸውን አሳይተዋል።

በኤልያስ ጋሎ

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት፦ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

የከፋና የቦንጋ ማንነት: - የተፈጥሮ ልዕልና እና የሰብዓዊነት ውብ ቅኔወደ ጥንታዊው የከፋ ምድርና ወደ ውቢቷ ቦንጋ ከተማ የሚደረግ ጉዞ ለነፍስ ልዩ የሆነ የዕርጋታና የጥበብ ስሜት ይሰጣል።...
22/05/2026

የከፋና የቦንጋ ማንነት: - የተፈጥሮ ልዕልና እና የሰብዓዊነት ውብ ቅኔ

ወደ ጥንታዊው የከፋ ምድርና ወደ ውቢቷ ቦንጋ ከተማ የሚደረግ ጉዞ ለነፍስ ልዩ የሆነ የዕርጋታና የጥበብ ስሜት ይሰጣል። ይህ ታሪካዊ ቀጠና በካርታ ላይ የሰፈረ መልክዓ-ምድር ብቻ አይደለም። ጥቅጥቅ ያሉ የዝናብ ጫካዎች (Rainforest)፣ የሉዓላዊነት ኩራትና የሰው ልጅ ረቂቅ ባህል በአንድነት የከረሙበት የኢትዮጵያዊነት ሕያው ምስክር እንጂ። የከፋና የቦንጋ እውነተኛ ማንነት ከተፈጥሮ ልግስና ጋር ተስማምቶ ከመኖር የሚቀዳ የጽናት፣ የትሕትና እና የሰላም ድንቅ ውህደት ነው። ይህቺ ምድር የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር በሰላም ሲኖር ምን ያህል ሥልጣኔና ክብረ-ነገር መገንባት እንደሚቻል ለዓለም የሚያስተምር ሕያው መድረክ ናት።

የዚህቺ ምድር የሕይወት ትርታ የሚጀምረው ከአረንጓዴው ጫካ፣ ከለመለሙ ሸለቆዎችና ከኮረብቶቿ ዘላለማዊ ግርማ ነው። ከቦንጋ ከፍታዎች ላይ ቆመው ቁልቁል ሲመለከቱ አካባቢው በጭጋግና በልምላሜ የተሸለመ ውብ የጥበብ ሥራ ይመስላል። በጫካው ጥላ ሥር የሚፈሱት ፏፏቴዎችና የወንዞች ድምፅ ከተፈጥሮ ረጋ ያለ እስትንፋስ ጋር ተቀላቅሎ ለየት ያለ የነፍስ ዕረፍት ይሰጣል። ማለዳ በቦንጋ ምድር ሲቀሰቀስ የሚነፍሰው ንጹሕ አየርና የማኅበረሰቡ ንቁ የሥራ ስሜት ተደምሮ በእያንዳንዱ ጎዳና ላይ አዲስ ተስፋንና ሕይወትን ይረጫል። ይህ የተፈጥሮ በረከት ከሕዝቡ ጥንታዊ የሞራል ልዕልና ጋር ፍጹም የተሳሰረ በመሆኑ ምድሪቱ የሰውና የተፈጥሮ የፍቅር መኖሪያ ሆና ትታያለች።

የከፋ ሕዝብ በረጋ ማንነቱ፣ በትሕትናውና ለእንግዳ ባለው ልባዊ ፍቅር ይታወቃል። ሰውን በሰውነቱ ብቻ አክብሮ የመቀበል፣ ለእንግዳ የልብ ጓዳውን በሰፊው የመክፈትና በቅንነት የማስተናገድ ትውፊት የሕይወታቸው ትልቁ መሠረት ነው። ወደ ቦንጋ የመጣ ሰው ፈጽሞ በምድሪቱ ላይ ባዕድ አይሆንም የሕዝቡ ደግነትና የልብ ሙቀት ሁሉንም እንደ እናት እቅፍ አሙቆ ይቀበላልና። በየመንደሩ በሚታየው የጎረቤት ፍቅርና መከባበር ውስጥ የሚስተዋለው ትልቁ እውነት ያ የማይበገር የአንድነት መንፈስ ነው። ይህ ማኅበረሰባዊ ትስስር የከፋን ምድር ለማንኛውም ዘመናት ውሽንፍር የማይበገር ጽኑ ግንብ አድርጎታል።

የቦንጋን ሕይወት ይበልጥ ማራኪና በማኅደር ውስጥ የማይረሳ የሚያደርገው በማኅበረሰቡ ውስጥ ያለው ጥልቅ የሰላምና የፍትሕ እሴት ነው። ለዘመናት የጸኑት የባህላዊ ዳኝነትና የሽምግልና ሥርዓቶች የሰው ልጅ ያለ ኃይልና ያለ መሣሪያ በቃል-ኪዳንና በትልቅ የሞራል ልዕልና እንዴት ፍጹም ሰላምን ማስፈን እንደሚችል በተግባር ያሳያል። በትላልቆቹ የዛፍ ጥላዎች ሥር የሚቀመጡት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የሚሰጡት ውሳኔ ከውኃ የጠራ ከዓለት የጠነከረ ነው። እዚያ አደባባይ ላይ ክህደትና ውሸት ፈጽሞ ቦታ የላቸውም ሰው ሰውን የሚያከብረው በውስጡ ባለው ማኅበራዊ ቃል-ኪዳንና በሰውነቱ ብቻ ነው።

ሲመሽና የቦንጋ መብራቶች በአረንጓዴው ሸለቆ ውስጥ እንደ ከዋክብት ፈገግ ሲሉ ከየቤቱ የሚሰማው የሰዎች ሳቅና ጨዋታ ሌላ የውበትና የፍልስፍና ምዕራፍ በይፋ ይከፈታል። እዚያ ሞቅ ባለ ማዕድ ዙሪያ የጥንቱ የጀግንነት ታሪክ በጥልቀት ይተረካል፣ የነገው የብልጽግና ራዕይ በስልት ይወጠናል ጥንታዊው ዕውቀትና የሕይወት ፍልስፍና ደግሞ ለልጆች ይተላለፋል። የቦንጋ ወጣቶች የፈጠራ ብቃት ንቁ የሥራ ተነሳሽነትና የተፈጥሮው ልምላሜ ከተማዋን ሁልጊዜም ወጣት፣ ሕያውና ተስፋ የተሞላች ያደርጋታል።

ዛዲግ አብርሃ
የአፍሌክስ ፕሬዝደንት

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

ወታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

የተቋማችንን ስምና መለያ በመጠቀም ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ስለ ስራ ግብር ቅናሽ ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው፡፡ስለተቋሙ ስራዎች ትክክለኛ መረጃዎችን የገንዘብ ሚኒስቴር የማህበራ...
21/05/2026

የተቋማችንን ስምና መለያ በመጠቀም ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ስለ ስራ ግብር ቅናሽ ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው፡፡

ስለተቋሙ ስራዎች ትክክለኛ መረጃዎችን የገንዘብ ሚኒስቴር የማህበራዊ ሚዲያ ገፆችን በመከተል ማግኘት ትችላለችሁ፡፡

መረጃው የገንዘብ ሚኒስቴር ማህበራዊ ሚዲያ ገፅ ነው።

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

ወታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫን አስመልክቶ ለወረዳ ፖሊስ አመራርና አባላት በምርጫ ስነምግባርና ደንብ ዙሪያ ላይ ስልጠና ተሰጠበካፋ ዞን ጨታ ወረዳ 7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫን አስመልክቶ ...
20/05/2026

7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫን አስመልክቶ ለወረዳ ፖሊስ አመራርና አባላት በምርጫ ስነምግባርና ደንብ ዙሪያ ላይ ስልጠና ተሰጠ

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ 7ተኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫን አስመልክቶ ለፖሊስ አመራርና አባላት በምርጫ ስነምግባርና ደንብ ዙሪያ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።

የስልጠናው ዋና ዓላማ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ሰላምና ወጥታ ለማስከበር የሚሰማሩ የፀጥታ አካላቶች የምርጫ ቦርድ ህግና ደንቦችን በመከተል ምርጫው ያለምንም ችግር እንዲጠናቀቅ ማድረግ እንደሆነም ተገልጿል።

ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፖሊስ አመራርና አባላት ገለልተኛ ሆኖ እንዲያስፈፅሙ በመድረክ ተመልክቷል።

ከሰላምና ከፀጥታ ጥበቃ ጎን ለጎን በየትኛውም የምርጫ ጣቢያዎች የሚገኙ የምርጫ ቁሳቁሶች ፍፁም አስተማማኝ በሆነ ሁኔታ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ተጠቁሟል።

በስልጠናው መድረክ ላይ የወረዳ ሠ/ፀ/ሚ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ክዳኔ፣ የዞን ፖሊስ መምሪያ ደጋፊ አመራር ረዳት ኢንስፔክተር ታረቀኝ ታምሩ፣የወረዳ ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር አንዳርጌ ደራ ተገኝተዋል።

በወጋዬሁ ወንድሙ

የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

ወታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

በሀገር አቀፍ ደረጃ የፋይዳ መታወቂያ ተመዝጋቢዎች ቁጥር 43 ሚሊየን ደረሰ በኢትዮጵያ የብሔራዊ መታወቂያ ፋይዳ ተመዝጋቢዎች ቁጥር 43 ሚሊየን መድረሱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታ...
20/05/2026

በሀገር አቀፍ ደረጃ የፋይዳ መታወቂያ ተመዝጋቢዎች ቁጥር 43 ሚሊየን ደረሰ

በኢትዮጵያ የብሔራዊ መታወቂያ ፋይዳ ተመዝጋቢዎች ቁጥር 43 ሚሊየን መድረሱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ዲጂታል መታወቂያን ከ100 በላይ በሚሆኑ የመንግሥትና የግል ተቋማት አገልግሎቶች ጋር በማስተሳሰር ዜጎች መረጃን መሰረት ያደረጉ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ አስችሏል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት እንዳመላከቱት፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 20 ሚሊየን ዜጎች ለብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ተመዝግበዋል፡፡

ይህም በመላው ሀገሪቱ የብሔራዊ መታወቂያ ፋይዳ ተመዝጋቢዎችን ቁጥር 43 ሚሊየን እንዳደረሰው ገልጸዋል።

በሌላ በኩል በዲጂታል ኢኮኖሚ ወሳኝ የሆነውን የሞባይልና የኢንተርኔት ተጠቀሚዎችን ቁጥር ለማሳደግ በተሰራው ሥራ በሀገሪቱ በአጠቃላይ 97 ሚሊዮን ዜጎች የሞባይል ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡

ከዚህ ውስጥ 84 ሚሊዮኑ በኢትዮ ቴሌኮም፣ 13 ሚሊዮኑ ደግሞ በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በኩል የተመዘገቡ ናቸው ብለዋል፡፡

የኢንተርኔት ተደራሽነት ለማሳደግ በተሰራው ሥራ በኢትዮ ቴሌኮም 49 ነጥብ 9 ሚሊዮን፣ በሰፋሪኮም ኢትዮጵያ 11 ነጥብ 1 ሚሊየን በድምሩ 61 ነጥብ 1 ሚሊየን ዜጎች የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።

በኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማፋጠንና ዜጎች አስተማማኝ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡

#ኢ.ፕ,ድ

Address

Kafa Cheta
Bonga

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Cheta Woreda Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share