Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Bonga
  • Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን

Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን cheta woreda govt comm affairs
የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

 #ካፋን ምን ያህል ያውቃሉ? በቅርብ ቀን ይጠብቁን !ካፋ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ውስጥ ካሉት 6ቱ ዞኖች አንዱና በቆዳ ስፋትና በህዝብ ብዛት እንደዚሁም በአጠቃላይ ሶሺዮ ኢኮ...
25/10/2025

#ካፋን ምን ያህል ያውቃሉ? በቅርብ ቀን ይጠብቁን !

ካፋ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ውስጥ ካሉት 6ቱ ዞኖች አንዱና በቆዳ ስፋትና በህዝብ ብዛት እንደዚሁም በአጠቃላይ ሶሺዮ ኢኮኖሚ አቅም ቀዳሚውን ስፍራ የያዘ ዞን ነው::

ስለሆነም ይህንን ሰፊ ታሪክ፣ ባህል፣ ወግ ፣ቁንቋና እሴት ያለውን የካፋ ዞን ሁለንተናዊ ገጽታ "ካፋን ምን ያህል ያውቃሉ?" በሚል የዝግጅት አምድ ማስተዋወቅ አስፈላጊና ወሳኝ ሆኖ ተገኝቷል::

በባለፎ ሳምንት ይህንን አጓጊ አምድ ለማብሰር እና ለማስተዋወቅ ያህል ውቢቷን "ሺሾእንዴን ምን ያህል ያውቃሉ?" በሚል በዚሁ ፌስቡክ ገጻችን ሀ ብለን ለእናንተው ለተከታዮቻችን እንካችሁ ማለታችን የሚታወስ ነው::

ከዚህ በማስከተል የዞኑ ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ ፣ ከባቢያዊ እና መልከዓ ምድራዊ ዳራዎችም የዚሁ አምድ አካል ይሆናሉ::

ካፋን ጨምሮ በዞኑ ለዘመናት ተዋደው ተሳስረውና በፍቅር ተጋምደው የኖሩ የ3ቱ ነባር ብሔር ብሔረሰቦች ማለትም የካፈቾ ፣ ናይና ፃራ ህዝቦች ባህል፣ ታሪክ፣ ቋንቋ፣ ወግና እሴት በዚሁ አምድ በሰፊው ይቃኛሉ::

የአኗኗር ፣ የአመጋገብ ፣ የአለባበስ ፣ የሰርግና ደስታ፣ የለቅሶና የሐዘን ብሎም ሌሎች ማህበራዊ መስተጋብርን አጉልቶ የሚያሳዩ እሴቶችም የዚሁ አምድ አካል ሆኖ ይተነተናሉ::

በተጨማሪም በዞኑ ስር የሚገኙ የ12ቱ ወረዳና የ5ቱ ከተሞች አጠቃላይ ታሪካዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ስነምህዳሪን መሰረት ያደረጉ የሶሺዮ ኢኮኖሚ መረጃዎችን ብሎም የመልማት አቅሞችን ከግምት ያስገቡ ዝርዝር መረጃዎች በዚሁ አምድ በቅደም ተከተል ለእናንተው ለተከታዮቻችን ይቀርባሉ::

በአጠቃላይ የእናንተ የውድ ተከታዮቻችን ደርሻ የሚሆነው በየወቅቱ በዚሁ "ካፋን ምን ያህል ያውቃሉ?" በሚል አምድ የሚቀርቡትን ተከታታይ እና አጓጊ መረጃዎች ሁሌም follow, Like,comment & share በማድረግ ለሌሎች በፍጥነት እንዲደርስ የዘወትር አጋርነት ድርሻችሁን መወጣት ብቻ ነው ::

"ካፋን ምን ያህል ያውቃሉ?"
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !

መረጃው የካፋ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው!

መረጃው የዞን ት/ት መምሪያ ማህበራዊ ትስስር ገፅ ነው

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

 !‎የ2018 ዓ/ም  የፀደቀው የመርሱ አባላት ከወረዳ ወረዳ የዝውውር  ይፋ መደረጉን የካፋ ዞን ትምህርት መምሪያ የመምህራንና ትምህርት አመራር አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አስታውቋል። ‎‎221...
24/10/2025

!

‎የ2018 ዓ/ም የፀደቀው የመርሱ አባላት ከወረዳ ወረዳ የዝውውር ይፋ መደረጉን የካፋ ዞን ትምህርት መምሪያ የመምህራንና ትምህርት አመራር አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አስታውቋል።

‎221 የመርሱ አባላት በዝውውሩ መካተታቸውን የገለፁት የመምሪያው የመምህራንና ትምህርት አመራር አስተዳደር ቡድን አስተባባሪና የዝውውር ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ጌታሁን ቦጋለ ቀደም ሲል 191 የመርሱ አባላት በፕሮፖዛል ደረጃ የተዛወሩ መሆናቸውን በማስታወስ በፕሮፖዛሉ ላይ የቀረቡ ቅሬታዎችን ኮሚቴው በጥልቀት በመመርመር ቅሬታ ላቀረቡ መምህራን መመሪያውን የተከተለ ምላሽ የተሰጠ መሆኑን አብራርተዋል።

‎በዚህም መሠረት የተሰራው ዝውውር በአምስቱም የዝውውር ነጥቦች ማለትም በአገልግሎት(80) ፣ በትዳር (51) ፣ በህመም (15) ፣ በስምምነት ቅይይር (50) እና በተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች (16) መምህራንን እንዲሁም 4 ር/መ/ር፣ 1 ም/ር/መ/ርና 1 ሱፐርቫይዘርን ያካተተ ሲሆን የወረዳዎችን ፊላጎት መሠረት በማድረግ በተለይ ትዳር እና ማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት መደረጉ ተጠቁሟል።

‎በመሆኑንም ዝውውር ያገኙ መምህራን በማሳሰቢያው መሠረት ለዝውውር እንቅስቃሴ የተፈቀደውን አንድ ሳምንት ጊዜ ብቻ በመጠቀም ደብዳቤ የመቀበልና ማህደራቸውን የማንቀሳቀስ ተግባር ፈፅመው ወደ መደበኛ ተግባራቸው እንዲገቡ ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ተጠቁሟል ።

መረጃው የዞን ት/ት መምሪያ ማህበራዊ ትስስር ገፅ ነው

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

የብሔር-ብሔረሰቦች ቀን መከበር  ኃብረ-ብሔራዊነትን ከማጠናከር ባለፈ ጠንካራ ሀገረ  መንግስት ግንባታ  አስተዋጽዖ  ከፍተኛ  ነው ÷ ክብርት ወ/ሮ አሚናት ሀሰን።ዴሞክራሲያዊ መግባባት  ለህ...
24/10/2025

የብሔር-ብሔረሰቦች ቀን መከበር ኃብረ-ብሔራዊነትን ከማጠናከር ባለፈ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ አስተዋጽዖ ከፍተኛ ነው ÷ ክብርት ወ/ሮ አሚናት ሀሰን።

ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት በሚል መሪ ሀሳብ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሔር-ብሔረሰቦች ቀን አስመልክቶ የካፋ ዞን ም/ቤት ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ተወያይተዋል።

የካፋ ዞን ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ እሸቱ ወጋሳ የውይይት ሰነድ አቅርበዋል።

የ20ኛ ብሔር-ብሔረሰቦች ቀን ደምቆ እንዲከበር የሚያስችል ዝግጅት ባለድርሻ አካላት በማሳተፍ መጀመሩን የምክር ቤቱ ም/አፈ-ጉባኤ አመላክተዋል።

የ20ኛ ዓመት የብሄር-ብሔረሰቦች ቀን በዓል ዝግጅት በውጤታማነት እንዲጠናቀቅና ደምቀው እንዲከበር ለማስቻል ተቀናጅቶ በመስራት የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ ተናግረዋል።

የብሔር-ብሔረሰቦች ቀን መከበር ኃብረ-ብሔራዊነትን ከማጠናከር ባለፈ ጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ የሚያበረክተው አስተዋጽዖ ከፍተኛ መሆኑን የካፋ ዞን ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ አሚናት ገለጸ።

የካፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ደመላሽ ንጉሴ ለብሔር-ብሔረሰቦች ቀን አከባበር ውጤታማነት በየደረጃ የሚገኙ ባለ ድርሻ አካላት ተቀናጅቶ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በመጨረሻም የካፋ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ አሚና ሀሰን የበዓል ዝግጅት የደመቀና አሳታፊ እንዲሆን ለማስቻል የሚመለከታቸው አካላት ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ዘገባው የካፋ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛ ጊዜ የሚካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ፤ በመጪው ግንቦት 24፤ 2018 ለማድረግ ምክረ ሃሳብ አቀረበ። ቦርዱ በምርጫው የሚገኘውን ውጤት ይፋ ለማድረግ፤ ...
24/10/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰባተኛ ጊዜ የሚካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ፤ በመጪው ግንቦት 24፤ 2018 ለማድረግ ምክረ ሃሳብ አቀረበ። ቦርዱ በምርጫው የሚገኘውን ውጤት ይፋ ለማድረግ፤ በረቂቅ የጊዜ ሰሌዳው ያስቀመጠው ዕለት ሰኔ 3፤ 2018 ነው።

ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ የጠቅላላ ምርጫውን ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ አዘጋጅቶ ለውይይት ያቀረበው፤ ከትላንት በስቲያ ሰኞ ጥቅምት 10፤ 2018 ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ባደረገው ምክክር ላይ ነበር። በአዲስ አበባው ስካይ ላይት ሆቴል በተካሄደው በዚህ ውይይት ላይ ከ60 በላይ በህጋዊ መንገድ የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች መሳተፋቸውን፤ በመድረኩ የታደሙ ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

መገናኛ ብዙሃን ባልተገኙበት በዚህ የውይይት መድረክ ላይ፤ ምርጫ ቦርድ የሰባተኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ዝርዝር የጊዜ ሰሌዳ አቅርቧል። “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው የጊዜ ሰሌዳ፤ 37 ተግባራት የሚከናወኑባቸውን ጊዜያት በቀን እና በወራት ከፋፍሎ አስቀምጧል።

በረቂቅ የጊዜ ሰሌዳው፤ ከህዳር መጀመሪያ እስከ ወሩ አጋማሽ ድረስ በምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የግል ዕጩዎች የምዝገባ ጥሪ ለማድረግ ታቅዷል። የምርጫ አስፈጻሚዎችን ዝርዝር ለፖለቲካ ፓርቲዎች እና ለህዝብ ይፋ ማድረግ፤ ህዳር 19 ተጀምሮ በጥር የመጀመሪያ ሳምንት ላይ ለማጠናቀቅ ታስቧል። ይህ መርሃ ግብር በሁለት ዙር የሚከናወን መሆኑ በረቂቅ የጊዜ ሰሌዳው ላይ ተመልክቷል።

በምርጫ የሚሳተፉ ዕጩዎች ምዝገባ እንዲከናወን የታቀደው ከታህሳስ መጀመሪያ እስከ ጥር መጀመሪያ ባለው ጊዜ ውስጥ ነው። የምረጡኝ ቅስቀሳ ወይም የምርጫ ዘመቻ ከታህሳስ 10 እስከ ግንቦት 19 ድረስ እንዲከናወን ያቀደው ምርጫ ቦርድ፤ ከግንቦት 20 እስከ 23 ያሉትን ቀናት ለጥሞና ጊዜ መድቧል። በእነዚህ ሶስት ቀናት ቅስቀሳ ማድረግ አይቻልም።

የድምጽ መስጫ ቀን አሊያም ምርጫ የሚከናወንበት ቀን እንዲሆን የታቀደው፤ ግንቦት 24፤ 2018 ነው። በዚሁ ዕለት እና በማግስቱ፤ የምርጫ ውጤት በምርጫ ጣቢያ ይፋ ለማድረግ ታቅዷል። በምርጫ ክልል ደረጃ ጊዜያዊ ውጤት ይፋ እንዲደረግ የታሰበው ደግሞ፤ ከግንቦት 25 ጀምሮ ባሉት አምስት ተከታታይ ቀናት እንደሆነ የወጡ መረጃዎች ይገልጻሉ።

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን። ይቀላቀሉ፣ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ ልዑክ የወጣት ለወጣት ግንኙነት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን እያካሄደ ነው  የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብል...
23/10/2025

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ ልዑክ የወጣት ለወጣት ግንኙነት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን እያካሄደ ነው

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወጣት ለወጣት ግንኙነት በወላይታ ዞን እያካሄደ ይገኛል።

"በጎነት ለአብሮነት" በሚል መሪ ቃል የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን የወሰን ተሻጋሪ የበጎ ስራና የወጣት ለወጣት ግንኙነት እያካሄዱ ይገኛል።

ልዑኩ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ጉኑኖ ከተማ ሲደርሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ሚካኤል ዋዳ፣ የወላይታ ዞን አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤልን ጨምሮ የክልልና የዞን ክንፍ አመራሮች እና ሌሎች ወጣት አደረጃጀቶች ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል።

የወላይታ ዞን የአደረጃጀት ዘርፍና የመንግስት ረዳት ተጠሪ ወ/ሮ ሰላማዊት ሳሙኤል እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ወ/ሮ ሰላማዊት በመልዕክታቸው እንደሀገር በወጣቶች ንቁ ተሳትፎ በርካታ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት በመከናወኑ ብዙ ህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ መሆናቸውንም ገልፀዋል።

የመጣችሁ ዓላማ ትልቅ ዋጋ ያለው መልካም ተግባር ነው ያሉት ወ/ሮ ሰላማዊት ይህም ወንድማማችነት እና እህተማማችነትን ያጠናክራልም ብለዋል።

ከዚህ በፊት አብሮ የኖረ የሁለቱም ክልል ህዝቦች እርስበርስ አብሮነትንና አንድነትን ይበልጥ የሚያጠናክር እንደሆነም አስገንዝበዋል።

የልዑካን ቡድኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ቆይታቸው የተለያዩ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎችን ያከናውናል ተብሎም ይጠበቃል ሲል የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

በከተማው ውስጥ ከቅርብ ግዜ ወዲህ እየተስተዋሉ ያሉ የስርቆት ወንጀሎችን ህዝቡ ከመንግስት ጎን በመሆን ተገቢ የማጣራት ስራ መስራት እንዳለበት ተገለፀ ሻማ፦ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም (የጨታ ...
22/10/2025

በከተማው ውስጥ ከቅርብ ግዜ ወዲህ እየተስተዋሉ ያሉ የስርቆት ወንጀሎችን ህዝቡ ከመንግስት ጎን በመሆን ተገቢ የማጣራት ስራ መስራት እንዳለበት ተገለፀ

ሻማ፦ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት) በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ የሻማ ማዘጋጃ ቤት የ2018 ዓ.ም የብልጽግና ፓርቲ የአንደኛ እሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀምና የወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ከሻማ ከተማ ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተደርጓል።

የሻማ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ስራአስኪያጅ አቶ አየሌ አደቆ ለውይይት ተሳታፊዎች የ2018 ዓ.ም የብልጽግና ፓርቲ አንደኛ እሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት አቅርቧል።

በውይይቱ የከተማ ሰላምና ፀጥታ እንድሁም መልካም አስተዳደር ጉዳዮችም በሰፊው ተነስቶ ውይይት ተደርጓል።

የከተማ ልማት ስራዎች በተመለከተ በግብርና ፣ በኮርደር ልማት ፣ በጤና ፣ በትምህርት ፣ በስራ ዕድል ፈጠራ እንድሁም የገቢ አሰባሰብ ስራ ሂደት ተጠናክሮ መሰራት እንደሚገባ የጨታ ወርዳ ሠ/ፀ/ሚ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሸሻ መኩሪያ ተናግሯል።

አቶ መሸሻ አክለውም ለከተማ ደህንነት ጠንቅ ለዕደገት እንቅፋት እየሆኑ የሚገኙ ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎች ፣ አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሬ ፣ ቁማር ፣ ስርቆትና መሰል ህገወጥ ተግባራቶችን ህዝቡ ከመንግስት ጎን በመቆም መታገል እንዳለበት አሳስበዋል።

ያለ ዕድሜያቸው በቁማርና በሌሎች አላስፈላጊ ሱስ ውስጥ የተጠመዱ ወጣቶች በአግባቡ ተደራጅተው መንግስት ባመቻቸው የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ በመሆን የስራ ባለበት መሆን እንዳለባቸው መክሯል።

በከተማው ውስጥ ከቅርብ ግዜ ወዲህ እየተስተዋሉ ያሉ የስርቆት ወንጀሎችን ህዝቡ ከመንግስት ጎን በመሆን ተገቢ የማጣራት ስራ መስራት እንዳለበትና ህግ የበላይነት ስራ እንዲሰራም ተጠይቋል።

በመጨረሻም አቶ መሸሻ ህዝቡ አካባቢውን ከስርቆትና ከሌሎች ወንጀሎች ነቅቶ መጠበቅ እንዳለበት ገልፀው በመንግስት በኩል በከተማው የፀጥታ ጉዳዮችን ክትትልና ቅኝት እንዲያደርጉ ለደህንነት አካላቶች ስምሪት ተሰጥቷል ብሏል።

ከውይይት ተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳቦች ፣ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የተነሳ ስሆን ለተነሱ ሀሳቦች ፣ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ከመድረክ ሰፊ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ ተጠናቋል።

በወጋዬሁ ወንድሙ

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

ባለሙያዎች መረጃ ለመሰብሰብ በሚሄዱበት ግዜ ህብረተሰብ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደረግ የወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰዩም ሻዎዬሮ ጠየቁ። ሻማ-ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም (የጨታ ወ...
21/10/2025

ባለሙያዎች መረጃ ለመሰብሰብ በሚሄዱበት ግዜ ህብረተሰብ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደረግ የወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰዩም ሻዎዬሮ ጠየቁ።

ሻማ-ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለማካሄድ የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ሚዛን አማን ቅ/ጽ/ቤት በወረዳ ግብረሀይል ተቋቁሟል።

መድረኩን የመሩት የወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰዩም ሻዎዬሮ ወቅታዊና ዘመኑ የሚጠይቀውን መረጃ ለመሰብሰብ መንግሥት በሀገር ደረጃ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች እያደረገ እንደሆነ ገልፀዋል።

ኃላፊው በወረዳ ደረጃ የግብርና ስራዎችን በተመለከተ ከዚህ ቀደም የመረጃ አሰባሰብ ስካሄድ መቆየቱን አንስተው በወቅቱ የታዩ ጥንካሬዎች ማስቀጠል እና የታዩ ክፍተቶችን ከግብረሀይል ጋር እየተመካከሩ መፍታት አስፈላጊ ነው ብለዋል።

የመረጃ አሰባሰብን አስመልክቶ በስታትስቲክስ አገልግሎት ሚዛን አማን ቅ/ጽ/ቤት የስታትስቲክስ ባለሙያ የሆኑት አቶ አማረ ገረመው በሀገር ደረጃ የተስተካከለ የመረጃ ስርዓት እንዲኖር የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ኤጀንሲ በሁሉም የሀገርቱ ክፍሎች በትኩረት እየሰራ እንደሆነ አብራርተዋል።

ባለሙያው በከተማና በገጠር አከባቢዎች ወቅታዊ የሆነ የዕለት ለዕለት እንቅስቃሴን ለመለየት፤ በገጠር ያለውን የኢኮኖሚ ሽግግር ለማወቅ፤ የድርጅቶች ቋትን ወቅታዊ ለማድረግ በሀገር ደረጃ የመረጃ አሰባሰብ ስራን በመስራት የቀጣይ የሀገር ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለመተንበይ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ የጎላ ድርሻ እንዳለው አክለዋል።

ከዚህ ቀደም በግብርና ድርጅቶች ቆጠራ ላይ የተለያዩ መረጃ የመሰብሰብ ስራ መሰራቱን አንስተው ከጥቅምት ወር ጀምሮ የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ ለማካሄድ በ16 የቆጠራ ቦታዎች ላይ ስራዎች መጀመራቸውን በማንሳት የግብረሀይል መቋቋሙ ጠቀሜታ እንዳለው አሳውቀዋል።

በመጨረሻም አቶ ስዩም ባለሙያዎች መረጃ ለመሰብሰብ በሚሄዱበት ግዜ ህብረተሰብ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደረግ ጠይቀው ግብረሀይሉም የሚጠበቅበትን እንደሚያደርግ አሳውቀዋል።

በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን። ይቀላቀሉ፣ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

የወተትና የስጋ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የእንስሳት ዝሪያ ማሻሻያ (ሲንክሮናይዜሽን) ስራ ጉልህ ሚና አለው ተባለ ሻማ፦ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት...
21/10/2025

የወተትና የስጋ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የእንስሳት ዝሪያ ማሻሻያ (ሲንክሮናይዜሽን) ስራ ጉልህ ሚና አለው ተባለ

ሻማ፦ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት) በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ የዳልጋ ከብት ዝሪያ ማሻሻያ(ሲንክሮናይዜሽን) ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በግብርና አ/ጥ/ህ/ስራ ልማት ጽ/ቤት የእንስሳት ክሊኒክ ቅጥር ግብ በይፋ ተጀምሯል።

የጨታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰሎሞን ኃይሌ በማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር የዳልጋ ከብት ዝርያ ማሻሻያ (ሲንክሮናይዜሽን)ፕሮግራም የእንስሳት ዝርያ ከማሻሻልም በተጨማሪ የወተት እና የሥጋ ምርትና ምርታማነት ለመጨመር ከፍተኛ አሰተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

‎ይህ የዘመቻ ሂደት ውጤታማ እንዲሆን ሁሉም መረባረብ እንዳለበት አንስቶ ውጤቱ በተጨባጭ እንድታይ በበቂ ሁኔታ የእንሰሳት መኖ ማዘጋጀትና ማቅረብ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የወተትና የስጋ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የእንስሳት ዝሪያ ማሻሻያ ስራ ጉልህ ሚና የሚጫወት መሆኑንም አንስቶ ለውጤታማነቱ ሁሉም አካላት ርብርብ እንዲያደረጉ መልዕክታቸውን አክለዋል።

መንግሰት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት ከፍተኛ ሀብት መድቦ የላከውን የዝርያ ማሻሻያን (ሲንክሮናይዜሽን) ህብረተሰቡ በተገቢው ተጠቃሚ ለመሆን በግዜው በማምጣት ማዳቀል እንዳለባቸው መልዕክት ያስተላለፉት ደግሞ የጨታ ወረዳ ግብርና አ/ጥ/ህ/ስራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸብር ስሳይ ናቸው።

አቶ አሸብር አክለውም ህብረተሰቡ የባለሙያዎችን ምክር በአግባቡ ተግባራዊ በማድረግ የከብቶችን አያያዝና እንክብካቤ በማስተካከል የወተትና የስጋ ምርትና ምርታማነትን ከፍ ማድረግ አለበት ብሏል።

‎በማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የወረዳ አስፈፃሚ አካላት፣ የግብርና አ/ጥ/ህ/ስራ ልማት ጽ/ቤት ኃለፍና የዘርፉ ባለሙያዎችን ጨምሮ የዞን ግብርና መምሪያ የእንስሳት ዓሳ ዘርፍ ባለሙያዎችም ተገኝተዋል።

‎በወጋዬሁ ወንድሙ

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

የትምህርት  ስብራትን ለመጠገን  የባለድርሻ  አካላት  ሚና ከፍተኛ ነው÷ አቶ ሙሉገታ መሸሻ ።በካፋ  ዞን  የአዳሪ  ትምህር ት ማስጀመሪያ  መርሃ ግብር ፕሮግራም በቢሻው ወልደዮሐንስ  ሁለ...
20/10/2025

የትምህርት ስብራትን ለመጠገን የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ ነው÷ አቶ ሙሉገታ መሸሻ ።

በካፋ ዞን የአዳሪ ትምህር ት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ፕሮግራም በቢሻው ወልደዮሐንስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተጀምሯል።

የካፋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ መሸሻ እንደ ዞናችን ከሚገኙ 60 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 603 ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲ የገቡ ቢሆኑም ከነዚህ መካከል ከፍተኛውን ውጤት ላስመዘገቡ የቢሻው ወልደ ዮሐንስ መምህራኖች እና ለሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርቧል።

አሁን ላይ በግቢው ውስጥ የተጀመረውን የአዳሪ ትምህርት አጠናክረው እንደምያስቀጥሉ እና ተማሪዎች
ዓላማቸውን ከግብ ለማድረስ ትኩረት ሰጥተው መማር እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።

ተግባሩን እንደ ባለበት የምያስተባብሩ የካፋ ልማት ማህበር ዋና ስራ አሰኪያጅ አቶ ብዙአየሁ ግርማ እንደ ካፋ ዞን ይህ ፕሮግራም ሳይጀመር መቆየቱ በፈጠረው ቁጭት በ2017 ዓ/ም ለሙከራ ያስጀመሩት 45 ተማሪዎች ውጤት የተሻለ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸው ገልፀዋል ።

ለውጤቱ ሚናቸውን ለተወጡት አንጋፋ መምህራኖች ምስጋናቸውን ያቀረቡት አቶ ብዙአየሁ በ2017 ዓ/ም ትምህርታቸውን ከተከታተሉት 45 ተማሪዎች መካከል 40ዎቹ ቀጥታ ወደ ዩኒቨርስቲ የገቡ ሲሆኑ የተቀሩትም የሪሚዲያል እድል ማግኘታቸውን ገልፀው በ2018 ዓ/ም 108 ተማሪዎችን እንደምያስተናግዱ ጠቅሰዋል።

ለተግባሩ ውጤታማነት የባለድርሻ አካላት ድጋፍ ወሳኝ ነው ያሉት የዴቻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወንዱ አደሜ ለቢሻው ወልዴዮሐንስ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎች 90ሺህ ብር የምያወጣ 30 ብርድ ልብስና ሌሎች ቁሳቁሶችን አበርክተው ድጋፉ ተጠናክሮ እንደምቀጥልም ጠቅሰዋል።

የተማሪ ወላጆች በበኩላቸው ልጆቻቸው ይህንን እድል በማግኘታቸው ደስታቸውን በመግለጽ ለተማሪዎች ከቤት ውስጥ የተሻለ ድጋፍና ክትትል እንደምያደርጉ ተናግረዋል።

ተማሪዎችም ባገኙት እድል ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው ከወላጆቻቸው የተለዩበት ዋነኛው ዓላማ የሆነውን ትምህርታቸው ላይ ትኩረት በመስጠት ለሀገራቸው እና ለራሳቸው የሚሆን ውጤት እንደምያስመዘግቡ ገልፀዋል።

በመጨረሻም ተማሪዎች የተማሪ ወላጆች እንድሁም በመርሃ ግብሩ የተገኙት ባለድርሻ አካላት የተማሪዎችን ማደሪያና አካባቢዎችን ጎብኝተዋል።

ዘገበው የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

"በማንሰራራት ወደ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት 1ኛ ዙር የፐብሊክ ግንባር ህብረት ኮንፈረንስ መድረክ ተካሄደ።ሻማ፦ጥቅምት 08/2018...
20/10/2025

"በማንሰራራት ወደ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት 1ኛ ዙር የፐብሊክ ግንባር ህብረት ኮንፈረንስ መድረክ ተካሄደ።

ሻማ፦ጥቅምት 08/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት "በማንሰራራት ወደ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ዙር የፐብሊክ ግንባር ህብረት ኮንፈረንስ መድረክ ተካሂዷል።

በኮንፈረንሱ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጨታ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፍ ወ/ሮ አበባሽ አበበ መንግስት የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ እውን ለማድረግና የሀገራችን ብልጽግና ለማረጋገጥ የወጣቶችን ብቁ ኃይልን በየአደረጃጀቱ ማጠናከርና የወጣቶችን ተሳትፎ በሚገባ ማሳደግ ያስፈልጋል ብሏል።

እንደሀገር ብሎም እንደወረዳችን የወጣቶች ቁጥር ካለው የህዝብ ቁጥር እጅግ የበዛ ነው ያሉት ኃላፍ ይህን ትኩስ ኃይል ለሀገር ዕድገትና ለውጥ በአግባቡ መጠቀም ይገባናል ብሏል።

ወ/ሮ አበባሽ አክለውም የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፓርቲው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ የሚገኝ መሆኑን ገልፀው ወጣቶች ሀገር ወዳድና ስራ ወዳድ በመሆን ለሀገር ዕድገትና ለውጥ የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው ብሏል።

የጨታ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ አስጨናቂ ሙሴ የ2018 ዓ.ም 1ኛ እሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት አቅርቧል።

በሪፖርቱ አቶ አስጨናቂ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎቶች በተለይ በጤና ፣ በመሰረተ ልማትና በሌሎች ዘርፎች ቀላል የማይባሉ ስራዎች ተሰርቷል ብሏል።

በሁሉም ማህበራዊ መሰረቶች የወጣቶች ክንፍ አደረጃጀት ማጠናከር ፣ ዓመታዊ መዋጮ መሰብሰብ ፣ አዳዲስ አባላት መመልመልና ሌሎች መሰል ጉዳዮች በቀጣይ ልዩ ትኩረት የሚሰራ መሆኑን ገልጿል።

መድረኩን በጋራ የመሩት የጨታ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አክሊሉ አለማየሁ የወጣቶች ክንፍን በተቀናጀ መልኩ በመስራትና የተቀላጠፈ ዉጤት ለማስመዝገብ የወጣቶች ኃይል ጉልህ ሚና እንዳለዉ ገልጿል።

በአንደኛ እሩብ ዓመት በወጣቶች ክንፍ ስራ አፈፃፀም ላይ የታዩ ጉድለቶችን ፓርቲው ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራ መሆኑን ተናግሮ ወጣቶችም ለሀገር ብልጽግና የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው ገልጿል።

የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የወጣቶች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ወጣቶች ከአልባሌና ከሱስ በመላቀቅ ለሀገሪቱ ዕድገት በልማትና በበጎ ተግባር ተሳታፊ መሆን አለበት ብሏል።

በመጨረሻም ከውይይት ተሳታፊዎች ለበጎ አድራጎት የሚሆን ሀብት የተሰበሰበ ስሆን በቀጣይ ለአቅመ ደካማ እናቶች ድጋፍ የሚደረግ መሆኑም ተገልጿል።

በወጋዬሁ ወንድሙ

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

በታቦተ ህጉ ላይ የተሳለቁና የኦርቶዶክስ እምነትን ያንቋሸሹ ወጣቶች በእስራት መቀጣታቸውን የዋቻ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቀ ።በከተማው ፖሊስ የታክቲክና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ማስተባበሪ...
19/10/2025

በታቦተ ህጉ ላይ የተሳለቁና የኦርቶዶክስ እምነትን ያንቋሸሹ ወጣቶች በእስራት መቀጣታቸውን የዋቻ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቀ ።

በከተማው ፖሊስ የታክቲክና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ማስተባበሪያ ዘርፍ ኃላፊ ሳጅን አክሊሉ ዓለሙ እንደገለጹት በዋቻ ከተማ አስተዳደር 02 ቀበሌ ያማ ተብሎ በሚጠራበት ሰፈር አምስት ወጣቶች መስከረም 26/2018 ዓ/ም ዕለተ እሁድ ከቀኑ 9:00 ሰዓት አካባቢ በ5ቱ ወጣቶች አስተባባሪነት አብረሃም ክፍል በሚል መጠሪያ በተከፈተ የቲክቶክ አኳውንት የኦርቶዶክስ እምነትን በማንቋሸሽና በታቦተ ህጉ ላይ በመሳለቅ ቪዲዮ ማጋራታቸውን ነው የገለጹት።

ሳጅን አክሊሉ አክለው አምስቱ ተከሳሾች የኦርቶዶክስ ታቦትን አስመስሎ በመቅረጽ በታቦተ ህጉ ላይ ከመሳለቅ ባለፈ በኃይማኖቶች መካከል ግጭትና እልቅት እንዲፈጠር ሆን ብሎ በማሰር ድርጊቱን መፈጸማቸውን አውስተዋል።

ይህንን ድርጊት በማስመልከት ጥቆማ የደረሰው የከተማው ፓሊስ ተጠርጣሪዎችን በህግ ጥላ ስር በማዋል ወንጀሉን ስለመፈጸማቸው የሚገልጽ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን በማደራጀት ምርመራውን አጣርቶ መዝገቡን ለከተማው ዐቃቤ ህግ ማስተላለፉን ይገልጻል።

የከተማው ዐቃቤ ህግም ከፖሊስ የቀረበለትን የምርመራ መዝገብ ተቀብሎ በተጠርጣሪዎች ላይ በፌዴራል የወንጀል አዋጅ ቁጥር 414/1996፣በወንጀለኛ መቅጫ ሥነሥርዓት አንቀጽ ቁጥር 32/1(ሀ) እና የጥላቻ ንግግር አዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 እና 7(1) ላይ የተደነገገውን ህግ ተላልፎ በመገኘት ክስ መስርቶባቸዋል።

በዚህም መሠረት የዋቻ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በተከሳሾች ላይ የቀረበውን ክስ በማጣራት ተከሳሾችንም ሆነ ሌሎችን ያስተምራል በሚል ጥቅምት 7/2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በአምስቱ ተከሳሾች ማለትም 1ኛ/ ወጣት አብረሃም ክፍሌ 2ኛ/ ወጣት አሥራት ኃይሌ 3ኛ/ ወጣት እዮብ መጫሎ 4ኛ/ ወጣት ሳሙኤል ታፈሰ እና 5ኛ/ተከሳሽ ወጣት ሳሙኤል ዘውዴ ላይ የአንድ ዓመት ጽኑ እስራት ወስኖባቸዋል።

በመጨረሻም የከተማው ፖሊስ አዛዥ ተወካይ ዋና ሳጅን ደነቀ ዳኜ ባስተላለፉት መልዕክት የከተማው ማህበረሰብ እንዲህ ዓይነት ወንጀል ፈጽመው የሚገኙ አካላት ስያጋጥሙት ለከተማው ፖሊስ ጥቆማ እንዲያደርሱ ጠይቀው የከተማው ወጣትም ሆነ በየትኛውም የዕድሜ ክልል ላይ የሚገኝ የህብረተሰብ ክፍል እንዲህ ዓይነት አጸያፊ የወንጀል ድርጊት ከመፈጸም እንዲቆጠብ ጠይቀዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የዋቻ ከተማ አስ/ር መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ነው!

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

በኮሙኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት መስኮች በዞኑ የተገኘው ስኬት የአመራሩና የዘርፉ ባለሙያዎች የቅንጅት ውጤት ነው÷ አቶ ታከለ ታምሩየካፋ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በ2017 ዓ/ም...
19/10/2025

በኮሙኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት መስኮች በዞኑ የተገኘው ስኬት የአመራሩና የዘርፉ ባለሙያዎች የቅንጅት ውጤት ነው÷ አቶ ታከለ ታምሩ

የካፋ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በ2017 ዓ/ም ሥራዎች አፈፃፀም ከክልል 1ኛ ደረጃ መውጣቱን ተከትሎ የምስጋና ፕሮግራም ተደርጓል::

በፕሮግራሙ ላይ በእንግድነት የተገኙት በካፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የመንግስት ረዳት ተጠሪና የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታከለ ታምሩ በዞኑ በተለያዩ ተቋማት እየተገኙ ባሉት ተደጋጋሚ ውጤቶችና ስኬቶች መደሰታቸውን ገልጸው ለዚህም እንኳን ደስ አለን ብለዋል::

አቶ ታከለ በመልዕክታቸው በዞኑ ኮሙኒኬሽን ሴክተር የተገኘው ስኬት ተገቢና የሚጠበቅ ነው ብለው ይህም የተቋሙ አመራር ጥንካሬና የመላው ሰራተኞች የመናበብና የመቀናጀት ውጤት በመሆኑ ለበለጠ ድል መዘጋጀት ከሁሉም ይጠበቃል ብለዋል::

አቶ ታከለ በመጨረሻም ውጤቱ እንዲመዘገብ እና ዕውቅና እንዲገኝ ከላይ እስከታችኛው ያሉት የኮሙኒኬሽን መዋቅሮች ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነው የብልጽግና ፓርቲና የዞኑ መንግስት በቀጣይ ለተቋሙ ስኬታማነት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋሉ ብለዋል::

የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊው አቶ አዳሙ እሸቱ በበኩላቸው ለላቀ ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የነበራቸውን መላው ሰራተኞችና በየደረጃው የሚገኙ የኮሙኒኬሽን አመራሮች: የዞኑ መንግስት እና ፓርቲ እንዲሁም የተለያዩ ባለድርሻ አካላትንና መላውን ህዝብ አመስግኗል::

አቶ አዳሙ አክሎ የተገኘው ስኬት በርካታ ውጣውረዶችን ታልፎ መሆኑን አንስተው ይህም ለቀጣይ ሥራችን መነሳሳትን የፈጠረ እና ተጨማሪ አቅም የሆነ ነው ብለዋል::

በመጨረሻም በተቋሙ የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ አካላትና ሥራ ሂደቶች ምስጋናና ዕውቅና ተበርክቶላቸዋል::

በፕሮግራሙ ላይ የዞኑ የመንግስት ረዳት ተጠሪዎች አቶ ታከለ ታምሩና አቶ ጋዎ አባመጫ:የዞኑ ፋይናንስ መምሪያ ኃላፊ አቶ መቅደስ ማሞ:ሌሎች የዞን አመራሮች:የማናጅመንት አባላትና የዞን ኮሙኒኬሽን ሴክተር ሰራተኞች ተገኝቷል ሲል የዘገበው የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

Address

Kafa Cheta
Bonga

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share