25/09/2025
በአዲሱ የትምህርት ዘመን የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ ከወዲሁ ተጨማሪ የድጋፍ ትምህርቶችን አጠናክሮ መስጠት በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ያግዛል ስሉ የጨታ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ ተናገሩ።
ሻማ:-መስከረም 15/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)
በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ወቅታዊ የትምህርት ስራ ዙሪያና በአዲሱ የ2018 ዓ/ም ዘመን ትምህርትን በተመለከተ ከወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ማኔጀመንት አካላት ጋር ውይይት ተደረጓል።
የውይይት መድረኩን የመሩት የወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ በትምህርት ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ ከዚህ በፊት የታዩ ክፍተቶችን ለይቶ መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል።
በአዲሱ የትምህርት ዘመን የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ ከወዲሁ ተጨማሪ የድጋፍ ትምህርቶችን አጠናክሮ መስጠት በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ያግዛል ያሉት አስተዳዳሪው የድጋፍ ትምህርቶች በተመረጡ አስተማሪዎች የመስጠት ጉዳይ በልዩ ትኩረት መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል።
አሁን ላለንበት ደረጃ እና እዚህ ለመድረሳችን ትላንት በቁጭትና በቁርጠኝነት ሳይታክቱ ያበቁንን መምህራንና የዘርፉ ደጋፊዎችን በማሰብ ዛሬን በቁጭት መስራት አለብን ያሉት አቶ ሰለሞን የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ሳይታክቱ መደገፍ እንዳለባቸው ጠይቀዋል።
የትምህርትን ስብራት ለመጠገን እና በዘርፉ የሚመዘገበውን የዉጤት ማሽቆልቆል ለመቅረፍና የተሻለ የትምህርት ጥራት ለማስመዝገብ የጽ/ቤት ባለሙያዎችና ማናጅመንቶች በቅንጅት መስራት እንዳለባቸውም ተነስቷል።
የትምህርት ዘርፍ ከሌሎች ተቋማት በተሻለ የሰው ኃይል ያለበትና በትምህርት ሳይንስ የተሻሉ በተባሉ አካላት የሚመራ ቢሆንም በዘርፉ እየተመዘገበ ያለ ዉጤቶች ግን እንብዛም አጥጋቢ ያለመሆናቸው ተነስቶ መፍትሔ ናቸው በተባሉ ሀሳቦች ላይ መክረዋል።
የመምህራን ድልደላ ስርዓት መጠናከርና በአግባቡ መሰራት እንዳለበት ያነሱት አስተዳዳሪው በቀጣይ የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብና የበቃ ተማሪን ለመፍጠር ህጋዊ እርምጃ በመምህራን ላይ በመውሰድ ብቁና የተሻሉ መምህራንን መፍጠርና እንዲበቁ ማድረግ ነገ የማይባል ነው ብለዋል።
ትውልድ ላይ በልዩ ትኩረት መስራትና መደገፍ የሁላችንም ኃላፊነት መሆን አለበት ያሉት አቶ ሰለሞን የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመፍጠር ዛሬ ላይ ማገኘት ያለበት አስፈላጊውን ትምህርት እንዲያገኝ አፅኖት ሰጥተን መስራት አለብን ብለዋል።
መምህራን በየትምህርት ቤቱ ያለመገኘት፣ የመማሪያ ቁሳቁስ እጥረት፣ የመምህራን ያለመዘጋጀትና በተሰማሩበት የትምህርት ዘርፍ ብቁ አለመሆን፣ ትምህርት ቤቶች ለተማሪ ምቹ አለመሆን፣ ተቀናጅቶ የመስራትና ኃላፊነትን በአግባቡ ያለመወጣትና ሌሎች ችግር በተማሪዎች ዉጤት ላይ እንቅፋት ስሆን መቆየታቸውን የመድረኩ ተሳታፊዎች አንስተዋል።
የትምህርት ስራ በተግባር የሚለካ ነው ያሉት የወረዳ ም/አስተዳዳሪና የሥራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ከተማ ከፍያለው
በሀገር ደረጃ የሚስተዋለው የትምህርት ስብራት ለመጠገን እንደሀገር እየተሰራ እንደሆነ ተነስቶ የትምህርት ስራ በተግባር የሚለካ እንደሆነና እንደወረዳ በፊት ከታዩ ክፍተቶች በመነሳትና በመገምገም በአዲሱ የትምህርት ዘመን መፍተሔ መፈለግና መሰረታዊ ችግሮችን ለይቶ በመፍታት ከውድቀት ለመነሳት ከአሁኑ አንስቶ መስራት ያስፈልጋል ተብለዋል።
የጽ/ቤት ማናጅመንት የዘርፉ ባለሙያዎችም ሆኑ የሚመለከታቸው አካላት በወረዳ ደረጃ የሚታየውን የትምህርት ውድቀት ለማስተካከልና ስብራቱን ለመጠገን የሚያስችል ቁመና ላይ ልሆኑ እንደሚገባ ተጠይቀዋል።
በመድረኩ ሁሉም የወረዳ አስተባባሪዎች፣ የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊና ማኔጀመንት አካላት እንዲሁም የጽ/ቤት ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0