Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Bonga
  • Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን

Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን cheta woreda govt comm affairs
የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

በአመራሩና በአባላቱ ዘንድ እምርታዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ እና የአስተሳሰብ አንድነትን ለመፈጠር ስልጠናው የጎላ ድርሻ አለው፦አቶ ነፃነት ብርሃኑሻማ:-ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መ...
30/08/2025

በአመራሩና በአባላቱ ዘንድ እምርታዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ እና የአስተሳሰብ አንድነትን ለመፈጠር ስልጠናው የጎላ ድርሻ አለው፦አቶ ነፃነት ብርሃኑ

ሻማ:-ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በተከታታይ ለሶስት ቀናት በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል ለወረዳና ቀበሌ መካከለኛና የበታች አመራርና ለቀበሌ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች ስሰጡ የቆየው የስልጠና መድረክ ተጠናቋል።

"ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በተሻገረ ህልም፣ በላቀ ትጋት፣ በአስተማማኝ ነገን መስራት"

በመድረኩ የተገኙት የካፋ ዛን ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት መምሪያ ኃላፊ አቶ ነፃነት ብርሃኑ በአመራሩና በአባላቱ ዘንድ እምርታዊ ብልፅግና ለማረጋገጥና የአስተሳሰብ አንድነትን ለመፈጠር ስልጠናው የጎላ ድርሻ አለው ብለዋል።

አቶ ነፃነት ብልፅግና በ2023 ዓ/ም ኢትዮጵያ የአፍርካ ተምሳሌት፣ በ2040 ዓ/ም የዓለም ብልፅግና ተረጋግጦ ኢትዮጵያ የዓለም ተምሳሌት ለመሆን ጠንካራ ትሰራለች በማለት አሁን ላይ በዕቅዷ መሰረት የኢትዮጵያ ተምሳሌት ሆናለች ነው ያለት።

የወረዳው መንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ዘዉዴ እንደገለፁት በተከታታይ ለሦስት ቀናት በሀገር ደረጃ የአመራሩን አቅም ይገነባል ተብሎ የተሰናዳውን የስልጠና ስነድ በወረዳ ደረጃ ሁሉም የመካከለኛና የበታች አመራር በድስፕሊን ተከታትሎ ማጠናቀቃቸውን አንስተዋል።

አቶ አለሙ ፓርቲያችን ብልፅግና ወደ ስልጣን ከመጣበት ግዜ ጀምሮ በረካታ የውስጥ ባንዳና የውጭ ባዳ ሀገሪቱን ለማድከም የተለያዩ ችግሮች መፍጠራቸውን ገልፀው ለፈተናዎች ሳይበገር በርካታ ሀገራዊ ድሎችን ያስመዘገበ መሆኑን አንስተው ለዚህም የአባይ ህዳሴ ግድብ በስኬት መጠናቀቁን ብቻውን ታላቅ መስክር ነው ብለዋል።

የወረዳ ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ ስልጠናው በሀገር ደረጃ ከፌዴራል ጀምሮ ለሁሉም ስሰጥ መምጣቱንና እስከ ታችናው ደጋፊ አባላት ድረስ እንደሚሰጥ አንስተው ድሎችን የሚያጎላ፣ ስኬቶችን የሚያስቀጥል እና ችግሮችን የሚጋፈጥ ብርቱ አመራርና አባል ለመፈጠር ያተኮረ ነው ብለዋል።

አቶ ሰለሞን በቀጣይ የህዝቡን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመፈታት ደረጃ በደረጃ ተይዞ እንደሚሰራ ገልፀው መንግስት የመንግስት ሰራተኛ ኑሮ ለማረጋጋት ያደረገውን የኑሮ ማሻሻያ ማድረጉን ተከትሎ አላስፈላጊ ዋጋ የሚጨምሩ አካላት ላይ እርምጃ ለመወሰድ ይሰራል ነው ያሉት።

በኢኮኖሚ የበለፀገች ሀገር ለመገንባት የበለፀገ እና በኢኮኖሚ እራሱን የቻለ ዜጋ መፍጠር እንደሚያስፈልግ የገለፁት አቶ ነፃነት ብርሃኑ ህብረተሰቡን የኢኮኖሚ ባለቤት ለማድረግ ሁሉም አካል ጠንክሮ እንዲሰራ ጠይቀዋል።

በመጨረሻም ከሁሉም የቀበሌ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር የወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የጋራ የግብ ስምምነት ተፈራርመዋል።

በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

ሶስተኛ ቀኑን ያስቆጠረው የወረዳ አመራሮች ስልጠና ዛሬም እየተካሄደ ይገኛል።ሻማ:-ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ብልፅግና ...
30/08/2025

ሶስተኛ ቀኑን ያስቆጠረው የወረዳ አመራሮች ስልጠና ዛሬም እየተካሄደ ይገኛል።

ሻማ:-ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር" በተሻገረ ህልም፣ በላቀ ትጋት፣ በአስተማማኝ ነገን መስራት በሚል መሪ ቃል ለወረዳ አመራሮች፣ ለቀበሌ አስተዳደርና ለቀበሌ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች ሶስተኛ ቀኑን ያስቆጠረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

በመድረኩም የወረዳ አስፈፃሚ አካላትና አመራሮች፣ የቀበሌ አስተዳደሮችና የቀበሌ በፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎች የተገኙ ስሆን መድረኩ ዛሬ ማጠቃለያውን ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል።

በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ሁለተኛ ቀኑን የያዘዉ "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር "በሚል  መሪ ሀሳብ የወረዳ አመራሮች እና የበታች አመራሮች ስልጠና ተጠናክረው ቀጥለዋል።ሻማ:-ነሐሴ 23/2017...
29/08/2025

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ሁለተኛ ቀኑን የያዘዉ "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር "በሚል መሪ ሀሳብ የወረዳ አመራሮች እና የበታች አመራሮች ስልጠና ተጠናክረው ቀጥለዋል።

ሻማ:-ነሐሴ 23/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በሁለተኛ ቀን ስልጠና "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር " በተሻገረ ህልም ፣በላቀ ትጋት ፣አስተማማኝ ነገን መስራት በሚል መሪ ቃል በቀረበዉ ሰነድ ላይ የወረዳ አመራሮች እና የበታች አመራሮች በቡድን እየተወያዩ ይገኛሉ።

ዘገባዉ የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ!

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር " በተሻገረ ህልም ፣በላቀ ትጋት ፣አስተማማኝ ነገን መስራት በሚል  መሪ ቃል በጨታ ወረዳ የወረዳ እና የበታች አመራሮች ስልጠና መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።ሻ...
28/08/2025

"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር " በተሻገረ ህልም ፣በላቀ ትጋት ፣አስተማማኝ ነገን መስራት በሚል መሪ ቃል በጨታ ወረዳ የወረዳ እና የበታች አመራሮች ስልጠና መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

ሻማ:-ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

የወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰሎሞን ኃይሌ እንደገለጹት ሁሉም አመራር አለም አቀፋዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ወጥ የሆነ ግንዛቤ ይዘዉ በአመለካከትና በተግባር አንድነት የተሻለ ለዉጥ ለማስመዝገብ ወሳኝ እንደሆነም ተናግረዋል ።

አቶ ሰሎሞን አክለውም እንደ ሀገር የለዉጡ መንግስት ከገባበት ጀምሮ በኢኮኖሚ፣በማህበራዊና በፓለቲካ ጉዳዮች ላይ በርካታ ለዉጦች መመዝገባቸዉን በዝርዝር አስረድተዋል።

የወረዳው መንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ በሆኑት በአቶ አለሙ ዘዉዴ "ኢትዮጵያ ወደ ተምሳሌት ሀገር " በሚል መሪ ቃል ለወረዳ አመራሮችና ለበታች አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

ዘገባዉ የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ!

ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇?? https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

በጨታ ወረዳ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ ግንባር ባለሙያዎች ተሰጠ።ሻማ:-ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)የካፋ ዞን ኢንዱስትሪና...
28/08/2025

በጨታ ወረዳ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ ግንባር ባለሙያዎች ተሰጠ።

ሻማ:-ነሐሴ 22/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

የካፋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን መምሪያ ከጨታ ወረዳ ኢንዱስትሪና ንግድ ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን ለወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ ግንባር ባለሙያዎች ተሰጥቷል።

የስልጠናውን መድረክ በንግግር ያስጀመሩት የወረዳ ኢንዱስትሪና ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ አበበ በቴክኖሎጂና በአርተፊሻል አስተውሎት አጠቃቀም የተሻለ ዜጋ ለመገንባት ኢትዮጵያ በትኩረት እየሰራች ትገኛለች ብለዋል።

ሁሉም ባለሙያ ስልጠናውን በዲስፕሊን መውሰድ እንዳለበት የጠቆሙት አቶ አጥናፉ አበበ ከዘመኑ ጋር እኩል ለመሄድ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ድርሻው የጎላ እንደሆነ አንስተዋል።

የካፋ ዞን ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን መምሪያ የኢኮቴ/መሰረት/ል/ዝር/አስ/ር/ቡ/መሪ አቶ አወል አባገሮ እና የዕቅድ/በ/ዝ/ክ/ግ/አስ/ሪ አቶ ታዬ ገ/ሚካኤል የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ሂደትን በተመለከተ ለሰልጣኞች ግንዛቤ አስጨብጠዋል።

ባለሙያዎቹ በ(Android developer fundamentals) በ(Artificial intelligence fundamentals) በ(data analysis fundamentals) እና በ(Programming fundamentals) ዙሪያ ስልጠና ሰጥተዋሉ።

አቶ አጥናፉ በበኩላቸው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በሀገር ደረጃ ለ5 ሚልዮን ሰልጣኞች እስከ 2027 እ.አ.አ ድረስ በነፃ እንደሚሰጥ አንስተው የወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ ግንባር ባለሙያዎች የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጠይቀዋል።

በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

28/08/2025
የተቀነሰም፤የተባረረም ሠራተኛ የለም።የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ለክልሉ ህዝቦች ተጠቃሚነት እየሰራ ይገኛል።ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል...
28/08/2025

የተቀነሰም፤የተባረረም ሠራተኛ የለም።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ለክልሉ ህዝቦች ተጠቃሚነት እየሰራ ይገኛል።

ክልሉ ከተመሰረተ ወዲህ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በዚህ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ ሌተቀን እየተጋ ነዉ።አንዳንድ የፖለቲካ ነጋዴዎች እና ሚዛናዊነት የጎደለዉን የአንድን ወገን አጀንዳ ይዘዉ የሚንቀሳቀሱ የማህበራዊ ሚዲያ ድህረ ገጾች በክልሉ የመንገዶች ባለስልጣን ሠራተኞች ከስራ ሊሰናበቱ ነዉ የሚል የፈጠራ ወሬ እያሰራጩ መሆኑን ተመልክተናል ።

የክልሉ መንግስት የትኛዉንም ዓይነት ዉሳኔ ከህዝብ ፍላጎትና ተጠቃሚነት አኳያ እየወሰነ እና ተግባራዊ እያደረገ የመሄድ ህገ መንግስታዊ ስልጣን ያለዉ ነዉ።ከአሁን ቀደም በክልሉ የታችኛዉ የአስተዳደር መዋቅር ያለዉ የሥራ መደብ ከኢፌዲሪ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር በመሆን መልሶ የመጣጣምና የማስተካከል ስራም ሰርቷል።

በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን ስር ባሉት ሶስቱ ዲስትሪክቶች አጠቃላይ የመዋቅሩን የመፈጸም አቅም ለማሳደግ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን ይህንን ሥራ የማይፈልጉ አካላት አሁን ላይ ለከንቱ ፖለቲካ ዓላማቸዉ ሀሰተኛ እና የክልሉ መንግስት ያልወሰነዉን ዉሳኔ እንደተወሰነ ተደርጎ የተሰራጨዉ መረጃ ስህተት መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።

እዉነቱን ከምንጩ ሳይጣሩ ይህንን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ የሚያሠራጩ አካላትም ከድርጊታቸዉ እንዲቆጠቡ እናሳስባለን ሲል የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል ።

በወረዳ ደረጃ ዞን አቀፍ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን 77ነጥብ 1በመቶ ማሳለፍ መቻሉን የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አሳወቀ።ሻማ:-ነሐሴ 21/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉ...
27/08/2025

በወረዳ ደረጃ ዞን አቀፍ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን 77ነጥብ 1በመቶ ማሳለፍ መቻሉን የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አሳወቀ።

ሻማ:-ነሐሴ 21/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

የጨታ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ዞን አቀፍ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 77 ነጥብ 1በመቶ ማሳለፍ መቻሉን አሳውቀዋል።

የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ክፍሌ ዞን አቀፍ ፈተናን ለመውሰድ ከተቀመጡ 517 ተማሪዎች ወደ ቀጣዩ ክፍል 399ተማሪዎች መዘዋወራቸውን አሳውቀዋል።

አክለውም አቶ ሙሉጌታ በወረዳ ደረጃ 50ነጥብ 9በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች በሁሉም የትምህርት አይነት ከ50 ነጥብ በላይ ማምጣታቸውን ገልፀው የተሸጋገሩሙ ሆነ የደገሙ ተማሪዎች በየትምህርት ቤት በመገኘት እንደየ ደረጃቸው እንዲመዘገቡ በማሳሰብ የሚመለከተው አካል የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

ድልድይ ባለመኖር ምክንያት በአንድ ክላስተር የሚኖሩ የአራት ቀበሌ ነዋሪዎች ዛሬም የእናቶችን ሞት እያስተናገዱ ይገኛሉ ተባለ። ሻማ:-ነሐሴ 21/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽ...
27/08/2025

ድልድይ ባለመኖር ምክንያት በአንድ ክላስተር የሚኖሩ የአራት ቀበሌ ነዋሪዎች ዛሬም የእናቶችን ሞት እያስተናገዱ ይገኛሉ ተባለ።

ሻማ:-ነሐሴ 21/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ፈለገ-ሰላም ምርጫ ክልል የኢፌዴሪ እና የክልል የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ከመረጣቸው ህዝብ ጋር በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

የፈለገ-ሰላም ምርጫ ክልል ህዝብ ተወካይ ምክር ቤት አባል አቶ ዳውድ መሐመድ ህግ የማውጣት፣ ተፈፃሚነት ላይ ከህዝብ ጋር መወያየት፣ ስራ ላይ ስለ መዋሉ ማረጋገጥና መሰል መሰረታዊ የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ እየተሰራ እንደሚሰራ አስረድተዋል።

ምክር ቤቱ ህግ የማውጣት፣ የወጣው ህግ ጠቀሜታ ላይ ከህዝብ ጋር መወያየት፣ ስራ ላይ ስለ መዋሉ ማረጋገጥና መሰል መሰረታዊ የህዝብ ተጠቃሚነት ላይ እንደሚሰሩ አክለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎችም የመንገድ ተደራሽነት፣ የሆስፒታል አገልግሎት፣ የብረት ማዕድን ወደ ስራ አለመግባት፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የሾካ ድልድይ፣ የባንክና የቴሌኮም አገልግሎት አለመኖር፣ ለተማሪዎች የመማሪያ ክፍልና ቁሳቁስ ያለመሟሏትና መሰል በወረዳ የሚታዩ የመሰረተ ልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አንስተዋል።

ኑሮ ውድነትና አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ፣ ሙስናና ብልሹ አሰራር፣ የወባ ወረርሽኝ እና የመድሀኒት አቅርቦት እጥረት፣ ትራንስፖርት ላይ ያሉ አላስፈላጊ ጭማሪዎችን እና ሌሎች ህገወጥና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመከላከል በህዝብ ተጠቃሚነት ላይ የሚያገለግሉ የተለያዩ ህጎች እያወጣ ብሆንም ተፈፃሚነታቸው እምብዛም እንዳልሆነ አክለዋል።

ድልድይ ባለመኖር ምክንያት በአንድ ክላስተር የሚኖሩ የአራት ቀበሌ ነዋሪዎች ዛሬም የእናቶች ሞትን እያስተናገዱ እንደሚገኙ ተገልጿል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ንጉሴ ወልደጊዮርጊስ በክልሉ የመንገድ መሰረተ ልማት ችግር እንዳለ በማንሳት የበጀት ችግሮችን በመቅረፍ በየደረጃው ለመፍታት እየተሰራ እንደሆነ እና በወረዳ ያሉ የህብረተሰብ ተሳትፎዎች መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል።

አቶ ንጉሴ እንደሀገር የኑሮ ውድነት ለመቀነስ መንግስት ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሆነ በማንሳት ችግሮችን ለመቅረፍ በነጋዴዎችና ተጠቃሚዎች አስተሳሰብ ላይ መስራት እንደሚጠበቅ አስቀምጠዋል።

በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተጀመሩ የልማት እንቅስቃሴዎች የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጎላ ድርሻ እንዳለው ያነሱት የወረዳ ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ በቀጣይ ተሳትፎን በማጠናከር የልማት ስራዎችን እናጠናክራለን ብለዋል።

ድልድይ ባለመኖር ምክንያት የአራት ቀበሌ ነዋሪዎች ዛሬም የተለያዩ እንግልት ውስጥ መኖራቸውን ያነሱት አስተዳዳሪው ወንዙን መሻገር ባለመቻላቸው የእናቶች ሞት አልቆመም ብሏል።

አክለው መንግስታዊ ባለሆኑ ድርጅቶች ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ጨምሮ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሆኑ በማንሳት የእድሉ ተጠቃሚዎችም የተፈጠረላቸው አጋጣሚ ወደ ውጤት በመቀየር የኢኮኖሚ ባለቤት እንዲሆኑ ጠይቀዋል።

በሀገር ደረጃ እኩል ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የፌዴራል መንግስት እንደሚሰራ ያነሱት አቶ ዳውድ አስተዳደራዊ ወጪዎችን በመቀነስ ከመንግስት የሚለቀቁ በጀቶችን በአግባቡ መጠቀም አለበት ብለዋል።

በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

27/08/2025
በጃፓን ቶኪዮ ሰርቶ ያለፈውን ታሪክ ለመዘከር በማለም በጃፓን ካሳማ ከተማ የመታሰቢያ መንገድ በስሙ ተሰይሞለታል፦ጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ … በኦሎምፒክ ውድድር አሸንፎ የወርቅ ሜዳ...
27/08/2025

በጃፓን ቶኪዮ ሰርቶ ያለፈውን ታሪክ ለመዘከር በማለም በጃፓን ካሳማ ከተማ የመታሰቢያ መንገድ በስሙ ተሰይሞለታል፦ጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ …

በኦሎምፒክ ውድድር አሸንፎ የወርቅ ሜዳሊያ መውሰድ የቻለ የመጀመሪያው አፍሪካዊ አትሌት ነው - ኢትዮጵያዊው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ፡፡

በድል ላይ ድል በመቀዳጀት እናት ሀገሩን ከተመኘው በላይ ሰንደቋ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ አድርጎ ያለፈ የአትሌቲክሱ የዘመናት ጀግና ነው፡፡

ከሀገሩ ልጆች ባሻገር አፍሪካውያን በኦሎምፒክ መድረክ ከፍ ብለው እንዲታዩና በድል እንዲደምቁ ፈር ቀዳጅ የአሸናፊነት አብነት ነው፡፡

በፈረንጆቹ 1960 በሮም ኦሎምፒክ በባዶ እግሩ ሮጦ የኦሎምፒክን ክብረወሰን በመስበር ጭምር ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካና ለመላው ጥቁር ህዝብ ድል ማብሰር ችሏል፡፡

ከውድድሩ አስቀድሞ ፈጽሞ ለአሸናፊነት ያልተጠበቀው አትሌት አበበ በቂላ ድል ማድረጉ በወቅቱ መነጋገሪያ አድርጎት ነበር፡፡

የጣልያን ጋዜጦች በድሉ ማግስት "ጣልያን ኢትዮጵያን ለመውረር በርካታ ወታደር አስፈልጓት ነበር ኢትዮጵያ ግን አንድ ወታደር ብቻ ልካ ድፍን ሮምን ወረረች" በማለት ስለ አስደናቂው ድል ማስነበባቸው ይነገራል፡፡

የጀግናው አትሌት አበበ ቢቂላ የሮም ገድል ብዙ አፍሪካውያን አትሌቶች በዓለም አቀፍ ውድድር እንዲሳተፉ ዕድል የፈጠረና ለድል ያነሳሳ ነበር፡፡

አበበ ቢቂላ በሮም በተቀዳጀው ድል የተደመመው የስፖርት ቤተሰብ በፈረንጆቹ 1964 በቶኪዮ ኦሎምፒክ ዳግም እሱን ለመመልከት በጉጉት ሊጠብቀው ግድ ብሎታል፡፡

ነገር ግን የቶኪዮ ኦሎምፒክ በተቃረበበት ጊዜ አበበ ቢቂላ ልምምድ ላይ እያለ ያጋጠመው ሕመም አብዝቶ ሲጠብቀው የነበረውን የስፖርት ቤተሰብ ያሳዘነ ነበር፡፡

አበበ ቢቂላ ከኢትዮጵያ የኦሎምፒክ ቡድን ጋር ወደ ቶኪዮ ቢጓዝም ውድድሩ ላይ ይሳተፋል ብሎ የጠበቀ ሰው አልነበረም፡፡

ጀግናው አትሌት ግን ከ41 ሀገራት ከተውጣጡ 79 ተወዳዳሪዎች ጋር ተወዳድሮ በድጋሚ ድል ከመቀዳጀት ባለፈ የራሱን ክብረ ወሰን በማሻሻል ሌላ ታሪክ መጻፍ ችሏል፡፡

አበበ በቶኪዮ ያሳየው ብቃት የኦሎምፒክ ማራቶን አስደናቂ ውድድሮች ተብለው በመጽሃፍ ከታተሙት ታሪኮች ውስጥ ዋና ተጠቃሽ መሆን የቻለ ሲሆን፥ እንከን የለሽ የማራቶን ሯጭ የሚል ስያሜ አስግኝቶለታል፡፡

2ኛውን ወርቅ ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለስ በአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ የጀግና አቀባበል የተደረገለት ጀግናው አትሌት፥ ከአቀባበሉ በኋላ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የሻምበልነት ማዕረግና አዲስ ቮልስ ዋገን መኪና ሸልመውታል።

ሻምበል አበበ ቢቂላ ከእነዚያ ደማቅ ድሎች በኋላ በአንድ ወቅት መኪና ሲያሽከረክር ባጋጠመው አደጋ ከወገቡ በታች ጉዳት ደርሶበት እግሮቹን ማንቀሳቀስ የማይችለበት ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር፡፡

ከአደጋው በኋላ እነኚያ ዓለምን ያስደነቁ እግሮች ዳግም መራመድ ባይችሉም የአትሌትነትና የስፖርተኛነት መንፈሱ እንደ ወትሮው ብርቱ ነበር፡፡

በተሸከርካሪ ወንበር አካል ጉዳተኞች በሚሳተፉባቸው ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በማሸነፍ በሌላ መድረክ የሀገሩን ሰንደቅ ዓላማ በዓለም አደባባይ እንዲውለበለብ አድርጓል፡፡

አበበ ቢቂላ ከኦሎምፒክ ድሎቹ በተጨማሪ በተለያዩ ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያን ወክሎ በመሳተፍ ድል ማድረግ የቻለ አትሌት እንደነበር ይታወሳል፡፡

በጃፓን ቶኪዮ ሰርቶ ያለፈውን ታሪክ ለመዘከር በማለም በጃፓን ካሳማ ከተማ ባሳለፍነው ሰኞ የመታሰቢያ መንገድ በስሙ ተሰይሞለታል፡፡

ጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ በሰራቸው ገድሎች ከዘመን ዘመን ሲወደስ የሚኖር ህያው ጀግና አትሌት ነው፡፡ ከFBC

ሻማ:-ነሐሴ 21/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

ከቤተሰቦቻቸው እጅ በማምለጥ ወደ ማያውቁበት አካባቢ ስጠፉ የነበሩ ህፃናትን አስመልሻለው አለ፦ የጨታ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት።ሻማ:-ነሐሴ 20/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉ...
26/08/2025

ከቤተሰቦቻቸው እጅ በማምለጥ ወደ ማያውቁበት አካባቢ ስጠፉ የነበሩ ህፃናትን አስመልሻለው አለ፦ የጨታ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት።

ሻማ:-ነሐሴ 20/2017 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

የካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ከቤተሰቦቻቸው እጅ በማምለጥ ወደ ማያውቁበት አካባቢ ስጠፉ የነበሩ ሁለት ህፃናትን ወደየ ቤተሰቦቻቸው ማስመለሱን ገልፀዋል።

የወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ጌትነት ደምሴ እንዳሳወቁት ከጨታ ወረዳ ወዳ ቀበሌ በመነሳት ስራ እንሰራለን በማለት በቀን 17/12/2017 ዓ/ም ከመኖሪያ ቤታቸው ስጠፉ የነበሩ ህፃን አርጋሽ አስናቀ እና አባይነሽ ከሮ የተባሉትን በመያዝ ለቤተሰቦቻቸው መመለስ መቻሉን ገልፀዋል።

ከአከባቢ መሰወራቸውን ከህፃናቶቹ ቤተሰቦች ጥቆማ የደረሰው የወረዳ ፖሊስ የተቀናጀ ክትትል በማድረግ ጨታ ወረዳ ባሽ-ቀይ ከተማ ከደረሱ በኃላ በዛው ዕለት በቀን 17/12/2017 ዓ/ም በቁጥጥር ስል ማዋሉን ፖሊስ አሳውቀዋል።

ህፃናቶቹ ተማሪዎች መሆናቸውን የገለፁት የህፃናቶቹ ቤተሰቦች ፖሊስ ላደረገው ትብብር በማመስገን ለልጆቻቸው አስፈላጊውን ትኩረትና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንደሚመልሱ አሳውቀዋል።

ጤነኛ ትውልድ ለመፍጠር የህፃናት ወላጆችና አሳዳጊዎች በህፃናት አስተዳደግ ላይ በቂ የሆነ ግንዛቤ እንዲይዙ የጠየቁት ምክትል ኢንስፔክተር ጌትነት ደምሴ ህፃናት ያለ እድሜያቸው ከቤተሰቦቻቸው በሚወጡበት ግዜ የጉልበት ብዝበዛና የበሽታ ተጠቂ እንደሚሆኑ በመግለፅ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

Address

Kafa Cheta
Bonga

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share