Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Bonga
  • Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን

Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን cheta woreda govt comm affairs
የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን

በአዲሱ የትምህርት ዘመን የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ ከወዲሁ ተጨማሪ የድጋፍ ትምህርቶችን አጠናክሮ መስጠት በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ያግዛል ስሉ የጨታ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ...
25/09/2025

በአዲሱ የትምህርት ዘመን የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ ከወዲሁ ተጨማሪ የድጋፍ ትምህርቶችን አጠናክሮ መስጠት በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ያግዛል ስሉ የጨታ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ ተናገሩ።

ሻማ:-መስከረም 15/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ወቅታዊ የትምህርት ስራ ዙሪያና በአዲሱ የ2018 ዓ/ም ዘመን ትምህርትን በተመለከተ ከወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ማኔጀመንት አካላት ጋር ውይይት ተደረጓል።

የውይይት መድረኩን የመሩት የወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ በትምህርት ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ ከዚህ በፊት የታዩ ክፍተቶችን ለይቶ መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል።

በአዲሱ የትምህርት ዘመን የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ ከወዲሁ ተጨማሪ የድጋፍ ትምህርቶችን አጠናክሮ መስጠት በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ያግዛል ያሉት አስተዳዳሪው የድጋፍ ትምህርቶች በተመረጡ አስተማሪዎች የመስጠት ጉዳይ በልዩ ትኩረት መሰራት እንዳለበት አሳስበዋል።

አሁን ላለንበት ደረጃ እና እዚህ ለመድረሳችን ትላንት በቁጭትና በቁርጠኝነት ሳይታክቱ ያበቁንን መምህራንና የዘርፉ ደጋፊዎችን በማሰብ ዛሬን በቁጭት መስራት አለብን ያሉት አቶ ሰለሞን የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ሳይታክቱ መደገፍ እንዳለባቸው ጠይቀዋል።

የትምህርትን ስብራት ለመጠገን እና በዘርፉ የሚመዘገበውን የዉጤት ማሽቆልቆል ለመቅረፍና የተሻለ የትምህርት ጥራት ለማስመዝገብ የጽ/ቤት ባለሙያዎችና ማናጅመንቶች በቅንጅት መስራት እንዳለባቸውም ተነስቷል።

የትምህርት ዘርፍ ከሌሎች ተቋማት በተሻለ የሰው ኃይል ያለበትና በትምህርት ሳይንስ የተሻሉ በተባሉ አካላት የሚመራ ቢሆንም በዘርፉ እየተመዘገበ ያለ ዉጤቶች ግን እንብዛም አጥጋቢ ያለመሆናቸው ተነስቶ መፍትሔ ናቸው በተባሉ ሀሳቦች ላይ መክረዋል።

የመምህራን ድልደላ ስርዓት መጠናከርና በአግባቡ መሰራት እንዳለበት ያነሱት አስተዳዳሪው በቀጣይ የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብና የበቃ ተማሪን ለመፍጠር ህጋዊ እርምጃ በመምህራን ላይ በመውሰድ ብቁና የተሻሉ መምህራንን መፍጠርና እንዲበቁ ማድረግ ነገ የማይባል ነው ብለዋል።

ትውልድ ላይ በልዩ ትኩረት መስራትና መደገፍ የሁላችንም ኃላፊነት መሆን አለበት ያሉት አቶ ሰለሞን የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመፍጠር ዛሬ ላይ ማገኘት ያለበት አስፈላጊውን ትምህርት እንዲያገኝ አፅኖት ሰጥተን መስራት አለብን ብለዋል።

መምህራን በየትምህርት ቤቱ ያለመገኘት፣ የመማሪያ ቁሳቁስ እጥረት፣ የመምህራን ያለመዘጋጀትና በተሰማሩበት የትምህርት ዘርፍ ብቁ አለመሆን፣ ትምህርት ቤቶች ለተማሪ ምቹ አለመሆን፣ ተቀናጅቶ የመስራትና ኃላፊነትን በአግባቡ ያለመወጣትና ሌሎች ችግር በተማሪዎች ዉጤት ላይ እንቅፋት ስሆን መቆየታቸውን የመድረኩ ተሳታፊዎች አንስተዋል።

የትምህርት ስራ በተግባር የሚለካ ነው ያሉት የወረዳ ም/አስተዳዳሪና የሥራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ከተማ ከፍያለው

በሀገር ደረጃ የሚስተዋለው የትምህርት ስብራት ለመጠገን እንደሀገር እየተሰራ እንደሆነ ተነስቶ የትምህርት ስራ በተግባር የሚለካ እንደሆነና እንደወረዳ በፊት ከታዩ ክፍተቶች በመነሳትና በመገምገም በአዲሱ የትምህርት ዘመን መፍተሔ መፈለግና መሰረታዊ ችግሮችን ለይቶ በመፍታት ከውድቀት ለመነሳት ከአሁኑ አንስቶ መስራት ያስፈልጋል ተብለዋል።

የጽ/ቤት ማናጅመንት የዘርፉ ባለሙያዎችም ሆኑ የሚመለከታቸው አካላት በወረዳ ደረጃ የሚታየውን የትምህርት ውድቀት ለማስተካከልና ስብራቱን ለመጠገን የሚያስችል ቁመና ላይ ልሆኑ እንደሚገባ ተጠይቀዋል።

በመድረኩ ሁሉም የወረዳ አስተባባሪዎች፣ የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊና ማኔጀመንት አካላት እንዲሁም የጽ/ቤት ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

የጨታ ወረዳ ባህል ቡድን የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ"ማሽቃሮ" በዓልን በቦንግ ሻንበቶ እያከበረ ይገኛል።ሻማ:-መስከረም 13/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)...
23/09/2025

የጨታ ወረዳ ባህል ቡድን የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ"ማሽቃሮ" በዓልን በቦንግ ሻንበቶ እያከበረ ይገኛል።

ሻማ:-መስከረም 13/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

የካፈቾ ብሄር ዘመን መለወጫ(ማሽቃሮ) በዓልን የጨታ ወረዳ ባህል ቡድን በቦንግ ሻኒበቶ በመገኘት በድምቀት እያከበረ ይገኛል።

ከዓመት አንደ የሚመጣና በብሔሩ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቀው የካፍቾ ብሄር ዘመን መለወጫ"የሜነ ሻድዮ" "ማሽቃሮ" በዓል በተለያዩ ባህላዊ ሙዚቃዎችና ትርዒቶች፣ በባህላዊ ቡና አዘገጃጀትና በመሳሰሉ ኩኔቶች መድመቁን ቀጥሏል።

በዓሉን ለማክበር በጫቴራሻ የተመራ የወረዳ ባህል ቡድን፣ የወረዳ አስተባባሪና አመራሮች፣ ህፃናቶች፣ ወጣቶች፣ ሴቶችና አዛውንቶች፣ የእምነት አባቶችና የባህል መሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የሚዲያ ባለቤቶችን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።

በስፍራው ተገኝተው በዓሉን የሚያከብሩ የጨታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ኃይሌ ልክ እንደወትሮ የካፍቾ ብሄር ዘመን መለወጫ በዓል በቦንጊ ሻንበቶ ተገኝተው የወረዳ ህዝብን በሚያሳይ መልኩ እየተከበረ እንደሆነ አንስተዋል።

አጋጣሚው የወረዳን ገፅታ ለመገንባትና የቱሪዝም ፍሰቱን ለመጨመር የጎላ ድርሻ እንዳለው በማከል እምቅ አቅሟን ለማጉላት እየሰራን ነው ብለዋል።

የወረዳ ብልፅግና ፓርት ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ዘውዴ በበኩላቸው ህዝቡ የራሱን ባህል እንዲጠበቅና ለዓለም እንዲያስተዋውቁ ብልፅግና ፓርቲ በትኩረት እንደሚሰራ አብራርተዋል።

መላው የካፋ ህዝብን እንኳን አደረሳችሁ በማለት የአባይ ህዳሴ ግድብ በተመረቀበትና የዘመናት የካፋ ህዝብ ጥያቄ የነበረው የካፋ ንጉሥ ዘውድ ምላሽ ባገኘበት ወቅት መሆኑ በዓሉን ድርብ ድርብርብ ያደርገዋል ብለዋል።

የወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ኃላፊ አቶ ዘማች ቡሾ እንኳን የካፍቾ ብሄር ዘመን መለወጫ(ማሽቃሮ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት በዓሉ ለሰላምና ለአንድነት ግንባታ ድርሻ የጎላ ነው ብለዋል።

"ማሽቃሮ" የህዝብ ለህዝብ ትስስርን በማጠናከር የጋራ እሴትን እያጎላ እንደሆነ የተጠቆመ ስሆን ከትውልድ ትውልድ እየተሸጋገረ እዚህ የደረሰውን የህዝብ ማንነት ሳይበረዝ ለማስቀጠል በትኩረት ይሰራል ተብሏል።

በዓሉ በተለያዩ ባህላዊ ኩኔቶች የካፋ፣ የሸካ፣ የሽናሻ፣ የዳውሮና ሌሎች ብሔሮችም ተገኝተው በዓሉን እየታደሙ ይገኛሉ።

እንኳን ለካፍቾ ዘመን መለወጫ (ማሽቃሮ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!
በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRk

በዋዜማው ዕለት የጨታ ወረዳ ባህል ልዑክ በካፍቾ ብሄር ዘመን መለወጫ(ማሽቃሮ) በዓል የተሰናዳውን የፌስቲቫልና ካርኒቫል ዝግጅት በአደባባይ እያቀረበ ይገኛል።ሻማ:-መስከረም 12/2018 ዓ.ም...
22/09/2025

በዋዜማው ዕለት የጨታ ወረዳ ባህል ልዑክ በካፍቾ ብሄር ዘመን መለወጫ(ማሽቃሮ) በዓል የተሰናዳውን የፌስቲቫልና ካርኒቫል ዝግጅት በአደባባይ እያቀረበ ይገኛል።

ሻማ:-መስከረም 12/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በዋዜማው ዕለት የጨታ ወረዳ ባህል ልዑክ በካፋ ህዝብ በጉጉት የሚጠበቀው እና በድምቀት የሚከበረው "ማሽቃሮ" የካፍቾ ብሄር ዘመን መለወጫ በዓልን በቦንጋ ከተማ እያከበረ ይገኛል።

የወረዳ ልዑክም በዓሉን በተለያዩ ባህላዊ ኩኔቶች እያደመቁ ስሆን ከዛሬ በተጨማሪ ነገ በቦንጊ ሻንበቶ በድምቀት ይከበራል መረጃውን ተከታትለን የምናደረሰው ይሆናል።

ሁሉም የከተማ አስተዳደሮችና ወረዳዎች(12ወራፎዎች) ከህፃናት እስከ አዛውንት በማሳተፍ በዓሉን በማድመቅ ላይ ይገኛሉ።

እንኳን ለካፍቾ ዘመን መለወጫ (ማሽቃሮ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!
በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ "ማሽቃሮ"  በዓል አካል የሆነዉ የፓናል ወይይት ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ይጀመራልየፓናል ውይይቱ "ማሽቃሮ" ለሠላም እና አብሮነት በሚል መሪ ቃል በቦንጋ ከተማ ባ...
22/09/2025

የካፈቾ ብሔር ዘመን መለወጫ "ማሽቃሮ" በዓል አካል የሆነዉ የፓናል ወይይት ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ይጀመራል

የፓናል ውይይቱ "ማሽቃሮ" ለሠላም እና አብሮነት በሚል መሪ ቃል በቦንጋ ከተማ ባህል አዳራሽ ነው የሚካሄደው።

በፓናል ወይይቱ የብሔሩ ተወላጆች እና ወዳጆች የመንግስት ከፍተኛ ስራ ኃላፊዎች ፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

ተናፋቂው "የማሽቃሮ" ድባብ  | የክረምቱ ጭጋግና ደመና ተወግዶ መስኩ በአደይ ሲሞሸር ተናፋቂው የማሽቃሮ ድባብ ሲቃረብ የሀገሬው ሰው ሸብረቡ ይደራል። የከፊቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል የሆ...
22/09/2025

ተናፋቂው "የማሽቃሮ" ድባብ

| የክረምቱ ጭጋግና ደመና ተወግዶ መስኩ በአደይ ሲሞሸር ተናፋቂው የማሽቃሮ ድባብ ሲቃረብ የሀገሬው ሰው ሸብረቡ ይደራል።

የከፊቾ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ማሽቃሮ" ጭጋጋማው የክረምት ወቅት አልፎ ብርሀናማው ጊዜ መግባቱ የሚበሰርበት ነው።

የእርቅ፣ የሰላም እና የአንድነት መገለጫ በሆነው ማሽቃሮ ቀጣዩ ጊዜ የፍቅርና የልማት እንዲሆን ሁሉም የአከባቢው ተወላጆች በሀይማኖት፣ ፆታና ዘር ሳይገደቡ በአብሮነት የሚያከብሩትና ምርቃት የሚያገኙበት በዓል ነው።

ማሽቃሮ በከፋ ህዝብ ዘንድ ህዝባዊ የሆኑ ታሪኮች የሚወሱበት፣ ባህል የሚከበርበትና ዘመን የሚለወጥበት ብቻ ሳይሆን የሰላም፣ የመተሳሰብ፣ የፍቅር፣ የልማት፣ የአብሮነት እና የተስፋ መግለጫ ነው።

በዓሉ እስኪደርስ ከሰው ባለፍ የለምለሟ ምድር አዕዋፋት በዝማሬያቸው እያጀቡ እንግዶችን ለመቀበል ይቋምጣሉ። ከጥቅጥ ደን የተዘጋጀው ማርም ይጨመቃል፣ የጤፍ ጠላውም ይጠመቃል፣ ሰንጋው ይሰናዳል። እለቱ ደርሶ ቡኖ ኡዮቴ(ቡና ጠጡ) ለመባባል አዋቂውም ሆነ ህፃናቶቹ የማሽቃሮዋን የንጋት ፀሀይ እጅጉን ይናፍቋታል።

የበዓሉ እለትም ህዝቡ ዋማ ቤድቶቴ (እንኳን አደረሳችሁ) እየተባባል በለመለመው መስክ ታጅቦ በዓል ማክበሪያ ስፍራ ወደሆነው ቦንጌ ሻንቤቶ (የከፋ ነገስታት መናገሻ) ያመራል።

የከፋ ዞን ዋና አስተዳደር እንዳሻው ከበደ እንደሚሉት፤ማሽቃሮ ከበርካታ ዘመናት በፊት እየተከበረ የቆ ቢሆንም በመሀል በነበሩ የስርዓት መቀያየሮች ተቋርጦ ቆይቷል። በዓሉን ከ1998 ጀምሮ እስካሁን በየዓመቱ ማክበር ተችሏል ይላሉ።

የክረምት ወቅት አልቆ በጋ መግባቱንና የዘመን መለወጥን ተከትሎ የሚካሄድ ኩነት መሆኑን የሚገልጹት አቶ እንዳሻው፤ ከፋዎች የአዝመራን ወቅት ተንተርሰው የሐምሌ ወር በገባ ከአምስተኛው ቀን ጀምሮ 77 ቀናትን በመቁጠር ማሽቃሮን እንደሚያከብሩ ያስረዳሉ፡፡

የዘንድሮው የማሽቃሮ በዓል መስከረም 12 እና 13 በድምቀት እንደሚከበር ገልጸው፣ በመስከረም 12 አከባቢውን ማልማት፣ ቋንቋንና ባህል ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ የሚመከርበት፣ መልካም የሰሩ እውቅና የሚያገኙበትና የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎችም የሚቀመጡበት የፓናል ውይይት እንደሚኖረ ይናገራሉ፡፡

የ18ቱን የቀድሞ ከፋ ነገስታት መካነ መቃብር (ሾሻ ሞጎ) የመጎብኘት እና ወደ ቦንጊ ሻምቤቶ (የጥንት የከፋ ነገስታት መናገሻ) በህብረት የሚኬድ መሆኑን በመግለጽ፣በሀገር ሽማግሌዎች ምረቃና መልካም ምኞት በዓሉ እንደሚከበር ይገልጻሉ፡፡

በእለቱም በዞኑ የሚገኙ 12 ወረዳዎችና 5ቱ ከተማ አስተዳደሮች የራሳቸውን ተፈጥሯዊ ሀብት የማስተዋወቅ፣ የፈረስ ግልቢያ፣ ባህላዊ ዜማዎች፣ ውዝዋዜዎችና ዎሀቤ ቶፒዮ (የቁንጅና ውድድር) እንደሚኖር ጠቁመዋል፡፡

በዓሉ ለዜጎች አንድነት፣ የአከባቢውን ሰላም ለማስጠበቅ፣ እርስ በእርስ ለመጠያየቅና ተፈጥሮን ለመንከባከብ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለውም አክለዋል።

በዓሉን ህዝቡ በባለቤትነት ይዞት ከትውልድ ወደ ትውልድ ማሸጋገርና በይበልጥ ማስተዋወቅ በሚቻልበት ሁኔታ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ እንዳሻው፤ ለዚህም የሚያግዝ ምሁራንን ያካተተና የራሱ ህገ ደንብ ያለው የባህል ምክር ቤት ተቋቁሞ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል ነው ያሉት።

የበዓሉን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበረሰባዊ ጠቀሜታ መለየት በሚቻልበት ዙሪያ ምሁራን ጥናት እያደረጉበት እንደሚገኝ ገልጸው፣ በዓሉን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ ለሚመለከተው አካል ጥያቄውን አቅርቦ ውሳኔው እየተጠበቀ እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡

የማሽቃሮን በዓል የአከባቢው ማህበረሰብ ሀይማኖት፣ ፆታና ብሄር ሳይለይ በአንድነት የሚያከብረው በመሆኑ ለሰላም ግንባታ ያለው ሚና ጉልህ መሆኑን ጠቅሰው፣ወጣቱ ትውልድም ይህን ባህል ተቀብሎ በደስታ እያከበረ ያለበት ሁኔታ መኖሩን ይጠቁማሉ።

ለበዓሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን፤ የአከባቢው ተወላጆችም በበዓል አከባበር ስነስርዓት ላይ እንዲታደሙ አስተዳዳሪው መልዕክት አስተላልፏል።

#ኢ ፕ ድ

#ማሽቃሮ #አብሮነት #ሰላም

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

በቦንጊ ሻንቤቶ በሚከበረው የካፍቾ ብሄር ዘመን መለወጫ(ማሽቃሮ) በዓል ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ የበዓሉ ኮሚቴዎች ተወያዩ።ሻማ:-መስከረም 11/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳ...
21/09/2025

በቦንጊ ሻንቤቶ በሚከበረው የካፍቾ ብሄር ዘመን መለወጫ(ማሽቃሮ) በዓል ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ የበዓሉ ኮሚቴዎች ተወያዩ።

ሻማ:-መስከረም 11/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

የካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት በዞን ደረጃ በቦንጊ ሻንቤቶ በሚከበረው የ2018 ዓ/ም የካፍቾ ብሄር ዘመን መለወጫ(ማሽቃሮ) በዓል ቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ከወረዳ በዓል ኮሚቴዎች ጋር ውይይት ተደረጓል።

የወረዳ ም/አስተዳዳሪና የሥራ ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ከተማ ከፍያለው በንግግራቸው የካፍቾ ብሄር ዘመን መለወጫ(ማሽቃሮ) በዓል ከቀበሌ ጀምሮ እየተከበረ መምጣቱን አስታውሶ ደረጃ በደረጃ በዓሉ በደማቅ ሁኔታ ማክበር መቻሉን ገልፀዋል።

አቶ ከተማ አያይዘውም በታሰበለት መልኩ በወረዳ ደረጃ በዓሉን በሰላምና በደማቅ ሁኔታ እንድናከብር የበዓሉ ኮሚቴዎች ትልቁን ድርሻ መወጣታቸውን አንስተው በማመስገን በዞን ደረጃ በቦንጊ ሻንቤቶም የተለመደው ድጋፍና አስተባባሪነታችሁ ይጠብቃል ብለዋል።

የወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘማች ቡሾ በዞን ደረጃ በሚከበረው በዓል ዙሪያ ለኮሚቴዎች ኦረንቴሽን ሰጥተው በድምቀትና ባህላዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ለማክበር ዝግጅት በጥሩ ሁኔታ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

ኃላፊው መስከረም 12/2018 ዓ/ም በዋዜማ ዕለት አደባባይ ላይ ጎልቶ የሚታይ የፌስቲቫልና የካርኒቫል ቅድመ ዝግጅት መደረጉን አክለው በበዓሉ ከህፃናት ጀምሮ በሁሉም ደረጃ ያሉ አካላት በዓሉን ያደምቃሉ ብለዋል።

በሌላ በኩል የብሄሩ ማንነት የሆነው ባህላዊ የቡና አዘገጃጀት በትኩረት እንደሚሰራ የጠቆሙት አቶ ዘማች የበዓሉ ዕለት በሶስት ደረጃ በንጉሡ ፊት ቡና የማፍላትና የግብዓት አዘገጃጀት የማሳየት ተግባር ዋንኛው እንደሆነ አብራርተዋል።

የበዓሉ ተሳታፊዎች በፕሮግራሙ ላይ ስታደሙ በባህላዊ ልብስ አምረው፣ ደምቀውና አሸብርቀው መገኘት እንዳለባቸው በማንሳት በበዓሉ ዙሪያ ግንዛቤ አስጨብጠዋል።

በመጨረሻም አቶ ከተማ በዓሉን በዓለም አቀፍ ደረጃ ዩኔስኮ ለማስመዝገብ በተቀናጀ መልኩ መስራት እንደሚጠበቅ አንስተው የበዓሉ ታዳሚዎች እና ኮሚቴዎች በአንድነት ለማክበር በተባለው ግዜ መገኘት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

እንኳን ለካፍቾ ዘመን መለወጫ (ማሽቃሮ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!
በኤልያስ ጋሎ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክ ገፃችንን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356
telegram https://t.me/+qw3dNLrRkgAyNjQ0

የሀገራችንን ህልውናና ብሔራዊ ጥቅሞች ለመጠበቅ ሠራዊቱ ከምንግዜውም በላይ ዝግጁ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የሀገራችንን ህልውናና ብሔራዊ ጥቅሞች ለመጠበቅና ለማስከበር ሠራዊቱ ከምንግ...
21/09/2025

የሀገራችንን ህልውናና ብሔራዊ ጥቅሞች ለመጠበቅ ሠራዊቱ ከምንግዜውም በላይ ዝግጁ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

የሀገራችንን ህልውናና ብሔራዊ ጥቅሞች ለመጠበቅና ለማስከበር ሠራዊቱ ከምንግዜውም በላይ ዝግጁ ነው አሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፡፡

የሁርሶ አጭር ኮርስ እጩ መኮንን ትምህርት ቤት የ26ኛ ንስር ኮርስ ሰልጣኞችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው ለተመራቂ መኮንኖች ባስተላለፉት መልዕክት፥ የቀደምት አርበኞች ልጆች በመሆናችሁ ሀገርን ጠብቃችሁ ለትውልድ ማስረከብ ይጠበቅባችኋል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ በንግግራቸው፥ ሠራዊታችን የትኛውንም ተልዕኮ በብቃትና በቁርጠኝነት መወጣት የሚያስችለውን የዘመኑን ወታደራዊ ሳይንስና ጥበብ ቀስሟል ነው ያሉት።

ተመራቂዎች በስልጠናው በቀሰማችሁት የንድፍና የተግባር ልምድና እውቀት ከፍ ብላችሁ እንደ ንስር በመብረር ለሀገር ከፍታና ሉዓላዊነት መስራት ይኖርባችኋል ብለዋል።

ሀገራችን የተፈጥሮ ሀብቷን እንዳትጠቀም የሚፈልጉ ጠላቶቿ ባንዳዎችን በመመልመልና የውስጥ ቀዳዳን በመፍጠር ሀገርን ለማተራመስ እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ይህን ታላቅ ህዝብና ሀገር የሚመጥን ዘመናዊ ሰራዊት ገንብተን የሀገርን ብሔራዊ ጥቅሞች በአስተማማኝ መንገድ የመጠበቅ ታሪካዊ ኃላፊነታችንን እየተወጣን እንገኛለን ነው ያሉት።

በዚሁ የዕጩ መኮንኖች የምረቃ ስነስርዓት ላይ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላን ጨምሮ ጀኔራል መኮንኖች እና የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ ከድር ጁሀር ተገኝተዋል።



ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR

የመከላከያ ሠራዊት አሁናዊ ቁመና የኢትዮጵያን ህልውና ለማይሹ አካላት መልዕክት የሚሰጥ ነው - ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴየመከላከያ ሠራዊት አሁናዊ ቁመና እና ዝግጁነት የኢትዮጵያን ህልውና ...
21/09/2025

የመከላከያ ሠራዊት አሁናዊ ቁመና የኢትዮጵያን ህልውና ለማይሹ አካላት መልዕክት የሚሰጥ ነው - ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ

የመከላከያ ሠራዊት አሁናዊ ቁመና እና ዝግጁነት የኢትዮጵያን ህልውና ለማይሹ አካላት ትልቅ መልዕክት የሚሰጥ ነው አሉ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ።

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቅራቢነት ከፍተኛ የጦር መኮንኖችን በሾሙበት ወቅት፤ ሹመቱ ከፍተኛ መኮንኖች ላሳዩት የስራ ጥንካሬ፣ ታማኝነትና ብርታት የተሰጠ ነው ብለዋል።

ውትድርና ለሀገር ሉዓላዊነት እና ለህዝብ ክብር ህይወትን አሳልፎ ለመስጠት ቃል ኪዳን የሚገባበት ታላቅ ሙያ መሆኑንም ገልጸዋል።

የጽኑ ወታደር ቋንቋው ሀገርና ህዝብን ማገልገል መሆኑን ጠቅሰው፣ የመከለከያ ሠራዊቱም በዚህ ረገድ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።

የሠራዊቱ አሁናዊ ዝግጁነት የኢትዮጵያን ህልውና ለማይሹ አካላት ትልቅ መልዕክት የሚሰጥ መሆኑንም አብራርተዋል።

መከላከያ ሠራዊት መልህቁ በሁሉም አግባብ ራስን መቻል እንዲሁም በቴክኖሎጂና ክህሎት ልቆ መገኘት መሆኑን መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ይህም የኢትዮጵያን ህላዊ ለማወክ በጋሻ ጃግሬነት ለመሰለፍ የሚከጅሉ ቡድኖች ባለቡት አካባቢ ትልቅ መድህን ነው ብለዋል።

የመከላከያ ሠራዊትን ዘመኑ ከደረሰበት ቴክኖሎጂ አስማምቶ የማይደፈር እንዲሆን ቀን ከሌት ለሰሩ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ መንገድ ሰላም፣ ልማትና ብልጽግና መሆኑን የተናገሩት ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፤ ይህን መንገድ ለማደናቀፍ የሚሹ አካላት ደግመው ደጋግመው ሊያስቡ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል።

“ሪፎርሙ ባይተገበር የግድቡ የመጠናቀቅ  ዕድል ዝቅተኛ ነበር” - ኢንጂነር ስለሺ በቀለ (ዶ/ር)  | ሪፎርሙ ባይተገበር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የመጠናቀቅ  ዕድል ዝቅተኛ ነበር ሲሉ ኢ...
21/09/2025

“ሪፎርሙ ባይተገበር የግድቡ የመጠናቀቅ ዕድል ዝቅተኛ ነበር”

- ኢንጂነር ስለሺ በቀለ (ዶ/ር)

| ሪፎርሙ ባይተገበር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የመጠናቀቅ ዕድል ዝቅተኛ ነበር ሲሉ ኢንጂነር ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ኢንጂነር ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) በአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ለውጡን ተከትሎ የተተገበረው ሪፎርም የተጓተተውንና ቅርቃር ውስጥ በመግባት መቆም ደረጃ ደርሶ የነበረውን የሕዳሴ ግድብ ለማጠናቀቅና ለውጤት ለማብቃት ዋነኛው መሰረት ሆኗል ብለዋል።

በዚህም ቴክኒካሊ የነበሩት የዲዛይን፣ የአቅርቦት እና የኤክስፖርቶች ችግሮች የተፈቱበት መሆኑን አንስተው፤ በኮንትራት አስተዳደርም አቅም ያለው የኮንትራት አስተዳደር በመለየትና ኢትዮጵያ ውስጥ ሠርተው የሚያውቁ ሦስት ኮንትራክተሮች እንዲገቡ መደረጉን ገልጸዋል፡፡

የቦርድ አወቃቀርና ኃላፊነት ላይ ያሉትም ጉዳዮች እንዲሁ በሪፎርሙ ታይተው የማሻሻል ሥራ ተሠርቶ እንደገና እንዲዋቀሩ ተደርጓል ብለዋል።

በሪፎርሙ የገንዘብና ሀብት ማሰባሰብ እንቅስቃሴው በከፍተኛ ደረጃ እንዲንቀሳቀስ የሕዝብ ተሳትፎ እንዲጎለብት ማድረግ የተቻለበት መሆኑንም አንስተዋል፡፡

ሪፎርሙ ባይተገበር ግድቡ የመጠናቀቅ ዕድሉ እጅግ በጣም ዝቅተኛ እንደነበር አንስተው፤ በአጠቃላይ የሪፎርም ሥራው የነበሩትን ደካማ አሠራሮች በማስተካከል የተሠራና ውጤት ያመጣ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

#ኢ ፕ ድ
Plus ጋዜጣ ፕላስ
#ህዳሴግድብ #ሪፎርም

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

 #ቦንጌ ሻምበቶ ደምቋል:አሸብርቋልም!የካፋ ማህበረሰብ ቱባ ባህል የሆነውን "ማሽቃሮ"በዓል በድምቀት ለማክበር በቦንጌ ሻምበቶ ሰማይ ስር  ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል።‎‎ የማሽቃሮን በዓል በቦንጌ...
21/09/2025

#ቦንጌ ሻምበቶ ደምቋል:አሸብርቋልም!

የካፋ ማህበረሰብ ቱባ ባህል የሆነውን "ማሽቃሮ"በዓል በድምቀት ለማክበር በቦንጌ ሻምበቶ ሰማይ ስር ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል።

‎ የማሽቃሮን በዓል በቦንጌ ሻምበቶ የባህል ቤቶችን ቀለም የመቀባትና አካባቢዉን የማፅዳት ስራ ትኩረት ስቧል።

‎ቦንጌ ሻምበቶ ሁሉም ዝግጁ ሆኖ መስከረም 13/2018 ዓ/ም
በጉጉት የሚጠበቀውን ክብረ በዓል ለማክበር እንግዶችን ለመቀበል ተሞሽሮ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል::

ይሄው ቅድሜ ዝግጅት በፎቶ ከስር ተቀምጦላቹሃል!

ኑ ማሽቃሮን አብረን እናክብር!

መረጃው የካፋ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

የ2018 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ አፈፃፀምና የትምህርት አጀማመር ዙሪያ ከክልል ደጋፊ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ ሻማ፦መስከረም 9/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ...
19/09/2025

የ2018 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ አፈፃፀምና የትምህርት አጀማመር ዙሪያ ከክልል ደጋፊ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ

ሻማ፦መስከረም 9/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በካፋ ዞን ጨታ ወረዳ የ2018 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ አፈፃፀምና የትምህርት አጀማመር ዙሪያ ከክልል ደጋፊ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።

የውይይት መድረኩን የመሩት የጨታ ወረዳ ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰሎሞን ኃይሌ የ2018 ዓ.ም የተማሪዎች ምዝገባ ሂደት ውጤታማ እንድሆንና የመማር ማስተማር ስራ በተባለው ግዜ ሠለዳ እንዲጀመር ከላይ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ተማሪዎችን ቤት ለቤት ልየታ ከማድረግ ጀምሮ እስከ መደበኛ ትምህርት ማስጀመሪያ ድረስ በወረዳው ቀላል የማይባሉ ስራዎች እየተሰራ ይገኛል ብሏል።

በአንድ አንድ ት/ት ቤቶች በተለያዩ ተግዳሮት የታሰበው ውጤት መመዝገብ አልተቻለም ያሉት አቶ ሰሎሞን ለውጤቱ አለመሳካት ምክንያት ናቸው የተባሉ ጉዳዮችን ለመፍታት ለወረዳ አመራሮች እና ለትምህርት ባለሙያዎች በሁሉም ትምህርት ቤቶች ስምሪት ተሰጥቶ የተጠናከረ ክትትል እየተደረገ ይገኛል ብሏል።

ተማሪዎች ወደ ት/ት ቤት መጥቶ እንዲማሩ የትምህርት ቤት አካባቢ ማፅዳትና መማሪያ ክፍሎችን ለመማር ማስተማር ምቹ ማራኪና ሳቢ እንድሆን እንድሁም ለመጠገን ዕቅድ ተይዘው ወደ ስራ እንደተገባ ተናግሯል።

የወረዳ ብልጽግና ፓርት ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለሙ ዘውዴ በበኩላቸው በወረዳው ከትምህርት ንቅናቄ ጀምሮ እስካሁን የተቀናጀ ስራ ስሰራ መቆየቱን ገለፀው በተሰጠው ትኩረት በቂ ውጤት ባለመምጣቱ ሁሉም አመራሮችና የትምህርት ባለሙያዎች የመስክ ግብረ መልስ ተደርጎ ዳግም ስምሪት ተሰጥቶ የተጠናከረ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል ብሏል።

የትምህርት ስራ የሁሉም ስራ በመሆኑ የተለዩ ውስንነቶች በትኩረት እንዲሰራ ከአስተባባሪ አካላት እስከ አመራሩ የመስክ ስምሪት ተሰጥቶ የተጠናከረ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግሯል።

በተሰሩ ስራዎች የታዩ በጎ ውጤቶችን ማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን ለማረም በወረዳ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እርብርብ እየተደረገ ይገኛል ብሏል።

የወረዳ ት/ት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ሙሉጌታ ክፍሌ የእስካሁን የተማሪዎች ምዝገባ ሂደት ፣ የተማሪዎች ትምህርት አጀማመር ፣ የመምህራን ውይይትና ሌሎች የእስካሁን የስራ አፈፃፀም ሪፖርት አቅርቧል።

በዚህም ከ1-12ኛ ክፍል የእስካሁን ምዝገባ ሂደት 7,823 ተማሪ ስሆን ከዕቅዱ አንፃር 62.17 ፐርሰንት ያልዘለለ መሆኑን ገልፀው አፈፃፀሙ ዝቅ እንድል ምክንያት ልሆኑ የሚችሉ ጉዳዮችን በመለየት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብሏል።

አቶ ሙሉጌታ አክለው በዘንድሮው ዓመት 25 የቅድመ አንደኛ ትምርህት ቤት ማስፋፍያ ለመስራት ዕቅድ ተይዞ እስካሁን 23 ት/ት ቤት ማስፋፊያ እንደተሰራ ገልጿል።

የክልል ደጋፊ አካላት የተማሪዎች ምገባና ምዝገባ ሂደት ፣ የትምህርት ቤቶች ጥገና ፣የመማሪያ መጽሐፍ ህትመትና የትምህርት ቤቶችን ለመማር ማስተማር ምቹ የማድረግ ስራዎች ግዜ ሳይሰጥ መስራት እንዳለባቸው በአጽንኦት ተናግሯል።

በወጋዬሁ ወንድሙ

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

የካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት አዲሱ በተሻሻለው የፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1395/2017 ዙሪያ ለተቋሙ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠሻማ፦መስከረም 9/2018 ዓ.ም...
19/09/2025

የካፋ ዞን ጨታ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት አዲሱ በተሻሻለው የፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1395/2017 ዙሪያ ለተቋሙ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ

ሻማ፦መስከረም 9/2018 ዓ.ም (የጨታ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

የስልጠና መድረኩን የመሩት ጨታ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ሀብታሙ በላይ አዲሱ አዋጅ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማጠናከር፣ የፍትሃዊነትን መርህ እና ግልፅነትን ለማስፈን ያለመ እንደሆነ ገልጿል።

አዲሱ አዋጅ ይበልጥ ፍትሃዊ ፣ ግልጽና ቀልጣፋ የግብር ስርዓት ለመገንባት የሚያስችል ጠንካራ ማዕቀፍ እንደሆነም አክለዋል።

የስልጠና ሰነድ ያቀረቡት የጨታ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት የትምህርትና ሥልጠና ሥራ ሂደት ተወካይ አስተባባሪ አቶ ታሪኩ ኃይሌ ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል የሚያርፍበትን የግብር ጫና መቀነስ ፣ የግብር መሰረት ማስፋት ፣ የግብር ስርዓቱ የሚታዩ የፍትሃዊነት ችግሮችን መቅረፍ ፣ግልጽኝነት በጎደለባቸው አንቀጾች የሚፈጠሩ ውጣውረዶችን ለመቀነስ አዲሱ የገቢ ግብር ማሻሻያ ዓላማ አድርጎ እንደቀረበ አብራርቷል።

የንግድ ማጭበርበርን ለመከላከል ስባል በተሻሻለው የፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1395/2017 ላይ በአንድ ቀን አንድ ግለሰብ ከ50 ሺ ብር በላይ ሽያጭ ማድረግና ያለደረሰኝ የንግድ ልውውጥ ማድረግ እንደማይችል በአዋጁ ተጠቅሷል።

በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ ዙሪያ እየተሰጠ ያለው ስልጠና የአዋጁን ዓላማዎች በመረዳትና ተግባር ላይ በማዋል የግብር ስርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ውጤታማ ለማድረግ ያለመ ነው።

የዲጂታል ግብር ከፋይ ማህበረሰብ ክፍሎችን ለማበራታት ስባል 5 በመቶ ብቻ ግብር የሚቆረጥ እንደሆነም በሰነዱ አቶ ታርኩ አስረድተዋል።

የስልጠና ሰነዱን የጨታ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት የትምህርትና ሥልጠና ሥራ ሂደት ተወካይ አስተባባሪ አቶ ታሪኩ ኃይሌ አቅርበው ሰፊ ውይይት ተደረጓል።

በወጋዬሁ ወንድሙ

ወቅታዊ ፣ ተዓማኒ ፣ ትኩስና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ፌስቡክና ቴሌግራም ገፆቻችን ይከታተላሉ ፣ይወዳጁ👇👇👇👇👇????

በፌስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100091368031356

በቴሌግራም፦https://t.me/C12g6/1057?single

በቲክቶክ፦https://vm.tiktok.com/ZMHtnCGMKnVKa-Th2vR/

Address

Kafa Cheta
Bonga

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kafa zone cheta woreda govt comm media ካፋ ዞን ጨታ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share