ከይር ፈላጊዎች ጀምዓ ካፋ ቦንጋ/Keyr Felagi

  • Home
  • Ethiopia
  • Bonga
  • ከይር ፈላጊዎች ጀምዓ ካፋ ቦንጋ/Keyr Felagi

ከይር ፈላጊዎች ጀምዓ ካፋ ቦንጋ/Keyr Felagi peace up on you
please donate to those who have a shortage of food for iftar

27/03/2025

ጥርጣሬን ከመከተል መቆጠብ
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

ጥርጣሬ የአንድን ነገር ትክክለኛ መሆን/አለመሆን ለመቀበል መቸገር ነው። ጥርጣሬ የማሰብ ምልክት ቢሆንም የማሰብ ሂደቱ የሚቋጨው ግን በማስረጃ እንጂ በራሱ በጥርጣሬው መሆን የለበትም። ጥርጣሬ ለእውነተኛነቱ ወይም ለሐሰተኛነቱ ማስረጃ ሊፈለግለት የሚገባ ነገር ሆኖ ሳለ ጥርጣሬን ራሱን እንደማስረጃ መውሰድ ስህተት ነው። ማጣራትና ማረጋገጥ እየተቻለ ጥርጣሬን መከተልም አግባብ አይደለም።

አንዳንዶች ጥርጣሬያቸውን ብቻ እንደ ማስረጀ ሲከተሉ ይታያል። ይህ ግን በቁርኣን የተነቀፈ ተግባር ነው። አላህ (ሱወ) እንዲህ ይላል...

"ለእነርሱ በዚህ ምንም እውቀት የላቸውም። የሚከተሉት ጥርጣሬን ብቻ ነው። ጥርጣሬ ከእውነት ምንም አያብቃቃም።" (ሱራ አል ነጅም፡ 28)

11/ ስሜትንና ዝንባሌን ከመከተል መቆጠብ
🍄🍄🍄🍄🍄🍄🍄🍄🍄🍄🍄🍄🍄

አንዳንዶች ለእስልምና ጥላቻ ከማሳየት በቀር ስለሃይማኖቱ ምንም አለማንበባቸው አሳዛኝ ተጨባጫችን ነው። ስለእስልምና ብዙ አሉባልታዎችን ሰምተዋል። አንዱንም ግን በራሳቸው ለማረጋገጥ አልሞከሩም። ማስረጃ ቢጠየቁም ማምጣት አይችሉም። ለያዟቸው አቋሞች ተጨባጭ ማስረጃ የላቸውም። ውስጣቸው ግን በአሉታዊ ስሜትና ኢስላምን በማጣጣል ዝንባሌ ተሞልቷል።

እንዲህ ዓይነት ሰዎች በመልዕክተኛው (ሰዐወ) ዘመን ነበሩ። አላህ ለያዙት አቋም ማስረጃ እንዲያቀርቡ ጥሪ እንዲያቀርቡላቸው ነቢዩ ሙሐመድን (ሰዐወ) አዘዛቸው። ሰዎቹ ግን ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ። ቁርኣኑ ይህንኑ ያወሳል...

"እሺ ባይሉህም የሚከሉት ዝንባሌዎቻቸውን ብቻ መሆኑን ዕወቅ። ከአላህም የሆነ መመሪያ ሳይኖረው ዝንባሌውን ከተከተለ ሰው ይበልጥ የጠመመ አንድም የለም።" (ሱራ አል ቀሶስ፡ 50)

ማስረጃን እንጂ የሰዎችን ከንቱ ስሜትና ፍላጎት መከተል አደገኛ መዘዝ አለው። ቁርኣን እንዲህ ሲል ገልጾታል...

"(ይህ) እውቀት ከመጣልህ በኋላ የእነርሱን ከንቱ ስሜቶች ብትከተል ከአላህ (ቅጣት የሚታደግህ) ረዳትም ጠባቂም አታገኝም።" (ሱራ አል ረዕድ፡ 37)

ሙሉውን ለማንበብ 👇👇👇

https://www.facebook.com/share/p/19JuC8H2Ji/

ጠዋትከፈጅር በፊት ከለይሉ ጥቂቱን መስገድ፣ ስሁር መመገብ እና ኢስቲግፋር ማብዛት!ከሰላት በኋላ ቀጥታ ተክቢራ መጀመር ከዛም ፀሀይ እስክትወጣ ቁርአን፣ተህሊል፣ተህሚድ በአጠቃላይ በዚክር ማሳለ...
26/06/2023

ጠዋት

ከፈጅር በፊት ከለይሉ ጥቂቱን መስገድ፣ ስሁር መመገብ እና ኢስቲግፋር ማብዛት!
ከሰላት በኋላ ቀጥታ ተክቢራ መጀመር ከዛም ፀሀይ እስክትወጣ ቁርአን፣ተህሊል፣ተህሚድ በአጠቃላይ በዚክር ማሳለፍ(አዝካረ ሰባህ ሳይረሳ)

ፀሀይ ስትወጣ የፀሃይ መውጣትን ሰላት እዛው ከመስገጃችን ሳንነሳ በመከወን ከረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ሀጅ የማድረግን ምንዳ እንዲጎናጸፍ
ለቀን ኢባዳ ያግዘናል ብለን ካሰብን መጠነኛ እኝቅልፍ እንተኛ። ስንነሳ በትንሹ 4 ረክኣ ሰላተ ዱሃ እንስገድ!

ከሰአት
ከዝሁር ሰላት በኋላ ቁርዐናችንን እንቀራለን።

የአረፋ ቀን ፆም!
ከአቢ ቀታዳ ተይዞ: ነቢዩ (ﷺ) ስለ አረፋ ቀን ፆም ተጠይቀው እንዲህ ብለዋል፦

﴿يُكَفِّرُ السَّنَةَ الماضِيَةَ والْباقِيَةَ﴾

“ያለፈውንና የመጪውን አመት ወንጀል ያስምራል።”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1162

ማስታወሻ፦ የአረፋ ቀን ፆም የሚፆመው ነገ ማክሰኞ ሰኔ 20 ነው።

16/06/2023

"ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከተበታተነ ይበላሻል፣ ይጠፋልም፣ ህብረት ሆነው ከተባበሩም ይበጃሉ፣ በበላይነት ገዢ ይሆናሉ። ጀመዓ፣ ህብረት ረህመት(ከአላህ እዝነት)ነው መለያየት ደግሞ ቅጣት ነው።"

📚 [ኢብኑ ተይሚያህ /አል ፈታዋ) (3/423)

06/05/2023

ከትናንት ጁምዓ የኩጥባ መልዕክት ውስጥ ዋንኛው
ሙስሊም በሚኖርበት አካባቢ እና በጎረበቱ ላይ በሚኖረዉ ኃላፊነት ላይ ነበር
ለራሱ የወደደዉን ለሌላዉ ወንድሙ ልወድ እንደሚገባ
ሰዎች በሚቀመጡበት ወይም በሚያርፉበት ጥላ ላይ፣
በመናፈሻዎች፣ ሰዎች በሚተላለፉበት መንገድ ላይ፣
በማንኛዉም አካል ለዉበት ተብሎ በየተተከለ ዛፍ ስር እና ማረፊያ በሆኑ ሳር ላይ ቁሻሻ መጣል ሽንት መሽናትም ሆነ ማበላሸት የተከለከለ መሆኑን የህንንም ነቢዩ(ሰዓወ) ይህን ድርጊት የፈጸመ የተረገመ ነዉ ማለታቸዉ ዋነኛው ነበር። ሙስሊም የተገነባበበት ስነ ምግባር ምን ያህል ላቅ ባለ መሰረት ላይ መሆኑን የሚያስተምር ነዉ፡፡ በተጨማሪ
ሰዉን ሆነ ሌላን እንስሳትን ለጉዳት ይጥላል ብሎ በማሰብ ከመንገድ ላይ አዋኪ የሆኑ ነገሮችን የሙዝ ልጣጭ እንኳ ቢሆን ያነሳ እንደ ትልቅ ሰደቃ ይቆጠርለታል፡፡
ቦንጋ ዳሩሰላም መስጂድ

18/04/2023

ዘካቱል ፊጥር /የፍስግ ምጽዋት/

 ዘካተል ፊጥር የረመዳን ወር ፆም መጠናቀቅ ተከትሎ በወቅቱ ሙስሊም ሁኖ በህይወት ባለ ሰው በነፍስ ወከፍ ግዴታ የሚሆን የዘካ / ሰደቃ/ አይነት ነው ፡፡
 እያንዳንዱ አባወራ ወይም እማወራ ወይም አስተዳዳሪ የራሱን ጨምሮ በእርሱ ስር እየቀለባቸው ባሉ ቤተሰቦቹ ሁሉ መስጠት ይኖርበታል ፡፡
★ ማስረጃ
 አብዱላህ ኢብን አባስ አላህ ይውደዳቸውና እንዲህ ይላሉ፤
‹‹የአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በ እርሳቸው ላይ ይሁን) ዘካተል ፊጥር ለፆመኛ በጾሙ ወቅት ከፈፀማቸው ጥቅም አልባ ውድቅ ንግግሮችና ተግባሮች ጥፋት ማፅጃ ይሆንለታል ። ለሚስኪኖች (ድሆች) መብል ሲሆን በግዴታ መልኩ ደንግገውታል ። ስለዚህም ከኢድ ሰላት በፊት (ዘካውን በመስጠት ግዴታውን የተወጣ) ተቀባይነት ያለው ዘካን ሰጥቷል፤ ከኢድ ሶላት ቦሃላ ዘካውን የሰጠ እንደማንኛውም ሰደቃ አንዱ እንደሆነ ይታሰብለታል ።))
(አቡዳውድ እና ኢብኑ ማጃህ ዘግበውታል)።
 ኢብኑ ሙንዚር አል ኢጅማዕ’ በተሰኘው ኪታባቸው ‹‹ዒልምን የተማርንባቸው ዑለሞች ሁሉ ዘካተል ፊጥር ግዴታ መሆኑን ተስማምተውበታል›› በማለት የ ኡለሞችን አጠቃላይ ስምምነት (ኢጅማዕ) የተገኘበት መሆኑን ጠቁመዎል ።
★ የተደነገገበት ጥበብ
ከላይ ግዴታነቱን ለማመላከት በተጠቀሰው ሀዲስ እንደተጠቀሰው ፣ ድሆች በባዕሉ (ዒድ) እለት ሰዎችን ከመለመን እንዲድኑና የእለቱ ደስታ ተካፋይ እንዲሆኑ ማድረግ እንዲሁም በፆም ወቅት ተከስተው ላለፉ አንዳንድ ጉድለቶች (ግድፈቶች) ማሟያ እንዲሆን ነው ።

የመረጃ ምንጭ ቢላሉል ሃበሺ የሙስሊሞች ግሩፕ

እባካችሁ በሰደቃ ላይ ይበልጥ የምንጠነክርበት ጊዜ ላይ ነን።
01/04/2023

እባካችሁ በሰደቃ ላይ ይበልጥ የምንጠነክርበት ጊዜ ላይ ነን።

01/04/2023

አላህ ሆይ!

✤ ጥልቁን ጉድጓድ ለነቢዩላህ ዩሱፍ (ዐ.ሰ)
✤ ድድሩን ብረት ለነቢዩላህ ዳውድ (ዐ.ሰ)
✤ የማይጨበጠውን ንፋስ ለነቢዩላህ ሱለይማን (ዐ.ሰ)
✤ ግዙፉን ዓሣ ነባሪን ለኘቢዩላህ ዩኑስ (ዐ.ሰ)
✤ ሞገደኛውን ባህር ለነቢዩላህ ሙሳ (ዐ.ሰ)
✤ ወላፈናማውን እሳት ለነቢዩላህ ኢብራሂም (ዐ.ሰ)
ያመቻቸህና ያገራህ ጌታ ሆይ! ባሮችህ የእዝነትህ
ፈላጊዎች ናቸውና እዘንላቸው። የከበዳቸውን አንድም
ሳይቀር አግራላቸው። የጨነቃቸውንም ሁሉ ፍታላቸው።

"... ጌታዬ ሆይ! እኔ ከመልካም ነገር ወደኔ ለምታደርገው ፈላጊ ነኝ"
[አል ቀሶስ : 2

28/03/2023

«ሰደቃ የሚሰጥ ሰው ሰደቃው ደሃ ሰው እጅ ላይ ከማረፏ በፊት አላህ እጅ ላይ የምታርፍ መሆኗን ቢያውቅ የሰጪው ሰው ደስታ ከተቀባዩ ደስታ ይበልጥ ነበር።»

ኢብኑል ቀይም

25/03/2023

የዘካ #ፋይዳዎች
~~~~
#ዘካ ለሰጪው የሚያስገኛቸው #ፋይዳዎች፡-
① ዘካ ከአምስቱ የኢስላም ምሰሶዎች አንዱ እንደመሆኑ በትክክል የሚሰጥ ሰው ይህን የኢስላሙን ምሰሶ ነው የሚያፀናው።
ባይሰጥ ደግሞ ይህን ምሰሶውን ነው የሚያናጋው።
② ዘካ በኢኽላስ እስከተወጣ ድረስ ኢማንን ይጨምራል፤ የአላህን ውዴታ ያጎናፅፋል።
③ ዘካ ወንጀልን ያብሳል። ነብዩ ﷺ "ውሃ እሳትን እንደሚያጠፋው ሶደቃ ሃጢአትን ያጠፋል" ብለዋል።
④ ዘካ ፈተናን መከራን ይመክታል።
⑤ ዘካ ማውጣት የአዛኝነት፣ የርህሩህነት፣ የተቆርቋሪነት ባህሪን ያላብሳል። ዛሬ ራስ ወዳድነት በነገሰበት ዘመን ለሙስሊም ወገን ከምላስ ባለፈ ከልብ መቆርቆርና ማዘን የእውነት ትልቅ መታደል ነው።
⑥ ዘካ የቀልብ መለዘብና በሞራል መገራትን ያጎናፅፋል። ከክፋት፣ ከስስት፣ ከድንበር ዘለል የዱንያ ፍቅር እንዲወጡ ሰዎችን ያግዛል።
⑦ ዘካ የህሊና እርካታን ፣ መንፈሳዊ ሰላምን፣ ስነ ልቦናዊ መረጋጋትን ያጎናፅፋል።
⑧ ዘካ ገንዘብን ያፋፋል፣ በረካ ይጨምርበታል።
⑨ ዘካ ለችግር ጊዜ ደራሽ ወገን እንዲኖረንም ይጠቅማል። መቼም ሁሌ ድሎት፣ ሁሌ ምቾት የለም። ዱንያ ተገለባባጭ ናት።

ዘካደካሞች እና ሚስኪኖች የረመዳን ጾምን ተጠናክረው እንዲጾሙ በማሰብ ሰለፎች የገንዘብ ዘካቸውን ሻህባን ወር ውስጥ ያወጡ ነበር።'' ኢብኑ ረጀብ ተናግረዋልይሄ ሀዲስ የሚነግረን ነገር ምንድነ...
22/03/2023

ዘካ
ደካሞች እና ሚስኪኖች የረመዳን ጾምን ተጠናክረው እንዲጾሙ በማሰብ ሰለፎች የገንዘብ ዘካቸውን ሻህባን ወር ውስጥ ያወጡ ነበር።'' ኢብኑ ረጀብ ተናግረዋል
ይሄ ሀዲስ የሚነግረን ነገር ምንድነው አቅም የሌላቸውን ሚስኪኖች እና ደካሞች የረመዳን ጾምን ተቸግረው እንዳይጾሙ እና የረመዳን ጾምን ጾመን ውለን ምንድነው ምናፈጥረው ብለው እያሳሰባቸው እየተጨነቁ በሀዘን እንዳይቀበሉ ለማድረግ ገንዘብ ያለው ሰው ላይ ሁሉ ግዴታ የሆነውን #ዘካ የግድ ረመዳን ውስጥ ብቻ ሳይሆን እንደሁኔታዎቹ ከዛም በፊት ማውጣት እንደሚቻል ነው የሚነግረን። በረመዳን ውስጥ የሚሰጠው ዘካ ተወዳጅነቱ እንዳለ ሆኖ ሳለ ማለት ነው።
ስለዚህ ገንዘብ ያላችሁ ባለሀብቶች የተቸገሩትን ወገኖቻችንን ለመርዳት እና ለማቋቋም ከፈለጋችሁ በዚህ ሰአት ሻህባን ወር ላይ ዘካቹን በማውጣት ችግራቸዉን አቅልሉ።

Address

Bonga

Telephone

+251923243455

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ከይር ፈላጊዎች ጀምዓ ካፋ ቦንጋ/Keyr Felagi posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ከይር ፈላጊዎች ጀምዓ ካፋ ቦንጋ/Keyr Felagi:

Share