የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication

የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication This is The official Butajira City Gov't COMM.fb page-ይህ ትክክለኛው የቡታጅራ ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን (fb)ፔጅ ነው፦

የስራ ዕድል ፈጠራ  የዜጎች የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ድህነትን ለመቀነስ ፍትሀዊ ዕድገት ለማረጋገጥና  የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን ለማስጠበቅ  ሚናው የጎላ መሆኑ ተገለፀ ። ጥቅምት 28/2018ዓ.ም ...
07/11/2025

የስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎች የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ድህነትን ለመቀነስ ፍትሀዊ ዕድገት ለማረጋገጥና የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን ለማስጠበቅ ሚናው የጎላ መሆኑ ተገለፀ ።

ጥቅምት 28/2018ዓ.ም ቡታጅራ

" ጠንካራ ቅንጅት ለዘላቂ የስራ እድል ፈጠራ እምርታ " በሚል መሪ ቃል የምስራቅ ጉራጌ ዞን ስራ ዕድል ፈጠረና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ የንቅናቄና የስራ እድል ፈጠራ ምክር ቤት የ2018 ዓ.ም የ4ወር አፈፃፀምና የተሻሻለ የግብ ስምምነት መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር እያካሄደ ነው።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ስራ ዕድል ፈጠረና ኢንተርፕራይዝ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ታጁ ነስሩ የስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎች የኑሮ ደረጃ በማሻሻል ድህነትን ከመቀነስና ፍትሀዊ ዕድገት ማረጋገጥ የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን ለማስጠበቅ ሚናው የጎላ መሆኑ ተናግረዋል ።

እንደ ሀገር ዘላቂና አስተማማኝ የስራ ዕድል ለመፍጠር የሪፎርም ስራዎች ተቀርጾ እየተሰራ መሆኑም ገልፈዋል።

መምሪያው በአራት ወር ውስጥ ከ15 ሺ በላይ ዜጎች ስራ መፍጠርሩንና ከ32 ሺ በላይ ስራ ፈላጊዎች ገበያ ተኮር ስልጠና መሰጠቱ ተናግረዋል ።

አያይዘውም ኢንተርፕራይዞች ተጠቃሚ ለማድረግ 583ሄ/ር መሬትና 37ሼዶች ማቅረብ መቻሉ አብራርተዋል ።

ቋሚ የስራ እድል ፈጠራ ለማሻሻል ፣ተዘዋዋሪ ፈንድ ና የውዝፍ እዳ አመላለስ ላይ እንዲሁም የስራ ፈላጊዎችና ኢንተርፕራይዞች በኢትዮጵያ ስራ ገበያ መረጃ ማስመዝገብ በተመለከተ ተሳታፊዎች በሰፊው እንዲመክሩበት ጠቁመዋል።

በመድረኩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተወካይና የትምህርት መምሪያ ሀላፊ አቶ ሰልማን ሳኒ፣የዞኑ ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ እንዳልካቸው ጌታቸው፤ የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊ ተወካይና የሚዲያ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ካሳሁን ቱጂ፤ የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዝዳንት አቶ ሁሴን ሽፋ፤ የመምሪያ ኃላፊዎች፤ የወረዳና ከተማ አስተዳደር አስተዳዳሪዎች፤ ከንቲባዎች የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤትሀላፊዎች፣ የስራ እድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ፅ/ቤት ሀላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው ።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ነው

በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ፆታዊ ጥቃቶች ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ሁሉም በንቃት መሳተፍ አለበት(ጥቅምት 27/2018)  በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ...
06/11/2025

በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ፆታዊ ጥቃቶች ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ሁሉም በንቃት መሳተፍ አለበት

(ጥቅምት 27/2018) በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት ከUNFPA ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመሆን በቡታጅራ ከተማ በ3ቱም ቀበሌ ሴቶች ህፃናትና ለተመረጡ ሞዴል እማወራዎች የግንዛቤ ስልጠና ሰጥተዋል።

የቡታጅራ ከተማ ሴቶች ህፃናት ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ተስፋነሽ አለሙ እንደገለፁት በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ፆታዊ ጥቃቶች ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ሁሉም በንቃት መሳተፍ ይኖርበታል።

በየግዜው የሚታዩ ጥቃትና ትንኮሳዎችን በመከላከልና በማስወገድ ሴቶችን ብቃት ችሎታቸው በማህበረሰቡ ጎልቶ እኩል ተሳተፊነት መሆን ላይ መስራት እንደሚገባም ገልፀዋል።

ስልጠናውን የሰጡት ሴቶች ህፃናት ጉዳዮች ጽ/ቤት ባለሙያ ወ/ሮ ፈትያ መሀመድ የሀገራችን ሴቶች ባለፉት ጊዜያት ይደርስባቸው የነበረው ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች ግርዛት ጠለፋ መቅረቱን አብራርተዋል።

ሴቶች አሁን ላይ በሀገር እድገት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ይበልጥ በሚያጎላ መልኩ ሚና መጫወት እንዳለባቸው ተናግረዋል

በመጨረሻም ሰልጣኞችም መልኩ ለዚህ ተጋላጭነት ላይ የቀሰሙት መረጃና መልዕክት ለህብረተሰቡ አስተምህሮቱ መጠናከር እንዳለበት ጠቁመዋል።

ህገ-ወጥ የንግድ ስራዎችን በመከላከል ረገድ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ንግድ ገበያ ልማት መምሪያ ገለፀ። መምሪያው ከአቋቋመው ግብረ-ሀይል በቡታጅራ ከተማ ንግድ ገበያ ልማ...
05/11/2025

ህገ-ወጥ የንግድ ስራዎችን በመከላከል ረገድ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ንግድ ገበያ ልማት መምሪያ ገለፀ።

መምሪያው ከአቋቋመው ግብረ-ሀይል በቡታጅራ ከተማ ንግድ ገበያ ልማት ጽ/ቤት ጋር በቅንጅት በመሆን በከተማው በንግዱ ዘርፍ የተሰማሩ የንግድ ድርጅቶች
ላይ የንግድ ህግ የማስከበር ስራ ሰርቷል።

ጥቅም 26/2018 ዓ.ም ቡታጅራ

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ንግድ ገበያ ልማት መምሪያ ኢንስፔክሽንና ሸማች ድጋፍ ዳይሮክተሬት ዳይሬክተር አቶ ሰይፈዲን ሙስበሀ በመስክ ምልከታ ወቅት እንደገለፁት በከተማው በእሬሻ ቀበሌ ላይ የሚገኙ የንግድ ድርጅቶች ህግ የማስከበር ስራና ህገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር ስራ ተሰርቷል ብለዋል።

በዚህም 54 የንግድ ድርጅቶች ላይ በተደረገ ፍተሻ 11 የንግድ ድርጅት ላይ ግኝት መገኙቱንና በዚህም 6 የንግድ ድርጅቶች ያለንግድ ምዝገባና ፈቃድ ሲሰሩ ተገኝተው መታሽጋቸውን ገልፀዋል።

ሌላው ይህ ኢንስፔክሽን ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ከደረጃ በታች ይዘው የሚገኙ ድርጅቶች ላይ የማሸግና ተመጣጣኝ ቅጣት እንደሚቀጣ ገልፀዋል።

በአጠቃላይ 10 (አስር ድርጅቶች) የማሸግና 1 (አንድ) የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን በመግለፅ በድምሩ 80.000 ብር የገንዘብ ቅጣት እርምጃ መወሰዱን ገልፀዋል።

በመጨረሻም በመጠቀሚ ጊዜ ያለፈበት ምርት በሰው ህይወት ላይ ገዳት የሚያደርሱ በመያዝ 11 ኮካ ኮላ, 8 እስፕራይትና 6 ፋንታ የማስወገድ ስራ መሰራቱ ተናግረዋል።

የዘገበው የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙንኬሽን ነው።

በከተማዋ ያለውን ዕድል በመጠቀም ለማልማት እየተሰራ ያለው ስራ አበረታች ነው(ጥቅምት 26/2018) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ ያለውን የተፈጥሮ ዕድል ፀጋ በመጠቀም ለማልማት እየተሰ...
05/11/2025

በከተማዋ ያለውን ዕድል በመጠቀም ለማልማት እየተሰራ ያለው ስራ አበረታች ነው

(ጥቅምት 26/2018) በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ ያለውን የተፈጥሮ ዕድል ፀጋ በመጠቀም ለማልማት እየተሰራ ያለው ስራ አበረታች መሆኑን የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የድጋፍና ክትትል ቡድን አባላት ገለፁ።

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት በቡታጅራ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግልት ዕቅድ አፈፃፀም መነሻ በማድረግ ድጋፍና ክትትል አድርጓል።

ቡታጅራ አርባን አግሪካልቸር የኢኮቱሪዝም ስራ ማስቀጠል ውጤታማ መሆን የሚያስችል መሆኑን እና ይህንኑ በማጠናከር ይበልጥ ለማልማት መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።

የድጋፍና ክትትል ቡድን አባላቱ በከተማው በመሰረተ ልማት እየተሰራ ያለው ስራ እጅግ አበረታች እንደሆነ አንስተው የዘርፉ ባለሙያዎች በእውቀት ልክ ይበልጥ መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

በከተማዋ የተሻለ ፀጋ መኖሩን የገለፁት አባላቱ በማስተባበር የተሻለ ስራ መስራት እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።

የድጋፍና የክትትል ቡድኑ በከተማ አስተዳደሩ ማዘጋጃ ቤታዊ ስራዎች አፈፃፀም በተቋሙ ተገኝተው ከተመለከቱ በኋላ እየተሰሩ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችንም ተመልክተዋል።

የኮሪደር ልማት የወንዝ ዳር ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ፣ከፈትኸል መስጂድ በደስታ- ጨርቃ ጨርቅ እስከ ዝዋይ መውጫ የአስፓልት መንገድ ግንባታ፣የክልሉ ቢሮ የህንፃ ግንባታ፣የባህል ቤት የልማት ፕሮጀክቶችን ምልከታ አድርገዋል።

በምልከታቸው እንዲሁም በተቋሙ የተመለከቱት የሩብ ዓመቱ የስራ አፈፃፀም በጥሩ የስራ እንቅስቃሴ ላይ ስለመሆናቸው አመላካች እንደሆነ ጠቁመዋል።

በቡታጅራ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ከሴቶች ክንፍ አባላት ጋር ለመወያየት የተዘጋጀው መድረክ ተጠናቀቀ(‎ጥቅምት 26/2018 )"ሚዲያ ለላቀ ልማት ለከተማችን ከፍታና ለዘላቂ ሰላም የሴ...
05/11/2025

በቡታጅራ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ከሴቶች ክንፍ አባላት ጋር ለመወያየት የተዘጋጀው መድረክ ተጠናቀቀ

(‎ጥቅምት 26/2018 )"ሚዲያ ለላቀ ልማት ለከተማችን ከፍታና ለዘላቂ ሰላም የሴቶች ሚና" በሚል መሪ ቃል የሴቶች ክንፍ አመራርና አባላት ሰፋ ያለ ውይይት አድርገዋል።

የመያያ ሰነድ በከተማው ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ የፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊ በሆኑት በወ/ሪት ሰብለ ተክሌ ቀርቦ የሴቶች ክንፍ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ከሆኑት ከወ/ሮ ዙለይካ ሱልጣን ጋር በጋራ ውይይቱን መርተውታል።

ለሀገር ብልጽግናና ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የሴቶች ተሳትፍ ከፍተኛ አበርክቶ ያለው ነው። ያለ ሴቶች ሙሉ ተሳትፎ ሰላምንና ብልጽግናን በዘላቂነት ማረጋገጥ አይቻልም።

በመሆኑም ሴቶች በሚዲያ አጠቃቀም ግንባር ቀደም ተሳታፊዎች መሆን እንደሚጠበቅባቸው በመድረኩ ተነስቷዋል።

ሚዲያን ለበጎ ተግባር ብቻ የመጠቀም ኃላፊነትን በተገቢው መወጣት፤ ከፋፋይና ጽንፈኛ የሆኑ የትኛውንም ዓይነት አስተሳሰቦችን በመርህ ላይ ቆሞ መታገል ከሴቶች እንደሚጠበቅም በመድረኩ በስፋት ተነስቷል።

ሴቶች ማህበራዊ ሚዲያን ሲጠቀሙ የማህበረሰቡን አንድነት ለማጠናከር ፣ ልማትን ለማረጋገጥ ፣ ለሰላም ግንባታ ፣ ለገዢ ትርክት ግንባታ ፣ ለዲሞክራሲ ባህል ግንባታና ለተጀመረው ሁለንተናዊ የኢትዮጵያ ብልጽግና ማረጋገጥ የሚያጠናክሩ ሀሳቦችን ላይ ማተኮር ይጠበቅበታል ተብሏል።

ሴቶች በተሰማሩባቸው የትምህርትና የስራ ዘርፎች ሁሉ ውጤታማ በመሆን የሀገራቸውን ሰላምና ብልጽግና ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው ተነስቷል።

የኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን ማጎልበት አስፈላጊ መሆኑ ፤ ለዚህም ፓርቲው የሚያወርዳቸውን ሁሉም ኢኒሼቲቮች መተግበርና ተጠቃሚ ለመሆን ጠንካሮች መሆን እንዳለባቸው ተነስቷል።

የፖለቲካዊ አቅማቸውን እንዲጎለብት መስራት ትኩረት ሊደረግበት አስፈላጊ መሆኑን ተነስቶ መድረኩ ተጠናቋል።

(መረጃው የቡታጅራ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ነው)

በቡታጅራ ከተማ አስተዳደር 31 ሺህ 250 የመማሪያ መጽሐፍ ለትምህርት ቤቶች  ተሰራጨ(ጥቅምት 26/2018) በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር 31 ሺህ 250  የመማሪያ መጽሐፍ...
05/11/2025

በቡታጅራ ከተማ አስተዳደር 31 ሺህ 250 የመማሪያ መጽሐፍ ለትምህርት ቤቶች ተሰራጨ

(ጥቅምት 26/2018) በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር 31 ሺህ 250 የመማሪያ መጽሐፍት ለትምህርት ቤቶች አስራጨ።

ለአንደኛና መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎች መማሪያ የሚሆን 31 ሺህ 250 መጽሐፍት 3 ሚሊየን 726 ሺህ 680 ብር ወጪ የታተመ መጽሐፍት ነው በዛሬው ዕለት የተሰራጨው።

የቡታጅራ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ የተማሪ መጽሐፍት አቅርቦት በትምህርቱ መጀመሪያ ለማሳካት ከፍተኛ ጥረት በማድረግ የተሰራ እንደሆነ ገልፀዋል።

የትምህርት ጥራት ውጤት ለማሻሻል ከቅድመ መደበኛ ሁሉንም አይነት አማራጮች በመጠቀም እየተሰራ መሆኑን የገለፁት ከንቲባው አጠቃላይ የተማሪ መፅሐፍ ጥምርታ ለማስተካከል ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።

የተማሪ ምገባ ፤የትምህርት ቤቶች ደረጃ የማሻሻል አዳዲስ ብሎኮችን የመገንባት፤ግብአት የማሟላት ትላልቅ ስራዎችን ከተማ አስተዳደሩ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

በ2017 የትምህርት ዘመን በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠቃለያ ፈተና #21.13% በማሳለፍ ከ10% በላይ ውጤት ማሻሻል እንደተቻለ አስታውሰዋል።

የአዳሪ ትምህርት ቤት ትልቅ የሆነውን ተቋም የመማር ማስተማር ስራ ለማስጀመር ሁሉም አይነት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውንም ከንቲባ አቶ አብዱ ጠቁመዋል።

ከተማ አስተዳደሩ የትምህርት ውጤት ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን እና ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የገለፁት ከንቲባ አብዱ አጋዥ አካላት ድጋፋቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል።

የከተማው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዶ አሊ 31 ሺህ 250 የመማሪያ መጽሐፍት ለአንደኛና መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ እስከ 8 ክፍል ተማሪዎች ተሰራጭቷል።

ከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን በዚህም 18 ሺህ የሚሆነውን የመጽሐፍት ህትመት ወጪ የሸፈነ እንደሆነ ጠቁመዋል።

የታተመው መጽሐፍት በከተማው ለሚገኙ ለመንግስትና ለግል ትምህርት ቤቶች ሁሉ ተደራሽ የሚሆን እንደሆነ የገለፁት ኃላፊው ትምህርት ቤቶች የተማሪ ወላጆችን በማስተባበር የመጽሐፍት ህትመቱ ላይ ተሳትፈዋል ብለዋል።

በዛሬው ዕለት ለትምህርት ቤቶች የተሰራጨው መጽሐፍ በከተማ አስተዳደሩ ፣በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች አስተባባሪነት የተማሪ ወላጆች በትብብር የታተመ መሆኑን አቶ አብዶ አሊ ገልፀዋል።

ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን፦
tiktok https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8v44ergN5SJ&_r=1
ቴሌግራም፦ https://t.me/ButajiraCommunication/58
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/buta1921/
ዩቲዩብ፦ https://youtube.com/
X ፦ https://mobile.twitter.com/ButajiraB
ኢንታግራም፦ https://www.instagram.com/butajirab

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ንግድ ገበያ ልማት መምሪያ የተቋቋመ ግብረ-ሃይል በቡታጅራ ከተማ የሚገኙ በንግዱ ዘርፍ የተሰማሩ ሸማቾች ማህበራትን ድጋፍና ክትትል አደረገጥቅምት 25/2018 መምሪያው በ...
04/11/2025

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ንግድ ገበያ ልማት መምሪያ የተቋቋመ ግብረ-ሃይል በቡታጅራ ከተማ የሚገኙ በንግዱ ዘርፍ የተሰማሩ ሸማቾች ማህበራትን ድጋፍና ክትትል አደረገ

ጥቅምት 25/2018 መምሪያው በመንገድ ዳር ላይ በህገ-ወጥ ንግድ የተሰማሩና ህገ-ወጥ ነዳጅ አዘዋዋሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ገልፆል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ንግድ ገበያ ልማት መምሪያ ከቡታጅራ ከተማ ንግድ ገበያ ልማት ጽ/ቤት ባለሙያዎች የተቋቋመ ግብረ-ሃይል በቡታጅራ ከተማ የሚገኙ ሸማቾች ማህበራት እና ማድያዎችን አሰራሮች ተመልክትዋል።

በከተማው የሚገኙ የተለያዩ የፍጆታ አቅራቢ ሸማቾች ማህበራት ላይ ያጋጠሙ ችግሮች በመለየት በቀጣይ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በቅንጅት በመሆን የሚያስፈልገውን ድጎማ ፤የዋጋና የገበያ ማረጋጋት ስራ እንደሚ ሰራ ገልፀዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የሱፐርቪዥን ቡድን በቡታጅራ ከተማ አስተዳደር እያደረገ የቆየውን የሱፐርቪዥን ስራ አጠናቀቀ‎ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም/ቡታጅራየክልሉ የሱ...
04/11/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የሱፐርቪዥን ቡድን በቡታጅራ ከተማ አስተዳደር እያደረገ የቆየውን የሱፐርቪዥን ስራ አጠናቀቀ

‎ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም/ቡታጅራ

የክልሉ የሱፐርቪዥን ቡድን አጠቃላይ በቡታጅራ ከተማ በ2018 በጀት ዓመት በ1ኛ ሩብ ዓመት ታቅደው የተተገበሩ ተግባራት መሠረት ያደረገ ድጋፍ አድርጎ በመጨረሻም ግብረ መልስ በመስጠት አጠናቋል።

የሱፐርቪዥን ቡድኑ በአቶ ቀድሩ አብደላ የክልሉ ትምህርትና ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር የተመራ ሲሆን ፣ አቶ አብራሃም አለሙ የክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና ወ/ሮ ማናዬ ዳዊት በክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ምክትል ኃላፊ በጋራ መርተውታል።

በሱፐርቪዥኑ የተለያዩ መድረኮች ተፈጥረዋል ፣ በከተማ ደረጃ አጠቃላይ የፓርቲው አባላትና አደረጃጀቶች ያሉበት ደረጃ ለማወቅ የፐብሊክ ሰርቫንትና በቀበሌዎች ደረጃ ያሉ የፓርቲው አባላት የፓርቲውን መመሪያዎች ፣ ደንቦችና አሰራሮች ምን ያህል አውቀው እየተገበሩ መሆኑን ለመረዳት የፊት ለፊት ጥልቅ ውይይቶች ተደርገዋል።

አባላቱ በመድረኮች ተገኝተው ከመግለጽ በተጨማሪ አጠቃላይ የፓርቲው አባላትና አደረጃጀቶች የመረጃ ፓኬጆችም በጥልቀት ታይተዋል።

በሱፐርቪዥኑ በከተማ ደረጃ በፓርቲው መሪነት ታቅደው የተከናወኑ ዋና ዋና የልማት እንቅስቃሴዎች በአካል በመዟዟር ተጎብኝተዋል።

የፓርቲው ኢኒሼቲቮች ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማቶች ፣ የ1 ከተማ 1 ፕሮጀክት(ፋርማሲ) ፣ የባህል ቤት ግንባታ ፣ የአስፓልት ግንባታ ፣ የኮሪደር ልማት ፣ የከተማ አስተዳደር ቢሮ G + 10 ህንጻ ግንባታ ፣ የወንዝ ዳርቻ ልማትና ሌሎችም የልማት እንቅስቃሴዎች ተጎብኝተዋል።

በ2018 ዓ.ም የከተማ አስተዳደሩ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በፓርቲው ታቅደው የተከናወኑ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት በከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ም/ኃላፊ በሆኑት በአቶ ባህሩ ዘርጋው በዝርዝር ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በማጠቃለያ መድረኩ የከተማው ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ ፣ የከተማው ዋና የመንግስት ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ማርቆስ ፣ የከተማው ምክትል ከንቲባ አቶ ደረጀ ጥላሁን ፣ የከተማው ረዳት የመንግስት ተጠሪና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መኮንን አሰፋ ፣ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ /ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ሻፊ ሽፋ እና አጠቃላይ የከተማው የፓርቲ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።

በመጨረሻም የሱፐርቪዥን ቡድኑ የማጠቃለያ ግብረ_መልስ ሰጥተው ያጠናቀቁ ሲሆን የከተማው አስተባባሪ ድጋፉን ለላቀ አፈጻጸም እንደሚጠቀሙበት አረጋግጠው መድረኩ በስኬት ተጠናቋል።

(መረጃው የቡታጅራ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ ቤት ነው)

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ  በ2017 በጀት ዓመት  የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ መዋቅሮች፤ አስተዋፅኦ ላበረከቱት ተቋማትና ግለሰቦች እውቅናና ሽልማት አበረከተ።...
04/11/2025

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ መዋቅሮች፤ አስተዋፅኦ ላበረከቱት ተቋማትና ግለሰቦች እውቅናና ሽልማት አበረከተ።

ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም (ቡታጅራ)

መምሪያው በመንገድ ግንባታና ጥገና ከፍተኛ አፈፃፀም በማስመዝገብ ፤ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ገቢ አሰባሰብ ስራ ላይ በማዋል በደረሰኝ ስርጭት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ መዋቅሮች የዋንጫ ሜዳሊያና የእውቅና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን በዚህም መሰረት፦

👉1ኛ ደረጃ የመስቃን ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት

👉2ኛ ደረጃ የሶዶ ወረዳት ራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት

👉3ኛ ደረጃ የደቡብ ሶዶ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት

# የመናኸሪያ መሰረተ ልማት የተሟላ በማድረረግና ኢ-ቲኬት በማስጀመር አገልግሎቱ ዘመናዊ በማድረግ ፣ የከተማ ታክሲ ትራንስፖርት በማስጀመር በአጠቃላይ የትራንስፖርት ዘርፋን ለማዘመን በተሰራው ስራ የቡታጅራ ከተማ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ፅ/ቤት የዕለቱ ልዩ ተሸላሚ መሆን ችሏል።

ከወረዳና ከተማ አስተዳደሮች የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው የመንገድ ደህንነት ባለሙያዎች ፤ ግንባር ቀደም የትራፊክ ፖሊሶች፤ መልካም ስነምግባር ያላቸው ሞዴል ሹፌሮች የሜዳሊያና የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።

የተሰጣቸ ኃላፊነት በተገቢው እየተወጡ ላሉ የተሽከርካሪዎች ባለንብረቶች ማህበራት፤ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋማት እና ባለድርሻ ተቋማት የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።

በመጨረሻም መምሪያው ከሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ጋር የ2018 ዓ.ም የግብ ስምምነት በመፈራረም መድረኩ ተጠናቋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

መንገድ የኢኮኖሚ ልማት እድገት የጀርባ አጥን መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ አስታወቀ።ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም (ቡታጅራ)መምሪያ የ2017ዓ.ም አፈፃፀም ሪ...
04/11/2025

መንገድ የኢኮኖሚ ልማት እድገት የጀርባ አጥን መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ አስታወቀ።

ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም (ቡታጅራ)

መምሪያ የ2017ዓ.ም አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018ዓ.ም የእቅድ ዝግጅት "ደህንነቱን የተጠበቀ የትራንስፖርት አገልግሎት እውን እንዲሆን የድርሻችንን እንወጣለን" በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ አካሄደ።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊና የዞኑ አስተዳደር ተወካይ የሆኑት አቶ ሰልማን ሳኒ እንደተናገሩት ከአሽከርከሪያዎች ብቃት አንፃር እየታዩ ያሉ ችግሮች በመቅረፍ አደጋዎችን መቀነስ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

አቶ ሰልማን አክለውም እንዳሉት ከመንገድ ልማት አንፃርም በህብረተሰብ ተሳትፎ ሁሉም አካባቢ ላይ መንገዶች ለማሰራት ተከታትሎ ከማስፈፀም አንፃር ሰፊ ስራዎች መሰራቱን አስረድተዋል።

በዩራፕ የተሰሩ መንገዶች ለተሽከርካሪዎችና ለእግረኞች ምቹ ሆነው እንዲያገለግሉ በየጊዜው እየተጠገኑ መሄድ እንዳለባቸው ተናግረዋል።

ተቋሙ ላይ ያሉ ሁለቱም ዘርፎች ማህበረሰቡ በሰፊው የሚገለገገልበት በመሆኑ ቀሪ ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ባለድርሻ አካላት የትራፊክና አደጋላይና የመንገል ልማት ላይ ግንዛቤ በመፍጠር ማህበረሰቡ እንዲያግዝ የጋራ መድረክ ማካሄድ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ አቶ አለማየሁ ጎሳዬ እንደተናገሩት የአሽከርካሪዎች አደጋ ለመቀነስ የማሰልጠኛ ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል።

ኃላፊው እንዳሉት ትራንስፖርት ላይ ያሉ ችግሮች ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ ተቋሙ ትኩረት በመስጠት አደጋዎች መቀነስ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በባለፈው በጀት ዓመት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት የተከናወኑ ተግባራቶች አመርቂ ውጤት የተመዘገበበት መሆኑን ተናግረዋል።

ማህበረሰቡ ላይ አስፈላጊው ግንዛቤ መፍጠር ይገባል ያሉት አቶ አለማየሁ ፅ/ቤቶች በቀጣይ ጊዜያት ትኩረት ሰጥተው መገምገም እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

መንገድ ለማህበረሰቡ ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ የተጀመሩ ውጤታማ ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም አክለዋል።

የመምሪያው ልማት ዕቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ዳሬክቶሬት ዳሬከክተር የሆኑት አቶ በለጠ ዲባባ በተቋሙ በ2017በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራትና በ2018ዓ.ም የ1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም በመድረኩ ተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

የትርፍና ታሪፍ ላይ ያሉ ችግሮች ለተቋሙ ብቻ የምንተወው ሳይሆን ሁሉም በርብርብ መስራት ከተቻለ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

የሚደርሱ አደጋዎች ለመቀነስ አሽከርካሪዎች እውቅና ባላቸው ማሰልጠኛ ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ ስልጠና እንዲወስዱ ትኩረት አድርጎ መስራት ያስፉልጋል ብለዋል።

የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ተግባራዊ እንዲሆኑ ተቋሙ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል ማድረጉንም አክለዋል።

በመጨረሻም ከመድረክ በአስተያየትና በጥያቄ በተነሱ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸው የውይይት መድረኩ ተጠናቋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ከተማችንን ውብ ማራኪ በማድረግ የብልፅግና ተምሳሌት እናደርጋለን(ጥቅምት 25/2018) በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃና ደን ልማ...
04/11/2025

የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ከተማችንን ውብ ማራኪ በማድረግ የብልፅግና ተምሳሌት እናደርጋለን

(ጥቅምት 25/2018) በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃና ደን ልማት ዩኒት በቡታጅራ ከተማ በኮሊደር ልማት የተተከሉ ችግኞች ውሀ የማጠጣትና የመንከባከብ ስራ አከናውኗል።

የዩኒቱ አስተባባሪ አቶ መሀመድ ጀማል በፕሮግራሙ ተገኝተው ችግኞች እንክብካቤ በማድረግ ለማፅደቅ ይሰራል።

የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ ከተማችንን ውብ ማራኪ በማድረግ የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን እየተሰራ ነው ያሉት ኃላፊው በከተማችን በኢኒሼቲቭ በርካታ ችግኞች መተከላቸውና አብዛኞቹ ችግኞች ፀድቀዋል ብለዋል።

ሁሉም የንግድ ድርጅቶችና መኖሪያ ቤቶች በአካባቢያቸው የተተከሉ የውበትና የደን ዛፎች የመንከባከብና በስድ እንሰሳት እንዳይበላሹ የመጠበቅ ኃላፊነቻየውን ሊወጡ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ችግኞችን መከባከብና ማጽደቅ ለሀገሪችን የአረንጓዴ አሻራ ጉዞ መሰረት መጣል ነው በመሆኑም ሁሉም ዜጋ በክረምት የተተከሉ ችግኞችን ጊዜ በመስጠት ሊከባከባቸው እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አቶ መሀመድ አክለውም አረንጓዴ አሻራ የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ አጀንዳ በመሆኑ በላቀ ተነሳሽነት፣ ቁርጠኝነትና አርዓያነት ማሳካት አለብን ብለዋል።

የመንከባከቡ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ መሀመድ አመላክተዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የአካባቢ ጥበቃና ደን ልማት ዩኒት ሰራተኞች በመገኘት ለተተከሉ ችግኞች የመንከባከብና ውሀ የማጠጣት ተግባር አከናውነዋል።

በቡታጅራ ከተማ በገቢ አሰባሰብ የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ተቋሞችና ባለሙያዎች እውቅናና ማበረታቻ ተሰጣቸውበምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት በገቢ አሰባሰ...
03/11/2025

በቡታጅራ ከተማ በገቢ አሰባሰብ የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ተቋሞችና ባለሙያዎች እውቅናና ማበረታቻ ተሰጣቸው

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የቡታጅራ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት በገቢ አሰባሰብ ስራ ላይ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተቋሞችና ባለሙያዎች እውቅናና ማበረታቻ ሰጥቷል።

የከተማው ገቢ ጽ/ቤት "ተቋምን በልህቀት ገቢን በስኬት" በሚል መሪ ቃል የ2017 የገቢ ጉባኤ እና የ2018 የ1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ ክንውን ላይ ውይይት ተካሄዷል።

በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ተቋማት ከከተማው ከንቲባ አቶ አብዱ አህመድ እጅ ሽልማታቸውን ተቀብለዋል።

በዚህም መሰረት ፦*ዘቢዳር ቀበሌ 1ኛ ሞተር ሳይክል ፣ኮምፒውተርና ፕሪንተር እና የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

*እሪንዛፍ ቀበሌ 2ኛ ኮምፒውተር ፕሪንተር እና የዋንጫ
*እሬሻ 3ኛ የኮምፒውተር ፕሪንተር እና የዋንጫ ተሸላሚ ህነዋል

የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ባለሙያዎች እውቅናና ሽልማት እና ለገቢ አሰባሰቡ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ተቋሞች እውቅና ተሰጥቷል።

የከተማው ገቢ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወልዩ ከበደ ከቀበሌ ገቢ ጽ/ቤት ኃላፊዎች በ2018 ዕቅድ ላይ የውል ስምምነት ተፈራርመዋል።

(ጥቅምት 24/2018 ቡታጅራ ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን)

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን Butajira City Gov't Communication:

Share