Ethio Love • Follow

Ethio Love • Follow I don' Know where i am going. አላህ የቀደረውን ሰው አይቀይረውም

23/02/2025
ኤርዶጋን ምስራቃዊ እየሩሳሌም ዋና ከተማዋ የሆነች የፍልስጤም ሉዓላዊ መንግስት እንዲመሰረት  ጥሪ አቀረቡየቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ከኢንዶኔዢያ አቻቸዉ ፕራቦዎ ሱቢያንቶ ጋር በ...
13/02/2025

ኤርዶጋን ምስራቃዊ እየሩሳሌም ዋና ከተማዋ የሆነች የፍልስጤም ሉዓላዊ መንግስት እንዲመሰረት ጥሪ አቀረቡ

የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ከኢንዶኔዢያ አቻቸዉ ፕራቦዎ ሱቢያንቶ ጋር በፍልስጤም ጉዳይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫው "ቱርኪ በጋዛ መልሶ ግንባታ ላይ ከኢንዶኔዥያ ጋር ተባብራ መስራትን ለመቀጠል" ያለንን ፍላጎት መግለጽ እንፈልጋለን ብለዋል።

ምስራቃዊ እየሩሳሌም ዋና ከተማዋ የሆነች የፍልስጤም ሉዓላዊ መንግስት ለመመስረትም ጥሪ አቅርበዋል።

ኤርዶጋን ጋዛ እና ፍልስጤማውያን ሰላም እስኪያገኙ ድረስ በቀጠናው ያሉ ሌሎች ሀገራት መረጋጋት እንደማይችሉ አስረግጠዋል።

“በእስራኤል ለ15 ወራት የዘለቀው ጥቃት ያደረሰው አጠቃላይ ጉዳት ወደ 100 ቢሊዮን ዶላር ይጠጋል።
በህጋዊ መርሆች መሰረት ይህ ጉዳት ከአድራጊው መሰብሰብ አለበት” ሲሉ እስራኤልን በመጥቀስ ወንጅለዋል።

በሌላ በኩል የአረብ ሊግ ዋና ጸሃፊ አህመድ አቡል ጌይት ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ሰርጥ እና ከዌስት ባንክ ማፈናቀል ለአካባቢው "ተቀባይነት የሌለው" ሲሉ ውድቅ አድርገዋል።

በዱባይ በተካሄደው የአለም መንግስታት ጉባኤ ላይ "የዛሬ ትኩረት በጋዛ ላይ ነው እናም ነገ ፍልስጤምን ታሪካዊ ነዋሪዎቿን ባዶ ለማድረግ በማሰብ ወደ ዌስት ባንክ ትሸጋገራለች" ሲሉ ተደምጠዋል።
"ይህን ሃሳብ ለ100 አመታት ሲዋጋ ለቆየው የአረቡ አለም ተቀባይነት የለውም።"

አቡል ጌይት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ለማስወጣት በያዙት እቅድ ላይ አስተያየት በመስጠት ንግግሩ በአረቡ አለም በስፋት የተወገዘ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህወሓትን ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ አገደህወሓት ላለፉት ወራት ለሁለት ተከፍሎ እሳጣ ገባ ውስጥ መግቱ ይታወቃልየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት...
13/02/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህወሓትን ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ አገደ

ህወሓት ላለፉት ወራት ለሁለት ተከፍሎ እሳጣ ገባ ውስጥ መግቱ ይታወቃል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)ን ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማገዱን አስታወቀ

ምርጫ ቦርድ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ህወሓት ለቀጣይ ሶስት ወራት “በምንም አይነት” ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ማገዱን አስታውቋል

ምርጫ ቦርዱ ህወሓትን "በልዩ ሁኔታ" በፓርቲነት መመዝገቡን አስታወቀ
ህወሓት በምርጫ ቦርድ በልዩ ፓርቲነት መመዝገቡን “አልቀበልም” አለ
ቦርዱ ፓርቲው በልዩ ሁኔታ ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራቶች ውስጥ፤ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ በሰተጠው ቀነ ገደብ ውስጥ ስብሰባ ጉባዔ ማድረግ አለመቻሉን ለመታገዱ ምክንያት መሆኑን አሰታውቋል

በዚህም መሰረት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ለቀጣይ ሶስት ወራት ከማንኛውም ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ መታገዱን ነው ቦርዱ ያስወቀው

ህወሓት በቀጣይ 3 ወራ ጊዜ ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ የሚያስችል “የእርምት እርምጃ” ካልወሰደ፤ የፓርቲው ምዘገባ በቀጥታ እንደሚሰረዝ ቦርዱ አሳስቧል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ በነሐሴ 2016ዓ.ል ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት “በልዩ ሁኔታ” መስጠቱ ይታወሳል

ህወሓት በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በልዩ ሁኔታ በፓርቲነት መመዝገቡን ተከትሎ የቦርዱን ውሳኔ እንደማይቀበለው ማስታወቁ ይታወሳል

ህወሓት ያቀረበው ጥያቄ ከፕሪቶሪያው ስምምነት፣ ከህግ እና ህወሓት እያደረገ ካለው ተጨባጭ እንቅስቃሴ አንፃር የተሰረዘውን ህጋዊ ሰውነት ወደነበረበት እንዲመለስ የሚል ብቻ ነው ማለቱም አይዘነጋም

12/02/2025

ከቅበት ከተማ አስተዳደር የተላለፈ መልዕክት
******************************************************
ለመላው የከተማ አስተዳደራችን ነዋሪዎች፤ ከተማችን "ቅበት" ከተቆረቆረች እነሆ 100 አመታት የተቆጠሩ ሲሆን በዚህ ሂደትም የህዝቡ አብሮ የመኖር፣ የመቻቻል፣ የአንድነት፣ የመረዳዳት፣ የመተሳሰብና የሰላም ተምሳሌትና ደሴት ሆና መቆየቷ ይታወቃል ።

ይሁን እንጂ በ2015 ዓ.ም የማህበረሰቡ አብሮት የነበረውን ሁሉአቀፍ መልካም እሴት በሚንድ መልኩ በጥቂት ግለሰቦች መነሻ የህዝባችን አንድነትና አብሮነትን በማናጋት በተፈጠረው ረብሻ የሰው ሂይወት እንዲያልፍ፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት እንዲደርስ፣ ህብረተሰቡ ከቀየው እንዲፈናቀል ማድረግ እንዲሁም ህብረተሰቡ ለዘመናት የገነባውን የአንድነት፣ አብሮ የመኖር፣ የመቻቻል፣ የመተሳሰብና የመረዳዳት ዕሴት በመሸርሸር በህዝቡ መካከል የአለመተማመን ሁኔታ መፈጠሩ የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው።

በወቅቱም የተፈጠረውን ችግር በመፍታት ሰላምን ለማስፈን አመራሩ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ጊዜና ጉልበቱን በመጠቀም ከዚህ ቀደም የነበረውን የማህበረሰቡን ሰላምና የአንድነት ዕሴት በመመለሱ ረገድና በከተማችን የተሻለ ሰላም እንዲሰፍን ከማድረግ ጎን ለጎን የማህበረሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ፍላጎት በመለየት ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

ይሁንና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጥቂት ግለሰቦች በማህበራዊ ሚዲያ ሀሰተኛ (fake) አካውንት በመክፈት የግል ፍላጎታቸውን ከከተማ አስተዳደሩ ሰላምና እየተከናወነ ካለው የልማት ተግባራት በማስቀደም እንዲሁም አመራሩን ከማንቋሸሽ ተሻግሮም ከዚህ ቀደም በርካታ መስዋዕትነት ያስከፈለው ረብሻና ብጥብጥ እንዲፈጠር በማለም እየተንቀሳቀሱ ይገኛል።

በመሆኑም የተከበረው ሰላምና ልማት ወዳዱ የከተማ አስተዳደራችን ማህበረሰብ፤ ትላንት ከተፈጠረው ረብሻ በመማር አሁን ካለው አመራር ጋር በመቀናጀት ጥገኛው እየረጨ ያለውን መርዝ በማምከን ፍሬ አልባ እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል ።

የቅበት ከተማ አስተዳደር ህዝብ ሰላም አማራጭ የሌለውና ለድርድር የማይቀርብ በመሆኑ የከተማ አስተዳዳሩ ማህበረሰብና ወጣቱ እንደወትሮው የአፍራሽ ሀይሉን ተልዕኮ በመኮነንና በመመከት የተጀመረው ልማት እንዲፋጠን በማድረጉ ረገድ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል።

በሂደቱም የሚፈጠሩ ችግሮችን ምክንያታዊ በሆነና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በመጠየቅና በምክንያት በመሞገት የከተማችንን ገጽታ በመገንባቱ ረገድ የበኩላችሁን እንድትወጡ ጥሪ በማቅረብ ሰላማችንን በማጽናት ብልጽግናችንን እናረጋግጥ።

06/02/2025
 #የሚስት  #ሀቅማህሙድ ጀማል  #ተከታይ ይሁኑ አላህ በደነገገው መሰረት ሚስቶች በባሎቻቸው ላይ ሀቅ አላቸው። እነዚህ መብቶች፦♦ የማስተዳደር ሀቅ እና♦ የመንከባከብ ሀቅበመባል በ2 መደብ ...
22/07/2024

#የሚስት #ሀቅ
ማህሙድ ጀማል #ተከታይ ይሁኑ
አላህ በደነገገው መሰረት ሚስቶች በባሎቻቸው ላይ ሀቅ አላቸው። እነዚህ መብቶች፦

♦ የማስተዳደር ሀቅ እና
♦ የመንከባከብ ሀቅ

በመባል በ2 መደብ ይከፈላሉ።

♦ «የማስተዳደር ሀቅ»

ባል የቤቱን ወጭ ሙሉበሙሉ መሸፈን ግዴታ አለበት። አላህ በቁርኣኑ እንደገለፀው፦

«ወንዶች በሴቶች ላይ ቋሚዎች አሳዳሪዎች ናቸው። አላህ ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ በማብለጡና ወንዶች ከገንዘቦቻቸው ለሴቶች በመስጠታቸው ነው።» ብሏል።
(ኒሳዕ፡ 34)

👉 ወንዱ ይህንን ግዴታውን በቂ ባልሆነ ምክንያት የማይሸፍን ከሆነ ሚስት አብራው ልትኖርም ወይም ትታው ልትሄድ ሙሉ መብት አላት። እንዲሁም የቤቱን ወጭ መሸፈን እስከሚችል ድረስ ግንኙነት ማድረግ አትገደድም።
(ፊቂህ አልሻፊዒ 3/155)

👉 የቤቱን ወጭ መሸፈን አለበት ሲባልም ለቤት አስቤዛ፣ ለልብስ፣ ለመዋቢያ ጌጣጌጥ እና መሰል ነገሮችን በቂ የሆነ ገንዘብ መስጠት ግዴታው ነው።

👉 ሚስት የራሷን የገቢ ምንጭ ካላት ደግሞ በፈቃደኝነት ለቤቷ ወጭ ማድረግ አልያም ለቤተሰቦቿ ወይም ለራሷ ለምትፈልገው የማዋል ሙሉ መብት አላት። ባል በገንዘቧ ላይ ማስገደድ አይችልም።

♦ «የመንከባከብ ሀቅ»

ሚስትን መንከባከብ በፈቃደኝነት የሚሰራ ሳይሆን ግዴታ ነው። ሚስት ለባሏ መታዘዝ ግዴታ እንዳለባት ባልም ሚስቱን በመልካም መያዝና መጠበቅ ግዴታው ነው

«ለእነርሱም ለሴቶች የዚያ በእነርሱ ላይ ያለባቸው ግዳጅ ብጤ በመልካም አኗኗር በባሎቻቸው ላይ መብት አላቸው።»
(በቀራህ፥ 228)

ባልየው ሚስቱን በሆነ ምክንያት ቢጠላ እንኳን መበደል አይፈቀድለትም። በመልካም እስኪለያዩ ወይም አላህ የወሰነውን እስኪያመጣ እንክብካቤን አለማጓደልና መታገስ ግዴታ ተጥሏል

«በመልካምም ተኗኗሩዋቸው። ብትጠሉዋቸውም ታገሱ። አንዳችን ነገር ብትጠሉ አላህም በእርሱ ብዙ ደግ ነገርን ሊያደርግ ይቻላልና።»
(ኒሳዕ፥ 19)

ነቢዩ (ዐሰወ) ሚስቶቻቸውን ምግብ ከማብሰልና ጫማቸውን ከመስፋት ጀምሮ በሁሉም ስራ ያግዙ የነበረ ሲሆን «ሴቶችን ተንከባከቡ። እሷ በወንዶች ላይ የተጣለች አደራ ናት።» ብለዋል

#የባል ሀቅ ይቀጥላል.........😍አንብቡ....👫

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Love • Follow posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share