meskan media network

meskan media network meskan media network is an online media, focuses on social matters. This is official page of meskan media network

የዝናና ታዋቂነት ጥማት አዲሱ ጣኦት💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢በአሕመዲን ጀበል🔥🔥🔥🔥🔥🔥ማህበራዊ ሚዲያ በሰዎች ልቦና የሚመለክ ጣኦት እየተከለ ነው።ሲጀምር የላይክ፥ የተከታይና የእይታ ብዛት፥ ቫይራል ...
08/12/2025

የዝናና ታዋቂነት ጥማት አዲሱ ጣኦት
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢
በአሕመዲን ጀበል
🔥🔥🔥🔥🔥🔥

ማህበራዊ ሚዲያ በሰዎች ልቦና የሚመለክ ጣኦት እየተከለ ነው።ሲጀምር የላይክ፥ የተከታይና የእይታ ብዛት፥ ቫይራል መሆን እያለ ነው።ቀጥሎም የእውቅና ቅቡለነትን መፈለግ ይከተላል። እነዚህ ሁሉ ለመልካም ዓላማና ስነምግባርን በተከተለ መንገድ ስንጓዝ የሥራችን ዉጤት ተከትለው የመጡ ከሆኑ ጠቃሚ ናቸው።

በማህበራዊ ሚዲያ ዝናና ታዋቂነት ወዲያው የሚገኝና አልጎሪዝም መር ናቸው። ከባዶ ጽሑፍ ከፎቶግራፍ ጋር የተለጠ ጽሑፍ ብዙ ሰው ይደርሳል። ከጽሑፍ ፎቶ ግራፍ ይልቅ ቪዲዮ በቀላሉ እይታ ያገኛል። ከተለመዱ ቪዲዮዎች ወጣ ያሉ ቪዲዮዎች የበለጠ ይሰራጫሉ።

የማህበራዊ ሚዲያ ይዘቶች እንዲሰራጩ የተቀመረው አልጎሪዝም የሚያበረታታውና የሚሸልመው የሰዎችን ትኩረት መሳብ ለሚችሉ ነገሮች ነው። ትኩረት በተሳበ ቁጥር ታዳሚ ይገኛል። ታዳሚ በተገኘ ቁጥር ማስታወቂያ የሚያሳያቸው ሰዎች በብዛት ይገኛሉ። እነርሱ በብዛት ተገኙ ማለት ማስታወቂያ ለማሰራት የሚመጡ ከፋዮች ይመጣሉ። ብዙ ከፋዮች ከመጡ ብዙ ገቢ ይገኛል። ከዚህ ስሌት በመነሳት አልጎሪዝሞቹ ብዙ ሰው እንዲሳብላቸው ወጣ ያሉና አነጋጋሪ ለሆኑ ድርጊቶችና ባህሪያት ቦታ ይሰጣሉ።

ከዚህ የተነሳ ይበልጥ ጋጠወጥና አነጋጋሪ የሆኑት በቀላሉ ታዋቂነትን መጎናጸፍ ይችላሉ። በዚህ ምክንያት ይህን የተረዱ ሰዎች እይታ ለማግኘት ሲሉ የራሳቸውን ሃይማኖት ህግጋት ጭምር ይጥሳሉ፤ የሌሎችንም ሃይማኖትና ማንነትን እስከ መሳደብ ደረሱ። ተከታዮችን ለመሳብ ሲሉም አጓጉል አለበባስ አልያም ወጣ ያለባህሪያትን በማሳየት ላይ ተጠመዱ። ይዘት ለመፍጠር ብለው ኃጢአት የሆኑና ትውልድ በካይ አስተሳሰቦችን ወደ ማግበስበስ ገቡ።

ከፍያለ እይታን ለማግኘት ሲሉ ከፊሎቹ ራሳቸው አወዛጋቢ አደረጉ። ከፊሎቹ ደግሞ አወዛጋቢ ነገሮችን እያነፈነፉና እየፈጠሩ በማስፈፋት ላይ ተጠመዱ። በዚህም የራሳቸውን ስብዕና አርክሰው የማህበረሰቡን የማንነትና የባህልን ድንበር ጣሱ። ለራሳቸው ገቢ ብቻ በማሰብ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ በሚረጩት አደገኛ መርዞች ቀጣዩ ትውልድ ከሞራልና ከባህል ያፈነገጠ አዲስ ማንነትና ባህል እንዲላበስ እየተጉ ነው።

ሌሎች ስምና ዝና የሚፈልጉ ተቋማት ምርታቸውን ለመሸጥ እንዲችሉ የነርሱ አዳማቂ ሆኑ። ሌሎች ደግሞ ከነርሱ ጎን ቆመው ታይታን ለማግኘት ሲሉ በነርሱ መድረክ እና ዝግጅቶች ላይ ታዳሚ ሆኑ።ሌሎች ደግሞ መወገዝን ፈርተው ዝምታን መረጡ። ሌሎች ደግሞ የጥፋቱን ገጽታ ቸል ብለው የጠቃሚነት ገጽታው ብቻ ጎልቶ እንዲታይ ተከላካይ ሆነው ቀረቡ።

በዚህም አካሄድ ስንትና ስንት ኃጢአቶችን ህዝቡን አለማመዱ። በፈጠራ ስም የአፍረተ ቢስነትን ልማድ ወጣቱ ላይ አስረጹ። በድራማ ስምም ጋጠወጥነት መዝናኛ ሆኖ ሕዝቡ እንዲጋት ተደረገ።ከዚህ የጥፋት ምንጭ የተጋተ ሰውም እየጣመው «እነርሱን አትንኩብኝ»፤ «አርኣያዎቼ ናቸው» ሲልም እስከ መደመጥ ተደረሰ። ሙስሊሞች ጭምር መገኘቱ በሚያሳፍር ቻናሎችና ይዘቶች ስር «ማሸአላህ» እያሉ ሲያዳንቁ መታየት ተለመደ።

ጥቂቶቹ ከሙስሊምነት ብዙውን ጥለው ሌሎች ደግሞ ሂጃብ መሳይ ሻሽ በራሳቸው ላይ ጣል አድርገው «በፍቅር ታሪክ ስም» የዝሙት ታሪኮችንና የሰዎችን ገበና እያፈላለጉ ለትውልዱ መጋት ተያያዙ። አላህ ሁላችንንም ወደ ቅኑ ጎዳና ይምራንና።

ወጣቱም ተምሮ ለራሱና ለሀገር ጠቃሚ ዜጋ ከመሆን ይልቅ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን ሆነ ምኞቱ። እንደነርሱ በመሆን በአቋራጭ ዝነኛና ሀብታም መሆን ይቻላል ብሎ ወደማመን አዘነበለ። ይህም በየቤቱ የትምህርት መማሪያ መጽሐፍ ሳይሆን ዘመናዊ ተንቃሳቃሽ ስልክ እንዲገዛለት የሚወተውት ወጣት እንዲበራከት አደረገ።

ጊዜውንም እነዚያ ጋጠወጦችን እያደነቀ ከነርሱ ስር ተጥዶ ሲቀመጥ ከትምህርት እየራቀ ሄደ። በነርሱ መንገድ በመሄድ ይበልጥ እይታ ለማግኘት፥ ታዋቂና ዝነኛ ለመሆን ከነርሱ የላቀና አዲስ ነገር ይዞ መገኘት አስፈላጊ ሆነ።

በዚሁ መንገድ አንዳንዶች ባለበትዳር የሆኑ ጥንዶችን በካሜራ ፊት እንዲሳሳሙ እያደረጉ ሲያቀርቡም ታዩ። ሌሎችም ከትዳር ዉጭ ያለን ግንኙነት «ፍቅረኞች» በሚል ታፔላ ሲሳሙ እያሳዩ የዝሙት መንፈስን በወጣቱ ልቦና መትከል ተያያዙት። ሌሎች ደግሞ የቅርብ ዘመዳሞችን፣ ከቤት ሠራተኞች ጋርና ከቅርብ ጓደኞች የትዳር አጋር ጋር የሚፈጸምን ዝሙትና ዉስልትናን በድራማና መዝናኛ ስም ማሰራጨቱን ተያያዙ። በዚህ አካሄድ በዝምታ ከታየ በሀገራችን ግልጽ የወሲብ ፊልም የሚሰራጭበት ጊዜ ሩቅ አይመስልም።

ሰዎችን ስላለማመዱ ብዙ ሰው በድንዛዜ ተውጦ ምላሹ ዝምታ ሆነ። ተቃውሞ የሚያሰሙ ጥቂቶች ቢኖሩም ሰሚ አጡ። ለዚህ መደበቂና ሽፋኑ መብት፥ነጻነት፥ መዝናኛና ፈጠራ ሆነ። ይባስ ብለው ትውልድን ገዳይ በሆነው መስክ «የፈጠራ ሽልማት» በሚል መድረኮቹን የቀጥታ የሚዲያ ሽፋን የሚሰጡ እና ስፖንሰር የሚያደርጉ ተቋማትም ተቀላቀሏቸው።

ለዝና ዓላማ ልብስን መልበስ
💥💥💥💥💥💥💥💥💥

አንድ ሰው ከኢስላም መርህ ጋር እስካልተቃረነ ድረሰ የሚያምርበትን ዉብ ልብስ መልበስ ችግር የለበትም። ሆኖም ጎልቶ በመታየት፥ ትኩረት በመሳብ ፥የበላይነትን በማሳየት፥ የሰዎችን እይታን በመሳብ ዉድድር ዉስጥ የገቡ አካላት አሉ። እነርሱ ልዩ ሆነው ለመታየት እና ለመታወቅ ሲሉ ሁሌም የተለ የዝና ፍለጋ አለባበስ መልበስን መንገዳቸው ያደርጋሉ።

በዚህ አደገኛ በሆነው አካሄድ ዉስጥ የትኩረጥ ጥማት፥ በሰዎች የመወደስ ፍላጎት፥ ይዩልኝ(ሪያእ)፥ መመጻደቅ፥ከሌሎች በላይ ሆኖ መታየት፥ የቅቡልነት ጉድለት፥ የራስን ስሜት ማምለክ አለበት።

ሰዎች ትኩረታቸውና ፍላጎታቸው በአላህ ዉዴታ ሳይሆን በሰዎች ማረጋገጫና ምስክርነት ላይ ከተንጠለጠለ በቅን ልቦና አላህን ማመለክ አስቸጋሪ ይሆናል። ለዚህም ነው ተግባር በአላህ ዘንድ የሚያስቀጣ ወንጀል የሆነው። ከዐብደላህ ኢብኑ ዑመር(ረዐ) በተላለፈ ዘገባ የአላህ መልዕክተኛ(ሰዐወ) በዚህ ጉዳይ ላይ እንዲህ ብለዋል፦
عن ابن عمر قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: من لبس ثوب شهرة في الدنيا، ألبسه الله ثوب مذلة يوم القيامة. رواه أحمد وأبو داود وابن ماجه، والنسائي
«በምድራዊ ዓለም የዝናን ልብስ የለበሰ ሰው፥ አላህ በእለተ ትንሳኤ የዉርደት ልብስን ያለብሰዋል። ከዚያም የእሳት መቀጣጠያ ያደርጋል።»(አቡዳውድ፥ ኢማም አሕመድ፥ ኢብኑ ማጃህ የዘገቡት)

የእውቅናና ዝና ልብስ በመልበስ በገጽታ ብቻ ልቆ ለመታየት መጓጓት እንዲሁም የሕይወት ዓላማንና አቅጣጫን መታወቅ ጋር ማቆራኘት መዘዙ አደገኛ ነው።

የገንዘብና ክብር መሻት ጉጉት መዘዝ
🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎🍎

ኢማም አህመድና ቲርሚዚይ ካዕብ ኢብኑ ማሊክን በማጣቀስ እንደዘገቡት የአላህ መልዕክተኛ(ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል:

«مَا ذِئْبَانِ جَائِعَانِ أُرْسِلَا فِي غَنَمٍ، بِأَفْسَدَ لَهَا مِنْ حِرْصِ الْمَرْءِ عَلَى الْمَالِ وَالشَّرَفِ لِدِينِهِ
‹‹በበግ(ፍየል) መንጋ መሃል የተለቀቁ ሁለት የተራቡ ተኩላዎች በመንጋው ላይ የሚያደርሱት ጥፋት፣ ለገንዘብና ለክብር(ስልጣን) ጉጉ የሆነ ሰው በዲኑ(ሃይማኖቱ) ላይ ከሚያደርሰው ጥፋት የከፋ አይደለም፡፡››

በዚህ ሀዲሳቸው የአላህ መልዕክተኛ(ሰዐወ) ሁለት የተራቡ ተኩላዎች በበግ መንጋ ላይ ከሚያደርሱት ጉዳት ፍጥነትና ስፋት ይልቅ የገንዘብ(المال) እና የክብር(الشرف) ጉጉት በአንድ ግለሰብ ሃይማኖት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ይከፋል። ለክብር መጓጓት የሚለው ከክብር ጋር የተያያዙ ለደረጃ፥ለዝና፥ ለስም፥ለስልጣን፥ለመወደስ ወዘተን መጓጓትን ይጨምራል።

ለገንዘብና ለክብር መጓጓት ሁለቱም የሰዎችን ዉስጣዊ ኒያን(የሀሳብ ዓላማን) ይበክላሉ። መመጻደቅን ያስከትላሉ። ሰዎችን እነርሱን ለማግኘት ሲል ወደ ኃጢአት ይመሩታል። ቅንነትን ያዳክማሉ። መተናነስን በማጥፋት ልታይ ልታይ ማለትን ያስከትላሉ።ሰዎች እነርሱን ለማግኘት ሲሉ የሃይማኖታቸውን ድንበር ጥሰውና እምነታቸውን ተቃርነው ጭምር እንዲጓዙ ይገፋፏቸዋል።

ለገንዘብ ሲሉ ኢስላምን እስከ መሸጥ ድረስ?
💥💥💥🍎🍎🍎💢💢💢🍎🍎💥💥

ሰዎች «የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው» የሚል ፈለግ ተከትለው ገንዘብን በየትኛው መንገድ የማግኘት ዝግጁነት ላይ ከደረሱ እጅግ አደገኛ ደረጃ ላይ ናቸው። አሁን ያለንበት ዘመን ሰዎች ለገንዘብ ሲሉ የማይሆኑት ነገር የሌለበት ደረጃ ደርሰው እያየን ነው። ሰዎች በቂላቂልነትም፥ በጋጠወጥነትም፥ ኢስላምን በመቃረንም፥ የሰዎችን ስም በማጥፋትም ሆነ ግጭት በመፍጠር ገንዘብ መስራት አለብን የሚሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።

በመሰል ሁኔታ ዉስጥ ሰምጦ አልያም በመሰል ሰዎች ተከቦ ያለሰው ሃይማኖቱ ራሱ አሳሰቢ ነው። ሙስሊም ነው ሲባል ሙስሊም የማይሰራውን ስራ ሲሰራ ይታያል። ጠዋት ደህና ሰው ነው ሲባል ማታ ሌላ ሆኖ ይገኛል። እንዴት በሚከተለው ኢስላም(ዲኑ) ላይ እንዲወስን አደረገው ብለን ልንገረም እንችላለን። ነገር ግን ይህን መሰል ሁኔታ ከአቡ ሁረይራ(ረዐ) እንደተላለፈው ዘገባ ነቢያችን(ሰዐወ) እንዲህ በማለት አስጠንቅቀውናል፦

"بادروا بالأعمال، فتناً كقطع الليل المظلم، يصبح الرجل فيها مؤمناً، ويمسي كافراً، أو يمسي مؤمناً ويصبح كافراً، يبيع دينه بعرض من الدنيا" رواه مسلم والترمذي وأحمد

«በመልካም ስራ ላይ ተሽቀዳደሙ። ከፊታችሁ እንደ ቁራጭ ሌሊት አይነት የጨለመ ፈተና አለ። አንድ ሰው አማኝ ሆኖ አንግቶ ከሃዲ ሆኖ ያመሻል፤ ወይም አማኝ ሆኖ ያመሽና ከሃዲ ሆኖ ያነጋል። ዲኑን (እምነቱን) በዱኒያዊ (ዓለማዊ) ጥቅማ ጥቅም ይሸጣል ።» (ሙስሊም፥ቲርሚዚና አሕመድ ዘግበውታል)

«ዋናው የተከታዮቼ መደሰት ነው»
🌄🌄🌄🌄🌅🌅🌅🌅🌅🌅

ሰዎች ከወደዱልኝ፥ ከተከተሉኝም፥ ካደነቁልኝም፤ ዝነኛ ከሆንኩ የአላህ መውደድ ወይም መጥቀም ደንታዬ አይደለም ማለት ነው። በማህበራዊ ሚዲያ ዓለም ሰዎች እይታን እንዳያጡ ሲሉ ተከታዮቻቸውን ማስደሰት፥ የነርሱን ፍላጎትና ጥያቄን መሙላት ቀዳሚ ዓላማቸው ይሆናል። ይህ ለሰዎች ሳይታወቃቸው ከልካይና ፈቃጃቸው አላህና ነቢዩ(ሰዐወ) መሆናቸው ቀርቶ ታዳሚያቸው ይሆናሉ። በሂደትም የታዳሚን ፍላጎት እየተከተሉ ርቀው ይሄዳሉ።

በሂደትም የሕዝብ አስተያየት አምላካቸው፥ እይታን ካስገኘ ጋጠወጥነት ማርኬቲንግ (የገበያ መሳቢያ) መገንዳቸው፥ መታየትና እይታ ማግኘት ማንነታቸው፥ የትኩረት ማዕከል መሆን ደግሞ ዓላማ ይሆናል። ሰዎችን ለማስደሰት ሲሉ ከአላህ ርቀው እርሱን ያስከፉታል። ለጊዜው ከበሬታ ያገኙ ቢመስላቸውም በሂደት ግን ለገንዘብ ሲሉ ምንም ከመሆን ወደ ኋላ የማይሉ እንደሆኑ ሲታወቁ በሰዎች ልብ የነበራቸው ስፍራ ይወርዳል። ይናቃሉ። ይጠላሉ።

በዚህ ጉዳይ ላይ ከዓኢሻ(ረዐ) በተላለፈ ዘገባ የአላህ መልዕክተኛ(ሰዐወ) አንዲህ ይሉናል፦
من التمس رضى الله بسخط الناس رضي الله عنه وأرضى الناس عن، ومن التمس رضا الناس بسخط الله سخط الله عليه وأسخط عليه الناس
«አላህን ለማስደሰት ሲል ሰዎችን ያስቆጣ ሰውን አላህ ይወደዋል፤ ሰዎችም እንዲወዱት ያደርጋል። ሰዎችን ለማስደሰት ሲልም አላህን ያስቆጣን ሰው አላህ ይቆጣበታል። ሰዎችም እንዲጠሉት ያደርገዋል።»(ቲርሚዚይ፥ ኢብኑ ሂባን እንዲሁም አልባኒ የዘገቡት)

«አላህን ፍራ» ሲባል በትዕቢት መወጠር
❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌

ከሃይማኖት ተቃርኖም ጭምር ቢሆን ዝናና ክብር፥ ገንዘብና ዉዳሴ ማግኘት የግለሰቡን ዉስጣዊ ማንነት ነጸብራቅ ነው።የደካማ እምነት ማንነት ማሳያ ነው። ለራስ ያነሰ ዋጋ የመስጠት እና በስሜት የመነዳት ማሳያ ነው።አንዳንዶች ይህን አውነታን ለመሸፋፈን «ልቤ ንጹሕ ነው። ዋናው ልብ ነው» የሚል መደበቂያ ምሽግ እስከ መገንባት ይደርሳሉ። እንደሚባለው ጽኑ እምነት በልቦና ቢኖር በእርግጥ ወደዉጭ ሳይወጣና ተደብቆ አይቀርም ነበር። የነርሱ ግን በግልጽና በሚታይ ሁኔታ ከአላህና መልዕክተኛው(ሰዐወ) ትዕዛዛት ሲቃረኑ ይታያሉ።

ይህ ጉዞ በመጨረሻ ግለሰቡን ከሃይማኖቱ እንዲርቅ በልቡም ከአላህ ይልቅ የዝና ጥማትና የገንዘብ ጉጉት እየነገሰ ይሄዳል። ከዚህ የተነሳም ከሃይማኖቱ የተቃረነ አለባበስ፥ ስነምግባር፥ በዓሊሞችና ዳኢዎች ላይ መሳለቅ፤ እንዲሁም ትኩረት ለመሳብ አወዛጋቢና አነጋጋሪ ነገሮችን ሆነ ብሎ ይተገብራል። ተከታይም ያፈራበታል።
በዚህ ደረጃ ላይ የደረሰ ሰው አላህን እንዲፈራ ቢመከር እንኳ ታዋቂነቱና ከርሱ ጋር ተያይዞ በተፈጠረበት የኩራት ስሜት ከስህተቱ ለመመለስ ሞት ሆኖ ይታየዋል። ከመመለስ ይልቅ «እኔ እኮ ብዙ ተከታይ አለኝ። መብቴም ነው። ስለኔ ምን ያገባችኋል!» በሚል ኩራት ልቡ በትዕቢት ይዋጣል።

ልቢናውን እያደነደነ በዚያው የኃጢአት ጉዞው ይቀጥላል። አላህ ከዚህ ይጠብቀንና ይህ የጥንት መናፍቃን ባህሪም ነበር። አላህ(ሱወ) በቁርኣን ስለነዚህ ዓይነት ሰዎች እንዲህ ይላል፦
وإذا قيل له اتق الله أخذته العزة بالإثم فحسبه جهنم ولبئس المهاد

«ለእርሱ በተባለም ጊዜ፤ትዕቢቱ በኃጢአት(ሥራ) ላይ ትገፋፈዋለች። ገሀነምም በቂው ናት፤(እርሷ) በእርግጥ የከፋች ምንጣፍ ናት።»(ሱረቱ አል-በቀራህ 2፡206)

ስሜት አምላኪ ትውልድ የመፈጠር አደጋ!
⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽

ኢስላም እንደሚያስተምረው በአማኝ ልብ ዉስጥ በብቸኝነት መንገስ ያለበት አላህ ብቻ ነው።ከአላህ ጋር ሌላ ጣኦት ማንገስ አይቻልም። በዝናና እውቀና ጥም የተሞላ ልብ በተመሳሳይ ጊዜ በአላህ ዉዴታ ሊሞላ አይቻለውም። የሰው የተፈጠረለት አንድ እንጂ ሁለት ልብ የለውም።አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦

مَا جَعَلَ اللّٰهُ لِرَجُلٍ مِنْ قَلْبَيْنِ فِي جَوْفِهِ
«አላህ ለአንድ ሰው በሆዱ ዉስጥ ሁለትን ልቦችን አላደረገም።»(አል-አሕዛብ፡4)

የሰው ልጅ ባለው አንዲት ልቦና ዉስጥ በዋናነት መንገስ ያለበት አንድ አላህ ብቻ ነው።በአላህ ምትክ ሌላ አካል እንዲነግስ ከተደረገ መዘዙ አደገኛ ነው። የታዋቂነት፥ የዝነኝነትና የላቀ ክብር ፍለጋ ጉዞ በሰዎች ልቦና ዉስጥ ቀስበቀስ በራስ መደነቅ፥ መወደስ መፈለግና ከንቱ ዉዳሴን የማሸት ስሜትን እያለመለሙ ነው።

ተገቢውን ትውልድ የማዳን ሥራ ካልተሰራ ቀጣዩ ትውልድ ከአላህ ይልቅ ዝንባሌውን አምላኩ አድርጎ የሚይዝ፥ ከቁርኣን ይልቅ በዝንባሌው የሚመራ ትውልድ ሊሆን እንደሚችል ምልክቶች እየታዩ ነው። ጊዜ ወስደን ማህበራዊ ሚዲያን ብንመለከት አላህ ምን ይላል? ነቢያችንስ(ሰዐወ) በዚህ ጉዳይ ላይ ምን አሉን? የሚለው ደንታቸው ያልሆነ ሙስሊሞች ጭምር እየተፈጠሩ ነው።

አይናችንን ከገለጥን እኛም ከአላህ ይልቅ ስሜቱን አምላኩ አድርጎ ስሜቱ የሚያዘውን ፍላጎት ለመሙላት የሚጣጣር ሰው ማየት ከባድ አይሆንም። መሰል ሰዎች እንደሚኖር አላህ ባይነግረን ኖሮ ስሜቱን የሚያመልክ ሰው ይኖራል ብሎ መናገር በከበደ ነበር። አላህ(ሱወ) እንዲህ ይለናል፦

أَفَرَأَيْتَ مَنِ اتَّخَذَ إِلَهَهُ هَوَاهُ
«ዝንባሌውን(ስሜቱን) አምላኩ አድርጎ የያዘውን ሰው አየህን!» (ቁርኣን፤ ሱራ አል-ጃሲያህ፡23)

«ሙስሊሞች ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የለባቸውምን?»
🏉🏉🏉🏉🏉🏉🏉🏉🏉🏉🏉🏉

በአዕምሯችሁ «ታዲዮ ሙስሊሞች ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የለባቸውም ማለት ነውን?» የሚል ጥያቄ ሊፈጠር ይችላል። መልሱ እያንዳንዱ ሙስሊም ተጽዕኖ ፈጣሪ ሊሆን ይገባል ነው። ግን ተጽዕኖ ራሱ ምንድነው?

ተጽዕኖ ማለት በሌሎች አስተሳሰብ፥ አመለካከት፥ ባህሪ፥ ዉሳኔ፥ ድርጊት ወዘተ ላይ ለውጥ ማምጣት ነው።

ጥያቄው ለውጡ አላህንና መልዕክተኛውን (ሰዐወ) ያስደስታቸዋል ወይንስ ያስቆጣቸዋል? የዝና ጥማት ግን ኢጎ፥ትኩረት መፈለግ፥ ዉጫዊ የሌሎች ምስክርነትና ዉዳሴን መሻት ነው።

ኢስላም ሙስሊሞች በመልካምና ሥነ ምግባርን በተከተለ መንገድ ተጽዕኖ ፈጣሪ እንዲሆኑ ይፈልጋል።ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆኖ ለሃይማኖታቸው፥ ለሕዝባቸውና ለሀገራቸው መልካም አስተዋጽዕኖ እንዲያበረክቱ ይሻል።በዚህም በጠቃሚነት ልቀው እንዲገኙም ይፈልጋል።

አላህም ዘንድ በልጠው የሚገኙትና የበለጠ የሚወደዱት በዚህ በመልካም መንገድ ከሌሎች በከተፍተኛ ደረጃ ጠቃሚ ሆነው በመገኘታቸው ነው። አላህ ዘንድ መለኪያው ታዋቂነት ሳይሆን ጠቃሚነት ነው። አላህ በሚወደውና የርሱን መመሪያ ለልተቃረነ መልኩ ከሌሎች የበለጠ የሰው ልጆቸን የበለጠ ሰው አላህ ዘንድ ይበልጥ ተዳጅና ይበልጥ በላጭ ነው።የአላህ መልዕክተኛ (ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦
خير الناس أنفعهم للناس
«ከሰዎች ሁሉ በላጩ ይበልጥ ለሰዎች ጠቃሚ የሆነው ነው።» (ጠበራኒ በአውሰጥ ላይ የዘገቡትና አልባኒ ሰሂህ ሲሉ ያጸቁት)

«ከሰዎች ሁሉ አላህ ዘንድ ይበልጥ ተወዳጁ ለሰዎች ይበልጥ ጠቃሚ የሆነው ሰው ነው።» (ጠበራኒ)
أحب الناس إلى الله أنفعهم للناس

በተቃራኒ ደግሞ አንዳች ጠቀሜታ በሌለው ጉዳይ ራስን መጥመድ፥ አላህን ማስደሰትን ወይንም ለራስም ሆነ ለሌሎች ጥቅም ማስገኘት በሌለበት መልኩ ዝናና ስም ማግኘትን ኢላማ ያደረገ ለታይታ የሚደረግ ነገር ሁሉ የተወገዘ ነው።በዚህ ዉስጥ የዝናና ዉዳሴ ሱሰኛ መሆን፥ ለመታወቅ ዓላማ መታወቅ፤ ትኩረት ለመሳብ ሲሉ ጋጠወጥ ተግባራትን ማድረግ ሁሉ የተወገዘ ነው።

ችግሩ ምኑ ላይ ነው?
🎁🎁🎁🎁🎁🎁

ስነምግባርን በተላበሰ መልኩ ዓላማው ወገንን ለመጥቀም በሚያበረክቱት እውቀት፥ ክህሎት ወይም በአገልጎት መታወቅ ወንጀል አይደለም። በማህበራዊ ሚዲያ ዓለም ችግሩ የሚያጋሩት ቁም ነገር አል ይዘት(content) ማመንጨት የማይችሉ በሆኑበት ሁኔታ መታወቅ መፈለግ ነው። ያኔ የሚያጋሩት እውቀት፥ ክህሎት፥ አገልግሎት ወይም አንዳች ጠቃሚ ነገር ስለማይኖራቸው ይዘቱ እነርሱ ራሳቸው ይሆናሉ። አካላቸው፥የአናኗር ሁኔታቸው፥ የቤታቸው ገበና፥ እና ፎቶ ግራፋቸው ይሆናል።

የመታየት፥የመታወቅ፥ የዝናና የትኩረት ፍላጎቱ የማህበራዊ ሚደያቸው ይዘቱ እነርሱ ራሳቸው ስለሆኑ ይበልጥ ራሳቸውን እንዲያራቁቱ፥ ይበልጥ ገበናቸው እንዲያጋልጡና ራሳቸውን እንዲያዋርዱ ይገፋፋቸዋ።

ዓላማው ወገንን ማገልገል ሆኖ በሚሰጡት ትምህርት፥ በምክር፥ በእርዳታ፥ ጠቃሚ ነገርን በመፍጠር እና ሌሎችን በቅንነት በመምራት መታወቅ ጥሩ ነገር ነው።ነገር ግን በተደጋጋሚ የራስን መልክ እየለጠፉ የሌሎችን አስተያየት መፈለግ፤ የራስን አካል፥ የህይወት ዘይቤ፥ ስሜቶች፥ የትዳር ሕይወት፥ ወዘተ ወደ መዝናኛ ይዘት መለወጥ፤ ትኩረት ለመሳብ የራስን ምስል ደጋግሞ መለጠፍ፤እውቅናን ሆነ ዝናን በሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ላይ ሳይሆን በራስ መልክ፥ ጸጉር፥ አካል ማድረግ፤ የራሰን ስብዕና የሕዝብ ፍጆታ ማዕክል ማድረግ፤

በሚያበረክቱት ጥቅም ሳይሆን እንደሰው ዝም ብሎ መወደድ፥ መደነቅ ወይም ሰዎች እንዲከተሉት መፈለግ ወዘተ ናቸው።

የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ እየፈጠረው ያለው አዝማሚያ አደገኛ ነው። በዝምታ ከታየ የቀጣዩ ትውልድ ሁኔታ አስጊ ነው። ተግቶ ሠርቶ ቁም ነገር ላይ መድረስ ፋራነት ተደርጎ ወደ መታየት ጀመረ።ሞራል፥ እምነትንና ሕግን ተቃርኖም ቢሆን ለሁሉም ነገር አቋራጭና ዉጤት የሚገኝበት መንገድን መፈለግ በተዳጊዎች ልቦና እየሰረጸ ነው።

የነቢያችን(ሰዐወ) ትንቢት ተፈጸመ
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢

የማህበራዊ ሚዲያዎቹ አልጎሪዝም ቀመር ትኩረት ሳቢና አነጋጋሪ ነገሮችን ማጉላት ላይ የተመሠረተ ነው። ከዚህ የተነሳ ትኩረት ለመሳብ ደፋር የሆኑት እየጎሉ እውቀትና ትምህርት፥ ምሁራዊ እይታና ስነምግባርን የተከተሉ ይዘቶች የሚገባቸውን ትኩረት ተነፈጉ። ከአዋቂነት ይልቅ ታዋቂነት ሚዛን አነሳ። ከጠቃሚነት ይልቅ ደፋርነት ቦታ አገኘ። በሚዲያዎቹ ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪዎቹ ሊቃውንት ሳይሆኑ ደፋር ቂላቂሎቹ በረከቱ።

ትኩረት ለመሳብና ተከታይ ለማብዛት በማይመለከታቸው ና እውቀቱ በሌላቸው ወሳኝ የሀገርና የሕዝብ ጉዳዮች ሁሉ የሚዘባርቁ በረከቱ። ይህ ደግሞ በእውቀት ያልጎለበቱ ተከታዮች አደናገረ። ብዙዎች ታዋቂነትና አዋቂነት አምታታቸው። ለገንዘብና ዝና ሲሉ ሐሰት እየፈበረኩ የሚያሰራጩት ታዋቂ በመሆናቸው ብቻ እንደ እውነተኞች ተቆጠሩ። እውነተኞች ደግሞ ታዋቂ ባለመሆናቸው ብቻ እንደሐሰተኞች ቦታ ተነፈጉ። ዘመኑ አደናጋሪ ሆነ። የሀገር እጣ ፈንታ፥ ወሳኝ በሆኑ የሕዝብ ጉዳዮች ቂላቂሎችና በእውቀታቸው ተራ የሆኑ ሰዎች የሚፈተፍቱበት ሆነ። ይህ ዘመን እንደሚከሰት ነቢያችን(ሰዐወ) የነገሩን ትንቢትም ተፈጽሞ ታየ።

ከአነስ ኢብኑ ማሊክ(ረዐ) እና ከአቡሁረይራ (ረዐ) በተላለፈ ዘገባ የአላህ መልዕክተኛ (ሰዐወ) እንዲህ በማለት ተናግረዋል፦
- سيأتِي على الناسِ سنواتٌ خدّاعاتٌ؛ يُصدَّقُ فيها الكاذِبُ، ويُكذَّبُ فيها الصادِقُ، ويُؤتَمَنُ فيها الخائِنُ، ويخَوَّنُ فيها الأمينُ، وينطِقُ فيها الرُّويْبِضَةُ . قِيلَ : وما الرُّويْبِضةُ ؟ قال : الرجُلُ التّافِهُ يتَكلَّمُ في أمرِ العامةِ
« አሉ። በዚህን ጊዜ «ሩወይቢዳዎች ማን ናቸው?» ተብለው ተጠየቁ። እርሳቸውም «ሩወይቢዳ ማለት ቂላቂል(ተራ) ሰው በአጠቃላይ ሕዝብ ጉዳይ የሚናገር ነው።» በማለት መለሱ።(ኢብኑ ማጃህ፥ አልባኒ በሰሂህ አል-ጃሚዕ ላይ የዘገቡት)

መፍትሄው ምንድነው?
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ማህበራዊ ሚዲያን ራቅ አልያም ተጽዕኖ ፈጣሪ አትሁን አይደለም። ዓላማው በግልጽ ተብራርቷል። አንድ ሰው አንድን ሥራ የአላህን ዉዴታ ፈገጎ በመልካም ሁኔታ አሳምሮ ሲሰራ ሰዎች በስራው ሊደሰቱ እና ሊወዱት ይችላሉ። ይህ አንዳች ችግር የለውም። የእርሱ አላማ አላህን ማስደሰት ነበር። አላህም ተደሰተበት። ሰዎች እንዲወዱመም አደረገ።

ስለዚህ ጉዳይ ከአቡዘር አልጊፋሪ(ረዐ) በተላለፈው ዘገባ የአላህ መልዕክተኛ(ሰዐወ) እንዲህ በማለት ተጠየቁ፦
الرجلُ يعملُ العملَ للهِ فيُحبُّهُ الناسُ عليهِ قال ذلك عاجلُ بشرى المؤمنِ
«አንድ ሰው መልካም ተግባርን ለአላህ ብሎ ሠርቶ ሰዎች በሥራው ምክንያት ቢወዱትስ? ተብለው ተጠየቁ። መልዕክተኛውም(ሰዐወ) «ያ ለአማኝ ቀድሞ የመጣለት ብሥራት ነው።» (ሙስሊም፥ ኢብኑ ማጃህ የዘገቡት)

ዝናና ስምን ለማጋበስ ሳይጓጉ ሚናን በአግባቢ መወጣትን ተከትሎ የሚገኝ እውቅና የአላህ ብሥራት ነው።ነገር ግን ሆነ ብሎ ለመታወቅና በሰዎች ለመደስ ብሎ ሥራ መሥራት ደግሞ ይዩልኝ ነው፤ ሆነ ብሎ ዝናና እውቅና ለማግኘት ሲሉ ኃጢአት መሥራት ደግሞ ድርብና እጥፍ ጥፋት ነው። የይሁልኝ በሽታ+ ኃጢአት ማለት ነው።

የዝናና ታዋቂነት ሱስ ደግሞ የቅንነት(ኢክላስ) ብክለት፥ የመልካም ሥራ መበላሽት ነው። ለመታወቅ ሲሉ መጥቀም ግን የይዩልኝ ዝና ፍለጋ ተግባር ነው።ስለሆነም «ሰግጥ ፈምስ» የሚለው ላንተ አይሰራም። አንተ በአላህ የምታምን ሙስሊም ነህ። አንቺም ነቢያችን የምትከተይ ሙስሊም ነሽና። የመጨረሻ ምክሬ የሚከተሉት ናቸው፦

1. ዓላማህ ትኩረት መሳብ ሳይሆን በቅን መንገድ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን ይሁን።

2. ጭብጨባና ሙገሳን የሚያሳድድ ሳይሆን ጠቃሚ ሆነህ መገኘት ላይ ትጋ።

3. ሌሎችን ማገልገል ላይ እንጂ ተከታይ ማፍራትን ኢላማህ አታድርግ።

4. ለዝናና ክብር የምትጋጋጥ ሳትሆን በተጽዕኖው ወደ ቅን መንገድ የሚመራ መሪ ሆነህ በመገኘት ጣር።

5. የአላህን ዉዴታን ማግኘትን እንጂ የሰዎችን ሙገሳና እርካታ ማግኘነን ግብህ አታድርግ።

6. የዝና ጥማትን ለሀገርና ወገን ወደ ሚጠቅም ተጽዕኖ ፈጣሪነት ለውጠው።

7. የመወደስ ረሀብ በዉስጥህ ከተፈጠረ ራስህን ገምግመህ ከዚያ ለመውጣት ትጋ።

8. በእጅህ ያለውን ማህበራዊ ሚዲያን ተጠያቂነት እንዳለብህ በመረዳት አላህንና ነቢዩን(ሰዐወ) በሚያስደስቱ ጉዳዮች ድምጽ ወደ መሆን የላቀ ግልጋሎት ፍላጎት አዙር።

9. ተኩረት የማግኘት ሱስን አላህን ማዕክል ባደረገ ማንነት በመገንባት ተካው።

10. ተጽዕኖ ፈጣሪነትነን አላህን በሚያስደስት፥ መልካም ትውልድን ለመፍጠር በቅንነትና በኃላፊነት ስሜት ተጠቀምበት።

11. የምትከተላቸውን ሰዎች ለይ። የምታጋራቸውን ነገሮች አስተውል። የመልካሞችን እንጂ የእኩያንን ፋናና ተጽዕኖን በማስፋት ላይ ተባባሪ አትሁን።

ዛሬም ሆነ ነገ፥ በዚህ ምድርም ሆነ በቀጣይ ዓለም በሰውም ሆነ በአላህ ፊት የሚያሳፍር ስፍራ ላይ አትገኝ።፥ የሚያስወቅስ ተግባር ተባባሪ አትሁን። የማህበራዊ ሚዲያ ዓለም አንዴ የጻፍካቸው ጽሑፎች፥ የተናገርከውን ንግግሮች እና የሠራኻቸው ቪዲዮዎች ከአጅህ ከወጡ በኋላ ላይመለሱ ተሰራጭተዋል። ሀሳብህን ብትቀይር ወይም መሳሳትህን አምነህ ይቅርታ ብትጠይቅ እንኳ የተሰራጩት እይታ እያገኙ ይቀጥላሉ።

አላህ ዘንድ የምትጠየቀው በአንተ ገጽ ላይ ባሉ ተከታዮች ብቻ አይደለም። ስንቶች ሞተው ጭምር አሻራቸው በማህበዊ ሚዲያ ላይ ለዓመታት ሲዘዋወሩ እያን ነው። ያንተን ፈለግ (አሻራ) ማለት ሀሳብን የተጋሩና የደረሳቸው ሁሉ የሚተገብሩነን ያጠቃልላል።ለነርሱ ተግባራት ሚና ነበረህና የነርሱ መጠየቅ እንዳለ ሆኖ በሚሠሩት ጥፋት ሁሉ አንተም ትጠየቅበታለህ ። ሞተህም ጭምር በመልካም ሥራህ እንደትወደሰው የእኩይ ሥራዎችህ ፋና(አሻራ) ይጻፍብሃል።በዚህ ጉዳይ ጌታችን አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦
إِنَّا نَحْنُ نُحْيِي الْمَوْتَىٰ وَنَكْتُبُ مَا قَدَّمُوا وَآثَارَهُمْ ۚ
وَكُلَّ شَيْءٍ أَحْصَيْنَاهُ فِي إِمَامٍ مُّبِينٍ
«እኛ ሙታንን በእርግጥ ሕያው እናደርጋለን። ያስቀደሙትንም ሥራ ፈለጎቻቸውንም እንጽፋለን። ነገሩን ሁሉ ገላጭ መሪ በኾነው መጽሐፍ ዉስጥ አጠቃለልነው።»(ሱራ ያሲን፡ 36፡12)

አላህ በሚወደው መንገድ ተጽዕኖ ፈጣሪ ለመሆን ቆርጠን እንነሳ።አበቃሁ።

Ahmedin Jebel-አሕመዲን ጀበል

"ስኬት ድፍረት ይጠይቃል" Courage is an essential ingredient for success(በዶ/ር ቢላል ሽብር)ድፍረት ፍርሃት ባለበት ሁኔታ ውስጥ እንኳ ቢሆን ትክክልና አስፈላጊ ...
01/12/2025

"ስኬት ድፍረት ይጠይቃል" Courage is an essential ingredient for success

(በዶ/ር ቢላል ሽብር)

ድፍረት ፍርሃት ባለበት ሁኔታ ውስጥ እንኳ ቢሆን ትክክልና አስፈላጊ የሆነውን ነገር ለመፈፀም የሚያስችል የመንፈስ ጥንካሬ ወይም ቆራጥነት ማለት ነው።
ታላቅ ስኬት ብዙውን ጊዜ ቀጥተኛ መንገድ አይደለም፤ መሰናክሎች፣ እርግጠኛ አለመሆን እንዲሁም የመውደቅና የመተቸት ስጋቶች የተሞላበት ነው።

ለስኬት ድፍረት ለምን ያስፈልጋል?

1. የመጀመር ድፍረት (Courage to Start): ትልቅ ውሳኔ ትልቅ ድፍረት ይጠይቃል!

የውጤቱ እርግጠኛነት ባልታወቀበት ሁኔታ ከምቾት ቀጠና (comfort zone) ለመውጣትና አዲስ ነገር ለመሞከር ድፍረት ያስፈልጋል።

2. የተለየ የመሆን ድፍረት (Courage to be different)

እውነተኛ ስኬት አብዛኛውን ጊዜ ነገሮችን በተለየ መንገድ መሥራት፣ አዲስ ራዕይ ይዞ መምጣት ወይም ሌሎች የሚነቅፉትን ሀሳብ መሞከር ይጠይቃል። ይህ ከፍተኛ ሞራላዊ ድፍረትን ይጠይቃል።

3. ከውድቀት በኋላ የመቀጠል ድፍረት (Courage to Keep Going)
ውድቀትን ተቀብሎ፣ ከስህተቱ ተምሮ ተስፋ ከመቁረጥ ይልቅ እንደገና ለመሞከር መወሰን ስነልቦናዊ ድፍረትን ይጠይቃል።

4. እርዳታ የመጠየቅ ድፍረት (Courage to Ask for Help)

እገዛ እንደሚያስፈልግ አምኖ መቀበል፣ ምክር ለመስማት ወይም ስራን ለሌላ ሰው ለመስጠት ትህትናና ድፍረት ያስፈልጋል።

5. የመጨረስ ድፍረት (Courage to Finish)

አንዳንድ ጊዜ በጣም ከባዱ ነገር መጀመር ሳይሆን፣ የጀመርነውን ነገር የመጨረሻ ግብ እስኪደረስበት ድረስ በትዕግስትና በፅናት መቀጠል ነው።

ስኬት የሚገኘው ፍርሃትን ከተጋፈጠ በኋላ ባለው ጎዳና ላይ ነው። የምንፈራቸው መሰናክሎች (ውድቀት፣ የሌሎች ፍርድ፣ እርግጠኛ አለመሆን) ድል ሲነሱ ስኬት ሽልማት ይሆናል።

ደፋር ለመሆን ምን ማድረግ ይጠበቅብን ይሁን?

https://www.facebook.com/share/p/16XoPzcPBK/

25/11/2025

ዛሬ ጠዋት የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ እዝ አዛዥ ጄነራል ዳግቪን አር ኤም አንደርሰንን አግኝቼ በቀጠናዊ የጸጥታ እና የበለጠ ትብብር ለማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገናል።

Har'a ganama Ajajaa Koomaandii Afrikaa Yunaayitid Isteetsi, Jeneraal Dagvin R.M. Anderson waliin dhimmoota nageenyaa naannawaafi haalota itti walta'insa caalaatti cimsuun danda'amu irratti marii'anneerra.

I welcomed General Dagvin R. M. Anderson, Commander of the U.S. Africa Command, this morning for a constructive exchange on regional security and opportunities for enhanced cooperation.

አማራን ከፋኖ በላይ የቀለበሰ ይኖር ይሆን?(በዓብድጀሊል ሸኽ አሊ ካሳ)              ★★★//💢//★★★ይህንን ቪዲዬ ትናንት ቀን ላይ "ጠብቅ የአንተም ተራ እንዲህ ይሆናል!" ከሚል ...
25/11/2025

አማራን ከፋኖ በላይ የቀለበሰ ይኖር ይሆን?

(በዓብድጀሊል ሸኽ አሊ ካሳ)

★★★//💢//★★★

ይህንን ቪዲዬ ትናንት ቀን ላይ "ጠብቅ የአንተም ተራ እንዲህ ይሆናል!" ከሚል ዛቻ ጋር ላኩልኝ። በዘግናኝ ድርጊታቸው ባዝንም የምጠብቀው እንደዚሁ ነው)

ያ በሊትሬቸር ለዚያውም መንፈሳዊ ሊትሬቸር ይመራ የነበረ ህዝብ የዛሬ 900 ዓመት ተሻግሮት በመጣው ባርባሪዝም እንደገና ይጠመቅ ይዟል።

በግጭት እና በፖለቲካዊ አለመረጋጋት ውስጥ ያሉ ማህበረሰቦች፣ ብዙውን ጊዜ የትግል አቅጣጫቸውን ስተው ወደ እርስ በርስ መበላላት (Internecine conflict) እና ወደ ማህበራዊ ውድመት የሚያመሩበት አጋጣሚ በታሪክ እና በፖለቲካ ሳይንስ ጥናቶች በተደጋጋሚ ታይቷል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል እየተንቀሳቀሰ ካለው የፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር ተያይዞ የሚነሱት ዘግናኝ ድርጊቶች፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እና የኢኮኖሚ ውድመቶች፣ ክልሉን ወደ አደገኛ የታሪክ ምዕራፍ እየገፉት መሆኑን የሚያመላክቱ ናቸው። ለዚህ ትንታኔ መነሻ የሚሆነው፣ የትናንቱን መሰል እጅግ ዘግናኝ እና አሰቃቂ ነውር ነው።

ይህ ቪዲዮ፣ "የአማራ ጠላት" ተብሎ የተፈረጀን አንድ ግለሰብ፣ በጭካኔ እጁ በመጥረቢያ ሲቆረጥ የሚያሳይ ሲሆን፣ ድርጊቱም በሰብዓዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል ብቻ ሳይሆን፣ በቡድኑ ውስጥ ያለውን የሥነ-ምግባር ውድቀት (Moral Decay) ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው። ይህ አይነቱ "ሳቬጅ" (Savage) ወይም አረመኔያዊ ድርጊት፣ ድንገተኛ ክስተት ሳይሆን፣ የቡድኑ አወቃቀር እና የአመራር ጥራት ውጤት መሆኑን በጥልቀት መመርመር ያስፈልጋል።

የዚህን ታጣቂ ቡድን ባህሪ ለመረዳት፣ የማህበራዊ ስነ-ልቦና (Social Psychology) እና የፖለቲካ ሶሺዮሎጂ መነጽርን መጠቀም ወሳኝ ነው። በአማራ ክልል የሚገኙ የፋኖ አደረጃጀት መሪዎች ዳራ ሲጠና፣ አብዛኞቹ በመደበኛ ትምህርት ያልገፉ (በ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ትምህርታቸውን ያቋረጡ)፣ ማህበራዊ መሰረታቸው ከመደበኛው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የወጣ (lumpenproletariat)፣ ማለትም የቀድሞ የመኪና ረዳቶች እና የጫኝ አውራጅነት ስራ ይሠሩ የነበሩ ከአረብ አገር ስደት የተመለሱ፣ ሊስትሮዎች ናቸው። ይበልጥ አሳሳቢው ጉዳይ ደግሞ፣ እነዚህ መሪዎች ተብለው የተሰየሙት አካላት በከፍተኛ የጫት፣ የመጠጥ እና የሲጋራ ሱስ የተጠቁ መሆናቸው ነው።

ማክስ ዌበር ስለ ስልጣን ምንጭ እና ስለ ካሪዝማቲክ መሪነት አንድ ትንታኔ አለው። አንድ የፖለቲካ ንቅናቄ በስነ-ምግባር እና በእውቀት ከታነጸ አመራር ሲርቅ፣ ወደ ወሮበላነት (Banditry) የመቀየር እድሉ ሰፊ ይሆናል። ከዚህ ቀደም በሽፍትነት እና ህዝብ በመዝረፍ ይታወቁ የነበሩ ግለሰቦች፣ ዛሬ "የነጻነት ታጋይ" የሚል ካባ ደርበው መሪ ሲሆኑ፣ የሚከተላቸውን ሰራዊት ባህሪ መገመት አዳጋች አይደለም። መሪዎቹ እነዚህ ከሆኑ፣ ተከታዮቹ ወይም ጀሌዎቹ ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ማሰብ፣ የክልሉን የወደፊት እጣ ፈንታ እጅግ አስፈሪ ያደርገዋል።

ይህ ቡድን በአማራ ክልል ላይ እያደረሰ ያለው ቀውስ ዘርፈ ብዙ ነው። በቅድሚያ፣ የቡድኑ እንቅስቃሴ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ መሰረት (Economic Base) በመናድ ላይ ያተኮረ ይመስላል። ክልሉ ለዘመናት የገነባውን እና ያከማቸውን የኢኮኖሚ ትርፍ (Economic Surplus) ማውደም፣ ነጋዴዎችን እና ባለሃብቶችን በማገት ሃብት መዝረፍ፣ እንዲሁም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችን ማስተጓጎል፣ ስልታዊ የሆነ የኢኮኖሚ ውድመት ተግባር ነው።

አንዳንድ የትጥቅ ትግሎች ከፖለቲካዊ ቅሬታ ይልቅ ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥቅማ ጥቅም እና ዘረፋ (Predatory rebellion) እንዴት እንደሚቀየሩ ጥቂት ላነበበ ሰው በአማራ ክልል እየታየ ያለውም ይኸው ነው። ቀደም ሲል የተሻለ የኢኮኖሚ አቅም የነበረው፣ ምርታማ ገበሬ እና ጠንካራ ነጋዴ በሙሉ ኢላማ ተደርጎ፣ ንብረቱ ተዘርፎ፣ እራሱ ታግቶ ወይም ተሰዶ አልቋል። ይህ ሁኔታ "ካፒታል ማሸሽ" (Capital Flight) የሚባለውን ኢኮኖሚያዊ ክስተት የፈጠረ ሲሆን፣ አቅም ያለው የማህበረሰብ ክፍል ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች አካባቢዎች እንዲሰደድ አስገድዶታል።

የቡድኑ የዘረፋ እና የጭካኔ ተግባር በከተማ ነዋሪዎች ላይ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን፣ ወደ ገጠርም የዘለቀ ነው። በተለይም "የሚሊሻ አባል ነው" ወይም "ከመንግሥት ጋር ንክኪ አለው" በሚል የሚጠረጠሩ ገበሬዎችን ኢላማ በማድረግ፣ ያላቸውን ጥንድ በሬ ሲዘርፉ፣ አንዱን ለባለቤቱ ትተው ሌላውን "የሚስትህ ፋንታ ነው" በሚል አስቂኝ እና አሳዛኝ ምክንያት ነድተው ማረዳቸው፣ የድርጊቱን ዝቅጠት ያሳያል። ይህ ድርጊት የገበሬውን የማምረት አቅም ከማዳከሙም በላይ፣ ማህበራዊ እሴቶችን የሚሸረሽር ነው። የኢኮኖሚው ውድመት በዚህ ብቻ አይቆምም፤ አሁን ላይ ቡድኑ ወደ ጂኦግራፊያዊ ወሰን ተሻጋሪ ዘረፋ (Transnational Extortion) ተሸጋግሯል። ልጆቻቸውን ወደ አረብ ሀገራት የላኩ ቤተሰቦች፣ "ልህሽ ብር ትላክ" እየተባሉ ከፍተኛ መከራ እና እንግልት እያስተናገዱ ነው። ይህ የሚያሳየው ቡድኑ የገንዘብ ምንጭ ለማግኘት ማንኛውንም የጭካኔ መንገድ ከመጠቀም ወደኋላ እንደማይል ነው።

በተጨማሪም፣ ቡድኑ በአማራ ህዝብ የወደፊት ተስፋ ላይ እየፈጸመ ያለው "የትውልድ ግድያ" (Generational Su***de) እጅግ አሳሳቢ ነው። መምህራን "ለምን አስተማራችሁ?" ተብለው፣ ተማሪዎች "ለምን ተማራችሁ?" ተብለው የመረሸናቸው ጉዳይ፣ "ፖሊቲሳይድ" (Politicicide) እና "ኤጁሳይድ" (Educide) ተብሎ በሚጠራው የዘር ማጥፋት ጥናት ዘርፍ ሊካተት የሚችል ነው። አንድ ማህበረሰብ ተተኪ አመራር፣ ምሁር እና አስተዳዳሪ እንዳይኖረው ማድረግ፣ የራስን ማህበረሰብ አከርካሪ እንደመስበር ይቆጠራል። ከቀበሌ እስከ ክልል ድረስ የአመራር እና የካድሬነት ልምድ ያላቸውን ግለሰቦች፣ "ለአማራ እንታገላለን" በሚሉ ወገኖች መረሸናቸው፣ ክልሉን ወደፊት የሚመራ እና የሚያስተዳድር የሰው ኃይል (Human Capital) እያራቆተ ነው። የሚሊሻ አባላትን አግቶ በመውሰድ አፍንጫን መፎነን፣ አይን ማጥፋት፣ እና በጓያ ማጠን የመሳሰሉት አረመኔያዊ ድርጊቶች፣ ቡድኑ ከሰብዓዊነት ዝቅ ብሎ ወደ አውሬነት የተቀየረበትን ደረጃ ያሳያሉ።

በዚህ ሁሉ ምስቅልቅል ውስጥ፣ የክልሉ ሙስሊሞች ጉዳይ እና በክልሉ ውስጥ እየደረሰባቸው ያለው ሰቆቃ በተለየ ትኩረት ሊታይ የሚገባው ነው። የዚህ ሁሉ ቀውስ እና የጥላቻ ትርክት (Narrative) ሰለባ የሆነው ሙስሊሙ ማህበረሰብ ነው። "የእስላም መንግሥት" የሚለውን መሠረተ ቢስ የፕሮፓጋንዳ ትርክት እንደ ሽፋን በመጠቀም፣ የመስጂድ ኢማሞች፣ የመስጂድ ኮሚቴዎች፣ የመጅሊስ አመራሮች እና ሙስሊም ወጣቶች በሁሉም ቀጠናዎች ተረሽነዋል፣ ታግተዋል፣ እንዲሁም ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል። ይህ ድርጊት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ሲገፋበት የነበረውን ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነት (Historical Injustice) የሚደግም እና የሚያባብስ ነው። አሁን ባለው ሁኔታ፣ ፋኖ ይህንን ታሪካዊ ጠባሳ በመጠቀም ሙስሊሙን እንደ "ሌላ" (The Other) በመፈረጅ ጥቃት መፈጸሙ፣ ቡድኑ ከማንኛውም የሞራል እና የፖለቲካ መርህ የራቀ መሆኑን ያረጋግጣል። ይህ አይነቱ ጥቃት፣ በሃይማኖቶች መካከል ያለውን አብሮነት የሚሸረሽር እና ሀገራዊ አንድነትን የሚፈታተን ነው።

የፋኖ ቡድኖች "ትግሉ እኔ ብቻ ነኝ፣ ሌላው ባንዳ ነው" በሚል ጠባብ እና አግላይ አስተሳሰብ የሚመራ ነው። ይህ አስተሳሰብ የተለየ ሀሳብን እና ህልውናን ያለመቀበል አደገኛእና ፅንፈኛ አካሄድ ነው ። የጠራ ህዝባዊ እና ፖለቲካዊ ዓላማ (Ideology) የሌለው፣ በስነ-ምግባር የላሸቁ (Ethically Degraded) አባላትን የያዘው ይህ ቡድን፣ አማራ ክልልን የሰው ልጅ ነፍስ መጫወቻ እና የደም ምድር አድርጎታል። አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ፣ አማራ ክልል በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በፖለቲካዊ ዘርፎች እየሞተ ነው። ክልሉ በሚያመርተው፣ በሚማረው እና በሚነግደው የሰው ኃይል ላይ በራሱ ልጆች እየተፈጸመ ያለው ሁለንተናዊ ውድመት ክልሉን ወደ "ዳርቻነት" (Peripherality) እየገፋው ነው። አንድ አካባቢ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ አቅሙ ሲዳከም፣ ወደ ጠርዝ ወይም ዳርቻነት (Periphery) ይገፋል። አማራ ክልልም፣ የማያርስ፣ የማይነግድ፣ የማይማር እና የማያስተምር ህዝብ ይዞ ከቀጠለ፣ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ተፅዕኖ ፈጣሪነቱን አጥቶ፣ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ዳርቻ (Marginalized Periphery) መሆኑ የማይቀር ነው። ይህ ሂደት ደግሞ፣ "አንድን ክልል ገድሎ ተቋምን ለማዳን የሚደረግ ሴራ" በሚል ሊተነተን የሚችል፣ ውስብስብ እና አደገኛ የታሪክ ምዕራፍ ነው።

ዐብዱልጀሊል ሸኽ ዐሊ ካሳ/ Abduljelil Ali

በተመረዘ ምግብ - የ 7ቱ  ህይወታቸው አለፈምግቡ በማንና እንዴት ተመረዘ?    | በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ  በአብሮነት እራት ተመግበዉ በጠና ከታመሙ   ...
21/11/2025

በተመረዘ ምግብ - የ 7ቱ ህይወታቸው አለፈ

ምግቡ በማንና እንዴት ተመረዘ?

| በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በአብሮነት እራት ተመግበዉ በጠና ከታመሙ ስምንት የአንድ ቤተሰብ አባላት ዉስጥ አባወራዉ ከስድስት ልጆቹ ጋር ሰባት የአንድ ቤተሰብ አባላት ህይወታቸዉ ማለፉን ፖሊስ ገልጿል።

የክልሉ ፖሊስ የወንጀል መረጃ ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ተወካይ ምክትል ኮማንደር ያለዉ ተመስገን እንደገለፁት በወረዳዉ መሰረተ ወገራም ቀበሌ ዳሾ ቆቶ ተብሎ በሚጠራዉ መንደር ህዳር 6 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 1:00 ሰዓት ስምንቱ የቤተሰብ አባላት አብረዉ እራት ከተመገቡ በኋላ በድንገት መታመማቸዉ ተናግረዋል።

በአብሮነት እራት እንደተመገቡ ብዙም ሳይቆዩ ከፍተኛ ለሆነ ህመም መዳረጋቸዉን መረጃ የደረሳቸዉ የአካባቢዉ ነዋሪዎች የተጎጂዎችን ህይወት ለማትረፍ ተረባርበዉ ወደ ሆስፒታል ማድረሳቸዉ ነዉ የተነገረዉ።

ቢሆንም ከተጎዱ የቤተሰቡ አባላት የ5 ዓመቱ መንግስቱ ኃይሌ ፣የ7 ዓመቱ መክብነ ኃይሌ እና የ17 ዓመቱ ተክሉ ኃይሌ የተባሉት ሶስቱ ወንድማማቾች በዕለቱ ሆስፒታል እንደደረሱ ህይወታቸዉ ማለፉን ነዉ የተገለፀዉ።

የተቀሩ ተጎጂዎችን ህይወት በህክምና ለማትረፍ ሀኪሞች ያልተቋረጠ ጥረት ቢያደርጉም የ14 ዓመቷ መቅደስ ኃይሌ እና የ15 ዓመቱ ገብሬ ኃይሌ የሁለቱ እህትና ወንድም ህይወት ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 11:00 ሰዓት ሲያልፍ የሟቾች ቁጥር ወደ አምስት አሻቀበ።

ከተቀሩት ተጎጂዎች ደግሞ የ1ዓመት ከ7 ወሩ ህፃን ሲሳይ ኃይሌ ህዳር 9 ቀን 2018 ዓ.ም ጥዋት 2:00 ሰዓት ላይ ህይወቱ ሲያልፍ የስድስቱ ሟች ልጆች አባት የሆነዉ አቶ ኃይሌ አበራ ህዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም ለሊት በሰመመን ዉስጥ ሆኖ ከእንቅልፉ ሳይነቃ ህልፈቱ እዉን ሆኖ ልብ ሰባሪና አሳዛኝ የሆነ ዜና ተደመጠ።

የባለቤቷንና የስድስት ልጆችዋን ህልፈት ለማወቅ ያልታደለችዉ ወይዘሮ ዳመነች ደንበል በሚኒሊክ ሆስፒታል በከፍተኛ የጥንቃቄ ክፍል ዉስጥ ሆና በህክምና እየተረዳች በህወት መኖሯን ነዉ ፖሊስ የተገለፀዉ።

ተጎጂዋ ቤተሰቡን በጅምላ ወደ ሞት ያወረደዉን ጉዳይ ልትተርክ በህይወት ትተርፍ ይሆን?ወይስ እሷም የባለቤቷና የልጆችዋ እጣ ገጥሟት ከቤተሰቡ መሀል አንድም ለወሬ ነጋሪ ሳይተርፍ በጅምላ እቺን አለም የመሰናበታቸዉ አሳዛኝ ዜና ይደመጣል? የሚለዉን ለመገመት ይከብዳል።

ፖሊስ ተጎጂዎች የተመገቡት ምግብ የተመረዘዉ በማንና እንዴት?የሚለዉን እዉነታ ለማረጋገጥና የተፈፀመዉን ድርጊት አጣርቶ እዉነታዉ ለማረጋገጥ ከምስራቅ ጉራጌ ዞን እና ከመስቃን ወረዳ የተወጣጣ የምርመራ አጣሪ ግብረ ኃይል አዋቅሮ ምርመራ የማጣራቱን ስራ መጀመሩን የተናገሩት ኮማንደር ያለዉ ተመስገን የምርመራ ግብረ ኃይሉ በድርጊቱ የሌሎች እጅ ሊኖር ይችላል በሚል ጥርጣሬ አስር ሰዎችን በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልፀዋል።

ተጎጂዎች በዳግማዊ ምንሊክ ሆስፒታል ህክምና ተከታትለዋል ያለዉ ፖሊስ የሟቾች የአስክሬን ምርመራ ዉጤት እየተጠበቀ መሆኑንና ስለጉዳዩ የተሻለ ፍንጭ ሊሰጥ እንደሚችል መረጃ ሊገኝ እንደሚችል ይገመታል።

የክልሉ ፖሊስ ሚድያ ክፍል ይህ ዜና በሚድያ ይፋ እስካደረገበት ሰዓት ድረስ ከስምንቱ ተጎጂዎች ዉስጥ አንዷ የሆነችዉ የቤቱ እማወራ በአዲስ አበባ ምንሊክ ሆስፒታል በህክምና እየተረዳች መሆኑን አረጋግጧል።

በተለያየ ጊዜ እቺን አለም የተቀላቀሉት ከ46 ዓመቱ አባት እስከ 1 ዓመት አ7 ወር እድሜ ያለዉ ህፃን እቺን አለም በተመሳሳይ ሰአት ለመሰናበት የተገደዱበት ተግባር የተለየ ግኝት ካለ መረጃዉን ለህዝብ ይፋ የምናደርግ ይሆናል።

ኮማንደር ታጁ ነጋሽ -ማ.ኢ.ፖ.ኮ

አዲሱ የኢትዮጵያችን ካርታ ይሆናል ተብሎ በብዙሃን ዘንድ የሚጠበቀው ካርታ ይህ ነው።ኢትዮጵያ ታሸንፋለች!!
12/11/2025

አዲሱ የኢትዮጵያችን ካርታ ይሆናል ተብሎ በብዙሃን ዘንድ የሚጠበቀው ካርታ ይህ ነው።

ኢትዮጵያ ታሸንፋለች!!

 "አገልጋይነት ክብር መሆኑን በተጻራሪው ደግሞ መሾም አድራጊ ፈጣሪነት አለመሆኑን መገንዘብ ይፈልጋል::"( )
31/10/2025



"አገልጋይነት ክብር መሆኑን በተጻራሪው ደግሞ መሾም አድራጊ ፈጣሪነት አለመሆኑን መገንዘብ ይፈልጋል::"

( )

ትችትና ተቃውሞ፡ የቃል ብልጠት ወይስ የሃሳብ ጥራት?(በአቡ ኸጣብ)​የመንቀፍ ቀላልነት​ትችትና ተቃውሞ ማንም ሰው ሊያደርገው የሚችል፣ ልዩ የሆነ ከፍተኛ ክህሎትም ሆነ ውስብስብ እውቀት የማይ...
31/10/2025

ትችትና ተቃውሞ፡ የቃል ብልጠት ወይስ የሃሳብ ጥራት?

(በአቡ ኸጣብ)

​የመንቀፍ ቀላልነት

​ትችትና ተቃውሞ ማንም ሰው ሊያደርገው የሚችል፣ ልዩ የሆነ ከፍተኛ ክህሎትም ሆነ ውስብስብ እውቀት የማይጠይቅ ተግባር ነው። አንድን ነገር መውደድ ወይም አለመውደድ ስሜት ሲሆን፣ ይህን ስሜት በቃል መግለጽ ደግሞ የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ መብት ነው።

​ክህሎት አልባነት: ለማንኛውም ሥራ ወይም ፕሮጀክት "ይሄ አይሠራም" ወይም "ስህተት ነው" ለማለት የሥራውን ጥልቀት ማወቅ አይጠበቅብንም። ለምሳሌ፣ የቤተ መንግሥት አሠራርን ሳያውቁ "መንግሥት መሥራት አልቻለም" ማለት ቀላል ነው።

​ስሜታዊ ምላሽ: ብዙ ጊዜ ትችት የሚመነጨው ከጥልቅ ትንተና ይልቅ ከቅሬታ፣ ከጥላቻ ወይም ከፖለቲካዊ አቋም ነው። ስሜት ደግሞ የሰውን ልጅ የመተንተን ችሎታ ያደበዝዛል።

​የኃላፊነት ክፍተት: ተቺው የተሻለ አማራጭ የማቅረብ ወይም የተነቀፈውን ነገር ውጤት የመሸከም ኃላፊነት ስለሌለበት፣ በነፃነት (እና አንዳንድ ጊዜ በቸልተኝነት) ይተቻል።

​ ገንቢ ትችት የዲሞክራሲ መሠረት እና የእድገት ምንጭ ነው። ነገር ግን፣ በትችትና ማንኳሰስ (ማጣጣል) መካከል ትልቅ የሥነ ምግባር እና የሃሳብ ጥራት ልዩነት አለ።

​❌ ማንኳሰስ (አፍራሽ ትችት)
​መንግሥትን ወይም ማንኛውንም ተቋም የሚቃወሙ አንዳንድ አካላት የሚያደርጉት ትልቁ ስህተት፣ የሚሠራውን ነገር ሁሉ ማንኳሰስና ማጣጣል ነው።

​ጥቅምን መካድ: ማንኳሰስ ማለት አንድ አካል ያከናወናቸው በጎ ተግባራት እና ያስመዘገባቸው አወንታዊ ለውጦች ቢኖሩም እንኳ፣ እነዚያን ሙሉ በሙሉ በመካድና በማንቋሸሽ ሁሉንም ነገር ጥቁር አድርጎ ማቅረብ ነው።

​የመፍትሄ እጦት: ዓላማው የተሻለ መፍትሔ ማምጣት ሳይሆን፣ ሥልጣን ላይ ያለውን አካል ማውረድ ብቻ ሲሆን፣ ትችቱ ወደ ባዶ ስድብ እና ፕሮፓጋንዳ ይቀየራል።

​ቅንነት ማጣት: እንዲህ ያለው ትችት የሚነሳው ከሀገር ፍቅር ወይም ከሕዝብ ጥቅም ይልቅ ከ ጥላቻ ወይም ከስልጣን ጥማት ነው። ይህ ደግሞ በሕብረተሰብ ዘንድ እርስ በርስ ያለውን መተማመን ያሳጣል።

​ትችት የህዝብ መብት ሲሆን፣ ማጣጣል ደግሞ የግብረገብነት ጉድለት ነው። ትችት የመሻሻል መንገድ ሲሆን፣ ማንኳሰስ ግን የጥላቻና የፍላጎት መንገድ ነው።
​ማንኛውም ሰው መንግሥትንም ሆነ ሌላን አካል ሲተች፣ የሚናገረው ነገር በቀላሉ ከሚገኝ የቃላት ብልጠት ይልቅ በ ጥልቅ እውቀት፣ በምክንያት እና በሃላፊነት ላይ የተመሠረተ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት።
የተሻለች አገር ለመፍጠር መትጋት ያለአግባብ መውቀስ ሳይሆን፣ ሥራን የሚገነባና የሚያበረታታ ገንቢ ትችት ማቅረብን ይጠይቃል።

Abu Khattab

"የ30 ቢሊዮን ዶላር ፕሮጀክቶች መጀመር ለኢትዮጵያ ጨዋታ ቀያሪ ነው፤ የልጆቻችንንም ዕድል የሚወስኑ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)EBC
30/10/2025

"የ30 ቢሊዮን ዶላር ፕሮጀክቶች መጀመር ለኢትዮጵያ ጨዋታ ቀያሪ ነው፤ የልጆቻችንንም ዕድል የሚወስኑ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

EBC

ኢትዮጵያ እና አሰብ ወደብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፦  | " በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ሰላም ሲፈጠር መጀመሪያ እኔ ወደ አስመራ ተጉዤ በኃላ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ወደ...
28/10/2025

ኢትዮጵያ እና አሰብ ወደብ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ፦

| " በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ሰላም ሲፈጠር መጀመሪያ እኔ ወደ አስመራ ተጉዤ በኃላ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ የመጀመሪያውን መድረክ ያደረግነው ሚሊኒየም አዳራሽ ነው። ብዙ ህዝብ ባለበት በቀጥታ ስርጭት። ካልሰማችሁ አሁን ዩትዩብ ላይ ግቡና ስሙት። የመጀመሪያው ስብሰባ #አሰብ ነው የሚለው እሳቸው ባሉበት። ለህዝብ በሚገባው ልክ።

ኤርትራ ስመላለስ አስመራን ካየው በኋላ ከክቡር ፕሬዚዳንቱ ጋራ አሰብ መሄድ እፈልጋለሁ ብዬ አሰብ ሄጄ ባህሩ ጋር ቆመን ያወራነው ነገር ምንድነው ስለ ወደብ ነው። ተማሳችሁ እዩ። የት ? ኤርትራ ምድር ውስጥ።

የመደመር ትውልድ መፅሀፍ ውስጥ በግልጽ ጂዮ ፖለቲክስን አስፍሬ የአሰብ ጉዳይን አስቀምጬ ለኤርትራ ባለስልጣናት በስጦታ ልኬላቸዋለሁ ሚስጥር አይደለም። ያቁታል። ከሁሉም ሌኬላቸዋለሁ።

የዛሬ 6 አመት 5 አመት ባህር ኃይል አቋቁመናል እና እዚህ ውስጥ (የብርጭቆ ውሃ ውስጥ) ልንዋኝ ነው ባህር ኃይል ያቋቋምነው ? ለምን ሰዎች ይሄን ደምረው ማየት እንደሚቸገሩ አይገበኝም።

ኢትዮጵያ ቀይ ባህር እንደሚያስፈልጋት ከለውጡ በፊት እናምን ነበር እንናገር ነበር ያኔ መደመጥ አንችልም ከጀመርንበት ቀን አስቶ ንግግሩ አለ። ያ ንግግር ግን ሰላማዊ መሆን አለበት።

የተከበሩ (ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔን ነው) እንዳነሱት ከኤርትራ መንግሥት ጋር ተስማምተን ከዚህ ወደ አሰብ የሚወስደውን መንገድ ጠግነናል እኮ እኛ። እንከፍታለን ብለን ጠግነናል ከጠገንን በኃላ ' ችግር አለብን ፖርቱ ተዳክሟል ' አሉን። አንዳንድ ሰው ፀቡ በአንድ ምሽት የመጣ ይመስለዋል እንደዛ አይደለም ታሪኩ ስለማንናገር ነው።

ወደ አሰብ መንገድ ጠግነን ከጨረስን በኃላ ' ፖርቱ ችግር አለበት ' ሲሉ የጋራ ወዳጅ የሆነ ሀገር ለምንነን ጀነሬተር እና ክሬን በእርዳታ ወደ ኤርትራ እንዲመጣ አድርገን አሰብ ወደብ ሲደርስ የኤርትራ መንግስት ' አልፈልግም ' ብሎ መለሰ። ያኔ ነው የገባን ይሄ ነገር ተስፋ የለውም የሚለው።

መንገድ ጠገንን፣ ለምንነን ብናመጣም ፍላጎት አልነበረም። ወደ ኤርትራ ልክ እንደ ሱዳን ፣ ልክ እንደ ጅቡቲ በኛ ወጪ የኤሌክትሪክ ኃይል ቀጥለን ኃይል እንስጣችሁ ጀነሬተር አትጠቀሙ ብንልም ' ቆይ እናስብበት ' ነው የተባለው።

ኢትዮጵያ ውስጥ የቤት ችግር አለ ፤ 1.5 ቤት እንገነባለም ብለናል። አሰብ ስሄድ ቤት አለ በር አለ ሰው የለም፤ ይሄ እውነተኛ ታሪክ ነው። ይሄን ከተማ መልሰን ህይወት እንስጠው ስራ ነው ህይወት የሚያመጣለት የሚል በየጊዜው ተነጋግረናል። ሁሉም የሚሄድ ልዑክ ተነጋግሮበታል።

በኤርትራ በኩል በግልጽ ባላወቅነው መንገድ ለዚያ ጉዳይ ምላሽ ለመስጠት ብዙ ዝግጁ አልነበሩም። እሱ ቀርቶ የከፈትናቸውን ድንበሮች በሰሜን በኩል ወዲያው ወዲያው ተዘጉ። የተዘጉት አሁን አይደለም እናተ ችግር እንዳለ ሳትሰሙ ነው የተዘጉት።

እና የኤርትራ ህዝብ አሁንም ወንድም ህዝብ ነው ፤ ምስኪን ህዝብ ነው ፤ ሀገሩን ለቆ እየተሰደደ ያለ ህዝብ ነው ከዚህ ህዝብ ጋር መስራት መተባበር ፍላጎታችን ነው በፍጹም የውጊያ መሻት የለንም። በህጋዊ መንገድ እና በንግግር ሊፈታ ይችላል።

ለብዙ ሀገራት በተናጠል ተናግሪያለሁ። ምክር ቤት መስማት ከፈለገ ግን ፦
- ለአሜሪካ
- ለቻይና
- ለራሽያ
- ለአውሮፓ
- ለአፍሪካ አሁን በተከበረው ምክር ቤት ፊት መግለጽ የምፈልገው ነገር የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ተጠቃሚነት ጉዳይ አይቀሬ ስለሆነ ቅድሚያ የምንሰጠው ሰላምና ንግግር ስለሆነ እባካችሁ ሸምግሉን እና መፍትሄ አምጡልን። ይኸው ጥያቄያችን።

' አዎ እንሸመግልላችኋለን ፣ ሰላም ያስፈልጋል ' እያሉ ማዘናጋት ከሆነ ግን ብዙ የሚሄድ አይመስለኝም ጉዳዩ። ይሄ እኔ ሰለፈለኩ እናተ ስለፈለጋችሁ አይደለም በተፈጥሮ አይሆንም ነገርየው። በአንድ ቀን እንመልሰውም በአንድ ቀን አላጣነውም። የተፈጥሮ ሂደቱን ተከትሎ ይሄዳል።

ከጌጡ ተመስገን ፔጅ የተወሰደ

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when meskan media network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to meskan media network:

Share