meskan media network

meskan media network meskan media network is an online media, focuses on social matters. This is official page of meskan media network

"ኢትዮጵያ ወደብ ያጣችበት መንገድ በጣም ያስቆጨኛል" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)  | ኢትዮጵያ ባለፉት 30 ዓመታት ወደብ አልባ ሆና የቆየችበት መንገድ በጣም የሚያስቆጭ እና...
08/06/2025

"ኢትዮጵያ ወደብ ያጣችበት መንገድ በጣም ያስቆጨኛል" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

| ኢትዮጵያ ባለፉት 30 ዓመታት ወደብ አልባ ሆና የቆየችበት መንገድ በጣም የሚያስቆጭ እና እርሳቸውም የሚቆጩበት እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናገረዋል፡፡

"ያስቆጨኛል ስል ብዙዎች ዘመን አመጣሽ ይመስላቸዋል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ "ይህ ጠቅላይ ሚኒስትር ስሆን የመጣ ሳይሆን ከዛሬ አሥራ አምስትም፣ አሥርም ዓመት በፊት አቋሜ እንደነበረ በቪዲዮ ማየት ይቻላል" ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ወደብ በማጣቷ ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባት ጠቅሰው፣ ኢትዮጵያ ሌላውን ሳትጎዳ መጠቀም እና ጉዳቷን መቀነስ ትችል እንደነበር ተናግረዋል፡፡

የተጎዳ እና የተሰበረ ሀገር በዘላቂነት የሰከነ ሰላም ያመጣል ብዬ አላስብም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ ይህ በዓለም ወደብ አልባ ሀገራት ታሪክ የሌለ ግፍ የሆነ አካሄድ በንግግር መፈታት አለበት ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል፡፡

"ኢትዮጵያውያን የራሳችንን የምናራክስበት ልክ ያሳዝነኛል፤ ብዙ ሀገራትን የማየት ዕድል አጋጥሞኛል፤ ኢትዮጵያ የምትራከስ ሀገር አይደለችም፤ ኢትዮጵያውያን የሚራከሱ አይደሉም፤ ኢትዮጵያውያን የራሳችንን አርክሰን የሌላውን አግዝፈን የምናይበት ልክ ያሳዝነኛል" በማለት ስለራሳችን ያለን ግምት ብዙ ነገር እንዳሳጣን አንስተዋል፡፡

በዚህም ምክንያት በሀገሩ ታሪክ የሚኮራ፣ ተነጋግሮ የሚግባባ እና የራሱን የማያራክስ ትውልድ እንዲፈጠር አብዝቼ እየሠራሁ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ፡፡

ጤነኛ እና በእድሜ ሽማግሌ ያልሆነ/ያልሆነች ወይም ከባድ የማይድን በሽታ የሌለው/የሌላት አቅሙ/አቅማ ላይ ተመርኩዞ/ዛ የማንም ሰው ሸክም ሳይሆን/ሳትሆን መኖር ይችላል/ትችላለች::የማንም ሸክ...
04/06/2025

ጤነኛ እና በእድሜ ሽማግሌ ያልሆነ/ያልሆነች ወይም ከባድ የማይድን በሽታ የሌለው/የሌላት አቅሙ/አቅማ ላይ ተመርኩዞ/ዛ የማንም ሰው ሸክም ሳይሆን/ሳትሆን መኖር ይችላል/ትችላለች::

የማንም ሸክም መሆን የለብንም::

ልመና መልኩን ቀይሮ ሲመጣ ማበረታታት የለብንም። ዋና ስራ ካለን እና ገቢው በቂ ካልሆነ እጃችን ላይ ምን ልንሸጠው የምንለው ክህሎት አለን? ሁሉም ዩንቨርስቲ ገብቶ መማር የለበትም ጥሩ ኑሮ ለመኖር

Based on my observation wanted to share my lived experience! I hope you will get something out of this post!

እኔ ስራ የጀመርኩት ልጅ እያለሁ ማትሪክን ስወድቅ ቁጭ ከምል ገጠርም ቢሆን እሄዳለሁ ብዬ የመጀመርያ ትምህርት ቤት አስተማሪ በመህን ነው። በዛን ወቅት የነበረኝ የትምህርት ውጤት ዩንቨርስቲ ስላላስገባኝ
እናም ከማገኘው ይ305 ብር ደሞዝ እቆጥብ ነበር።

እናም መፅሃፍቶችን ገዝቼ ስራ ከጀመርኩበት ወር አንስቶ በትርፍ ሰዓቴ ማትሪክን በፕራይቬት ለመፈተን አጠና ነበር። በዚያንወቅት አብረውኝ አስተማሪ የነበሩት ብዙዎቹ ይስቁብኝ ነበር።

እግዚአብሄርም ረድቶኝ ዩኒቨርስቲ ገባሁ። እየሰራሁ ስማር ስለነበር የማንም ሸክም አልነበርኩም። ሁለተኛ ድግሪዬን ልማር ስራ ሳቋርጥ ሶስት አመት በገጠር ልማት እና የሰባት አመታት የከተማ ልማት ላይ የስራ ልምድ ነበረኝ።

ሶስተኛ ድግሪዬን ተምሬ ስመለስ በልምድ በስራ ቦታ ያወቅሁትን ሳይንሳዊ ለማድረግ አልከበደኝም። ምርምርም መፃፍ እና በተለየ መልክ ፖሊሲ መተንተን ጥሩ ሆነልኝ።

ከ 19 አመቴ ጀምሮ እስከ 38 አመቴ ስማር (TTI, BA,MA, PhD) እናም ስሰራ ቆየሁ። አሁንም እየሰራሁ ነው። በአቅሜ እኖርም ነበር። ሰርግ መደገሻ ብዙ ብር ስላልነበረን ድግስ አልደገስንም። ሰርጋችን ፐብሊክ ቦታ ነበር እናም there were only snacks and drinks😀😀

ለምንድን ነው ይህን መፃፍ ያስገደደኝ??

አሁን አሁን መለመን ሌላ መልክ ይዞ መታል። ሰዎች ከገቢያቸው በላይ ስለሚያወጡ ብክነት እና እዳ ላይ የተመሰረተ ኑሮ ተለምዳል። አንዳንዱ ከሰው ለምኖ እና ተበድሮ ሊዝናና ሌላ ሃገር ይሄዳል። ይህ በእውነት ሁሌ ይገርመኛል።

ልጄን ልድር ነውና ገንዘብ ስለማይበቃኝ እርዱኝ የሚል አባት የባንክ ቁጥሩን ፅፎ በምንሰራበት ብታ ሲጠይቅ አይቻለሁ።

ኑሮ ከባድ ነውና ደምዜ አልበቃኝም እና ....የመሳሰሉ ጥያቄዎች አያለሁ ይደርሱኛልም። እናም ልምድ ለማካፈል ነው የወደድኩት ሰዉ እንዲጠቀምበት።

ያኔ የእኔ ደሞዝ በቂ አልነበረም ስለዚህ ወጭዎቼን ከገንዘቤ ጋር አመዛዝኜ የምፈልገውን ሳይሆን የሚያስፈልገኝን ብቻ ነበር የምገዛው።

ጤነኛ የአበላል ስርዓት ዘርግቼ ነበር። እንደውም ከዛችው ደሞዝ ቤተሰብ እረዳ ነበር።

ውጭ ለትምህርት በነበርኩበት ግዜ ገቢዬ ስለማይበቃኝ ለብቻዬ ቤት አልንተከራየሁም። ቤት ተከራይተው ክፍላቸውን ከሚያከራዩ ጋር የክፍሉን ከፍዬ ነበር የምማረው። ምክንያቱም ኪችን የጋራ ስለሆነ ለጥናት ባይመችም ላይብረሪም ነበር የማጠናው።

እና ታድያ የእኛ አገር ከተማዎች ባለ ሁለት ሶስት ክፍል አፓርታማ ስላላቸው ደሞዛቸው የማይበቃቸው በጋራ ተከራይተው ኪችን እና ሳሎን በጋራ እየተጠቀሙ የኪራይ ወጭያቸውን ለምን እንደማይቀንሱ አይገባኝም

ብዙ ሰው ውጭ ይመገባል ገቢው ትንሽ ከሆነ ቤት መስራት ብዙ ስለሚያተርፍ ለዚያውም ጤነኛ ስለሆነ ውጭ መብላትን ለምን አየተውም?? በትንሹ 600 መቶ ብር የሚያስከፍል ጥብስ ውጭ ከመብላት በ500 ብር ግማሽ ኪሎ ስጋ በመግዛት ከአትክልት እና ሽሮ ጋር ለ 4 ግዜ የሚሆን ምግብ መስራት ይቻላል።

ደሞ ወንዶች ማብሰል ስለማንችል ነው እንዳትሉኝ😂😂 በአለም ላይ የታወቁ ሼፎች (ምግብ አብሳዮች ) ወንድች ናቸው። እኛም ሃገር በጣም ውዱ ሬስቶራንት ባለቤት ወንድ ነው።

ከዩቱይብ ላይ እያያችሁ ራሳችሁን ምግብ ማብሰል አስተምሩ! ራሳችሁን ቻሉ😀😀 ገንዘባችሁን ቆጥቡ

ነውራችን የህይወት ክህሎት ስልጠና በመውሰድ እናም የMindSet-ማይንድሴት ለውጥ በማምጣት ሃላፊነትን በመውሰድ መቀየር እንችላለን።

ልመና ሰርቶ መኖር ለሚችል ሰው ነውር ነው። ሰጭዎችም ችግሩን እንዲባባስ አትተባበሩ!!

ተጻፈ
በዶ/ር መሰረት ካሳሁን

`               "ጌጌዮ ~~~`````````````````~~~~~~~ጌጌዮ" መነሻ ቃሉ "የገግ፣የገጉ፣የገገና፣ የገገናሙ ፣የገግሙወኹ፣ የገግሙዌት" ሌላም ሌላም ተጨማሪ ሰፋ ያለ የእኛ...
27/05/2025

` "ጌጌዮ
~~~`````````````````~~~~~~~
ጌጌዮ" መነሻ ቃሉ "የገግ፣የገጉ፣የገገና፣ የገገናሙ ፣የገግሙወኹ፣ የገግሙዌት" ሌላም ሌላም ተጨማሪ ሰፋ ያለ የእኛነት ትርጓሜ የሚሰጥ ሲሆን በመስቃን አጎራባች ህዝቦች የጋራ ወይም ነጠላ ትርጓሜ እየተሰጠው የሚጠቀሙበት የቀበሊኛ ወይም የመስቃንኛ ቃል ነው።

~~በቀደምይ አባቶች ታሪክ ሴት ልጆቻቸው ሲድሩ ወይም አዲስ ጎጆ ከባል ወገን ትዳር ስትመሰርት በባዶ አትሸኝም ቢያንሽ በትንሹ አንድ ወይንም ጥጃ ወይንም ጊደር ይሰጥ ነበር።

~ለአዲስ ተጋቢ ሙሽሮች ትዳር ሲመሰርቱ የሚሰጥ ቁሳቁስ የቤት ግብር ወይም የቃቃት ግብር በመባል ሲታወቅ የቁም ከብት ወይም ልዩ ልዩ የቤት እንስሳ ሲሆን ጌጌዮ በመባል ይጠራል።

~~ጌጌዮ ትዳር እንዲፀና ለሴት ሙሽራ በቤተሰቦችዋ መልካም ፈቃድ የሚበረከት ለአዲስ ጎጆ መውጫ የቤት እንስሳት እንዲያረቡ የሚሰጥ ምርጡ የመስቃን ማህበረሰብ ባህል ነው።

~~ይህ መልካም የመስቃን ማህበረሰብ ድንቅ እሴት አዲስ ትዳር በአቅም እጦት እንዳይፈርስ የሚረዳ በወጣትነት ጋብቻ የሚመሰርቱ ይህን የጌጌዮ ስጦታ የኢኮኖሚ መነሻ ይሆናቸው ዘንድ ታስቦ የተቀመረ የጥንት የመስቃን አባቶች የተደነገገ ድንቅ እሴት ነው።

~~በመስቃን ማህበረሰብ ዘንድ ጋብቻ ክቡር ነው። በጣም ከፍ ያለ ምክኒያት ካላጋጠመ በስተቀር በኢኮኖሚ እጥረት ትዳር አይፈርም።

~~በመስቃን ለአንዲት ሙሽራ በሆነ ምክኒያት ጌጌዮ ወይም የጎጆ መውጫ ስጥታ በቤተሰብ ዘንድ ድንገት አዲስ ትዳር ስትመሰርት ይህ የጌጌዮ ወይም ለርቢ የሚሆን የቤት እንስሳት ስጦታ ካልተበረከተ አዲስ ጎጆ ወጪ ሙሽሮቹ እራሳቸው እንዲችሉ (ወኪያ) 1/2 ትርፍ የሚያገኙበት የቤት እንስሳትም አቅም ባላቸው በዘመድ ይሁን በጎረቤት ተቀብለው የሚያረቡበትም ነባር ዘዴም አለ።

~~ጌጌዮ በመስቃን ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች አሉት ከነዚም ዋነኞቹ እራስን ለማስቻል ቀዳሚው ዘዴ ቢሆንም ለአዲስ ጎጆ ወጪ ሙሽሮት ቢዚ ሆነው ትዳርን እንዲላመዱ ይረዳል።

ጌጌዮ በሴት ሙሽራ ቤተሰብ ወደ ወንዱ ቤተሰብ ሲሰጥ ጋብቻው እንዲፀና እንደ "ጉዳ" መተሳሰርም ይቆጠራል።

የጌጌዮ አሰጣጥ ሃይማኖትና ዘርን የማይገድበው በመልካም ፈቃድ የሚደረግ ምርጡ የመስቃን ባሕል ነው።

ያለውን ድንቅ እሴት ለቀጣዩ ትውልድ ለማሳወቅ ጥረት የማያደርግ ነገውን ምንም እንዳይኖረው ከማድረግ አይተናነስም።

ብዠ ይቡሪዬ ከሞ የምሽም የዛይ።

የመስቃን ማህበረሰብ አቃፊ እንግዳ ተቀባይ  ያለውን አካፍሎ አክብሮ እና ተከብሮ የሚኖር ሃይማኖተኛ የሆነ ኩሩ ማህበረሰብ ነው።~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~የመስቃን ማ...
23/05/2025

የመስቃን ማህበረሰብ አቃፊ እንግዳ ተቀባይ ያለውን አካፍሎ አክብሮ እና ተከብሮ የሚኖር ሃይማኖተኛ የሆነ ኩሩ ማህበረሰብ ነው።
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
የመስቃን ማህበረሰብ አቃፊ እንግዳ ተቀባይ ያለውን አካፍሎ የሚኖር ሃይማኖተኛ የሆነ ኩሩ ማህበረሰብ ነው።

በመስቃን ግጭት አፋታት ታሪክ እድሜ ጠገቡ ከ16ኛው ምዕተ አመት ጀምሮ የአጎራባች ህዝቦችን ግጭት እየፈታ እያስታረቀ፣ እየዳኘ እስካሁን በስራ ላይ ያለ የፈራገዘኘ የዳኝነት ስርአት ቢኖርም በመስቃን በ63 ዋና ዋና ጎሳዎች በእያንዳንዳቸው በተዋረድ በመንደር፣ በሰፈር፣ በጎጥ፣ በቀበሌ እና በሞጣ እንዲሁም በስሙት ሰንጋ የሚሰየሙ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ አስታራቂ ሽማግሌ (የገኝ ባሊቅ) በሚል በቡድን በጎሳ በታላቅ ልጆች (በበኽር ቤት) ይሰየማሉ።

በጣም አስገራሚው ታሪክ በጥንት ዘመን ግጭት ፈቺ አስታራቂ ተብለው በየ ጎሳው የሚመረጡ አስታራቂ ሽማግሌዎች
ሀ// ነብ"ሠ ያልሆኑ በታሪካዊ ሲወርድ ሲዋረድ በመጣ ባህላዊ ምግብ የሚመገቡ እንደነበር ታሪክ አዋቂ አባቶች ዘንድ ይነገራል።

ለ// የሚበሉበት እና የሚጠጡበት እቃ እንኳ ከብረት ነክ የተሰሩ መጠጫ እቃዎች ለምሳሌ ኒኬል ጣሳ ተብሎ ከሚጠራው እቃ ለመጠጫነት እንደማይጠቀሙ እንደሆነ በጥንት ታሪክ አዋቂ አባቶች ይነገራል።

ሐ// በአለባበስ ደረጃ ብረት ነክ የሌለው ወይም ያልተቀላቀለበት ልብስ ይለብሱ እንደነበር እና ለድጋፍ የሚይዙት ምርኩዝ (ሲካ) እንኳን ቢሆን የእንጨት መሆን እንዳለበት በእድሜ ጠገብ አባቶች ይነገራል።

ማለትም ምንም የብረት ዘር ያልነካው እንደሆነ በታሪክ አዋቂ አያቶች በአፅንኦት ይነገራል።

መ// በጥንት ዘመን ለችግር ፈቺ አስታራቂ ተብለው የሚመረጡ አባቶች የሚኖሩበት ቤት እንኳ ብረት ነክ ያልነካው ለምሳሌ በዘመናዊው የቆርቆሮ ቤት መሆን እንደሌለበት ይነገራል።

~በነዚህም በ63 የመስቃን ዋና ዋና ጎሳዎች በተዋረድ በአሸማጋይነት እርከን የሚሰየሙት ችግር ፈቺ ተብለው የሚሰየሙት ግጭት ፈቺ አስታራቂ ሽማግሎዎች ሲሰየሙ የሚያሟሉት መስፈት

1// የሚሰየመው ሽማግሌ ከየትኛው ጎሳ መሆኑ ሊታወቅና የሁሉም ጎሳ በእኩል የሚያከብር እና የሚወድ መሆኑ ይረጋገጣል ።

2// ጤነኛኛ በአካባቢው የብዙ ቋንቋ የመናገር ችሎታ ያለውና ከዘመናዊ ፖለቲካ ንኪኪነት የሌለው መሆን ይጠበቅበታል።

3// የማይሰርቅ፣ የማይዋሽ የማያጭበረብርና ለሃይማኖቱ ተገዥ የሆነ ፈጣሪውን የሚፈራ ቂመኛ ያልሆነ መሆን ይጠበቅበታል።

4// ያላገባ ከሆነ በቤተሰቡ ዘንድ ታማኝ የሆነ በእናት በአባት ወይም በቅርብ በሃይማኖተኛ ቤተሰብ በስርአት ያደገ መሆኑ ይረጋገጣል።

5// ያገባ እና ባለትዳር የሆነ እንደሆን ከመሰረተው ትዳሩን በስርአት የሚመራ እና ጠንካራ ራዕይ ኖሮት ቤቱን የሚንከባከብ መሆኑ ይረጋገጣል።

6// ከጎረቤት እና ከአካባቢው ማህበረሰብ በማንኛውም ሁኔታ ሰላማዊ ትሁትና ጎረቤቱን የሚጠብቅ እና አክባሪ መሆኑ ይረጋገጣል።

7// በጋብቻ ተሳስሮ የሚያቅ ከሆነ በተደጋጋሚ ትዳር መስርቶ ያልፈታ መሆኑ ይረጋገጣል።

8// በዘመኑ በጥቁር ዳኛ ከግለሰቦች ጋር የረጅም ጊዜ የክስ ሂደት ያላስተናገደ ወይም በምንም መልኩ ሃሰት ያልመሰከረ እውነተኛ ሰው መሆኑ ይረጋገጣል።

9// እድሜው በጣም ለጋ ወጣት ባይሆን ይመረጣል፣ ለጋ ወጣት የሆነ እንደሆን ግልፍተኛ ያልሆነ ትሁት፣ ሰው አክባሪ በመልካም በሃይማኖተኛ ቤተሰብ ያደገ መሆኑ ይረጋገጣል።

11// የምንም ነገር ሱሰኛ ያልሆነ አቋሙ የሰውኛ ባህሪ ያለው በተለያዩ ጊዜ እና ሰአት አቋሙ የማይቀያይር መሆኑ ይረጋገጣል።

12// ሌባ ፣ነጣቂ፣ ቀማኛ፣ በራሱ ስራ የሚተዳደር በተለያዩ ጊዜያት በሰዎች ብድር እየወሰደ ብድር ያልመለሰ ወይም የሰው ገንዘብ እና የሰው እንባ ያለበት ሆኖ ከሰዎች ጋር ያልተጋጨ መሆኑ ይረጋገጣል።

13// የጀርባ ታሪኩ በመጥፎ የማይጠረጠር ዝሙትኛ ያልሆነ ነውርን እንደ ነውር የሚጠየፍ የማህበረሰቡን እሴት እና ታሪክ ከሚያጎድፉ ነገሮች የራቀ መሆኑ ይረጋገጣል።

14// ሮስ ወይም የሮስ ትኸ ባሪያ ወይም የባሪያ ልጅ ያልሆነ ማንኛውም እውነተኛ ፍርድ ያለምንም አድሎ የሁለት ወይም የሶስት የአራት ሰዎች ጉዳይ ሰምቶ እና ተረድቶ በእውነት ያለምንም ተፅዕኖ እና ፍርሃት መፍረድ የሚችል መሆኑ ይረጋገጣል።
ምክኒያቱም በጥንት ባህል ባሪያ ጌታውን አይዳኝም።

15// ከራሱ ጋር ያልተጣላ ፍፁም ጤነኛ የሆነ ነገሮችን የማያወሳስብ አተም ትክልል አንቺም ትክክል የማይል ወላዋይ አለመሆኑ ይረጋገጣል።

17// የአንድን ጎሳ ከሌላው የማያበላልጥ እኩል እይታ ያለው እና ለሁሉም ጎሳዎች እንዲሁም የአጎራባች ብሄሮች እና ህዝቦች ክብር ያለው መሆኑ ይረጋገጣል።

18// ለግጭት ፈቺ አስታራቂነት ከታጨበት ወይም ከተሾመበት ሰአት ጀምሮ ከአስታራቂ ባልደረቦቹ ጋር መልካም ቅቡልነት ያለው እና ሚስጥር ጠባቂ መሆኑ የተመሰከረለት መሆኑ ይረጋገጣል።

19// ድሆችን የሚጠብቅ በፍርድ ሂደት ላይ ሃብታም ድሃ የማይል ሁሉም እይታው እኩል የሚያይ ንዋይ የማያታልለው ሆዱ የሚወድ ጉበኛ መሆን አለመሆኑ ይረጋገጣል።

20// በምንም መልኩ የጥንት አባቶች ፈለግ ለመከተል ጥረት የሚያደርግ ወይም ከዘመናዊነት ይልቅ ነባር ባህልና እና ቅርሥን የሚጠብቅ መሆኑ ይረጋገጣል።

21//በሚኖርበት አካባቢ ሰዎችን ከአድመኝነት፣ ከከፋፋይነት፣ከመሰሪነት ከውሸታምነት ፣ ከስግብግብነት፣ ከተንኮል ሰሪነት፣ ከጥንቆላ ወይም ከጠንቋይ ቀላቢነት የራቀ መሆኑ ይረጋገጣል።

22// እንዚህ ከላይ የተዘረዘሩ መስፈርቶች የማያሟላ በምንም የመስቃን ማህበረሰብ መዳኘት፣ የማስታረቅ ስልጣን አይሰጠው።
ምክንያቱም ከምንም በፊት ከራስ ጋር መታረቅ ይቀድማልና~~~

~~ቀድሞ ለራሱ ያልሆነ ለማንም ምንም ሊሆን አይችልም፣
ከራሱ ጋር የተጣላ ከራሱ ጋር ሳይታረቅ ማንንም ሊያስታርቅ አይችልም። የጥንት እድሜ ጠገብ አባቶች እንዲህም አይነት መርህ ነበራቸው"""""

ይህ የጥንት የመስቃን አባቶች ህዝብን ከህዝብ ሳይጋጭ በፍትሃዊነት በሰላም፣ በፍቅር እንዲኖር ሃገር እና ህዝብን በመልካም ኖሮ መጨረሻው እንዲያምር መልካም የሆነ ትውልድ ለማፍራት ጠቀሜታው የላቀ መሆኑ ታውቆ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲሸጋገር ማቆየት ያስፈልጋል።

ይህ ድንቅ የሆነ በመስቃን ማህበረሰብ የሽማግሌ ቡድን አወቃቀር የግጭት አፈታት እና የእርቅ ስርዓት ለመከውን በእድሜ ጠገብ አባቶች ይጠቀሙበት የነበረ የአወቃቀር ሴራ (ደንብ) ወይም የንቡር ታሪክ ሲሆን ይህ ታላቅ የማህበረሰብ ድንቅ እሴት ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ሊንከባከበውና ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፍ መጠበቅ ያስፈልጋል።

በርቼ በመስቃን በጥበበኛ አባቶች እንዲህ ይገለፃል።~~~~~~~~~~~~~~~~በርቼ ታሪክ አዋቂ ጥበበኛ አባቶች የፈያ በርቼ እና የቡሼ በርቼ በማለት ለሁለት ይከፍሉታል።የመልካም ነገር ወይም ...
21/05/2025

በርቼ በመስቃን በጥበበኛ አባቶች እንዲህ ይገለፃል።
~~~~~~~~~~~~~~~~
በርቼ ታሪክ አዋቂ ጥበበኛ አባቶች የፈያ በርቼ እና የቡሼ በርቼ በማለት ለሁለት ይከፍሉታል።
የመልካም ነገር ወይም የፈያ "በርቼ" በመልካም ነገርን መተባበርን ሲያበረታቱ "የቡሼ በርቼ በግፍ አለመተባበርን ትውልድ እንዳይከስም ያስጠነቅቁበታል።

~~የፈያ "በርቼ" አምላካቸውን ከሚፈሩ ከመልካም ሰሪ መልካሞች ይገኛል ።

የመልካም ሰሪ ትውልዱ በመስቃን አባቶች አባባል "የጡር ገኝ" በጡር ያድረ ወይም የጡር ሽላ ኤገርዝ በማለት ሲገልፁት የፈያ በርቼተኘ የትውልድ ትውልዱም ቀጣይነት ያለው በመጥፎ የማይተባበር ዘሩ የተባረከ ነው ይሉታል።

~~የመጥፎ ነገር ወይም የቡሼ"በርቼ" በክፉዎች፣ከአላዋቂዎች፣ ከትቢተኞች፣ ከተንኮለኞች፣ ከሴረኞች፣ ከአድመኞች ፣ ፍትህ ከሚያጎድሉ ከበዳይ ከአላዋቂ ጥጋበኞች የሚገኝ ሲሆን ውጤቱም የከፋ ነው።

~~ የቡሼ በርቼ" ፍትህ አሰፍናለሁ በሚል አካል ፍትህ የተጓደለባቸው ሰዎች ፍትህን ፍለጋ በርቼ ተጀፍ የደር ብቻ በማለት መልዕክታቸው ለፈጠራቸው አምላክ የተበደሉበትን ጉዳይ እየጠቀሱ "ጉዌታ የዥኒ" በማለት ፈጣሪ አላህን በእውን እንዲካሱ በማሰብ የሚለማመኑበት ስርአት ሲሆን~~

~~ ጥበበኛ የመስቃን አባቶች እንደሚሉን "በርቼ" በግፍና በውሸት ፍትህ አሰፍናለሁ የሚል አካል በማን አለብኝነት በትዕቢት ፍትህ ያጓደለ እንደሆነ የፍትህ አጉዳዩ የግፈኛው ትውልድ ቀድሞ ያጠፋል።

~~የቡሼ "በርቼ" ከዘር ዘር የሚተላለፍ ትውልድን ክፉኛ የሚጎዳ የተበዳይ የመጨረሻው እርግማን ነው።

~~የቡሼ በርቼ በአባቶች ሲገለፅ "በፌልቃ(በጡፋ) ቢዘነጎ ወይም በማን አለብኝነት በሚናገሩ ለጥጋበኞች ድህነትን ያወርሳል።

~~የቡሼ በርቼ በመስቃን አባቶች እንዲህም ይገለፃል ፍትህ አጉዳዮችን በአደባባይ ያዋርዳል።
የጎበዝ አለቃ በአገልጋዩ አይነግስም።
"የዋጂነት" ሓሮተኹ የሮሰኹ ይኸን እያሉም ይናገራሉ።

~~የቡሼ በርቼ በአባቶች አገላለፅ ገኝም ጨኘትም ጡር ቤነን ይጠፋ በማለት አጥብቀው ያስጠነቅቃሉ፣ አጥብቀውም ይመክራሉ።

~~የቡሼ በርቼ በእድሜ ጠገብ አባቶች ሲነገር በርቼ መጀመሪያ የሚያጠቃው ግፍ ሰሪ ወይም "በፌልቃ"ወይም በጥጋብ ግፍ ተናጋሪውን ከዘር ዘሩ ያጠቃል።

~~ ቡሼ በርቼ በታላላቅ አባቶች ሲገለፅ ትውልድ ሲቀጭጭ የሚያጀግን ጀግና፣ አዋቂን ሃቅ ፈራጅ አስታራቂ ሽማግሌ ያሳጣል፣

~~በሌላ በኩል ታላላቅ ታሪክ አዋቂ አባቶችና በጎበዝ አለቆች "በበርቼ" በተጠፋፉ አለመከባበርን፣ አለመደማመጥን፣ ሃይ ባይ የሌለው፣ ሽማግሌ አልባ እያለ የሌለ ፈሪ የሆነ ትውልድ ይፈጠርና በሁሉም ዘንድ የተናቀ ይሆናል።

~~በአንዳድ በኩል ጥበበኛ አባቶች እንዲህም በማለት ይገልፁታል፣ "ጉርዝ ዬነወ ቤት ግርዝና አግራዥም ኤነ" እያሉም የግፍ ግርዝና አጥብቀው ያስጠነቅቃሉ።

~~አንዳንድ የመስቃን አባቶች እንደሚሉት በግፍ ሰሪ ወይም ከግፈኛ ተባባሪ ቤተሰብ ፈሪ እንጂ እራሱን የሚያከብር ሃገርና ቤተሰቡን የሚያስከብር ታሪክ ሰሪ ልጅ አይወለድም።

~~የመስቃን አዋቂ አባቶች አጥብቀው ግፍ ሰሪን ይጠየፋሉ።
የግፈኛ አባል ያልሆነ በግፍ አይተባበርም እያሉ አጥብቀው ይናገራሉ።

~~የግፍ "በርቼ" በግርዝና በጊዜ ካልተቋጨ በየት በኩል መምጣቱ የማይታወቅ ትውልድን የሚያላሽቅ ለጊዜው የግፈኞች የተመቸ በሚመስል መልኩ ከሓላው ግን አደገኛ መዘዝ ከዘር ዘር እንደሚተላለፍ በግፈኛ ቤተሰብ የሚታይ ዘር እንደማይወጣለትም ይነገራል ።

በግፍ የሚተባበር መነሻው እንጂ መዳረሻው መልካም አይሆንም፣
የበርቼ ቃሉ ቀላል ቢመስልም የተበዳይን እንባ የሚያካክስ ትውልድን የሚያከስም መሆኑ አባቶች ይናገራሉ።

~~~~በስተመጨረሻም የግፍ ሰሪ ሰባት ዘሩ "በበርቼ" ወጥመድ ተይዞ አዋቂውን ሳያውቅ በአላዋቂ እየተመራ የሚያጣላ እንጂ የሚያስታርቅ ሽማግሌ እጥቶ የጨነገፈ ትውልድ ኹኖ ቁልቁል እያደገ በእየለቱ እየተዋረደ ይኖራል።

ከአቶ ሐሰን ከድር ሲማ ገጽ የተወሰደየመስቃን ማህበረሰብ በአፍ መፍቻ ቋንቋው ትምህርት ለማስጀመር የፊደላት ማስቀረፅና የቃላት አሰባሰብ ከተጀመረ 3 አመቱ እንደሆነ ብዙ ሰው የሚያውቀው እውነ...
03/05/2025

ከአቶ ሐሰን ከድር ሲማ ገጽ የተወሰደ

የመስቃን ማህበረሰብ በአፍ መፍቻ ቋንቋው ትምህርት ለማስጀመር የፊደላት ማስቀረፅና የቃላት አሰባሰብ ከተጀመረ 3 አመቱ እንደሆነ ብዙ ሰው የሚያውቀው እውነት ነው። የኮምፒተርም መተግበሪያ ተሰርቶለት በእጅ ከገባ 2 አመት አልፎታል። የሞባይል መተግበሪያ ተሰርቶለት በክፍያ ችግር ምክንያት ነው የቆመው። እውቅና ለመስጠት ባይፈለግም በዚህ ዙሪያ ብዙ የተለፋበት ስራ ነው። ነገር ግን 4ቱም የመስቃን መዋቅሮች በአንድ ተሰባስበው አተገባበሩ ላይ መወያየት የሚጠይቅ ነው። ሙያ በልብ ነው ሰርቻለሁ አሰርቻለሁ ማለት አይጠቅምም ዋናው ስራ ነው።

ከአማርኛው የፊደል ገበታ በተጨማሪ የመስቃንኛ ቋንቋና የአነጋገር ዘዬ ለመፃፍ ወደ 12 ፊደላት ተለይተው ተቀርፀውና ተዘጋጅተው ከቀረቡ ቆይቷል። በመስቃን ወረዳ ምክር ቤትም ለውይይት ቀርቦ የፀደቀም ስራ ነበረ። አሁንም አልዘገየም በትኩረት ሊሰራበት የሚገባ ነውና መደገፍ የምትፈልጉ ካላቹ፣ በፊደላቱ ላይ ሀሳብና አስተያየት ያላቹ አካላት በሩ ክፍት ነው በኮመንት አስተምሩን። መሳደብ፣ መፈራረጁ ይቅርና እንማማር።

አዘጋጅ የመስቃን ወረዳ ባለሙያዎች

1. አርቲስት ሰመሩ ስርዋጃ
2. አቶ ወልዩ አህመድ(computer science) ባለሙያ
ነበሩ ምስጋናም ጥቅምም ሳይፈልጉ እንቅልፍ አጥተው የሰሩትን ስራ ማሳነስ አይሁንብን ለዚህ ስራ ወጪ ድጋፍ ያደረጉና ምስጋና የሚገባቸው

1.ሙባረክ መሀመድ አንደታ 30ሺ ብር

2. ዶ/ር ሁሴን ሀሰን 10ሺ

3. ዶ//ር ሸምሱ ሰማን ( ዶር ሸምሱ መ/ክሊኒክ) 10ሺ ብር
4. ዶ/ር ሰመረዲን( ፎያት የጥርስ ክሊኒክ) 10ሻ ብር በድምሩ 60ሺ ብር በወቅቱ ድጋፍ አድርገዋል እናመሠግናለን። ሌሎቻችንስ?

27/04/2025
ዜና ቴሌቶንበሪያድ ሳኡዲ አረቢያ በመስቃን ልማት ማህበር አስተባባሪነት ለምስራቅ ጉራጌ ዞን ማጠናከሪያ የቴሌቶን መርሐ ግብር በደመቀ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል።
25/04/2025

ዜና ቴሌቶን

በሪያድ ሳኡዲ አረቢያ በመስቃን ልማት ማህበር አስተባባሪነት ለምስራቅ ጉራጌ ዞን ማጠናከሪያ የቴሌቶን መርሐ ግብር በደመቀ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል።

25/04/2025

በሪያድ ሳኡዲ አረቢያ በመስቃን ልማት ማህበር አስተባባሪነት ለምስራቅ ጉራጌ ዞን ማጠናከሪያ የቴሌቶን መርሐ ግብር በደመቀ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን አመራሮች በዛሬ ዕለት በሪያድ ሳውዲ አረቢያ የሚከናወነውን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ማጣናከሪያ የቶሌቶን መርሐ ግብር ላይ ለመሳተፍ ሪያድ ከተማ ስለመግባታቸው ተሰምቷል። የመስ...
25/04/2025

የምስራቅ ጉራጌ ዞን አመራሮች በዛሬ ዕለት በሪያድ ሳውዲ አረቢያ የሚከናወነውን የምስራቅ ጉራጌ ዞን ማጣናከሪያ የቶሌቶን መርሐ ግብር ላይ ለመሳተፍ ሪያድ ከተማ ስለመግባታቸው ተሰምቷል። የመስቃን ልማት ማህበር ሪያድ ቅርንጫፍ በሪያድ እና አካባቢው የሚገኙ የቤተ መስቃን ተወላጆችን በተደራጀ መልኩ በመቀስቀሱ መርሐ ግብሩ በስኬት ይጠናቀቃል ተብሎ ይገመታል።

09/03/2025

የተደፈርነው እኛ ነን። እንደተቋም ክስ እንመሰርታለን።‼

Ustaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ.

Address

Butajira

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when meskan media network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to meskan media network:

Share