22/10/2025
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ በልማት በሰላምና በመልካም አስተዳደር ተያያዥ ጉዳዮች "ሰላም እና ልማት" በሚል መሪ ቃል የምክክር መድረክ ተካሄደ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጥቅምት 12/2018(የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮምንኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት)
በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ ከቀበሌ አመራሮች ፣ስራ አስኪያጆች የስላም ኮምቴ አባላት እና ከሚኒሻ አባላት፣ ከወረዳው ከሰላም ፀጥታ አካላት ፣ አመራሮች፣ ከባለድርሻ አካላት በተገኙበት ''ሰላምና ልማት'' በሚል መሪ ቃል በሰላምና በመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ የምክክር መድረክ ተካሄደ ።
የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ተካልኝ ንጉሴ የተሰሩ የሰላም ግንባታና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ውጤታማ መሆናቸው በመግቢያ ንግግራቸው ገልፀው ።
አሁን የተገኘው አንፃራዊ ሰላም እንዲቀጥል የልማት፣ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል በማለት የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ተካልኝ ንጉሴ አያይዘው አሳስበዋል።
ከዚህ ቀደም የነበረው የሰላም እጦት በየደረጃው ያለው አካል ማህበረሰቡን በማሳተፍ የህግና የባላይነት የማስከበሩ ተግባር በመጠናከሩ እና የሰላም ውይይቱም በየማህበራዊ መሰረቱ በመወያየቱ በመግባባት አንድነትበመፍጠር በቅንጅት በመስራቱ እና በተሰሩ የሰላምና የፀጥታ ስራ አንፃራዊ ሰላም መምጣቱን ተናግረው።
በዚህ አካባቢ ግጭትና መፈናቀል የክልሉ መንግስት ባደረገው ድጋፍ፣ በዞኑና በማረቆ ልዩ ወረዳ አመራሮች ህዝቦች ባደረጉት አስተዋፆ ግጭቱ መፍታት መቻሉን ገልፀው በቀጣይም
አሁን የተገኘው እንፃራዊ ስላም ዘላቂ እንዲሆን በሁለቱም ማህበረስብ በየአካባቢው የሰላም ኮሚቴ ውይይት መቀጠል አለበት ያሉ ሲሆን ከምንጊዜውም በተሻለ ሁኔታ ሰላም ማፅናት ተግባር ሁሉም ሊረባረብ ይገባል ብለዋል ።
በቀጣይ በየቀበሌው የማህበረሰብ ውይይቶች የሰላም ኮሚቴ ውይይት ፣በየቀበሌው የሰላም ጠንቅ ጉዳዮች የመልካም አስተዳደር የጉዳዮች ሳይንቁ ከስርስር መፍታት ይገባል ብለዋል።
በተለይ ከአገልግሎት አሰጣጥ እንግልት መፍጠር፣ ለብልሹ አሰራር ማመቻቸት፣ የመልካም አስተዳደር እጦት ምክንያት የሚሆኑ አገልግሎቶች ከመታወቅያ አስጣጥ ፣የወሳኝ ኩነት አገልግሎት ችግር የሚፈጥር ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል በማለት የመምርያ ሀለፊው በምምክር መድርኩ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምርያ ኃላፊ አቶ ተካልኝ ኑግሴ በመድረኩ እንደገለፁት ዘላቂ ሠላምን በማጽናት የተረጋጋችና ልማቷ የተረጋገጠባትን፣ ዞን፣ ወረዳ፣ ቀበሌ ለመፍጠር ተግተን ልንሠራ ይገባል ብለዋል።
ሠላም የጽናት፣ የመረጋጋት ውጤት ነው ያሉት ኃላፊው ሠላምን የሚያደናቅፉ ተግባራትን ህብረተሰቡም ሆነ ባለድርሻ አካላት በጋራ መታገል እንደሚኖርባቸው አመላክተዋል።
በተገኘው ስላም ሁለቱም መዋቅሮች ልማት ላይ መሆናቸው ጠቅሰው እርስ በእርስ የአንዱ ልማት አንዱ እየተደጋገፈ ያለበት ሁኔታ በቅርቡ ለማረቆ ገራድ ሆስፒታል እና
የማረቆ ልዩ ወረዳ መንግስት እና ህዝቡ ለወጃ ንቡር አጠቃላይ ኮንፕሬሄንሲፍ ጤና ኬላ ግንባታ የተደረገው ድጋፍ ማሳያ በመሆኑን ከመድረኩ ተንስቷል
ዞኑ የምስራቅ መስቃን ወረዳ አርሶ አደሩም እንዲሁም የአብሮነት የወንድማማችነት እህትማማችነት መገለጫ የሆነው የማረቆ ሆስፒታል ግንባታ ሰንጋ ገቢ ማድረጋቸውን የዞኑ ማህበረስብ እና የወረዳው መንግስት እና አርሶአደር የገንዘብ የስንጋ ድጋፍ መደረጉ በመጥቀስ ለዚህ ስኬት ለተጉ ሁሉ በመድረኩ ምስጋና ቀርብዋል።
የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና ግብርና ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አለሙ ግዛው ከግብርና አንፃር አካባቢው ከፍተኛ አቅም ያለው እንዲሁም በዚህ አመት እንድም ማሳ ጦሙ ያደረ እንዴለለ ገልፀው።
በስላም እጦት ሁለቱም መዋቅሮች ከክልሉ ጋር ተቀናጅተው ማህበረስቡን በማሳተፍ ከዚህ ቀደም ያልታረሱ መሬት በስብል መሸፈኑን ገልፀው ሰብል አስባስቡ ስራ በአብሮነት በመደጋገፍ በባህላችን በደቦ በመተጋዝ እህል የማስባስቡ ተግባር እና የስላሙ ማፅናት ተግባር በሁለቱም ማህበረስቦች ተጥናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በመድረኩ እንድተናገሩት የሰላም ዋጋ ለኛ ከኛ በላይ የሚረዳው የለም ያሉ ሲሆን በስላም ኮምቴ ውይይቶች ፣ሮንድ ጥበቃ ፣ ደስ በሚል ሁኔታ የተጀመረው የህዝብ ለህዝብ ትስስሮች እና መደጋገፎች በማጠናከር እንስራለን ብለዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች አክለው እንድተናገሩት ለዚህ ስላም መገኘት የዞን የልዩ ወርዳ፣ የወረዳ ፣የክልል አመራሮች እና የፀታ አካላት በተለይ ለክልሉ ክቡር ፕሬዝዳንት ክቡር እንደሻው ጣስው ለሰላሙ ጉዳይ ቅድምያ ሰጥተው እስከ ቀበሌ ወርደው ለስሩት ስራ ምስጋናቸው ገልፀዋል።
በመጨረም በግጭት ምክንያት ተፈናቅለው የተመለሱ ተፈናቃዮች ያሉበት የእርሻ ስብላቸው በመስክ ጎብኘት ተከናውናል።
በመድረኩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ስላም እና ፀጥታ መምርያ ሀላፊ አቶ ተካልኝ ኑግሴ፣ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ ግብር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አለሙ ግዛው እና የወረዳው ፓርቲ ጽ/ቤት አመራሮችአስተባባሪ አካላት ፣የምስራቅ መስቃን አፈጉባዔ ክብርት ወ/ሮ መዲና ኤርጎሻ ጨምሮ የዞን የወረዳና አጠቃላይ አመራር ፣ የሀይማኖት አባቶች የስላም ኮምቴዎች ፣የቀበሌ አመራሮ ፣ስራ አስኪያጆች የፀጥታ እና ስላም ፅ/ቤት ፣ሚኒሻ ፅ/ቤት ተሳትፈዋል