በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት This is the official page of በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መ/ኮ/ጉ /ፅ/ቤት

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ በልማት በሰላምና በመልካም  አስተዳደር ተያያዥ ጉዳዮች "ሰላም እና ልማት" በሚል መሪ ቃል የምክክር መድረክ ተካሄደ!! ።።።።።።።።።።።።።።።።...
22/10/2025

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ በልማት በሰላምና በመልካም አስተዳደር ተያያዥ ጉዳዮች "ሰላም እና ልማት" በሚል መሪ ቃል የምክክር መድረክ ተካሄደ!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ጥቅምት 12/2018(የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮምንኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት)

በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ ከቀበሌ አመራሮች ፣ስራ አስኪያጆች የስላም ኮምቴ አባላት እና ከሚኒሻ አባላት፣ ከወረዳው ከሰላም ፀጥታ አካላት ፣ አመራሮች፣ ከባለድርሻ አካላት በተገኙበት ''ሰላምና ልማት'' በሚል መሪ ቃል በሰላምና በመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ የምክክር መድረክ ተካሄደ ።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ተካልኝ ንጉሴ የተሰሩ የሰላም ግንባታና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ውጤታማ መሆናቸው በመግቢያ ንግግራቸው ገልፀው ።

አሁን የተገኘው አንፃራዊ ሰላም እንዲቀጥል የልማት፣ የሰላምና የመልካም አስተዳደር ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል በማለት የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ተካልኝ ንጉሴ አያይዘው አሳስበዋል።

ከዚህ ቀደም የነበረው የሰላም እጦት በየደረጃው ያለው አካል ማህበረሰቡን በማሳተፍ የህግና የባላይነት የማስከበሩ ተግባር በመጠናከሩ እና የሰላም ውይይቱም በየማህበራዊ መሰረቱ በመወያየቱ በመግባባት አንድነትበመፍጠር በቅንጅት በመስራቱ እና በተሰሩ የሰላምና የፀጥታ ስራ አንፃራዊ ሰላም መምጣቱን ተናግረው።

በዚህ አካባቢ ግጭትና መፈናቀል የክልሉ መንግስት ባደረገው ድጋፍ፣ በዞኑና በማረቆ ልዩ ወረዳ አመራሮች ህዝቦች ባደረጉት አስተዋፆ ግጭቱ መፍታት መቻሉን ገልፀው በቀጣይም

አሁን የተገኘው እንፃራዊ ስላም ዘላቂ እንዲሆን በሁለቱም ማህበረስብ በየአካባቢው የሰላም ኮሚቴ ውይይት መቀጠል አለበት ያሉ ሲሆን ከምንጊዜውም በተሻለ ሁኔታ ሰላም ማፅናት ተግባር ሁሉም ሊረባረብ ይገባል ብለዋል ።

በቀጣይ በየቀበሌው የማህበረሰብ ውይይቶች የሰላም ኮሚቴ ውይይት ፣በየቀበሌው የሰላም ጠንቅ ጉዳዮች የመልካም አስተዳደር የጉዳዮች ሳይንቁ ከስርስር መፍታት ይገባል ብለዋል።

በተለይ ከአገልግሎት አሰጣጥ እንግልት መፍጠር፣ ለብልሹ አሰራር ማመቻቸት፣ የመልካም አስተዳደር እጦት ምክንያት የሚሆኑ አገልግሎቶች ከመታወቅያ አስጣጥ ፣የወሳኝ ኩነት አገልግሎት ችግር የሚፈጥር ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል በማለት የመምርያ ሀለፊው በምምክር መድርኩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምርያ ኃላፊ አቶ ተካልኝ ኑግሴ በመድረኩ እንደገለፁት ዘላቂ ሠላምን በማጽናት የተረጋጋችና ልማቷ የተረጋገጠባትን፣ ዞን፣ ወረዳ፣ ቀበሌ ለመፍጠር ተግተን ልንሠራ ይገባል ብለዋል።

ሠላም የጽናት፣ የመረጋጋት ውጤት ነው ያሉት ኃላፊው ሠላምን የሚያደናቅፉ ተግባራትን ህብረተሰቡም ሆነ ባለድርሻ አካላት በጋራ መታገል እንደሚኖርባቸው አመላክተዋል።

በተገኘው ስላም ሁለቱም መዋቅሮች ልማት ላይ መሆናቸው ጠቅሰው እርስ በእርስ የአንዱ ልማት አንዱ እየተደጋገፈ ያለበት ሁኔታ በቅርቡ ለማረቆ ገራድ ሆስፒታል እና
የማረቆ ልዩ ወረዳ መንግስት እና ህዝቡ ለወጃ ንቡር አጠቃላይ ኮንፕሬሄንሲፍ ጤና ኬላ ግንባታ የተደረገው ድጋፍ ማሳያ በመሆኑን ከመድረኩ ተንስቷል

ዞኑ የምስራቅ መስቃን ወረዳ አርሶ አደሩም እንዲሁም የአብሮነት የወንድማማችነት እህትማማችነት መገለጫ የሆነው የማረቆ ሆስፒታል ግንባታ ሰንጋ ገቢ ማድረጋቸውን የዞኑ ማህበረስብ እና የወረዳው መንግስት እና አርሶአደር የገንዘብ የስንጋ ድጋፍ መደረጉ በመጥቀስ ለዚህ ስኬት ለተጉ ሁሉ በመድረኩ ምስጋና ቀርብዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና ግብርና ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አለሙ ግዛው ከግብርና አንፃር አካባቢው ከፍተኛ አቅም ያለው እንዲሁም በዚህ አመት እንድም ማሳ ጦሙ ያደረ እንዴለለ ገልፀው።

በስላም እጦት ሁለቱም መዋቅሮች ከክልሉ ጋር ተቀናጅተው ማህበረስቡን በማሳተፍ ከዚህ ቀደም ያልታረሱ መሬት በስብል መሸፈኑን ገልፀው ሰብል አስባስቡ ስራ በአብሮነት በመደጋገፍ በባህላችን በደቦ በመተጋዝ እህል የማስባስቡ ተግባር እና የስላሙ ማፅናት ተግባር በሁለቱም ማህበረስቦች ተጥናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በመድረኩ እንድተናገሩት የሰላም ዋጋ ለኛ ከኛ በላይ የሚረዳው የለም ያሉ ሲሆን በስላም ኮምቴ ውይይቶች ፣ሮንድ ጥበቃ ፣ ደስ በሚል ሁኔታ የተጀመረው የህዝብ ለህዝብ ትስስሮች እና መደጋገፎች በማጠናከር እንስራለን ብለዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች አክለው እንድተናገሩት ለዚህ ስላም መገኘት የዞን የልዩ ወርዳ፣ የወረዳ ፣የክልል አመራሮች እና የፀታ አካላት በተለይ ለክልሉ ክቡር ፕሬዝዳንት ክቡር እንደሻው ጣስው ለሰላሙ ጉዳይ ቅድምያ ሰጥተው እስከ ቀበሌ ወርደው ለስሩት ስራ ምስጋናቸው ገልፀዋል።

በመጨረም በግጭት ምክንያት ተፈናቅለው የተመለሱ ተፈናቃዮች ያሉበት የእርሻ ስብላቸው በመስክ ጎብኘት ተከናውናል።

በመድረኩ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ስላም እና ፀጥታ መምርያ ሀላፊ አቶ ተካልኝ ኑግሴ፣ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ ግብር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አለሙ ግዛው እና የወረዳው ፓርቲ ጽ/ቤት አመራሮችአስተባባሪ አካላት ፣የምስራቅ መስቃን አፈጉባዔ ክብርት ወ/ሮ መዲና ኤርጎሻ ጨምሮ የዞን የወረዳና አጠቃላይ አመራር ፣ የሀይማኖት አባቶች የስላም ኮምቴዎች ፣የቀበሌ አመራሮ ፣ስራ አስኪያጆች የፀጥታ እና ስላም ፅ/ቤት ፣ሚኒሻ ፅ/ቤት ተሳትፈዋል

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት የተቀናጀ የህጻናት የክትባት ዘመቻ ሊያካሄድ ነው!!።።።።።።።።።።።።።ጥቅምት12/2018የምስራቅ መስቃን ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ከነገ ጥቅምት 13 ...
22/10/2025

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት የተቀናጀ የህጻናት የክትባት ዘመቻ ሊያካሄድ ነው!!
።።።።።።።።።።።።።
ጥቅምት12/2018

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ከነገ ጥቅምት 13 ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የተቀናጀ የህጻናት ቤት ለቤት ክትባት ዘመቻ ሊያካሂድ መሆኑን አስታውቋል።

ይህ ዘመቻ ዕድሜያቸው ከ12 እስከ 59 ወር ባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ፣ ክትባት ያልተከተቡ ወይም ጀምረው ያቋረጡ ህጻናትን ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ ሲሆን፣ የክትባቱ አገልግሎት በየቀበሌው ከቤት ወደ ቤት በመዘዋወር ይሰጣል።

የጤና ጽህፈት ቤቱ ይህንን ዘመቻ ውጤታማ በሆነ መንገድ ለማካሄድ እንዲቻል ከዘመቻው አስቀድሞ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክም አካሂዷል።

ከክትባቱ አሰጣጥ ጋር ተያይዞ በጽ/ቤቱ የእናቶችና ህጻናት የስራ ዘርፍ ፈጻሚ አቶ ጀማል ኑሪ ስለጠና ሰጥተዋል።

የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩን ያስጀመሩት የምስራቅ መስቃን ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ገነሞ ወልዴ ክትባቱ በአስተማማኝ ሁኔታ የጤና ስርዓታችን ለመገንባት የሚያስችል መሠረታዊ መሣሪያ መሆኑን ክትባት ገልጸዋል።

በዚህ ዘመን የጤና ስርዓታችንን በሚገባ በመጠበቅ ልጆቻችን ከተለያዩ በሽታዎች የሚከላከሉ ክትባቶችን በመስጠት ልንታደግ ይገባል ብለዋል።

ይህ አስር ቀናት የሚወስደው የተቀናጀ የክትባት ዘመቻ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ምክንያቶች የክትባት አገልግሎት ሳይደርሳቸው የቀሩ ወይም የመጀመሪያ ዙር ክትባቶችን ወስደው ቀጣይ ዙሮችን ያቋረጡ ህጻናትን ሙሉ በሙሉ ለመመለስ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል።

የጤና ባለሙያዎቻችን በየቀበሌው በመዘዋወር አገልግሎቱን ለማዳረስ ዝግጁ ናቸው ሲሉ አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም ሁሉም ወላጆች ዕድሜያቸው ከ12 እስከ 59 ወር ባለው የዕድሜ ክልል የሚገኙ ልጆቻቸው ክትባቱን እንዲያገኙ በማድረግ ለጤናማ ትውልድ ምስረታ ላይ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

በዞኑ  በ2017/2018 የምርት ዘመን 13 ሺህ 775 ሄክታር  መሬት በስንዴ ሰብል በኩታ ገጠም ለምቷል የምስራቅ ጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ ገለፀ። ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ምየምስራቅ ...
22/10/2025

በዞኑ በ2017/2018 የምርት ዘመን 13 ሺህ 775 ሄክታር መሬት በስንዴ ሰብል በኩታ ገጠም ለምቷል የምስራቅ ጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ ገለፀ።

ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ በ2017/2018 የምርት ዘመን 13 ሺህ 775 ሄክታር መሬት በስንዴ ሰብል በኩታ ገጠም እየለማ መሆኑ አሳውቋል።

በምርት ዘመኑ በዞኑ 19 ሺ 997 ሄክታር መሬት በስንዴ ሰብል መሸፈን መልማቱን ተመልክቷል።

በዞኑ የሶዶ ወረዳ ከ14 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ሰብል የለማ ሲሆን ከዚህም ከ10 ሺህ ሄ/ር በላይ መሬት በኩታ-ገጠም ማልማት ተችሏል።

በወረዳው ውድገት ቀበሌ ውላድ ሴሩ ክላስተርና ሶሎቄ ቀበሌ ክላስተር የለማ ማሳ በምስል፦

የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ከአሰላ ፋና ኤፍ ኤም 90.0 ጋር መስራት የሚያስችለው "ጎረጎር"  የፕሮግራም ስያሜ ያለው የአየር ሰዓት ውል ስምምነት ተፈራረመ።።።።።።...
21/10/2025

የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ከአሰላ ፋና ኤፍ ኤም 90.0 ጋር መስራት የሚያስችለው "ጎረጎር" የፕሮግራም ስያሜ ያለው የአየር ሰዓት ውል ስምምነት ተፈራረመ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም(የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮምንኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት)

የወረዳውን የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራት ተገቢውን የህዝብ ግንኙነት ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤቱ ገለፀ።

የወረዳው ፀጋዎች የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራት ተገቢውን የህዝብ ግንኙነት ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤ ገልጿል።

ፅ/ቤቱ ከአሰላ ፋና ኤፍ ኤም 90.0 ጋር መስራት የሚያስችለው የአየር ሰዓት ውል ስምምነት ተፈራርሟል።

የወረዳው የሰላም፤ የልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳዮችና የኢንቨስትመንት የወረዳው ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ የማህበረስቡ ባህል ወግ ዕሴቶች ወቅታዊ ጉዳዮች በተለይ አርሶ አደሩ የግብር አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ፀጋዎች የመረጃ አማራጮች ለማስተዋወቅ እንዲረዳ በዲጂታል ቴክኖሎጂ፤ብሮድካስቲንግና የገፅ ለገፅ ስራዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የፅ/ቤቱ ሀላፊ አቶ በህረዲን ከማል ተናግረዋል።

ወረዳው ያለውን ውስን ግብዓት በመጠቀም ጠንካራ የህዝብ ግንኙነት ስራዎች በመስራት መንግስትና ህዝብን ህዝብና መንግስትን ለማገናኘት በልዩ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል።

በበጀት ዓመቱ የወረዳው ማህበረሰብ በስፋት ተደራሽ የሚሆነውን የአሰላ ፋና ኤፍ ኤም 90.0 በሳምንታዊ ፕሮግራም ውል በመግባት ስራዎች አጠናክሮ ለመስራት መፈራረማቸው ገልፀዋል።

የወረዳው መንግስት ፅ/ቤቱ በሰው ሃይልና ግብዓት በማደራጀት የላቀ የህዝብ ግንኙነት ስራዎች ጥረት እየተደረገ መሆኑንና መላው የወረዳው ማህበረሰብ በሚኖረው በሳምንቱ ባለዉ ሰዓት ፕሮግራሙን አሰላ ፋና ኤፍ ኤም "ጎረጎር " በተስኘ የአየር ፕሮግራም በየሳምንቱ ዘውትር ስኞ ከምሽቱ 1:00 ስዓት እስላ ፋና ኤፋ ኤም 90.0 እንድትከታተሉ እናሳውቃለን።

የምስራቅ መስቃን ወርዳ ጤና ፅ/ቤት  ለተደራጁ ማህበራት የንጽህና መጠበቂያ የሞዲስ ማምረቻ(ማዘጋጃ) እና የልብስ መስፍያ ማሽን ርክክብ ፈፀመ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ጥቅምት11  ...
21/10/2025

የምስራቅ መስቃን ወርዳ ጤና ፅ/ቤት ለተደራጁ ማህበራት የንጽህና መጠበቂያ የሞዲስ ማምረቻ(ማዘጋጃ) እና የልብስ መስፍያ ማሽን ርክክብ ፈፀመ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ጥቅምት11 ፣2018ዓ.(የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮምንኬሽን)

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤና ፕሮግራሞችና የበሽታ መከላከል ለማህበራት ድጋፍ የወረዳው ጤና ፅ/ቤት የወረዳው ጤና ፅ/ቤት ሀለፊ አቶ ገነሞ ወልዴ የወርዳው ፋይናስ ፅ/ቤት ሃለፊ አቶ ብርሃኑ ፈይሳ በተገኙበት ሀይጂንና ሳንቴሽን ስራ ሂደት ሀላፊ አቶ ይልማ ፅጌ፣የፅ/ቤት ባለሙያ የሚዲያ አካላት በተገኙበት ርክክብ ተፅመዋል።

የተደረገው ድጋፍ በማህበሮቹ አማካይነት
በጤና በጥቃቅን እና አነስተኛ ለተደራጁ ማህበራት የንጽህና መጠበቂያ የሞዲስ ማምረቻ(ማዘጋጃ)ማሽን ወይም የልብስ መስፊያ መኪና እና ቁሳቁስ ርክክብ መፈጸም እና ለመሐበራቱ ድጋፍ ተደርጉዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የወባ በሽታን ወረርሽኝ ለመከላከል የሚያስችል የፀረ-ወባ  ትንኝ መከላከያ ኬሚካል ርጭት የባለሙያዎች ስልጠና የተግባር ስልጠና ስጠ ፡፡።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።...
21/10/2025

የምስራቅ መስቃን ወረዳ የወባ በሽታን ወረርሽኝ ለመከላከል የሚያስችል የፀረ-ወባ ትንኝ መከላከያ ኬሚካል ርጭት የባለሙያዎች ስልጠና የተግባር ስልጠና ስጠ ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም
የምስራቅ መስቃን ወረዳ በሚገኙ የወባ ጫና ባለባቸዉ ቀበሌዎች ለሚከሄደዉ የፀረ ወባ ኬሚካል ርጭት ለሚሰማሩ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጥዋል።

ለሠልጣኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ የተጀመረ ሲሆን የተግባርና የክህሎት ስልጠና በመስጠት ተጠናቁዋል።

በስልጠናዉ ማስጀመሪያ ላይ ተገኝተዉ መልዕክት ያስተላለፉ በምስራቅ መስቃን ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገነሞ ወልዴ በመልዕክታቸዉ ለዚህ ስራ የተመለመሉ ሰራተኞች በቀበሌዎቻቸዉ ጥሩ ስነ ምግባር ያላቸዉና ከዚህ በፊትም ልምዱ ያላቸዉ በመሆኑ የሪጭት ስራዉን ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በተሰጣቸው ስልጠና መሰረት በጥራት እንድያከናዉኑ አሳስበዋል።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ምክትል ሀላፊ እና የበሽታ መከላከል ሀላፊ በስልጠናው ወቅት ለሰልጣኞች እንደተናገሩት ውቅቱ የወባ በሽታ ተጋላጭ ወረዳው የወባ ተጋላጭ መሆኑን በመጥቀስ በስለጠናው መስረት ርጭት መደረግ እንዳለበት እና ሂደቱም በጥብቅ ዲስፒሊን ክትትል እንደሚደረግ አሳስበዋል።

በስልጠናዉ የምስራቅ መስቃን ወረዳ ጤና ባለሙያዎች ስለ ስልጠናው ሙያዊ የተግባር ስልጠና በስለጠናቹት መስረት ርጭት መስጠት ይስባል ብለዋል።

ስልጣኞቹም እደተናገሩት በስለጠናው መደስታቸው እና ለቀጣይ ስራ የሚሆን በርጭት ወቅት ከቅድመ ጥንቃቄ እና ስለ ኬምካል አጠቃቅም አረጫጨት በቂ እውቀት እና የተግባር ስልጠና መውስዳቸው ገልፀዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ የሱፐርቪዥን ቡድን በምስራቅ መስቃን ወረዳ የተከናወኑ የክረምት በጎፈቃድና የክረምት የስፖርት ተግባራቶችን ገምግሟል።።።።።።።ጥቅምት11/2018የ...
21/10/2025

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ የሱፐርቪዥን ቡድን በምስራቅ መስቃን ወረዳ የተከናወኑ የክረምት በጎፈቃድና የክረምት የስፖርት ተግባራቶችን ገምግሟል።
።።።።።።
ጥቅምት11/2018
የሱፐርቪዥን ቡድኑ በወረዳው በክረምቱ የተከናወኑ በተለያዩ ተቋማትና አካላቶች የተከናወኑ የበጎፈቃድ አግልግሎት አካል የሆኑ ስራዎችን ተመልክቷል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ የልማት እቅድ ባለሙያና የቡድኑ መሪ አቶ እሸቱ ወልዴ እና የመምሪያው የስፖርት ዘርፍ ባለሙያ አቶ ኑሪ መሀመድ በድጋፍና ክትትሉ ወቅት ተገኝተው እንዳሉት ወረዳው ላይ በስፖርት ዘርፍና በወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተሰሩት ስራዎች አበረታች እና ውጤታማ እንደነበሩ የገለፁ ሲሆን

እንዲሁም በአረጋውያንና አቅመ ደካሞች ቤት ግንባታው ዘርፍም ከዚህ ቀደም የተሻለ እንቅስቃሴ የተከናወነ መሆኑን በመግለፅ ወደ ፊት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አንስተዋል።

ቡድኑ በተቋም ደረጃ ያሉ መረጃዎችን ከገመገመ በኋላ በተለያዩ ቀበሌ የተሰሩ የበጎፈቃድና የልማት ስራዎችን የመስክ ምልከታ በማድረግ የድጋፍና ክትትል ስራውን አጠናቋል።

የዞኑን የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራት  ተገቢውን የህዝብ ግንኙነት ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ገለጸ። ጥቅምት ...
21/10/2025

የዞኑን የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራት ተገቢውን የህዝብ ግንኙነት ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ገለጸ።
ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም

የዞኑን የልማትና መልካም አስተዳደር ተግባራት ተገቢውን የህዝብ ግንኙነት ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ገልጿል።

መምሪያው ከአሰላ ፋና ኤፍ ኤም 90.0 ጋር መስራት የሚያስችለው የአየር ሰዓት ውል ስምምነት ተፈራርሟል

የዞኑ የሰላም፤የልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳዮችና የኢንቨስትመንት አማራጮች ለማስተዋወቅ እንዲረዳ በዲጂታል ቴክኖሎጂ፤ብሮድካስቲንግና የገፅ ለገፅ ስራዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የመምሪያው ኃላፊ አቶ ነጋልኝ አለሙ ተናግረዋል።

መምሪያው ያለውን ውስን ግብዓት በመጠቀም ጠንካራ የህዝብ ግንኙነት ስራዎች በመስራት መንግስትና ህዝብን ህዝብና መንግስትን ለማገናኘት በልዩ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል።

በበጀት ዓመቱ የዞኑ ማህበረሰብ በስፋት ተደራሽ የሚሆነውን የአሰላ ፋና ኤፍ ኤም 90.0 በሳምንታዊ ፕሮግራም ውል በመግባት ስራዎች አጠናክሮ ለመስራት መፈራረማቸው ገልፀዋል።

በሰው ሃይልና ግብዓት በማደራጀት የላቀ የህዝብ ግንኙነት ስራዎች ጥረት እየተደረገ መሆኑንና መላው የዞኑ ማህበረሰብ በሚኖረው በሳምንቱ ሰኞ ከ10:00_11:00 ባለዉ ሰዓት ፕሮግራሙን አሰላ ፋና ኤፍ ኤም 90.0 እንድትከታተሉ እናሳውቃለን።

በምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ምዕራብ መስቃን ቀበሌ  ልዩ ስሙ ጎሎቦ  98 ሄክታር ማሳ ላይ የለማ የጤፍ ክላስተር በምስል:- በ141 አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም ማሳ ማልማት ላይ የተሳተ...
21/10/2025

በምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ ምዕራብ መስቃን ቀበሌ ልዩ ስሙ ጎሎቦ 98 ሄክታር ማሳ ላይ የለማ የጤፍ ክላስተር በምስል:-

በ141 አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም ማሳ ማልማት ላይ የተሳተፉ ሲሆን በመልካም ቁመና ላይ ይገኛል።

ጥቅምት 11/2018

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል  የብልጽግና ፓርቲ የህብረትና የቤተሰብ አመራሮች  በወቅታዊ ክልላዊ ፓለቲካዊና የፀጥታ ሁኔታዎች ላይ ውይይት እያደረጉ ነው፤‎ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም‎‎በማዕከላዊ...
21/10/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የህብረትና የቤተሰብ አመራሮች በወቅታዊ ክልላዊ ፓለቲካዊና የፀጥታ ሁኔታዎች ላይ ውይይት እያደረጉ ነው፤

‎ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም

‎በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የህብረትና የቤተሰብ አመራሮች በወቅታዊ ክልላዊ የፖለቲካና የፀጥታ ሁኔታዎች ላይ በሰባቱም ክላስተሮች፣ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ውይይት እያደረጉ ነው።

 #እንኳን ደስ አላቹህ ደስ አለን     #አቤም ደስ ባረነ ባረናሁ!!!  #አቤም ተብላለቅነ ተብላለኩ!!የምስራቅ መስቃን ወረዳ ኮምንኬሽን የፊስቡክ ይህ ገፅ 25ሺህ ተከታይ መድረሱ አስመልክ...
20/10/2025

#እንኳን ደስ አላቹህ ደስ አለን

#አቤም ደስ ባረነ ባረናሁ!!!

#አቤም ተብላለቅነ ተብላለኩ!!

የምስራቅ መስቃን ወረዳ ኮምንኬሽን የፊስቡክ ይህ ገፅ 25ሺህ ተከታይ መድረሱ አስመልክቶ የፊስቡክ ካምፓኒ ሜታ ካምፓኒ ለዚህ ሚዲያ ተከታይ በሙሉ Congra እንኳን ደስ አላቹሁ በማለት መልዕክቱን ልኳል።

ይህ ፔጅ ሚዲያ ለዚህ ደረጃ የደረስው የናተ የዚህ ፔጅ ተከታዮቻችን በምንስራው ስራ እየበረታታቹሁን እኛን ምርጫቹ ስለአደረጋቹሁን ነው እና የናተ የዚህ ፔጅ ተከታዮች በቀጣይም ይህ ፔጅ ከፍ እንዲል follow,like,invite, share እንድታደርጉልን
ጥሪ መልዕክት እናስተላልፋለን።

I've just reached 25K followers! Thank you for continuing support. I could never have made it without each one of you. 🙏🤗🎉

20/10/2025

መገንጠለም መጠቅለልም አይሰራም!!!

Address

Ensseno
Butajira

Telephone

+251924705963

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት:

Share