በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Butajira
  • በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት This is the official page of በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መ/ኮ/ጉ /ፅ/ቤት

‎‎የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት  ያዘጋጀው የ2017 ዓ/ም የፓለቲካና የንቅናቄ ስራዎች ዓመታዊ ማጠቃለያ ኮንፈረንስና የ2018 ዕቅድ ኦረንቴሽን ዞናል መድረክ ተካሂዷል።‎‎...
17/06/2025

‎‎የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ያዘጋጀው የ2017 ዓ/ም የፓለቲካና የንቅናቄ ስራዎች ዓመታዊ ማጠቃለያ ኮንፈረንስና የ2018 ዕቅድ ኦረንቴሽን ዞናል መድረክ ተካሂዷል።

‎ሰኔ 10/2017 ዓ/ም

‎በመድረኩ የዞኑ ጠቅላላ አመራሮችና በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የሰባቱም መዋቅሮች የፓርቲ አመራሮች በተገኙበት የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የ2017 ዓ/ም የፓለቲካና የንቅናቄ ስራዎች ዓመታዊ አፈፃፀም ሪፓርት እና የ2018 ዕቅድ፤ እንዲሁም የዞኑ የብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን የ2017 ዓ/ም ሪፓርት በፅ/ቤቱ ኃላፊ በወ/ሮ ጀሚላ ጎሳ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።

‎የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር ዋና የመንግስት ተጠሪና የዞኑ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መሰለ ጫካ እንዳሉት በዓመቱ ውጤታማ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በመፈፀም ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ የቻልንበት ዓመት ነውና ለዚህ ውጤት የሀሉም መዋቅር አስተዋጽኦ ከፍተኛ የነበረ በመሆኑ ሁሉም መዋቅራችን ከፍተኛ ምስጋና ይገባዋል ብለዋል።

‎ኃላፊው አቶ መሰለ አክለውም እንዳሉት የአመራራችን የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ይበልጥ የማጠናከር፣ ብልሹ አሰራሮችን ፈጥኖ የማረም፣ ተቋማዊ አሰራርን ተክሎ ተግባር መፈፀም፣ የብልፅግና ቤተሰብ እና ህብረቶችን ማጠናከርና አባልን የመገንባት፣ አባል የማፍራት፣ የፀጥታ ስራን በትኩረት መምራት፣ ሚዲያ ላይ ንቁ በጎ ተሳትፎ ማድረግ እንዲሁም በትራንስፎርሜሽን አጀንዳዎች ያሉን የተሻሉ አፈፃፀሞችን በቀጣይም በዘጠና ቀን ዕቅዳችን ብሎም በ2018 ዓመታዊ ዕቅድ ላይ አካተን በላቀ ደረጃ በመፈፀም የህዝባችንን ተጠቃሚነት ማሳደግ ብሎም ሀገራዊ ሁለንተናዊ ብልፅግናችን ለማረጋገጥ ለሚደረገው ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊኖረው በሚችል መልኩ በርትተን መስራት ይገባናል በማለት ካስገነዘቡ በኋላ በሌሎችም ተያያዥ ተግባራት ላይ የስራ መመሪያ ሰጥተዋል።

‎የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር ረዳት የመንግስት ተጠሪና የዞኑ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የፓለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መሰረት ሽፋ በበኩላቸው እንዳሉት በዓመቱ በርካታ ውጤታማ ተግባር መከናወኑን ገልፀው በቀጣይም ተግባራትን በአደረጃጀት መምራት፣ ፓለቲካሊ የተተነተነ መረጃ መስጠት፣ አደረጃጀቶችን ማጠናከርና የአባላት ጥራት ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ካሉ በኋላ በንቅናቄ የሚመሩ ተግባራት ላይ የተሰራው ውጤታማ ስራ በቀጣይ ዘጠና ቀናትም አጠናክሮ ማስቀጠል እና ዘላቂ ሰላም የማረጋገጥ ጉዳይ ላይ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል በማለት አስገንዝበዋል።

‎የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር ረዳት የመንግስት ተጠሪና የዞኑ የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አህመድ ኑሪ በሰጡት አስተያየት እንዳሉት አደረጃጀቶችን ከማጠናከር አኳያ በትኩረት መስራት፣ ብልፅግና ፓርቲያችን የህዝባችንን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ያለበትን ሁኔታ በተገቢው የፓለቲካ ስራ በመስራት ፓርቲያችን በህዝቡ ዘንድ ያለውን ቅቡልነት ለማሳደግ መስራት ይገባናል ብለዋል።

‎በውይይቱ በተለይም የ2017 በጀት ዓመት በቀረበው ሪፓርት ላይ የውይይቱ ተሳታፊ አመራሮች በሰጡት አስተያየት እንዳሉት የተገባደደው የ2017 የስራ ዘመን በፓርቲ መደበኛ ተግባራትም እንዲሁም በፓርቲ መሪነት በተከናወኑ የንቅናቄ ተግባራት ላይ ምንም እንኳ በቅርቡ የተደራጀ ዞን ቢሆንም ዋና ዋና የህዝብን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበት የስራ ዓመት እንደነበር ከእያንዳንዱ አጀንዳ አኳያ በዝርዝር አስተያየት የተሰጠ ሲሆን፤ ከብልፅግና ኢንስፔክሽንና ስነምግባር ኮሚሽን አኳያም አደረጃጀቱን ከማጠናከር ባለፈ በፓርቲ ዲሲፕሊን የፓርቲ ተግባር እንዲፈፀምና ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት የተሰሩ ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩ አስተያየት ተሰጥቷል።

‎ከዚህ ባሻገርም በውስን ጉዳዮች በሚፈለገው ልክ ውጤት ያልመጣባቸው ተግባራት ላይ በቀጣዩ የስራ ዓመት የሚክስ ተግባር ለመፈፀም ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

‎በመጨረሻም ከ2017 የስራ ዓመት አፈፃፀም አኳያ ለነበሩ የተሻሉ አፈፃፀሞች ለወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የዕውቅናና የምስክር ወረቀት በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ነው።

በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሚካሄደው ሁለተኛው ዙር የእግር ኳስ ሻምፒዮና ውድድር የምስራቅ መስቃን ወረዳ እግር ኳስ ቡድን  ( ነበልባሎቹ)  ከየም እግር ኳስ ቡድን በማዕከላዊ...
17/06/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በሚካሄደው ሁለተኛው ዙር የእግር ኳስ ሻምፒዮና ውድድር የምስራቅ መስቃን ወረዳ እግር ኳስ ቡድን ( ነበልባሎቹ) ከየም እግር ኳስ ቡድን በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል የክለቦች ሻምፒዮና ዉድድር ጨዋታ ።

የምስራቅ መስቃን ወረዳ
እግር ኳስ ቡድን ( ነበልባሎቹ) 1--0 የም


"ድል ለነበልባሎቹ"!!!!
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቀጣይ 90 ቀናት እቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄደ!ሰኔ 10-10-2017 ዓ.ም የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርት...
17/06/2025

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቀጣይ 90 ቀናት እቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄደ!

ሰኔ 10-10-2017 ዓ.ም

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ በቀጣይ ከሰኔ 05 እስከ ነሃሴ 05 በሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጎሳዬ " በዛሬው ዕለት ከዞናችን መዋቅሮች ጋር ያከናወነው የ90 ቀናት እቅድ ውይይት በዋና ዋና ተግባራት ላይ ያተኮረ ነው ያሉ ሲሆን፤

ከእነዚህም የመናኸሪያ አገልግሎት አሰጣጥ፣የመናኸሪያ ቦታዎች በአረንጓዴ አሻራ ማስዋብ ላይ ሰፊ ውይይት መደረጉን አስታውቀዋል።

ሃላፊው አያይዘውም በተለይ ትርፍ መጫን፣ ትርፍ ማስከፈል፣ተሳፋሪን ማስተጓጎል፣ ከመናኸሪያ ውጪ መጫንና ማራገፍ ላይ ጥብቅ ውይይት ተደርጓል ያሉ ሲሆን፤

በክረምት የሚከናወኑ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስመልክቶም በሁሉም የዞኑ መዋቅር የከተማ መናኸሪያዎች ጊቢ ውስጥ የሚተከሉ የጥላ ዛፍ አይነቶችና ብዛት ድልድል ጭምር አከናውነናል ብለዋል።

ሲያጠቃልሉም የታቀደው የ90 ቀናት እቅድ ከክልል ጀምሮ የተያዘ አቅጣጫ በመሆኑ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ይደረጋልም ብለዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ምክትልና የትራንስፖርት ዘርፍ ሃላፊ አቶ አብዱ አሊ በበኩላቸው" በዛሬው ዕለት የተካሄደው የ90 ቀናት እቅድ የባለድርሻ አካላት ውይይት በትኩረት የሚተገበር እና በቅንጅትና በቅርበት የሚከናወን በመሆኑ በየደረጃው ከክልል ጀምሮ ካሉ የፊት አመራሮች ጀምሮ እየተመራ የመጣ ሲሆን፣ እንደዞንም በመዋቅሩ ካሉ ባለድርሻዎች ጋር ውይይት ተደርጓል ብለዋል።

በመቀጠልም አያይዘው በተለይ ከመናኸሪያ ኢ-ቲኬቲንግ አገልግሎት አጠቃቀም፣ ከጫኝና አውራጅ ስነ-ምግባር ስልጠና አሰጣጥና መሰል ተግባራት ጋር ተያይዞም ጠንካራ ስራ እንደሚሰራም አስገንዝበዋል።

ሲያጠቃልሉም በክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብርም የመንገድ ላይ የተከማቸ ውሃ ማፋሰስ፣ ጉቶ መንቀል፣ ዜብራ መቀባትና አደጋዎች መከላከል ላይ በቁርጠኝነት ይሰራልም ብለዋል።

በመድረኩም የወረዳና የከተማ የትራንስፖርትና መንገድ ልማት ፅ/ቤት ሃላፊዎችና የዘርፍ ሃላፊዎች እና ሌሎችም ተሳትፈዋል።

ሲል የዘገበው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

‎‎የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የ2017 ዓ/ም የፓለቲካና የንቅናቄ ስራዎች ዓመታዊ ማጠቃለያ ኮንፈረንስና የ2018 ዕቅድ ኦረንቴሽን ዞናል መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።‎‎ ...
17/06/2025


‎የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የ2017 ዓ/ም የፓለቲካና የንቅናቄ ስራዎች ዓመታዊ ማጠቃለያ ኮንፈረንስና የ2018 ዕቅድ ኦረንቴሽን ዞናል መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

‎ ሰኔ 10/2017 ዓ/ም

‎የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት እንዳሉት በበጀት ዓመቱ በዋና ዋና ተግባራት ለአብነት በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በገቢ፣ በንግድና ገበያ ልማት ወዘተ በንቅናቄ የመራናቸው ተግባራት በአብዛኛው የተሻለ አፈፃፀም የተመዘገበባቸውና የህዝባችንን ተጠቃሚነት ማሳደግ የተቻለበት ዓመት የነበረ ሲሆን የሚቀጥለው የስራ ዓመት ጠንካራ ጎናችንን የበለጠ በማጎልበትና ውስንነታችንን የሚክስ ተግባር በማከናውን የህዝባችንን የላቀ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ መሆን አለበት በማለት አስገንዝበዋል።

‎በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የ2017 ዓ/ም የፓለቲካና የንቅናቄ ስራዎች ዓመታዊ ማጠቃለያ ኮንፈረንስ እና የ2018 ዕቅድ ኦረንቴሽን ዞናል መድረክ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን በመድረኩ የ2017 አፈፃፀም ሪፓርት እና የ2018 ዓ/ም ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ይካሄድበታል ተብሎ ይጠበቃል።

‎በአሁኑ ወቅት የ2017 ዓ/ም ሪፓርት በዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት የፓለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ በአቶ መሰረት ሽፋ እየቀረበ ይገኛል።


ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ነው።

"በዓለም ታሪክ ከኪነ-ጥበብ የተለየ ሥልጣኔ የለም" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ...
16/06/2025

"በዓለም ታሪክ ከኪነ-ጥበብ የተለየ ሥልጣኔ የለም" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተውጣጡ የኪነ-ጥበብ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር ባደረጉት ውይይት በዓለም ታሪክ ከኪነ-ጥበብ የተለየ ሥልጣኔ አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡

"ኢትዮጵያን ጨምሮ ሥልጣኔን ያመጡ ሀገራት ከኪነ-ጥበብ የተለዩ አይደሉም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኪነ-ጥበብ በጥልቅ የማሰብ ኃይል ስላለው ለሥልጣኔ መንገድ ከፋች ነው ብለዋል፡፡

ኪነ-ጥበብ ተፈጥሮን የማንበብ፣ ያየውን የተረዳውን ነገር አቅም ስላለው የትኛውም ፈጠራ ከዚያ ውጭ እንዳልመጣ ጠቅሰዋል፡፡

የሁሉም ፈጠራ መነሻ አመንጪ ኪነ-ጥበብ መሆኑን ዳቪንቼ የሳለውን የአውሮፕላን ምስል ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ አውሮፕላን እንደ ሀሳብ ያኔ በዳቪንቼ ባይሳል ኖሮ ቀጣዩ ትውልድ የዛሬውን አውሮፕላን አይሠራም ነበር ብለዋል፡፡

በመሆኑም ኪነ-ጥበብ ማደግ ለሚፈልግ ማንኛውም ሀገር በጣም ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ "ኪነ-ጥበብ ወሳኝ የሚሆነው ግን የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የኪነ-ጥበብን ካባ አክብረው መያዝ የሚችሉ ከሆነ ነው" ብለዋል፡፡

በለሚ ታደሰ

16/06/2025

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድና አርቲስቶች!

16/06/2025
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከተወጣጡ የጥበቡ ማኅበረሰብ ተወካዮች  ጋር ያካሄዱትን ውይይት ዛሬ ምሽት ሰኔ 9 በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን ...
16/06/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከተወጣጡ የጥበቡ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር ያካሄዱትን ውይይት ዛሬ ምሽት ሰኔ 9 በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን ከምሽቱ 2:30 ላይ ይከታተሉ።

አዲስ አበባ የተወለደው ምርጡ አዳጊው ሳይንቲስት  - ሔማን በቀለ********************ታይም መፅሔት የዓመቱ ምርጥ ልጅ በሚል በፊት ገጹ አትሞታል። በርካታ ዓለም ዓቀፍ መገናኛ ብዙ...
16/06/2025

አዲስ አበባ የተወለደው ምርጡ አዳጊው ሳይንቲስት - ሔማን በቀለ
********************

ታይም መፅሔት የዓመቱ ምርጥ ልጅ በሚል በፊት ገጹ አትሞታል። በርካታ ዓለም ዓቀፍ መገናኛ ብዙኃንም አዳጊው ሳይንቲስት በሚል ሰፊ የዘገባ ሽፋን ሰጥተውታል። ሔማን በቀለ ወንድወሰን ሙሉ ስሙ ነው።

በአዲስ አበባ የተወለደው ሔማን በአራት ዓመቱ ነበር ወደአሜሪካ ቨርጂኒያ ከቤተሰቡ ጋር ያቀናው። እናቱ ወይዘሮ ሙሉእመቤት ጌታቸው መምህር ሲሆኑ፤ አባቱ ደግሞ በዩኤስኤአይዲ የሰው ሃብት ባለሙያ ናቸው።

የሳይንስ ፍላጎቱ በልጅነቱ የሰረጸበት ሔማን ገና 7 ዓመት ሳይሞላው ነበር ቤት ውስጥ ያገኛቸውን ጎጂ ያልሆኑ ኬሚካሎች በማዋሃድ መመራመር የጀመረው።

የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በሮበርት ፎረስት የተከታተለው አዳጊው፤ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በካርተር ጂ ዉድሰን እየተከታተለ ይገኛል።

በትምህርት ቤቱ ላብራቶሪዎች የተሻሻሉ ዕውቀቶችን እያገኘ ያደገው ሔማን፤ በ11 ዓመቱ የቆዳ ካንሰር ላይ ያተኮረ ምርምርን ማድረግ እንደጀመረ ግለ ታሪኩ ያስረዳል።

በኢትዮጵያ የሚያጋጥመው ለፀሐይ ብርሃን ጨረራ በስፋት የመጋለጥ ችግርን መገንዘቡ ለምርምር ሀሳቡ መነሾ እንደሆነው አዳጊው ሳይንቲስት ይገልጻል። ይህንን ችግር ለመፍታት ደግሞ በሳሙና መልክ የሚዘጋጅ ሕክምናን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የምርምር ሃሳብ ነድፎ ወደ ስራ መግባቱን ነው የሚያስረዳው።

ሃሳቡንም 3 ኤም የወጣቶች ዓለም አቀፍ የሳይንስ ውድድር ላይ አቅርቦ እ.አ.አ በ2023 ተቀባይነትን በማግኘቱ አሸናፊ መሆን ችሏል። ውድድሩን በማሸነፉም ለስራው የሚያግዙት ከፍተኛ ሳይንቲስቶችን አግኝቷል።

በውድደሩ አሸናፊ በመሆኑ ያገኘውን 25 ሺህ ዶላር ለቀጣይ የምርምር ስራዎቹ ያዋለው አዳጊው፤ ጥረቱን በማጠናከርም የቆዳ ካንሰርን የሚያክም ሳሙና በማዘጋጀት ካንሰርን በማከም ረገድ ከፍተኛ ውጤት የታየበትን ምርምር አፍልቋል።

ይህ ለቆዳ ካንሰርን ሕክምና የሚውለው ሳሙና አቅምን ባገናዘበ መልኩ ለበርካቶች ተደራሽ ለማድረግ ዓላማ እንዳለው በአንድ ወቅት ለሲኤንኤን ተናግሯል። የ15 ዓመቱ ታዳጊ በምርምር ሥራው አማካኝነት ለጀግና ወጣቶች የሚበረከተውን የግሎሪያ ባሮንን ሽልማት አግኝቷል።

የዓመቱ የአሜሪካ የዓመቱ ምርጥ ታዳጊ ሳይንቲስት የሚል ስያሜም ተሰጥቶታል። በአሁኑ ወቅት በጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ተጨማሪ ምርምር እያደረገ ይገኛል።

ሔማን ለምርምር ውጤቱ ከአሜሪካን የምግብና መድኃኒት አስተዳደር (FDA) ዕውቅና ማግኘትና እ.አ.አ እስከ 2028 ድረስ ምርቱን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሰራጨት የሚያስችል ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ማቋቋምን አቅዶ እየሰራ ይገኛል።

ይህን ይበል የሚያሰኝ ምርምሩን በተመለከተም በበርካታ ዓለም አቀፍ ግዙፍ መድረኮች ላይ ቀርቦ ገለጻ እያደረገ የሚገኘው ትውልደ ኢትዮጵያዊው፤ ለበርካታ ታዳጊዎች ዓርዓያ የሚሆን ሥራ እያከናወነ ነው።

እሱንና ሁለት እህቶቹን በትችላላችሁ መንፈስ ያሳደጉ ቤተሰቦቹን ያመሰገነው ሔማን፤ ነገ የተሻለ ነው ሲል ይገልጻል።

በጌትነት ተስፋማርያም

የአመለካከትና የተግባር መቀራረብ በመዋቅሮቻችን መካከል እንዲፈጠር የሚያችል የሱፐርቪዥን ስራ ይከናወናል፦  አቶ ይሁን አሰፋሰኔ፣09/2017 ዓ.ም በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል...
16/06/2025

የአመለካከትና የተግባር መቀራረብ በመዋቅሮቻችን መካከል እንዲፈጠር የሚያችል የሱፐርቪዥን ስራ ይከናወናል፦ አቶ ይሁን አሰፋ

ሰኔ፣09/2017 ዓ.ም

በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ2017 ማጠቃለያና የ2018 በጀት አመት የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ዙሪያ የሱፐርቪዥን ስምሪት ለሚወጡ አመራሮች ኦረንቴሽን ተሰጥቷል።

በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይሁን አሰፋ በ2017 በጀት ዓመት በዓመቱ መጀመሪያ ዓመቱ የመስፈንጠር ዓመት ነው በሚል ሦስት ዋና ዋና ግቦች አስቀምጠን ወደ ሥራ የተገባ ሲሆን ክልሉን የብልጽግና ተምሳሌት፣ የተሞክሮ ቅመራ ማዕከል እና የተረጋጋና ሰላማዊ ክልል የማድረግ ውጥኖች ተይዘው ወደ ስራ መገባቱንም ጠቅሰዋል።

እነዚሁኑ ተግባራት ምን ያህል ስኬታማ እንደተደረጉ ምልከታ ይደረጋል ብለዋል።በምልከታው ሂደት የተመዘገቡ ስኬቶችና ተግዳሮቶች ጥልቀት ባለው መንገድ ይፈተሻሉ ሲሉም አክለዋል።

አቶ ይሁን የ2017 በጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ዋና ዋና ንቅናቄ ስራዎች አፈጻጸም የፓርቲ ስራዎች የአደረጃጀትና የአባላት ቁመና ያለው ሁኔታ ዙሪያ በጥልቀት ምልከታዎች እንደሚያደረጉም አስታውቀዋል።

በዚህም የአመለካከትና የተግባር መቀራረብ በመዋቅሮቻችንና አደረጃጀቶች መካከል እንዲፈጠር የሚያስችል ድጋፍ መስጠትና ለ2018 በጀት ዓመት ተልዕኮ የተሳካ ዝግጅት ለማድረግ የሚያስችል ምልከታ ስለመሆኑም አቶ ይሁን አብራርተዋል።

የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይግለጡ አብዛ በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ሶስት ዙር በፓርቲና በመንግስት ስራዎች በሁሉም መዋቅር የሱፐርቪዥን ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው በዚኛው ዙር ከሱፐርቪዥን ተግባሮች በኋላ የተሰጡ ግብረመልሶች ተግባራዊ መደረጋቸው ላይ ምልከታ ይደረጋል ብለዋል።

በየደረጃው ያለ አመራራችን የመንግስት ተልዕኮዎችና ኢኒሼቲቮችን ውጤታማ በማድረግ የአገልጋይነት ቁመናን መገንባቱን እንዲሁም የህዝብ ተጠቃሚነትና እርካታ በማስገኘት ረገድ ያለበት ቁመና እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።

ፈጣን እና ትኩስ መረጃ እንዳደርስዎ የፌስቡክ ገፃችንን 👇 ይከታተሉ።

የጥንቃቄ_መልዕክት📢በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትየኤም ፖክስ (Mpox) በሽታ ስጋት እንደሆነ አመላክቷል❗️❗️❗️።።።።።።።።።።።።።።።ሰኔ7 -2017 ዓ.ም  (የም...
15/06/2025

የጥንቃቄ_መልዕክት📢
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
የኤም ፖክስ (Mpox) በሽታ ስጋት እንደሆነ አመላክቷል❗️❗️❗️
።።።።።።።።።።።።።።።
ሰኔ7 -2017 ዓ.ም (የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት)

ኤም ፖክስ ወይም በተለምዶ የዝንጀሮ ፈንጣጣ በመባል የሚታወቀው በከፍተኛ ፍጥነት ከሚሰራጩ በሽታዎች አንዱ መሆኑንና የአለም አቀፍ የጤና ስጋት ሆኖ የተመዘገበ በሽታ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ማሙሽ ሁሴን ተገልጿል።

የኤም ፖክስ ቫይረስ የተገኘባቸው ግለሰቦች እንደ ሽፍታ፣ ሳል፣ ትኩሳት፣ የራስ ምታት፣ የንፍፊት ማበጥ፣ የቆዳ ቁስለትና ድካም፣ የጡንቻና የጀርባ ህመም ምልክቶች የሚታይባቸዉ መሆኑን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር የተናገሩ ሲሆን፤ በሽታው በተለይም ታማሚዎች አካል ላይ ቁስል ካለ በቀላሉ የሚተላለፍ ሲሆን በንክኪ እና የቅርብ ትንፋሽ ግንኙነት ዋነኛ መተላለፊያ መንገዶች ናቸዉ ብለዋል።

በክልል ደረጃ በሽታው ያለበትን ደረጃ የሚከታተል ግብረ ሃይል ተቋቁሞ በየቀኑ በክልሉ መዋቅር የመገምገም ስራ እየተሰራ መሆኑን ተገልጿል።

ህብረተሰቡ ከኤም ፖክስ በሽታ ራሱን ለመጠበቅ የኤም ፖክስ ምልክቶች ካሉባቸው ታማሚዎች ንክኪ በመቀነስ፣ ታማሚዎቹ የተጠቀሙባቸውን ቁሳቁሶች፣ አልባሳትና መኝታ በአግባቡ ሳያጸዱ ባለመጠቀም፣ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛዎችን በመጠቀም፣ የግል እና የእጅ ንፅህና በመጠበቅ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ እያሳሰብን የኤም ፖክስ ምልክቶች የሚያሳይ ማንኛዉም ሰው በሚገኝበት ወቅት ወደ ህክምና ቦታ መሄድ ይገባዋል ተብሏል።

በኢትዮጵያ ግንቦት 17/2017 ዓ.ም በላብራቶሪ ምርመራ ኤም ፖክስ እንደተገኘ የተረጋገጠ ሲሆን፤ በኦሮሚያ ክልል ሞያሌ ከተማ አስተዳደር የ21 ቀን ህጻን በበሽታው መያዙ መረጋገጡ እና በተደረጉት ቀጣይ ምርመራዎች የህጻኑ እናት እንዲሁም ወደ ጎረቤት ሃገር የጉዞ ታሪክ ያለው የህጻኑ አባት ኤም ፖክስ እንደተገኘባቸው ለማረጋገጥ መቻሉን የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ያወጣው መረጃ ያመላክታል፡፡

በዚህም መሰረት ይህ መረጃ እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ 19 ሰዎች በበሽታው መያዛቸውን መረጃው አመላክቷል።

ቴሌግራም፦ t.me/misrakmeskanworedacommunication

🌍ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/mesrakmeskan

🌍ኢ-ሜይል፦[email protected]

🌍ዩትዩብ፦https://youtube.com/channel/UCH3dI7vy2ULtrlosd_GtqcQ

🌍ቲዊተር:-https://x.com/mesrakemeskanw/status/1909712523563077837?t=ZEFwqe7tO-vOrysBZuZX7g&s=19

🌍ኢንስታግራም:-https://www.instagram.com/meserakemeskanwereda?igsh=MW1qOTV6emQ5YjRobA

14/06/2025

Address

Ensseno
Butajira

Telephone

+251924705963

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሸን ጉዳዮች ፅ/ቤት:

Share