ብርሀን ሚዲያ

ብርሀን ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ብርሀን ሚዲያ, railway, Debre Birhan.

የሹመት መረጃ ፤የአብክመ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አረጋ ከበደ ከጥቅምት 15/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተለያዩ የክልል ተቋማት አመራሮች ሹመት ሰጥተዋል ።ሹመት የተሰጣቸው አመራሮች የአመራር ...
26/10/2025

የሹመት መረጃ ፤

የአብክመ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አረጋ ከበደ ከጥቅምት 15/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተለያዩ የክልል ተቋማት አመራሮች ሹመት ሰጥተዋል ።

ሹመት የተሰጣቸው አመራሮች የአመራር ብቃት፣ የስራ ልምድ፣ የትምህርት ዝግጅት እና ስነ ምግባራቸውን መሰረት በማድረግ ነው።

በዚህም መሰረት :-

1. ዶ/ር አማኑኤል ፈረደ ፡ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ

2. አቶ ደረጀ ማንደፍሮ ዳመነ፡ የግብርና ቢሮ ኃላፊ

3. አቶ ጥላሁን ወርቅነህ ተክሌ፡ የትምህርት ቢሮ ኃላፊ

4. አቶ አታላይ ጥላሁን፡ የገንዘብ ቢሮ ኃላፊ

5. ዶ/ር ዳኝነት ፈንታ መኮነን፡ የውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ

6. ዶ/ር ጋሻው ሙጨ ፡ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ

7. ዶ/ር ሞላ መልካሙ፡ የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ

8. ዶ/ር መንገሻ ፈንታው፡ የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ

9. አቶ አባይ መንግስቴ፡ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ

10. አቶ አሰፋ ሲሳይ ተሾመ፡ የኮንስትራክሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር

11. ዶ/ር ማተቤ ታፈረ፡ የአማራ ስቴት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት

12. አቶ እሱባለው መሰለ ፀጋየ፡ የአማራ ስቴት ዩኒቨርስቲ ምክትል ፕሬዚዳንት

13. አቶ እርዚቅ ኢሳ፡ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የርዕሰ መስተዳደር ህዝብ ግንኙነት አማካሪ

14. አቶ ይትባረክ አወቀ፡ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ

15. ዶ/ር ዘላለም ልጃለም፡ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የርዕሰ መስተዳደሩ ፀጥታ ጉዳዮች አማካሪ

16. ዶ/ር ፈንታየ ጥበቡ፡ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የርዕሰ መስተዳድሩ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ

17. ዶ/ር ወልደትንሳኤ መኮነን ፈለቀ፡ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአብክመ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ አማካሪ

18. ዶ/ር ሰይድ እሸቴ፡ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የመሬት ቢሮ አማካሪ

19. አቶ አብይ አበባው ተስፋሁን፡ በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የርዕሰ መስተዳድሩ ስትራቴጂክ ዘርፍ አማካሪ

20. ዶ/ር ምትኩ አለማየሁ፡ የፕላን ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር

21. አቶ ወርቁ ያየህ፡ የህብረተሰብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ

22. አቶ አዲስ በየነ፡ የባህል፣ ኪነ ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽ/ቤት ኃላፊ

23. አቶ አየልኝ መሳፍንት፡ የግብርና ቢሮ መስኖ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

24. ወ/ሮ መሰሉ ብርሃኑ ካሳው፡ የግብርና ቢሮ ተፈጥሮ ሀብት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

25. ወ/ሮ እታገኝ አደመ ገላው፡ የግብርና ቢሮ ምግብ ዋስትና ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

26. አቶ ዘውዱ ማለደ፡ የመንገድ፣ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

27. አቶ ጋሻው ተቀባ፡ የባህል፣ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የስፖርት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

28. አቶ ዘላለም አረጋ ፡ የሴ/ህ/ወጣቶች ቢሮ ወጣት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

29. አቶ ነጋ ይስማው፡ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

30. ዶ/ር ለዓለም ጥላሁን ፡ የፕላንና ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

31. ወ/ሮ ስመኝ ዋሴ፡ የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

32. አቶ ጋሻው እሸቱ፡ በምክትል ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የርዕሰ መስተዳደሩ ህዝብ ግንኙነት ረዳት አማካሪ

33. ዶ/ር ተስፋሁን ተናኘ ፈሩህ፡ የፕላን ኢንስቲቲዩት ምክትል ዳይሬክተር

34. አቶ ገ/ማርያም ይርጋ፡ የባህል፣ ኪነ ጥበብ እና ዝክረ ታሪክ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ

35. ወ/ሮ የሺ ካሴ፡ የባህል፣ ኪነ ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ በመሆን ሹመት ተሰጥተዋል ።

ኢትዮጵያ ትልቅ የሀይማኖት አባት አጣች 😥
19/10/2025

ኢትዮጵያ ትልቅ የሀይማኖት አባት አጣች 😥

የተሿሚዎችና የሀገር መከላከያ ደሞዝ በአዲሱ መመሪያ መሠረት
12/10/2025

የተሿሚዎችና የሀገር መከላከያ ደሞዝ በአዲሱ መመሪያ መሠረት

ደብረ ብርሃን ከተማ እጅፕ አካባቢ  ገፅታ በከፊል።
12/10/2025

ደብረ ብርሃን ከተማ እጅፕ አካባቢ ገፅታ በከፊል።

12/10/2025
በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የገጠር ኢኮኖሚ ከላስተር አስተባባሪ እና ግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) የተሳተፉበት ጉብኝት በደብረ ብርሀን ከተማ በሚገኘው የብራዉን ፉድ ኢንደስ...
07/10/2025

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የገጠር ኢኮኖሚ ከላስተር አስተባባሪ እና ግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) የተሳተፉበት ጉብኝት በደብረ ብርሀን ከተማ በሚገኘው የብራዉን ፉድ ኢንደስትሪ ተከናወነ፤

ስለ ፋብሪካው ፋይዳ ገለጻ የሰጡት የብራውን ፉድ ምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ አብርሃም በሰጡት ማብራሪያ ከ5.6 ቢሊየን ብር በላይ እየተገነባ የሚገኘው ፋብሪካው አስፈላጊውን የማሽነሪ ተከላ ሒደት በማጠናቀቅ በቅርቡ ወደ ማምረት ምዕራፍ እንደሚሸጋገር ገልጸዋል።

ፋብሪካው ሲጠናቀቅ ሊሰጣቸው የሚችሉ የምርት አይነቶችን ያብራሩት ስራ አስኪያጁ በቫይታሚን የበለጸገ ዱቄት፣ የህጻናት አልሚ ምግብ፣CDB+ ፣ለቢራ ፋብሪካ ገብስን የሚተካ የበቆሎ ብቅል፣ የእንስሳት መኖ ተረፈ ምርት የሚያመርት መሆኑን ገልጸዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የገጠር ኢኮኖሚ ከላስተር አስተባባሪ እና ግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ(ዶ/ር) ከለውጥ አመታት ወዲህ የደብረ ብርሀን ከተማ የኢንደስትሪ መዳረሻ ከመሆኗ ባሻገር ሀገራችን ለተለመችው ሁለንተናዊ ብልጽግና መሰረት የሚጥል ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በዛሬው እለት በጉብኝታቸው የተመለከቱት የብራዉን ግድ ፋብሪካ የሚጠቀማቸው ግብዓቶች ሙሉ በሙሉ በሀገራችን የሚገኝ በመሆኑ ግብርናውን ከኢንደስትሪው ጋር የማስተሳሰር ግባችንን እውን የሚያደርግ እንደኾነ ገልጸዋል።

በጥቅሉ የተገነቡ የሚገኙ ተስፋ ሰጪ ፋብሪካዎች የከተማ አመራሩ ለኢንቨስትመንት የሰጠው ትኩርተ ከፍተኛ እንደሆነ አመላካች መሆኑን ዶ/ር ድረስ ሳህሉ ገልፀዋል።

በጉብኝቱ የደብረ ብርሀን ከተማ ተከዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸት የደብረ ብርሀን ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ጌታቸው፣ የሰሜን ሸዋ ብልፅግና ፖርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ አበበ ጨምሮ ሌሎች የከተማው አስተዳደር እና የዞን አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።

  |  የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አዲሱን የመንግሥት ሰራተኞች የቀን ውሎ አበል አከፋፈል ይፋ አድርጓል።በተጨማሪም ኮሚሽኑ ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ለመንግሥት የፌዴራል ተቋማት ...
05/10/2025

| የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አዲሱን የመንግሥት ሰራተኞች የቀን ውሎ አበል አከፋፈል ይፋ አድርጓል።

በተጨማሪም ኮሚሽኑ ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ለመንግሥት የፌዴራል ተቋማት የሰው ሀብት እና ብቃት ሥራ አስፈፃሚዎች በአዲሱ የመንግሥት ሰራተኞች ደሞዝ እና የአበል አከፋፈል ዙሪያ መመሪያ ተሰቷል።

ለሀገራችን የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች አርዓያ የሆነ ተግባር እንሆ   የተባረከ ወጣት ኮሜዲያን በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደርበኮሜዲያን እሸቱ መለሰ አማካኝነት የተቋቋመው "ለመጽደቅ የዘለቄታ"...
05/10/2025

ለሀገራችን የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች አርዓያ የሆነ ተግባር እንሆ

የተባረከ ወጣት ኮሜዲያን

በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር
በኮሜዲያን እሸቱ መለሰ አማካኝነት የተቋቋመው "ለመጽደቅ የዘለቄታ" የተሰኘ ሀገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅት በደብረ ብርሃን ከተማ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማስገንባት የመሠረት ድንጋይ አስቀምጧል።

ፕሮጀክቱ የአዳሪ ትምህርት ቤት፣ ፊዚኦ ቴራፒ ትምህርት ቤት፣ የተለያዩ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች፣ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክቶች፣ የኮሜዲያን ተሰጥኦ ማበልጸጊያ ትምህርት ቤት፣ ለሴቶች እና እናቶች የቢዝነስ ሥራ ማሠልጠኛ የሥራ ማዕከል ፕሮጀክቶችን በአካባቢዉ ላይ ያከናውናል ተብሏል።

በስድስት ሄክታር መሬት ላይ የሚገነባው ፕሮጀክቱ በደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር በእምዬ ምኒልክ ክፍለ ከተማ ሎሬት አፈ ወርቅ ተክሌ ቀበሌ ሥር በሚገኘው ጋንጎና ቦራሌ ንዑሥ ቀበሌዎች ላይ እንደሚገነባ ተገልጿል።

የሐዘን መግለጫ! በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አረርቲ ቅድስት ማርያም ቤተ-ክርስቲያን አዲስ እየተገነባ የሚገኘውን ሕንፃ በመጎብኘት ላይ ያሉ ምዕመናን ላይ በመወጣጫ መደርመስ ሳቢያ በደረሰው አስደ...
01/10/2025

የሐዘን መግለጫ!

በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አረርቲ ቅድስት ማርያም ቤተ-ክርስቲያን አዲስ እየተገነባ የሚገኘውን ሕንፃ በመጎብኘት ላይ ያሉ ምዕመናን ላይ በመወጣጫ መደርመስ ሳቢያ በደረሰው አስደንጋጭ ኅልፈተ-ሕይወት እና የአካል ጉዳት እጅጉን አዝነናል።

ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጆች መፅናናትን እንመኛለን።

ነፍስ ይማር!

የመስቀል ደመራ በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ አፄ ዘርዐ ያዕቆብ አደባባይ በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ እየተከበረ ነው።
26/09/2025

የመስቀል ደመራ በዓል በደብረ ብርሃን ከተማ አፄ ዘርዐ ያዕቆብ አደባባይ በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ እየተከበረ ነው።

Address

Railway
Debre Birhan

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ብርሀን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ብርሀን ሚዲያ:

Share