ብርሀን ሚዲያ

ብርሀን ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ብርሀን ሚዲያ, Debre Birhan.

በ2017 ዓ.ም ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 252 ባለሃብቶች ፈቃድ መስጠቱን የደብረ ብርሃን ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀደብረ ብርሃን፤ሀምሌ 14/2017...
21/07/2025

በ2017 ዓ.ም ከ36 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 252 ባለሃብቶች ፈቃድ መስጠቱን የደብረ ብርሃን ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ

ደብረ ብርሃን፤ሀምሌ 14/2017 (ደብመኮ):- መምሪያው የ2017 ዓ.ም አፈፃጸም ግምገማ እና የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ትውውቅ መድረክ እያካሄደ ነው።

የደብረ ብርሃን ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃን ገብረህይወት እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለ200 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ 36 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 252 ባለሃብቶች ፈቃድ መሠጠቱን አስታውቀዋል።

ከነዚህ ውስጥ ለ55 ባለ ሃብቶች ከ70 ሄክታር በላይ መሬት መሠጠቱን ገልጸው ሁሉም ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ ሲገቡ ከ21 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩም አመልክተዋል።

በተያያዘም በ2017 ዓ.ም 16 ኢንዱስትሪዎችን ወደ ምርት ለማሸጋገር ታቅዶ ለ5 ሺህ 200 ዜጎች የሥራ ዕድል የፈጠሩ 25 አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ምርት ሥራ ማስገባት መቻሉን አስረድተዋል።

እንዲሁም ከ58 በላይ ኢንዱስትሪዎች ተኪ ምርት ማምረት መቻላቸውን እና 8 ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ለውጭ ገበያ ምርታቸውን መላካቸውን ነው ኃላፊ ያብራሩት።

የደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ልማት ለተከታታይ 3 ዓመት በክልል ደረጃ አንደኛ በመውጣት የዋንጫ ተሸላሚ መኾን መቻሉን ጠቅሰው ለዚህ ስኬት እንዲበቃ በትጋት ለሠሩ የሥራ ኃላፊዎችንና ባለሙያዎችን አመስግነዋል።

የ2017 በጀት ዓመት አፈፃጸምና የ2018 ዓ.ም ዕቅድ አቶ ብርሃን አቅርበዋል።

ከዚህም በላይ የሚገባህ መሪ
20/07/2025

ከዚህም በላይ የሚገባህ መሪ

የድጋፍ ትብብር ስለመጠየቅየደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪ እና የቀድሞው ብርሃኑ ሙዚቃ ቤት ባለቤት የሆኑት አቶ ብርሃን ንባብ በንግድ ስራ ተሰማርተው የሚገኙ ሲሆን በንግድ ሂደት በባጃጅ መምጣትና...
17/07/2025

የድጋፍ ትብብር ስለመጠየቅ

የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪ እና የቀድሞው ብርሃኑ ሙዚቃ ቤት ባለቤት የሆኑት አቶ ብርሃን ንባብ በንግድ ስራ ተሰማርተው የሚገኙ ሲሆን በንግድ ሂደት በባጃጅ መምጣትና ሽያጭ ዘርፍ ተሰማርተው የ42 ሚሊዮን ብር እዳ እንደመጣባቸውና የመኖሪያ ቤታቸው G+1 እንዲሁም የድርጅታቸው ህንፃ G+3 እንዲሸጥ ተወስኖ እዳቸውን የሚሸፍን ባለመሆኑ ሁሉም ትብብር እንዲያደርግላቸው ይጠይቃሉ ።

የባንክ ሂሳብ ቁጥር - 1000696262587
ላቀው ሳህሌ እና አሰግድ እና እሸቴ በሚል ለዚሁ አላማ በጥምር በተከፈተው አካውንት ቁጥር እንድታስገቡላቸው ይጠይቃሉ ።

ከመሬት ሃብት ህዝብ ተጠቃሚ እንዲኾን ሴት መሪዎች ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል ተባለደብረ ብርሃን፤ሀምሌ 10/2017 (ደብመኮ)፡-የደብረ ብርሃን ከተማ መሬት መምሪያ  የደቡብ ኮሪያን የመሬት ሃብ...
17/07/2025

ከመሬት ሃብት ህዝብ ተጠቃሚ እንዲኾን ሴት መሪዎች ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል ተባለ

ደብረ ብርሃን፤ሀምሌ 10/2017 (ደብመኮ)፡-የደብረ ብርሃን ከተማ መሬት መምሪያ የደቡብ ኮሪያን የመሬት ሃብት አጠቃቀም ተሞክሮ ለሴት አመራሮች አካፍሏል፡፡

የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ እታለማሁ ይምታቱ የደቡብ ኮሪያን የመሬት ሃብት አያያዝና አጠቃቀም ተሞክሮ ለከተማና ለክፍለ ከተማ ሴት አመራሮች አካፍለዋል፡፡

ደቡብ ኮሪያ በፍጥነት ያደገች፣የመሬት ሃብት አጠቃቀሟም በቴክኖሎጂ የታገዘና የዘመነ እንደኾነም አብራርተዋል፡፡

ኢትዮጵያና ደቡብ ኮሪያ ዓመታትን የተሻገረ መልካም ግንኙነት ያላቸው ሀገሮች መኾናቸውን አስታውሰዋል።

አባቶቻችን ለኮሪያ ነፃነት የከፈሉትን ዋጋ ባለመርሳት ኮሪያውያን የመሬት ሃብታችንን አያያዝና አጠቃቀም ለማዘመን ድጋፍ እያደረጉ ስለመኾኑም ነው የተናገሩት፡፡

የደብረ ብርሃን ከተማ መሬት መምሪያ የከተማ የመሬት መረጃን የማዘመን ስራ አጠናክሮ እየሰራ መሆኑን አመላክተዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ቅመም አሽኔ የውይይት መድረኩን ሲያጠቃልሉ እንደገለጹት ተሞክሮው ተቀምሮ ለሴት መሪዎች መቅረቡ የሚያስመሰግን መልካም ሥራ ነው ብለዋል፡፡

መሬት የህዝብና የመንግሰት ትልቁ ሃብት ስለኾነ በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል ተሞክሮ ፋይዳው የጎላ ስለመኾኑም አመልክተዋል።

በተለይም ቴክኖሎጂን በመጠቀም ከመሬት ሃብት ህዝብ ተጠቃሚ እንዲኾን ሴት መሪዎች ግንባር ቀደም ሚናቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በከተማ ደረጃ የመሬት መረጃ አያያዝ ሥርዓትን ለማዘመን የተያዘው ዕቅድ እንዲሳካ ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባም ነው ወይዘሮ ቅመም ያስገነዘቡት።

በደብረብርሃን ከተማ  የጋራ መኖሪያ ቤት ለመገንባት  እየተካሄደ ያለው  ምዝገባ  ተራዘመ  ‎‎‎ከተማው በርካታ ዜጎችን የቤት ባለቤት ለማድረግ፣ የተሻለ መሠረተ ልማት ለማሟላት እና የጋራ መ...
17/07/2025

በደብረብርሃን ከተማ የጋራ መኖሪያ ቤት ለመገንባት እየተካሄደ ያለው ምዝገባ ተራዘመ
‎‎‎
ከተማው በርካታ ዜጎችን የቤት ባለቤት ለማድረግ፣ የተሻለ መሠረተ ልማት ለማሟላት እና የጋራ መኖሪያ ቤት ለመገንባት ምዘገባ እያካሄደ መኾኑን የደብረብርሃን ከተማ አሥተዳር ገልጿል።

ከተመዝጋቢ ዜጎች ፍላጎት በመነሳት የከተማ አስተዳደሩ ህብረት ስራ ተጠሪ ፅህፈት ቤት ምዝገባውን እስከ ሐምሌ 18/2017 ማራዘሙን አሥታውቋል ::

ነዳጅን ለመቆጣጠር እና ችግሮችን ለመፍታት  በደብረ ብርሃን ከተማ ውይይት ተደረገየደብረ ብርሃን ከተማ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ በነዳጅ አቅርቦትና ሥርጭት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር  ...
17/07/2025

ነዳጅን ለመቆጣጠር እና ችግሮችን ለመፍታት በደብረ ብርሃን ከተማ ውይይት ተደረገ

የደብረ ብርሃን ከተማ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ በነዳጅ አቅርቦትና ሥርጭት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡

ባጃጆች፣ዳማሶች፣የቤት መኪኖች በተደጋጋሚ በመሰለፍ ነዳጅ ከማደያ በመቅዳትና በጥቁር ገበያ በመሸጥ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት የሚሄዱበት ርቀት አደገኛ መኾኑ፤የረጂም ርቀት ተሸርካሪዎች ከዚህ ከተማ ነዳጅ ቀድተው ወደ ለሌላ ቦታ ለመውሰድ ጥረት እንደሚደረግ ተጠቁሟል።

ማደያዎች በእጅ መንሻ ነዳጅ ለማይገባው አካል መቅዳት፣ ከአሰራር ውጭ በሃይላንድና በጀሪካን ነዳጅ በህገ ወጥ መንገድ እየቀዱ በጥቁር ገበያ በመሸጥ ለኑሮ ውድነት መባባስ መንሥዔ መኾናቸው እና ሌሎች በርካታ ጥያቄዎች፣ሀሳብ አስተያየቶች ተነስተው ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ከነዳጅ አቅርቦት ባሻገር ሥርጭቱ ላይ መሠረታዊ ችግር እንዳለ የደብረ ብርሃን ከተማ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ይርጋለም ምስጋናው አንስተዋል፡፡

የተቋማቸው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጠንካራ የድጋፍና የክትትል ሥርዓት ዘርግተው በትጋት በመሥራታቸው ችግሩ ከዚህ በላይ እንዳይሰፋ ማድረግ መቻሉንም ነው ያብራሩት፡፡

ነገር ግን ሥራው ለአንድ ተቋም ብቻ የሚተው ሳይኾን በቅንጅት የሚፈጸም እንደኾነ አንስተዋል።

በመኾኑም የነዳጅ አቅርቦትና ሥርጭት ህግን ያከበረ እንዲኾን ባላድርሻ አካላት ተቋማቸውን መደገፍ እንዳለባቸው ኃላፊዋ አስገንዝበዋል፡፡

ነዳጅ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን በማሳለጥ የሀገሪቱ የልማት ግቦች እንዲሳኩ ዋና ሞተር መኾኑን የደብረ ብርሃን ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ የተከበሩ ሰለሞን ጌታቸው አብራርተዋል፡፡

ከአቅርቦት በዘለለ ሥርጭት ላይ ያለውን ጉድለት በማስተካከል ውድ የኾነውን የገር ሃብት በአግባቡ ማስተዳደርና ጥቅም ላይ ማዋል የአመራሩና በየደረጃው የባለድርሻ አካላት ኃላፊነት እንደኾነም አመልክተዋል፡፡

ለዚህም ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጠናከር ህገ ወጥነትን በጋራ መከላከል እንደሚያስፈልግ ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸት የምክክር መድረኩን ሲያጠቃልሉ እንደገለጹት ወቅታዊ ሁኔታውን እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም በአቅርቦት እጥረት ሰበብ ሥርጭቱን የማዛባትና ያላግባብ ከነዳጅ ለመጠቀም የሚደረግ ጥረት መቆምና መስተካከል እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡

ለዚህም ከመምሪያ እስከታችኛው የአስተዳደር እርከን ያለውን የህገ ወጥ መከላከል ግብረ ሃይል በማጠናከር ወደ ሥራ በማስገባትና የተጠያቂነት ሥርዓት በማስፈን ነዳጅ ሥርጭት ላይ የሚስተዋለውን ብልሽት በጋራ ማስተካከል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ነዳጅን በበላይነት እንዲያስተዳድር ኃላፊነት ከተሰጠው ተቋም ውጭ የትኛውም የፀጥታ መዋቅር ጣልቃ መግባት እንደማይችል ጠቁመዋል፡፡

ለመስኖ፣ለወፍጮና ወሳኝ ለኾኑ የልማት ሥራዎች ነዳጅ የሚሠራጭበት ሥርዓት እንደሚዘረጋም ከንቲባ በድሉ አመልክተዋል።

ለተግባራዊነቱ ሁሉም ባላድረሻ አካላት ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው የሥራ መመሪያ ሠጥተዋል፡፡

የበጎ ፍቃድ ስራ እየተገመገመ መመራቱ ለውጤቱ መሻሻል ጉልህ ሚና አለውና በርቱ ደ/ብርሃን በዚህ ተግባር ሁሌም ግንባር ቀደም ነው 👏👏👏
16/07/2025

የበጎ ፍቃድ ስራ እየተገመገመ መመራቱ ለውጤቱ መሻሻል ጉልህ ሚና አለውና በርቱ

ደ/ብርሃን በዚህ ተግባር ሁሌም ግንባር ቀደም ነው 👏👏👏

የደብረ ብርሃን  ቅድስት ስላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት ተከብሮ በሠላም ተጠናቋል
14/07/2025

የደብረ ብርሃን ቅድስት ስላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት ተከብሮ በሠላም ተጠናቋል

06/07/2025
መምሪያው  ቀደም ሲል ለተደራጁ 100 የመኖሪያ ቤት ማህበራት ቦታ እያዘጋጀ መሆኑን ገለጸ። የደብረ ብርሃን ከተማ መሬት መምሪያ 150 ሄክታር መሬት በአጭር ጊዜ የቅየሳ ስራውንና የአርሶ አደ...
20/06/2025

መምሪያው ቀደም ሲል ለተደራጁ 100 የመኖሪያ ቤት ማህበራት ቦታ እያዘጋጀ መሆኑን ገለጸ።

የደብረ ብርሃን ከተማ መሬት መምሪያ 150 ሄክታር መሬት በአጭር ጊዜ የቅየሳ ስራውንና የአርሶ አደሩን የካሳ ስሌት ለማጠናቅ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።

የመምሪያው ሃላፊ ወይዘሮ እታለማሁ ይምታቱ እንደገለጹት ለ100 የመኖሪያ ቤት ማህበራት 150 ሄክታር መሬት የቅየሳ ስራውንና የአርሶ አደሩን የካሳ ስሌት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል።

ሥራውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ከተቋማቸው ባለሙያዎች በተጨማሪ የሰሜን ሸዋ ዞን ባለሙያዎችን አሳትፈው ሥራው በርብርብ እየተሰራ ስለመሆኑም አብራርተዋል።

አርሶ አደር ኪዳኑ መኮንን እና አርሶ አደር ወንዳጥር ኀይለማሪያም እንደገለጹት መንግሥት መሬታቸውን ለልማት ፈልጎታል ተብለን በተደጋጋሚ ውይይት አድርገናል። መሬት የመንግሥትና የህዝብ ሀብት መኾኑን ተረድተን አምነንበት በፈቃዳችን ማሳችንን አስረክበናል ብለዋል።

በሚከፈላቸው ካሳም የተሻሻለ ዝርያ ያላቸውን ከብቶች በማርባትና ተዛማጅ የልማት ሥራዎች ላይ ለመሰማራት ዕቅድ እንዳላቸው አመልክተዋል።

ነገር ግን የራሳችንም ሆነ የልጆቻችን የመስሪያና የመኖሪ ቦታችንም ጎን ለጎን ሊታሰብበት ይገባል።ይኽን ተግባር ከተማ አስተዳደሩ በትኩረት ይዞ መሥራትና መደገፍ አለበት ሲሉም ተናግረዋል።

Via~ DBCC

ከተማው ለአዲስ ባጃጆች አዲስ ታርጋም ሆነ ዝውውር ላልተወሰነ ጊዜ የማይሰጥ መሆኑን  ገለጸደብረብርሃን፣ መጋቢት 24/2017 ዓ/ም (ደብመኮ)፦ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከመጋቢት 30...
02/04/2025

ከተማው ለአዲስ ባጃጆች አዲስ ታርጋም ሆነ ዝውውር ላልተወሰነ ጊዜ የማይሰጥ መሆኑን ገለጸ

ደብረብርሃን፣ መጋቢት 24/2017 ዓ/ም (ደብመኮ)፦ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከመጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ለአዲስ ባጃጆች አዲስ ታርጋም ሆነ ከሌላ ቦታ በዝውውር የሚመጡ የባጃጅ ባለንብረቶችን ላልተወሰነ ጊዜ የማያስተናግድ መሆኑን አስታውቋል።

ከተማ አስተዳደሩ ከመጋቢት 30 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ አዲስ ታርጋም ሆነ ከሌላ ቦታ በዝውውር ለምታመጡ የባጃጆች ባለንብረቶች የዝውውር አሰራር የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።

በሂደት ላይ ያላችሁ በቀሩት ቀናቶች በከተማው ትራንስፖርት ጽህፈት ቤት ተመዝግባችሁ በማህበር እንዲትታቀፉ ሲል አመላክቷል።

ይህ መፍትሄ የተወሰደው የትራፊክ መጨናነቅን ለማስተዳደርና በቂ የባጃጅ ትራንስፖርት በከተማው እንዳለ ጠቅሶ አንዱ የህዝብ ጥያቄ መሆኑን አንስቷል።

በቀጣይ ሌሎች መፍትሄዎችን እንደሚወስድ ተመላክቷል።

Address

Debre Birhan

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ብርሀን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ብርሀን ሚዲያ:

Share