Eng'r MohammedJewad- ኢ/ር መሃመድ ጀዋድ

Eng'r MohammedJewad- ኢ/ር መሃመድ ጀዋድ ነፃ፣ ፍትሃዊ ሃሳብ

15/09/2025

‼️
📌 ❌



 #ግእዝ፡  🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥📌🔥🔥🔥 የአማራ ክልል ባለስልጣናት በሞዐ ተዋህዶ አስተሳስብና ፍልስፍና የተጠለፈው ገና ህወሃት/ኢህደግ መንግስት ሳይወድቅ ነበር፡፡ በ2010 የኢህአዲግ አገዛ...
14/09/2025

#ግእዝ፡
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥📌🔥🔥🔥

የአማራ ክልል ባለስልጣናት በሞዐ ተዋህዶ አስተሳስብና ፍልስፍና የተጠለፈው ገና ህወሃት/ኢህደግ መንግስት ሳይወድቅ ነበር፡፡ በ2010 የኢህአዲግ አገዛዝ በህዝብ ትግል ወድቆ የዶ/ር አብይ አህመድ መንግስት ሲመጣ በሞዐ ተዋህዶ አስተሳሰብ የተጠለፈው የአማራ ክልል መንግስት እቅድ ኢትጵያን ወደ 1966 መመለስ ነበር፡፡ የደርግና የኢህአግ ዘመንን ልክ እንደ ኢማም አህመድ (1529 _1543) የባከነና በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የማይመዘገብ ዘመን አድርጎ መውስድ ነበር፡፡ ይህንንም ለማሳካት አብይን ለመጠቀም ብዙ ስራ ተሰርቷል፡፡ የሞዓ ተዋህዶ አስተሳሰብ መጀመርያ አካባቢ ያሸነፈ ቢመስለውም ቀስበቀስ አብይም ይህን አመለካከት እንደማይገዛው ብሎም የሀገሪቱ ህዝቦች ነበራዊ ሁኔታ የዘውዳዊ ስርዓቱን ለመመለስ እንደማይፈቅድ ሲገባው አላማውን በሀይል ለማሳካት የአማራ ክልልና ከተሞችን (በተለይም አድስ አበባን) መቆጣጠር እንዳለበት አቋም ወስዶ በህቡዕ መንቀስቀስ ጀመረ ባንድ በኩል ጫካ ሀይል ማሰልጠን በሌላ በኩል ደግሞ የመንግስት ቢሮክራሲውን መጥለፍ ጀመረ፡፡ ከጥቂት አመታት በህዋላ አድስ አበባም ከጁ እንደወጣች የገባው ይህ የዘውዳዊ መንግስት ናፋቂ ሀይል ልክ ህወሃት ጓዟን ነቅላ መቀሌ እንደገባቸው ጓዙን ነቅሎ ባህር ዳርና ገዳም ገባ፡፡ ሞዐ ተዋህዶ የክልሉን ሙሉ መዋቅር በመቆጣጠር ስራውን ጀመረ፡፡ የዚህ ቡድን ሀይል በአራት ምሽጎች መሽጎ ስራውን መስራት ጀመረ፡፡

📌 ፡ በጫካ የመሸገው ሀይል ራሱን የአማራ ፋኖ ብሎ ሲጠራ አላማው የትጥቅ ትግል ማድረግ፣ በክልሉ ውስጥ ብልጽግናን የሚደግፉ ሀይሎችን ማገትና ማሥወገድ፣ ህዝብ በብልጽግና መንግስት ላይ እንዳምጽ ህዝብን ማማረር ነው፡፡

📌 ፡ ይህ ራሱን ራሱን የአማራ የዲያስፖራ ብሎ የሚጠራው ቡድን፡፡ የዲያስፖራው ቡድን ሀላፊነቱ ገንዝብ ማፈላለግ፤ ሚድያን በመቆጣጠር ፕሮፓጋንዳ መስራት፣ ከቻለ የአለም መንግስታትን አማራና ኦርቶዶክስ ተጭቁኗል ብሎ ማሳመን ነው፡፡
📌 ፡ ይህ ሀይል ከቀበሌ እስከ ፌደራል ባለው የመንግስት መዋቅር ውስጥ የገባውና የክልሉን መዋቅር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የተቆጣጠረው የሞዓ ተዋህዶ ሀይል ነው፡፡ የህ ሀይል ተልኮው አንደኛ በክልሉ የሚወጡ ፓሊሲዎችን የኦርቶዶክስ ተዋሀዶን ፍላጎት የሚያረካና ያመካለ፣ ለዘውዳዊ ስርዓት መደላድል እንድሆኑ አድርጎ ማውጣት፣ ሁለተኛ መረጃዎችንና የመንግስት ሚስጢሮችን ከፌደራሉ ብልጽግና በማውጣት ለጫካው ሀይል፣ ለዲያስፖራው ሀይልና ለዩኒቨርሲቲው ሀይል ማቀበል ነው፡፡ በተለይ ፋኖን በሚመለከት የሚወሰኑ ወታደራዊ ሚስጥሮች በአስቸኳይ ጫካ ላለው ሀይል እንድደርሰው ያደርጋል፡፡ ለመከላከያው የተሳሳተ መረጃ በመስጠት መከላከያው እንድመታ ያደርጋል፡፡ በአጠቃላይ መንግስታዊ ስልጣኑን እንደ ልባስ በመጠቀም የብልጽግና መንግስትን ከውስጥ ለመጣል ይሰራል፡፡

📌 ፡ ይህ ሃይል ተልኮው ሁለት ነው፡፡ ይህ ሀይል የዩኒቨርሲቲውን አመራርነት በመቆጣጠር አንደኛ የፋይናንስ ምንጭ መሆን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሰው ሃልይ ነው፡፡ የሰው ሃይል ሲባል ዩኒቨርሲቲው ያሉ መምህራኖችን በመጠቀም እቅድ ያወጣል፣ ስልጠና ይሰጣሉ፣ በራሪ ወረቀትቶችን ያዘጋጃሉ፣ አስፈላጊ ሲሆን ተማሪ ያሳምጻል፣ ይገድላል ያስገድላል።
ይህ የህቡዕ አሰራሩ እየተነቃበት ሲመጣና የነደፈው ስልትና ስትራቴጅ እደከሸፈ ሲገባው አሁን ደግሞ የግዕዝን አጀንዳ እንደ አድስ ስልትና ስትራቴጂ ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ የግዕዝ አጀንዳ በከተማ የመሸገው የሞዓ ተዋህዶ አጀንዳ እንጅ ፈጽሞ የህዝብ አጀንዳ አይደለም፡፡ የአማራ ህዝብም ፍላጎት ልጆቹ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ተምረው በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ትውልድ እንደሆኑ፤ በአለም ገበያ እንድወዳደሩ ነው፡፡ በቋንቋ ደረጃም ቢሆን እንደ እንግሊዘኛ፣ ፈረንሳይኛ፣ አረብኛና ቻይንኛ የመሳሰሉ ቋንቋዎችን ተምሮ አለም ጋር መግባባት እንጅ ማንም ሳይነካው ራሱን አጥፍቶ ገዳምና ቤተ ክህነት ውስጥ የተቀበረ ቋንቋን ከመቃብር መቀስቀስ ለአማራ ህዝብ አይጠቅመውም፡፡

ነገር ግን በተለይ ወሎ አካባቢ አንጻራዊ ሰላም መኖሩና መማር ማስተማር አለማቋረጡ በከተማ ተልዕኮ የተሰጠውን የአማራ ክልል ባለስልጣናት/ብልጽግና (ሞዐ ተዋህዶ) ሀላፊነትህን በብቃት አልተወጣህብ በሚል አስገምግሞታል፡፡ በመሆንኑም የክልሉ መንግስት ውስጥ የተሰገሰገው ሞዓ ተዋህዶ እቅድ በ2018 በሙስሊም በዝ የክልሉ አካባቢዎች ትርምስ መፍጠር፣ የመማር ማስተማር ሂደቱን ማስተጓጎልና ህዝብ በብልጽግና መንግስት ላይ አመኔታ እንዳይኖረው ማድረግ ነው፡፡ ይህንን እውን ለማድረግ በግዕዝ ቋንቋ ስም የቤተ ክህነት ትምህርትን በመላው አማራ ክልል ውስጥ እንድሰጥ ማድረግ የሚለው ውሳኔ ተውስኗል፡፡

ለዚህ ፕሮጀክት አራቱም ሀይላት የተለያየ ድርሻ ሲሰጣቸው፡-

📌 በዩኒቨርሲቲ የመሸገው ሀይል የከሪኩለም ስራ እንድሰራ አሳይመንቱን ውስዷል፡፡ ለዚህ ወሎ ዩኒቨርሲቲና ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተልኮውን ውስዶው ከቀሳውስት ጋር በመምከርና በመተባበር በትምህርት ቤቶች የሚሰጡትን ሀይማኖታዊ ትምህርት በግዕዝ ትምህርት ስም አዘጋጀትዋል፡፡ ይህንንም ሂደት ሞዐ ተዋህዶ ቅዳሜታ (መስከረም 03/2018) ለዚሁ አለማ በሚሰራው በአማራ ቲቪ በመቅረብ ፍንጭ ሰጥቷል፡፡

📌 በአማራ ብልጽግና ውስጥ የመሸገው ሀይል ጉዳዩን በክልሉ ፓርላም እንድወሰን በማድረግ ህጋዊ ለማመሰል ሰርቷል፡፡

📌 የዲያስፖራው ቡድን ልክ ግዕዝ ውስጥ አለም ያልደረሰበት እውቀት/ሳይንስ ያለ በማስመስል ፕሮፓጋንዳ ስራውን እንድሰራ አሳይመንት ተስጥቶቷል፣ ሰርቷልም፡፡

📌 ጫካ ያለው ሀይል ደግሞ በ2018 ዓ/ም ትምህርት መከልከሉን እንድተውና እንዳውም ትብብር እንዳደርግ ሀላፊነቱን ወስዷል፡፡ ለዚህም አይነተኛ ማሳያ የሚሆነው በግዕዝ ቋንቋ ስም የተዘጋጀው ሀይማኖታዊ ትምህርት ተቃውሞ ሲገጥመው (መስከረም 03/2018) ትምህርትን እከለክላለሁ ብሎ መግለጫ አውጥቷል፡፡

ሌላው መታወቅ ያለበት ይህ ሀይል ብዘሀነትን ስለማይቀበል ግዕዝን እንደ አንድ ቋንቋ በክልሉ ማሰጠቱ እንደ ኦሮምኛና ትግረኛ ያሉ የፌደራል ቋንቋዎች በክልሉ እንዳይሰጡ በሩን መዝጋቱ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሌሎች ህቦችን ቋንቋ ላለመማር የሂደበትን ርቀትና ለሌሎች ህዝቦች ያለውን ንቄት ያሳይል፡፡

በመሆኑም እኛ የወሎ ህዝቦች የሚከተሉትን ጥያቄዎችና ምክረ ሃሳቦች ለፌደራሉ መንግስት ማቅረብ እንፈልጋለ፡-

🔥 ሀይማኖትና ትምህርት ይለያያሉ ትምህርት ሴኩላር ነው የሚለውን የሀገሪቱን ህግና አሰራር በመጣስ ምንም ህዝብ ሳይወያይበት ክልሉ ውስጥ ከኖራችሁ እኛ ያመጣነውን ነገር ከመቀበል ውጭ አማራጭ የላችሁም በማለት በግዕዝ ቋንቋ ሰበብ በህጻናት ላይ ሀይማኖታዊ ትምህርት ሊጫንብን ስለሆነ የትምህርት ሚኒስተርና ፌደራሉ መንግስት በአስቸኳይ እንዳቆምልን፡፡

🔥 በቅርቡ የሞዐ ተዋህዶው መስራች ቄስ ፈንታሁን ዋቄ በግልጽ እንደተናገሩት አማራ ክልል ያለው ብልጽና ሀይል ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ በሞዐ ተዋህዶ ተጠልፏል፡፡ የአማራ ክልል ብልጽግና የሚሰራው የሞዐ ተዋህዶ አስተሳስብ እንድነግስ እና ብልጽግና መንግስት በህዝብ እንድጠላና እድወድቅ ነው፡፡ በመሆኑም የአማራ ክልል መዋቅርን በደንብ እንድፈትሽ ምክረ ሀሳብ እናቀርባለን፡፡

🔥የክልሉ መንግስት የወሎ ህዝቦችን ከፈለገ ለማጥፋት ካልቻለ ደግሞ ማንነታቸውን በመደፍጠጥ የሞዐ ተዋህዶ አራማጅ ማድረግ ነው፡፡ በመሆኑም የወሎ ህዝብ የራሱ እሴት ያለው በብዝሀ ብሄርና ሀይማኖት የሚያምን ህዝብ ስለሆነ የራሱ ክልል መስርቶ እራሱን በራሱ እንዳስተዳድር እንድፈቀድለት ስንል
ጥያቄ አዘል ምክረ ሀሳብ እናቀርባል፡፡

ማሻአላህ የኦለማ ምክር ቤት ማብራሪያ የሰጠበትና የቀጣዩ ምርጫ በወረዳ መጅሊስ ዋና ፕሬዝዳንና ምክትል ፕሬዝዳን እንድሁም  ዋና ፀሀፊ ኢስላማዊ(ሸሪአ) እውቀት መመዘኛ ማደረጉና አሊሞችን መሪ...
06/08/2025

ማሻአላህ የኦለማ ምክር ቤት ማብራሪያ የሰጠበትና የቀጣዩ ምርጫ በወረዳ መጅሊስ ዋና ፕሬዝዳንና ምክትል ፕሬዝዳን እንድሁም ዋና ፀሀፊ ኢስላማዊ(ሸሪአ) እውቀት መመዘኛ ማደረጉና አሊሞችን መሪ ማድረጉ በጣም ትልቅ የሆነ ሙስሊሞችና ኢስላም እንደታረቁ የሚያደርግ ስራ ነው።

06/08/2025

📍ለጽኑ ተቋማዊ ለዉጥ በትጋት እንሰራለን🖋
በደቡብ ወሎ በሚገኙ 29ቱም ወረዳዎች (ወረዳዎች) የመራጮች ምዝገባን በይፋ ተጀምሯል።
ይህም በዞኑ ነጻ የሆኑ የእስልምና ተቋማት መመስረት ታሪካዊ ምዕራፍ ነው። አስተዳደራዊ እርምጃ ብቻ ሳይሆን በሀይማኖት ተቋም ግንባታ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እና የማህበረሰብ ባለቤትነትን መሰረት ያደረገ ተግባር ነው። ለብዙ ትውልዶች የወሎ ህዝበ ሙስሊም ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን የሚመሩ መዋቅሮችን በመቅረጽ የመሳተፍ መብቱን ለማስመለስ ሲመኝ የነበረ ሲሆን የዛሬው እርምጃ ያንን ራዕይ እውን ለማድረግ ቅርብ ሆኗል።
ወደ ተቋማዊ ነፃነት የተደረገው ጉዞ ያለ ተቃዋሚ አልነበረም። ከኢስላማዊው ማህበረሰብ ውስጥም ሆነ ከውጪ ራሳቸውን የቻሉ ኢስላማዊ ተቋማትን የሚከላከሉ ወይም የሚጠይቁ ግለሰቦች እና ቡድኖች አሉ። አንዳንድ የውጭ ተቺዎች በፖለቲካዊ ዓላማዎች የሚነዱ ቢሆኑም፣ ውስጣዊ ተቃውሞ ብዙውን ጊዜ ከፍርሃት፣ ከእዉቀት ማነስ፣ ከተሳሳተ መረጃ ወይም ጣልቃ ገብነትነ አቋም ናፋቂነትና ታማኝነት የመነጨ ነው። ይህ ውስብስብነት ፈተናው መዋቅራዊ ብቻ ሳይሆን ጥልቅ ርዕዮተ ዓለም እና ባህላዊ፣ የታሰበ ተሳትፎ እና ሁሉን አቀፍ ውይይት የሚጠይቅ መሆኑን ያሳያል።

በዞኑ 1.1 ሚሊዮን የሚጠጉ መራጮች ለመመዝገብ አቅደን በእንቅስቃሴ ላይ ስንሆን በምርጫው መመሪያ መሰረት በዛሬዉ እለት ከክልላቸን የምርጫ ቦርድ በተሰጠን ድጋፍ 131 መስጂዶች ምዝገባ አስጀምረናል። ከ2 ሺ አምስት መቶ በላይ መስጅዶች ምዝገባ ለማካሄድ መንገዱን ጀምረናል፡፡
የህዝቡ ቁርጠኝነት እንዳለ ሆኖ በርካታ ውስጣዊ እና ውጫዊ ሁኔታዎች የምርጫውን ሂደት ለስላሳነት ማደናቀፍ ቀጥለዋል። እነዚህም እንደባለፈው ስርዓት የፖለቲካ ጣልቃገብነት ናፋቂዎች ፣ የአስተዳደር መጓተት፣ በቂ ሀብት አለማግኘት፣ እና አንዳንድ ጊዜ በለውጥ ስጋት የሚሰማቸውን በንቃት ማበላሸት ናቸው። በተጨማሪም ተሳትፎን ለማሳሳት እና የጋራ ውሳኔን ለማዳከም የተሳሳቱ የመረጃ ዘመቻዎች እና የፍርሀት ዘመቻዎች ተዘርግተዋል። በተለይ ሙስሊሙ ነፃና ገለልተኛ ተቋም እንዳይኖረዉ የዉስጥ ልዩነትን የሚያራግቡና ሙስሊሙ ተቋም አልባ ሆኖ እንዲቀጥል እንዲሁም በገለልተኛ የምርጫ አስፈፃሚ ዉስጥ የራሳቸዉን አጀንዳ ለማራመድ ሙስሊሙን ለማባጣበጥ ተግተዉ የሚሰሩ ኃይሎች መኖራቸዉ ተደርሶበታል፡፡ የደቡብ ወሎ ሙስሊም ማህበረሰብን ፍላጎት በትክክል የሚያንፀባርቅ፣ ፍትሃዊ፣ ግልጽ እና ሁሉንም ያሳተፈ የምርጫ ሂደት ለማረጋገጥ እነዚህ መሰናክሎች እውቅናና ስልታዊ በሆነ መንገድ መፍታሄ እያስቀመጥን ምዘገባዉን በህብረተሰባችን ዓቅምና አዉቀት በአላህ ፈቃድ እንደጀመርነዉ እናጠናቅቃለን።
ዛሬ ሀምሌ 5 ቀን 2017 በወሎ ሙስሊሞች ለሀይማኖታዊ ፍትህ፣ ውክልና እና በእኩልነት የማስተዳደር ትግል ረጅም እና ብዙ ጊዜ በሚያሳምም ታሪክ ውስጥ እንደ ታላቅ ቀን ሆኖ ቆሟል። ይህ ማህበረሰብ ለመቶ አመታት የተገለበትን የፅናት እና የጋራ መንፈስ ማሳያ ነው። ይህ ቀን የወሎ ሙስሊሞች በፍትህ፣ በአንድነት እና በእስልምና መርሆች በመመራት በንቃት ተሳትፎ የእምነት ተቋሞቻቸውን ትክክለኛ የባለቤትነት መብት የሚያገኙበት አዲስ ምዕራፍ መጀመሩ ያወሳል።
ይህ ወደ አድስ፣ አካታችነት እና ተቋማዊ ታማኝነት ሰፋ ያለ እንቅስቃሴ ውስጥ የመጀመሪያው እርምጃ ሆኖ ተመዝግቧል። በዚህ ሂደት ውስጥ የሁሉም ሙስሊሞች ንቁ ተሳትፎ የዜግነት ግዴታ ብቻ ሳይሆን ከእኛ በፊት ለነበሩትም ሆነ ለሚከተሏቸው አካላት የሞራል ኃላፊነትም ጭምር ነው። ይህንን ለውጥ በጥበብ፣ ግልጽነት፣ በቡድንና በጋራ የመወሰን እና በእምነት ላይ የተመሰረተ ፍትህን በማያወላውል ቁርጠኝነት እናስፋፋለን።

የማስተዋወቂያ እና ህዝብ ግንኙነት
የደቡብ ወሎ ዞን ኢስላሚክ ጠቅላይ ምክር ቤት ምርጫ ቦርድ

ቻናሉን ይቀላቀሉ ! 📍

06/08/2025

ብቁ የመጅሊስ መሪዎችን ወደፊት በማምጣት የህዝበ ሙስሊሙን ጥያቄ ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ይገባል‼️
ልዩነትን ማጥበብ ሙስሊሙን አንድነት መጠበቅ ይገባል።

መኮንን ላዕከ ተዋናይና ቀልድ አዋቂ ብቻ አይደለም፤ ለተፈጥሮና ለማህበረሰባዊ እሴቶች ያለው መረዳትም የተለየ ነው። ቆንጆ ውይይት ተከታተሉ። የኑሴንም ቻናሉ ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ሼር እና...
01/08/2025

መኮንን ላዕከ ተዋናይና ቀልድ አዋቂ ብቻ አይደለም፤ ለተፈጥሮና ለማህበረሰባዊ እሴቶች ያለው መረዳትም የተለየ ነው። ቆንጆ ውይይት ተከታተሉ። የኑሴንም ቻናሉ ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ሼር እናድርግ። ቀጣዩ እንግዳ እገሌ ቢሆን ብሎ ጥቆማ መስጠትም ይቻላል።

መኮንን ላዕከ በሀገራችን ከሚገኙ አንጋፋ ተዋንያን አንዱ ነው። በፊልም፣ በቴአትር፣ በኮሜዲና በድራማዎች ላይ በመተወን ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያገኘ ሲሆነ በእስካሁኑ ቆይታው በፊልሙ ዘ...

01/08/2025

የሞዓ ተዋህዶ ጉዳይ እንዲህ ጥርት ብሎ መውጣቱ በጣም አሪፍ ነው።

27/05/2025

"በህይወቴ የሚፀፅተኝ ነገር ቢኖር ከብልፅግና ጋር መቆሜ ነው ... አንድም ቀን ቢሆን እራሱ ፅዋው መራራ ነው"... መሳይ መኮንን ከብልፅግና ጋር በድጋሚ አብሮ እንዲሰራ በሜጀር ጀነራል ተስፋይ አያሌው ሲጠየቅ የሰጠው ምላሽ ነው 😀

ሰው በዚህ ልክ ብልፅግናን የሚጠየፍበት ጊዜ ላይ ደረሰን። ኢህአዴግ እንደዚህ ቢባል ኖሮ .."በስብሰናል ፣ ሬት ሬት ብለናል" ... ብሎ በቅፅበት ግምገማ ማድረግ ይጀምር ነበር።

ብልፅግና ግን ለውጡ ፣ እድገቱ ያመጣው በጎ ተፅዕኖ ነው ብሎ በለመደው የፕሮፓጋንዳ ማጀብያ ጭፈራ መወራጨቱን ቀጥሏል 😀

 INSA- የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር   በዘርፉ ተሰጥኦና ፍላጎት ያላቸው ታዳጊ ወጣት ተማሪዎችን በክረምት/ሰመር ትሪፕ ለማሰልጠን ይፈልጋል።ፍላጎቱ ያላችሁ ቀጥሎ ባለው Link...
27/05/2025



INSA- የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በዘርፉ ተሰጥኦና ፍላጎት ያላቸው ታዳጊ ወጣት ተማሪዎችን በክረምት/ሰመር ትሪፕ ለማሰልጠን ይፈልጋል።
ፍላጎቱ ያላችሁ ቀጥሎ ባለው Link በመግባት በፍጥነት መመዝገብ ትችላላችሁ።

https://talent.insa.gov.et/?fbclid=IwZXh0bgNhZW0CMTEAAR5o32GAV-zSO4pk2NwL3Asz_1pNn5edHzBfZ1HYrAx2AUYaEAWT_b86cCKWZA_aem_N_l7t3f7HXx2yV08-LxJnw

ወላጆች ፍላጎት ያላቸውና በዘርፉ ላይ ሆቢ ያላቸው ልጆቻችሁን ፍላጎት ካላቸው አግዟቸውና እንዲመዘገቡና እንዲመረጡ ርዷቸው።

Address

Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Eng'r MohammedJewad- ኢ/ር መሃመድ ጀዋድ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share