29/11/2025
መገን አፈጣጠር መገን አንቺ ሆየ
እንዴት አድርጎ ነዉ የሰራሽ ጌታየ
ሁሉም ሸጋ ሸጋ ከወዲያ እስከወዲህ
ልቤን አፍዛችሁ እረፉት እንግዲህ
እኔም እግሬ ሲሮጥ ከጎጃም ተነስቶ
ከሞጣ ባህርዳር ጋሸና እና እስታይሽ ሁሉን ተመልክቶ
በወልዲያ ዙሮ በ መርሳ ዉርጌሳ
በዉጫሌ እና ሀይቅ ደሴ ላይ ተመርቶ
አደንዝዞኝ ቀረ በወሎዎች ሽቶ
ይህ አልበቃዉ ብሎ በፀሎት ብመለስ ወደ ሀገሬ ሞጣ
ቶሎ ድረስ ብሎ መልክት እየመጣ
አላስችለኝ ብሎ ወሰንኩኝ ልመጣ
እናማ ቆንጅየ መገን የወሎ ልጅ
ሳላይሽ አልቀርም የፈጀዉን ቢፈጅ
ብየ ወሰንኩኝ እና በአንድ ልብ ሁኜ
በ መርጦለማርያም በአባይ በበርሃዉ
ጉዞየን ጀምሬ ገና በማለዳዉ
አንቺን ለማየት አይኔ እንዳማተረ
እንደ አሰበ አልቀረም ይኼው ተጀመረ
ከመካነ ሰላም ገና ከመድረሴ
አሁን ለምን ይሆን ከንፈሬን መላሴ 😂
ይህ አልበቃኝ ብሎ ዶባን አቋርጨ በገራዶ በኩል ገባሁኝ ከደሴ
ከደሴ ገብቸ አይኔ እያማተረ በየ መስመሩ ዳር ያቆመኝ ጀመረ
አቤት ምን አይነት ነው ደሴ ገራ ገሩ
ከእዚህ ላይ አስቀሪኝ ይፈፀም ነገሩ።
ሙሉጌታ አበበ
ወሎ ደሴ