ወሎ ደሴ

ምነው የጁን ባየ!ይሄ በየወንዙ ኮፋ አገዳ በልቶ አጃኢብ የሚለው፣የየጁን አዋየ ያልቀመሰው ሰው ነው።እንጅማ ቢቀምሰው የየጁን አዋየ፣የየጁን ጥንቅሽ፣እንደው የጁን የጁን፣ የጁን ይል ነበረ ሲነ...
16/07/2025

ምነው የጁን ባየ!

ይሄ በየወንዙ ኮፋ አገዳ በልቶ አጃኢብ የሚለው፣
የየጁን አዋየ ያልቀመሰው ሰው ነው።

እንጅማ ቢቀምሰው የየጁን አዋየ፣
የየጁን ጥንቅሽ፣
እንደው የጁን የጁን፣
የጁን ይል ነበረ ሲነጋ ሲመሽ።
ደስየ ደምሌ

እሷ የ24 ዓመት ወጣት ነበረች። ከኮሌጅ ትምህርቷን እንዳጠናቀቀች ነበር።እሱ የ3 ወር ህፃን ነበር። ከአንድ ሆስፒታል ውጪ በካርቶን ሳጥን ውስጥ ተጥሎ የተገኘው እንዲህ ከሚል ማስታወሻ ጋር ...
15/07/2025

እሷ የ24 ዓመት ወጣት ነበረች። ከኮሌጅ ትምህርቷን እንዳጠናቀቀች ነበር።
እሱ የ3 ወር ህፃን ነበር። ከአንድ ሆስፒታል ውጪ በካርቶን ሳጥን ውስጥ ተጥሎ የተገኘው እንዲህ ከሚል ማስታወሻ ጋር ነበር፦
"ይቅርታ አድርጉልኝ። እባካችሁ ውደዱት።"
ማንም ሊወስደው አልመጣም።
ቤተሰብም ሆነ ወገን አልጠየቀውም። ምንም የስልክ ጥሪ አልነበረም... ዝምታ ብቻ።
በዜና ላይ "ህፃኑ ኤልያስ" ብለው ሰየሙት። ነገር ግን ሁሉም ሰው መጨረሻው የመንግስት የህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ እንደሚሆን ገምቶ ነበር።
ከእሷ በቀር።
ራሄል እናት የመሆን ምንም እቅድ አልነበራትም። እሷ በሆስፒታሉ የህፃናት ማቆያ ክፍል በበጎ ፈቃደኝነት ታገለግል ነበር።
ነገር ግን ለመጀመሪያ ጊዜ እቅፍ ስታደርገው፣ ጥቃቅን እጆቹ ጣቷን አጥብቀው ያዙና ሊለቋት አልቻሉም።
ልቧም አልለቀቀውም።
የጉዲፈቻ ተቋሙ "ገና ወጣት ነሽ፣ ብቻሽን ነሽ፣ ልምድም የለሽም" አሏት።
እሷም እንዲህ አለቻቸው፦
"ባል ላይኖረኝ ይችላል። ገንዘብም ላይኖረኝ ይችላል። ነገር ግን ፍቅር አለኝ። እሱ ደግሞ ከምንም ነገር በላይ የሚያስፈልገው ይሄንን ነው።"
ኤልያስን በጉዲፈቻ ወሰደችው።
የእሷ ነጭ ቆዳና የእሱ ጠይም ሉጫ ፀጉር የብዙዎችን አይን ይስብ ነበር።
የሰዎችን ሹክሹክታ ትሰማ ነበር፦
"በፍፁም ልጇ አይመስልም!"
"አመት እንኳን አትቆይም።"
"ሲያድግ ይጠላታል።"
ነገር ግን ነፋስና ዝናብ ሲበረታ እንዴት ተጠግቷት ከእቅፏ እንደማይወጣ አላዩም።
ወይም ደግሞ የፒያኖ ትምህርቱን ክፍያ ለመሸፈን ብቻ ሶስት ስራዎችን እንደምትሰራ አላወቁም።
ወይም ለመጀመሪያ ጊዜ "እማዬ" ብሎ ሲጠራት እንዴት በእንባ እንደታጠበችም አላዩም።
ጀግንነትን፣ የመኝታ ሰዓት ታሪኮችን እና ወሰን የሌለውን ፍቅር እየመገበች አሳደገችው።
ዓመታት ነጎዱ።
ኤልያስም ቁመናው ገዝፎ፣ ደግና ብሩህ አዕምሮ ያለው ወጣት ሆነ።
18 ዓመት ሲሞላውም በነፃ የትምህርት ዕድል የሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ገባ።
በምረቃው የእራት ግብዣ ላይ መድረክ ላይ ወጥቶ እንዲህ አለ፦
"ሰዎች ሁልጊዜ 'እውነተኛ እናትህ ወዴት ናት?' እያሉ ይጠይቁኝ ነበር።
መልሱ ይኸውላችሁ፤ እሷ እዚች ጋር ናት።
ማንም ያልፈለገኝን እኔን የመረጠችኝ ሴት።
ስም፣ ቤትና የወደፊት ተስፋ የሰጠችኝ።
እሷ ምናልባት አልወለደችኝም ይሆናል...
ነገር ግን ህይወቴን አትርፋለች።"
በክፍሉ ውስጥ የነበሩት ሁሉ አለቀሱ።
ራሄልም እንባዋን መቆጣጠር አቃታት።
ኤልያስ ግን ፈገግ ብሎ በጆሮዋ እንዲህ ሲል ሹክ አላት፦
"እማዬ፣ አሁንም እጄን እንደያዝሽልኝ ነው። እኔም በፍፁም አልለቅሽም።"

(ከማሕበራዊ ሚዲያ የተገኘ)❤️❤️

ሀገር እና ቀለም።።።።።።።።።።።።በዱበርቴ ልሳን ፣በገንዳው ወዳጃ ፣ወሎ ያንቺን ሀገር ፣ጀማው ተጎናብሶ !እያደር አቃንቶት ... ከፍ አርጓት ላደራ ፣በሩቅ ይታየኛል ፣የሸጋ ልጅ ቀዬ እንደ...
14/07/2025

ሀገር እና ቀለም
።።።።።።።።።።።።
በዱበርቴ ልሳን ፣
በገንዳው ወዳጃ ፣
ወሎ ያንቺን ሀገር ፣
ጀማው ተጎናብሶ !
እያደር አቃንቶት ... ከፍ አርጓት ላደራ ፣
በሩቅ ይታየኛል ፣
የሸጋ ልጅ ቀዬ እንደ መዲና በር ... እንደ መካ
ጎራ ።
( ከቶ ምን ይገዳል ... !
አዎና ...
በወሎ ሃሪማ ፣
ለሓድራው ባለሟል ፣
ገንዳው ረውጮ ያብሽሩ በረካ በስምሽ ሲጀባ ፣
ጎራ አይጋርደውም ...
የጁን በጁ ብሎት ሰው የመሆን ቱፍታ ለኸልቁ
ሲገባ ።
አይቸውስ የለ ... !
መንደራ ገደማ ፣
የነ ሸህ ለጋን ጥጥ ከራሃማ አፍርቶ ፣
አረዳው ፈርቅጦ ... በመጀኑ ዳምጦ ፣
ያብሮነቱ ጋቢ ፣
የፍቅር ቢሊኮው ለሰላሙ ሽምን - ሃራ ተደውሮ

ይሄው ዛሬም ድረስ ...
ስንቱ ነጃ ወጣ ... መውሊድና ሸጋ ባንድ ቀን
ዘይሮ ።
ሻሂ ከንፈርዋ ...
ዳማ ከሴየዋ ...
ወዝሽን የያዘው ፣
የጎንቢሶው ሽታ ቢቀለኝ እያለ ፣
ያንጨፈጨፈበት ጨረቲ ገላና ጠይሟል
እስታሁን ፣
ከዛ ቀን ጀምሮ
የታጠበው ሁሉ ፣
ስንቱን ቀልቡን ይዞ ... ስንቱ ይጥል ይሆን !?
ያገሩ ላይትላይ ፣
ምሱን ሊልስ ሲሻው ፣
በሳቅሽ መወከል ቆሌው ጋር ተናሽጦ ገንዳው
ሲወበራ ፣
አይጠገብ ደሴ አድባርና ቆሌው መልካው ባ‘ንቺ
አበራ።
መገን !
የፍቅር አዝመራ ፣
መርሳ ላይ ሊያዘምር ፣
የሳቅሽ ቡቃያ በጨቆርሳው እራሽ መታጀ
ሲወጣው ፣
ቢርቢሳ ያገሳል ...
ቦርከና ጋር ሸርኮ ጥርስሽን ሊያጠጣው ።
ተዛማ ምን አለ ...
ወሎ የሳቅ መኸር ፣
የሳዱላው ዛላ የሸጋ ልጅ ፍሬ
እንደ ውልብኝ እሸት ፣
ታሽቶ ተፈልፍሎ ባገር ልጅ ሲሰፈር ፣
ዳበስ አርጎ መግመጥ የጠየመ ገላ የመከከ
ከንፈር ።
( ፈሽረክ ትይዋለሽ ... ! )
በጦሳ ገላ ላይ ፣
ተንፏቆ እሚገባው ፣
ጥርስሽ ነው ሰማይ ... ሳቅሽ ነው ጀንበሩ ፣
የዳውዶ ደጃፍ ... የገራዶ በሩ ።
( ፈሽረክ ትይዋለሽ ... ! )
♬ « እሄድ እሄድና እላለሁ እረፉ ፣
የጥርሷ ውቃራት እየታየኝ ዘርፉ ። » ♬
ሲዘፈን ፣
ጭርታ ሲከፈን ፣
የጁ ሲያስተጋባ ... ውሎ ሲያደገድግ ፣
እስክስ ያለ ሰው ነው ... !
ወገቡ ‘ሚጥብቅ ... ትክሻው የሚያድግ ።
-
እስክስስስ ፣
እስክስስስ ፣።!
ብቻ ...
ጉማይሰሪ ጉማው ፣
መጋለይ ሥመራው ፣
ኧረ ገና ገና ... !
እግረኛየዋዬ ኧረ ገና መቸ ፣
አንቺን ያለው ጀዋድ ፣
እያደር ሊኩልሽ ወቅቱ እየገጠመ እየተመቻቸ ።
_________
ሙሀመድ ሙፍቲ ( ጀዋድ )

የወሎ ልጅ ሆነሽ ንግግር ባታውቂ፤ጥርሥሽ ይናገራል ቶሎ ቶሎ ሳቂ።ወሎ ደሴ
13/07/2025

የወሎ ልጅ ሆነሽ ንግግር ባታውቂ፤
ጥርሥሽ ይናገራል ቶሎ ቶሎ ሳቂ።
ወሎ ደሴ

እረ ጅስሟን አይቶ______________ግልብጥብጥ  የሚለው ጉንጯ እንደ_ዝሃራአገሯ የጁ ነው በላይኛው ላስታ በታችኛው ሃራእንደምንም ብሎ ከቤቷ ባጠገብ ቤቴ በተሰራእንዴት አለም ነበር ጧት ማ...
12/07/2025

እረ ጅስሟን አይቶ
______________
ግልብጥብጥ የሚለው ጉንጯ እንደ_ዝሃራ
አገሯ የጁ ነው በላይኛው ላስታ በታችኛው ሃራ
እንደምንም ብሎ ከቤቷ ባጠገብ ቤቴ በተሰራ
እንዴት አለም ነበር
ጧት ማታ ሰላምታ ጧት ማታ ዚያራ!
@ ወሎ ሚድያ

ደሴና ሸጋ ልጅ ፤ክረምትና ደሴ!!!!!!መንበረ ፀሃይ ላይ፤አይጠየፍ ጋራው፤ከሚካኤል ቀዬ፤ኢያሱ ሚካኤል፤እግሩን እንዳይበርደው፤ብቻውን ሲያመሽ፤ጃኖ ደርቤለት፤በርኖስ ቀጥየለት፤ሸዋ በር በታች ተ...
12/07/2025

ደሴና ሸጋ ልጅ ፤ክረምትና ደሴ!!!!!!

መንበረ ፀሃይ ላይ፤
አይጠየፍ ጋራው፤
ከሚካኤል ቀዬ፤
ኢያሱ ሚካኤል፤
እግሩን እንዳይበርደው፤
ብቻውን ሲያመሽ፤
ጃኖ ደርቤለት፤
በርኖስ ቀጥየለት፤
ሸዋ በር በታች ተቀምጬልሽ፤
እኔን ቆፈን ፈጀኝ፤
እኔን ብርድ ቆጋኝ፤
አንች ቦለቂያ፤ ብርጉድ እየሞቅሽ።
እትትትትት እትቱ በረደኝ፤ ካለሁበት ቦታ፤
ወይ መጥተሽ አልሳምሽኝ፤ አላክሽልኝ ኩታ፤
ያንዘፈዝፈኛል፤
ክረምትና ናፍቆት፤ ብርድና ትዝታ።
ብርድ ነው እያሉ፤
ውርጭ ነው እያሉ፤ ድዴን ያደረቀው፤
ለካስ መቅረትሽ ነው፤
የአንገትሽን ግርጌ፤ መሳም የናፈቀው።
ጦሳን ያህል ጋቢ፤
ጀሜን ያህል ኩታ፤
ዳውዶን ያህል ጃኖ፤
አረብ ገንዳን ያህል፤
የተንተረከከ የመከከ ከንፈር፤ ቤት አስቀምጠሽ፤
መንበረ ፀሃይ ላይ፤
የሚካኤል አሽከር፤
ዘብ ልጠብቅ ብዬ፤ እኔ ሞትኩልሽ።
ሀኪሞቹ ሁላ፤
ብርድ ነው እያሉ፤
ውርጭ ነው እያሉ፤
ቆፈን ነው እያሉ፤ የያዘኝ በሽታ፤
መገን እርጎ ሙሄ፤
ያሽርህ ልትለኝ፤
ታቹን ከሳላይሽ፤ ካገር ግዛት መጥታ፤
ገምሸርሸር ብትል፤ አንገቴ ስር ገብታ፤
ጅስሜ ተሟሟቀ፤ ወገቤ ተፈታ።
በክረምት ቆፈን፤ በደሴ ሰማይ፤
የሸጋ ልጅ ትንፋሽ፤ ይጠገባል ወይ????
((ጃ ኖ)))

በአንድ ወቅት አንዲት ሴት ማህተመ ጋንዲን "አፈቅርሀለሁ።" ትለዋለች። ጋንዲም "ያንቺ ፍቅር ይበዛብኛል ከጀርባዬ ያለው ወንድሜ ግን ወጣትና ቆንጆ ነው እሱን ጠይቂው ይላታል።ሴቷ ዞር ብላ ካ...
11/07/2025

በአንድ ወቅት አንዲት ሴት ማህተመ ጋንዲን "አፈቅርሀለሁ።" ትለዋለች።
ጋንዲም "ያንቺ ፍቅር ይበዛብኛል ከጀርባዬ ያለው ወንድሜ ግን ወጣትና ቆንጆ ነው እሱን ጠይቂው ይላታል።ሴቷ ዞር ብላ ካየች በኋላ
" ማንም የለም እኮ ጋንዲ "አለችው።
ጋንዲም " ሲጀመር የምትወጂኝ ከሆነ ወደ ኋላ ዞረሽ አታይም ነበር " አላት።

የማስፋፊያ ስራው በመጠናቀቅ ላይ ያለው የወሎ ኮምቦልቻ ኤርፖርት።@ አንቻሮ ሚድያ
09/07/2025

የማስፋፊያ ስራው በመጠናቀቅ ላይ ያለው
የወሎ ኮምቦልቻ ኤርፖርት።
@ አንቻሮ ሚድያ

ደሴ ከተማን ከጦሳ ተራራ ላይ ሆነው ሲያይዋት ያላት ገፅታ !@ ደሴ ከተማ ባህል ቱርዝም
09/07/2025

ደሴ ከተማን ከጦሳ ተራራ ላይ ሆነው ሲያይዋት ያላት ገፅታ !
@ ደሴ ከተማ ባህል ቱርዝም

የሸጋ መፍለቂያ _የጥበብ ባለቤት:የስልጣኔ ምንጭ_የአብሮነት ተምሳሌት  አገራችን ደሴ_ስማችን ወሎዬ:ፍቅራችን ማራኪ_ከሰው የተለዬከሼህ ከቄሶቹ _ወሎ ተወልጀ:የመዋደድ ድግስ_አይጠፋም ከደጀ።የ...
06/07/2025

የሸጋ መፍለቂያ _የጥበብ ባለቤት:
የስልጣኔ ምንጭ_የአብሮነት ተምሳሌት

አገራችን ደሴ_ስማችን ወሎዬ:
ፍቅራችን ማራኪ_ከሰው የተለዬ

ከሼህ ከቄሶቹ _ወሎ ተወልጀ:
የመዋደድ ድግስ_አይጠፋም ከደጀ።

የታሪክ ባለቤት_ባለ ብዙ ዝና:
የደጋጎቹ ዘር _ ሸጋ ሸሞንሟና።

"ያለ ሀገር ነጻነት፣ ያለ ባህር በር ብልጽግና የለም!" "መታጠር፣ መዘጋትና መታፈን" ፍትሀዊ ነውን ? የጥንቱ የሀገራችን ሰው በርግጥም ከባህር ጋር የተቆራኘ ነበር፤ እጣንና የዝሆን ጥርስ ...
06/07/2025

"ያለ ሀገር ነጻነት፣ ያለ ባህር በር ብልጽግና የለም!"
"መታጠር፣ መዘጋትና መታፈን" ፍትሀዊ ነውን ?

የጥንቱ የሀገራችን ሰው በርግጥም ከባህር ጋር የተቆራኘ ነበር፤

እጣንና የዝሆን ጥርስ ጭኖ ለመካከለኛውና ለሩቅ ምስራቅ ገበያ የሚያቀርብ ረጅም ተጓዥ ባህርተኛም ነበር፤

ወንድ ልጁንም "ባህሩ" ብሎ እየሰየመ፤

የባህር ጠረፍ ግዛት አስተዳዳሪውንም "ባህረ-ነጋሽ" ብሎ እየሰየመ፤

"ያለ ሀገር ነጻነት፣ ያለ ባህር በር ብልጽግና የለም!" እያለ ለሺ ዘመናትም ጠረፉን ሲጠብቅና ሲዋደቅ ኖሮ....

በአንድ ክፉ የታሪክ አጋጣሚ ሁለት ኢትዮጵያ-ጠል የአጎት ልጆች በሸፍጥና በሴራ ሀገራችን ኢትዮጵያን የባህር በር አሳጧት።
ይህንንም ተቀበሉ ይሉናል።

ሰፊው የባህሩ ጠረፍ ለሁላችንም የሚበቃ ሆኖ ሳለ፤ "መታጠር፣ መዘጋትና መታፈን" ፍትሀዊ ነውን ?

የኢኖቬሽን ሚኒስትሩ ቀብራራው ወሎዬ ፕሮፌሰር በለጠ ሞላ ጌታሁን

እንግዲህ መንዙማ!!!!እንዲህ ወደ ቃሉ....እንዲህ ወደ መጂት ፤ ላዩን ወደ ገታ፤የመድሁ አረሆ....የመንዙማው ውበት፤በድንገት ተረታ።የነቢ ሙሽራ፤ የሶሃቦቹ ዘር፤በአጀሙ ምንሽር፤ በመድሁ ሞ...
03/07/2025

እንግዲህ መንዙማ!!!!

እንዲህ ወደ ቃሉ....
እንዲህ ወደ መጂት ፤ ላዩን ወደ ገታ፤
የመድሁ አረሆ....
የመንዙማው ውበት፤በድንገት ተረታ።

የነቢ ሙሽራ፤ የሶሃቦቹ ዘር፤
በአጀሙ ምንሽር፤ በመድሁ ሞይዘር፤
መሻኢኮቹ ጋር ፤ ዱኣ እየተኮሰ፤
እንደ አዳራሽ ማሾ፤ በአገሩ በወንዙ እየተለኮሰ፤
የሚያምረው መሀመድ...
በመድሁ ጥይት፤ የሙሲባን ክምር፤ በድምፁ አፈረሰ።

በአንቻሮ በገታ በላይኛው ቃሉ፤
የላይ ገንዳው ዘማች....
በመንዙማው አጀብ፤ ሃድራ ያደምቃሉ፤
ሃየ በል እያሉ...
የጀማውን ንጉስ ይነቀንቃሉ።

መንዙማን የሚያህል፤የቀልብ ማርገቢያ፤ ወሎ ባይታደል፤
አይወጣውም ነበር፤ የኑሮን ፈተና፤ የዱኒያውን ገደል።

እንግዲህ መንዙማ፤ አላህ ይድረስልሽ፥
ዱንያን ንቋት ሄደ...
ነቢ ዘይኔ እያለ፤ መንዙመኛው ልጅሽ።

ነፍስ ይማር፤ ሸህ መሃመድ ሁሴን

(ጃኖ መንግስቱ ዘገየ፤ከ ሃራ መንደራ ዳንዮል አወል ቀበሌ)

Address

Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ወሎ ደሴ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share