Wollo news media

Wollo news media news on wollo

ዘንድሮ 8ኛ ክፍል ፈተና ላይ የመጣ ጥያቄ ነው አሉ 🤣የእሼቱ ጎብየ ጥያቄ አይነት
11/06/2025

ዘንድሮ 8ኛ ክፍል ፈተና ላይ የመጣ ጥያቄ ነው አሉ 🤣
የእሼቱ ጎብየ ጥያቄ አይነት

06/06/2025
በዚህ ሠአት የአማራ ክልልን ፖለቲካ ከያዘው በሽታ  እንዲያገግም ለማድረግ   መታዘዝ ያለበት ትክክለኛ መድሀኒት የወሎ የፖለቲካ ስነልቦና ነው።   በአማራ ክልል ፖለቲካ ውስጥ ደግሞ ወሎን ከ...
03/06/2025

በዚህ ሠአት የአማራ ክልልን ፖለቲካ ከያዘው በሽታ እንዲያገግም ለማድረግ መታዘዝ ያለበት ትክክለኛ መድሀኒት የወሎ የፖለቲካ ስነልቦና ነው።

በአማራ ክልል ፖለቲካ ውስጥ ደግሞ ወሎን ከያዘው የአጨብጫቢነት በሽታ አገግሞ በራሱ ፀንቶ እንዲቆምና ተፎካካሪ እንዲሆን ለማድረግ ሊታዘዝለት የሚገባው መድሀኒት የጎጃም የፖለቲካ ንቃት እንዲሁም የወሎ ኮምቦልቻ ከተማ አካታች ስርአት (Inclusive system ) ነው።

በእያንዳንዳችን ውስጥ ያለውን በሽታ በመፈራራት ጭንብል ከላይ ከላይ እያስመሠሉ በመሸፋፈን ከበሽታው ማገገም አንችልም።

በሽታችንን ያለምንም ፍርሃትና መሸማቀቅ ፈንቅለን በማውጣት መነጋገር መቻል አለብን።

በእያንዳንዳችን ውስጥ ላለው የበሽታ አይነት ትክክለኛ መድሀኒት ካልታዘዘ በስተቀር ከያዘን የውስጥ ህመም በቀላሉ አገግመን መዳን አንችልም።‼️

የደሴ ልጅ በመሆኔ ኩራት እንዲሰማኝ ከሚያደርጉኝ "የደሴ ልጆች" መሀል ዛሬ አንዱን ላስተዋውቃችሁ 💚💛❤️ዛሬ ጁመኣ ነው። እጅግ በጣም ስለማደንቃቸው እና ከእርሳቸው ጋር አንድ ሀገር በመወለዴ...
03/06/2025

የደሴ ልጅ በመሆኔ ኩራት እንዲሰማኝ ከሚያደርጉኝ "የደሴ ልጆች" መሀል ዛሬ አንዱን ላስተዋውቃችሁ 💚💛❤️
ዛሬ ጁመኣ ነው። እጅግ በጣም ስለማደንቃቸው እና ከእርሳቸው ጋር አንድ ሀገር በመወለዴ ከምኮራባቸው የደሴ ልጆች መሀል አንዱን ላስተዋውቃችሁ። (ዩኒቨርሲቲ እያለን እኔና መሰል የደሴ ልጆች የደሴው በላይ ዘለቀ) እያልን ነበር የምንጠራቸው) ሼህ ሰዒድ ሙሐመድ ሷዲቅ 💚💛❤️ ስለ ሼህ ሰዒድ ሙሐመድ የኢትዮጵያ ዝነኛ ደራሲያን ብዙ ፅፈዋል። ከበዓሉ ግርማ እስከ ስብሃት ገ/እግዚአብሔር፣ ከጳውሎስ ኞኞ እስከ ፀጋዬ ገ/ መድን ሼህ ሰዒድን አድንቆ ያልፃፈ የለም። ለመሆኑ ሼህ ሰዒድ ሙሐመድ ማን ናቸው ?
የሼህ ሰዒድ እናት ዘምዘም ሰዒድ ከእትየ መነን አስፋው ዓሊ ቦሩ ጋር በእኩል እርቀት ላይ የሚገኝ ዝምድና ነበራቸው፡፡ ዘምዘም የድንቂቱ ቦሩ የልጅ ልጅ ሲሆኑ ልዕልት መነን ደግሞ የአሊ ቦሩ የልጅ ልጅ ነበሩ። ይህም ማለት ዘምዘምና ልዕልት መነን የእህትና የወንድም የልጅ ልጆች ነበሩ ማለት ነው።
አባታቸው ደግሞ ሼህ ሙሐመድ ሷዲቅ ናቸው፡፡ በ1842 - 1901 በዘመናዊ ተቋማት ሳይተኩ ከከሰሙት ጥንታዊ የትምህርትና የባህል ማዕከሎች አንዱ ተደርጎ የሚወሰድ ማዕከል የመሰረቱ ታላቅ መምህር ነበሩ። በዚሁ ማዕከላቸው ውስጥም በአንድ ጊዜ ከ500 እስከ 800 ያስተናግዱበት ነበር፡፡ ፕ/ር ሁሴን አህመድ "lslamic Literature and religious revival in Ethiopia" ባሉት መፅሐፋቸው ላይ "ይህ ማዕከላቸው በተለይ ሰማንያ ስመ ጥር መምህራን ስለማፍራቱ ይነግሩናል" በረጅሙ የእስልምና ታሪክ ወስጥ አራት መዝሃቦች (school of thoughts) ገዥ ሆነው ዘልቀዋል፡፡ ከአራቱ መዝሃቦች ውስጥ አንዱ እና አገራችንን ጨምሮ በመላው ሙስሊም አለም ዘንድ ሰፊ ተከታይ ያፈራው በኢማም አሽ- ሻፊኢይ (767-820) የተመሰረተውና በስማቸው የተጠራው የሻፊኢይ መዝሃብ ነው፡፡ ማርታ ቶርሲኒ ክሮዝ የተባሉ ፀሐፊ "state and religion in the constitution፡ politics of Ethiopia" በተሰኜ ድንቅ መፅሐፋቸው "ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው የዚህ መዝሃብ ሊቃውንቶች መካከል ሼህ ሙሐመድ ሷዲቅ ግንባር ቀደም ሆነው የሚጠቀሱ ናቸው፡፡" ይሉናል፡፡ ዶ/ር አህመድ ሐሰን ኡመር ደግሞ "በብዙ የኢትዮጵያ ሙስሊም ምሁራን ዘንድ "ሁለተኛው ሻፊኢይ" የሚል ቅፅል ስም ወጥቶላቸው እንደነበር "A preliminary note on religions in Ethiopia" ባሉት መፅሐፍ ላይ ጠቀስ ያረጉታል፡፡
እንግዲህ የኔ ናፍቆት ከእመት ዘምዘም ሰዒድና ከሼህ ሙሐመድ ሷዲቅ ደሴ ከተማ ሜጠሮ ሰፈር ላይ ነው የተወለዱት። በነገራችን ላይ ሼህ ሰዒድ ሙሐመድ ሷዲቅ በተወለዱበት ደሴ ከተማ ላይ በ1943 ዓ.ም አገር ጉድ ባሰኜ በደመቀ ሰርግ ከዘይነብ አብደላ ጋር ትዳር የመሰረቱ ጊዜ ጣሊያን ጥሎት የሄደው 13 ክፍሎች ያሉት ትልቅ መኖርያ ቤታቸውን አንድ ቀን ለማስቃኜት እሞክራለሁ!)
ሼህ ሰዒድ ሙሐመድ የጳውሎስ ኞኞ፣ የስብሐት ገ/ እግዚአብሔር፣ የበዓሉ ግርማ እና የሌሎች ስመ ጥር ደራስያት አስተማሪ እንደነበሩ፡፡ እራሱ ጳውሎስ ኞኞ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከመፃፉም በላይ ዘነበ ወላ የተባለው ደራሲ "ማስታዎሻ" ሲል በፃፈው የጋሽ ስብሃትን ታሪክ በሚተርከው በፅሀፉ ላይ ስብሃት ለሼህ ሰዒድ የነበራቸውን አድናቆት ፅፏል። እንዳለጌታ ከበደ የተባለው ደራሲም የበዓሉ ግርማ ህይወትና ስራዎች በተሰኜው መፅሀፉ ላይ "እውቀት ሞልቶ የፈሰሰባቸው" ሲል ሼህ ሰዒድ ሷዲቅ ስም ጠርቶ ጠቅሷል።
ሼህ ሰዒድ ሷዲቅ ከንጉሱ ጋር በነበረ

 # የወሎከብዙ ጥቂቶቹ  ጥያቄዎች ከታች ተዘርዝረውልካል አንብብና የት ደረሱ ብለህ ጠይቅ። #ወሎ ብለውም ለወጥራት ተጠይፈውህ ነበር ሪፈር አድርግ።የወሎ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች ትላንትና ዛ...
31/05/2025

# የወሎከብዙ ጥቂቶቹ ጥያቄዎች ከታች ተዘርዝረውልካል አንብብና የት ደረሱ ብለህ ጠይቅ።
#ወሎ ብለውም ለወጥራት ተጠይፈውህ ነበር ሪፈር አድርግ።
የወሎ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች ትላንትና ዛሬ ‼️
*********
እንደሚታወቀው ወሎ የቀደምት ስልጣኔ ባለቤት ፣ የአለማቀፋዊ ቅርስ ባለቤት ፣ የታላላቅ ሀይማኖታዊ እና ታሪካዊ ቦታዎች ባለቤት እንድሁም በሀገራችን አንቱ የተባሉ የሀይማኖር አባቶች እና የሀይማኖት ትምህርት ምንጭ መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው።

✍️ሆኖም ግን በዚህ ህዝብ ላይ በሚከሰቱ ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች እና አደጋዎች እንድሁም መንግስት መር መዋቅራዊ ( ክልላዊ እና ፌደራላዊ ) ደባ እና ሸፍጥ ህዝቡ አካባቢውን ለቆ እንዲሰደት፣ በአካባቢው እንዳያለማ ፣ እንዳይማር ፣ እንዳይነቃ ፣ እንዳይደራጅ ፣ አንድ እንዳይሆን በሁለቱ ምክኒያቶች ተሰርቶበታል።

✍️ይህነንም ተከትሎ ወሎ የነበረውን ከፍታ ፣ ወግ ፣ እሴት ፣ ባህል ፣ ማንነት ፣ ታሪክ ፣ ኢኮኖሚው እና የፖለቲካውን ልዕልና እንዲያጣ ሆኗል።

✍️ ወሎ በአጼው ዘመነ መንግስት የሀገሪቱ ዋና መናገሻ የነበረች ፣ እንድሁም ትልቅ የፖለቲካ ማዕከል የነበረ ሲሆን በቅርቡ እንኳን በሃገራችን #ከመርካቶ በመቀጠል ትልቁ የንግድ ማዕከል ወሎ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው።

✍️ ወደ ዋናው ጉዳየ ስገባ የወሎ ህዝብ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር በመሆን ያን አፋኝ የህወሃት ስርዓት ግንባር ቀደም ሆኖ ለህዝቡ እኩል ተጠቃሚነት ፣ ማህበራዊ ፍትህ ፣ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ፣ እኩል የመልማት እና የማደግ መሰረታዊ እና አንኳር ጥያቄዎችን በማንገብ መላው የሀገራችን ህዝቦች ጋር በመሆን በመታገል ህወሃትን የመጨረሻ ቀብ- ሯን ወልድያ ላይ በማድረግ ለውጡ እንድመታ አስችሏል።

✍️ይህም ሲሆን ማህበረሰቡ ከለውጡ በፊት እና ቡሃላ ይዟቸው የነበሩ ጥያቄዎች የመሰረተ ልማት ፣ የትምህርት ፣ የጤና ፣ የመንገድ ፣ መብራት እና ሌሎች ጥያቄዎች ነበሩ። ከነዙህም ውስጥ ዋና ዋና ወቹ

🌴 የወሎ ተሪሸሪ እና ኬር ሆስፒታል

🌴 የኮምቦልቻ ሃራ ገቢያ ባቡር ፕሮጀክት

🌴የደሴ ኮምቦልቻ ሽንቁር መንገድ ፕሮጀክት

🌴 የመካነ ሰላም አየር መንገድ ፕሮጀክት

🌴የዋግ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ

🌴የቆቦ ጊራና ውሃ ፕሮጀክት

🌴 የወሎ ህዝብ የመብራት ሀይል አቅርቦት ችግር

🌴የመርሳ ቆዳ እና ሌጦ ፋብሪካ መቆም

🌴 የሰቆጣ አስፋልት ስራ

🌴የወሎ ሀይቆች ልማት ፕሮጀክት

🌴 የነ ጊሸን ማርያም አስፋልት ስራ

🌴የወሎ ዞኖች እና ወረዳዎች በጀት ጉዳይ

🌴እና ሌሎች መሰረታዊ ጥያቄ የነበሩ ሲሆን ፦

✍️ነገር ግን ዛሬ ደግሞ የወሎ ህዝብ በይበልጥ ከለውጡ ማግስት በማንቻውም የሀገሪቱ ክፍል በሚደርሱ ግጭቶች ፣ ረብሻዎች ፣ ጦርነት እና የዘር ማጥፋት ተግባራት የገፈቱ ቀማሽ እርሱ እና እርሱ ብቻ ነው።

✍️ በዚህ 4 ዓመት ውስጥ በመቶ ሺዎች የሚጠጉ የማህበረሰባችን ክፍሎች ከሶማልያ ፣ ከኦሮምያ ፣ ከደቡብ እና ከትግራይ ተፈናቅለው ሲገኙ ይህን የማህበረሰብ ክፍል በስሙ ለምኖ የግል ኪሱን እና ስልጣኑን ያራዘመ እንጅ አንድም የጠየቀው መንግስት የለም።

✍️ሩቅ ሳንሄድ በህወሀት ወረ ራ ሰሞን የወሎ ህዝብ ሙሉ ንብረቱ ተዘርፏል ፣ ወድሟል ፣ ተቃጥሏል። ይህን ውድመት ለሀገር የተከፈለ መስዋትነት ነው ብሎ ድጋፍ ያደረገ አንድም የክልልሞ ሆነ የፌደራል መንግስት እንድሁም NGO የለም።

ይህነንም ተከትሎ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተፈናቅሎ የመጣው ማህበረሰብ ፣ በጦርነት ንብረቱ የተዘረፈበት ፣ የተቃጠለበት ማህበረሰብ ያለ ማንም ጠያቂ ሜዳ ላይ ቀርቷል

31/05/2025

# የወሎከብዙ ጥቂቶቹ ጥያቄዎች ከታች ተዘርዝረውልካል አንብብና የት ደረሱ ብለህ ጠይቅ።
#ወሎ ብለውም ለወጥራት ተጠይፈውህ ነበር ሪፈር አድርግ።
የወሎ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች ትላንትና ዛሬ ‼️
*********
እንደሚታወቀው ወሎ የቀደምት ስልጣኔ ባለቤት ፣ የአለማቀፋዊ ቅርስ ባለቤት ፣ የታላላቅ ሀይማኖታዊ እና ታሪካዊ ቦታዎች ባለቤት እንድሁም በሀገራችን አንቱ የተባሉ የሀይማኖር አባቶች እና የሀይማኖት ትምህርት ምንጭ መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው።

✍️ሆኖም ግን በዚህ ህዝብ ላይ በሚከሰቱ ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች እና አደጋዎች እንድሁም መንግስት መር መዋቅራዊ ( ክልላዊ እና ፌደራላዊ ) ደባ እና ሸፍጥ ህዝቡ አካባቢውን ለቆ እንዲሰደት፣ በአካባቢው እንዳያለማ ፣ እንዳይማር ፣ እንዳይነቃ ፣ እንዳይደራጅ ፣ አንድ እንዳይሆን በሁለቱ ምክኒያቶች ተሰርቶበታል።

✍️ይህነንም ተከትሎ ወሎ የነበረውን ከፍታ ፣ ወግ ፣ እሴት ፣ ባህል ፣ ማንነት ፣ ታሪክ ፣ ኢኮኖሚው እና የፖለቲካውን ልዕልና እንዲያጣ ሆኗል።

✍️ ወሎ በአጼው ዘመነ መንግስት የሀገሪቱ ዋና መናገሻ የነበረች ፣ እንድሁም ትልቅ የፖለቲካ ማዕከል የነበረ ሲሆን በቅርቡ እንኳን በሃገራችን #ከመርካቶ በመቀጠል ትልቁ የንግድ ማዕከል ወሎ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው።

✍️ ወደ ዋናው ጉዳየ ስገባ የወሎ ህዝብ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር በመሆን ያን አፋኝ የህወሃት ስርዓት ግንባር ቀደም ሆኖ ለህዝቡ እኩል ተጠቃሚነት ፣ ማህበራዊ ፍትህ ፣ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ፣ እኩል የመልማት እና የማደግ መሰረታዊ እና አንኳር ጥያቄዎችን በማንገብ መላው የሀገራችን ህዝቦች ጋር በመሆን በመታገል ህወሃትን የመጨረሻ ቀብ- ሯን ወልድያ ላይ በማድረግ ለውጡ እንድመታ አስችሏል።

✍️ይህም ሲሆን ማህበረሰቡ ከለውጡ በፊት እና ቡሃላ ይዟቸው የነበሩ ጥያቄዎች የመሰረተ ልማት ፣ የትምህርት ፣ የጤና ፣ የመንገድ ፣ መብራት እና ሌሎች ጥያቄዎች ነበሩ። ከነዙህም ውስጥ ዋና ዋና ወቹ

🌴 የወሎ ተሪሸሪ እና ኬር ሆስፒታል

🌴 የኮምቦልቻ ሃራ ገቢያ ባቡር ፕሮጀክት

🌴የደሴ ኮምቦልቻ ሽንቁር መንገድ ፕሮጀክት

🌴 የመካነ ሰላም አየር መንገድ ፕሮጀክት

🌴የዋግ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ

🌴የቆቦ ጊራና ውሃ ፕሮጀክት

🌴 የወሎ ህዝብ የመብራት ሀይል አቅርቦት ችግር

🌴የመርሳ ቆዳ እና ሌጦ ፋብሪካ መቆም

🌴 የሰቆጣ አስፋልት ስራ

🌴የወሎ ሀይቆች ልማት ፕሮጀክት

🌴 የነ ጊሸን ማርያም አስፋልት ስራ

🌴የወሎ ዞኖች እና ወረዳዎች በጀት ጉዳይ

🌴እና ሌሎች መሰረታዊ ጥያቄ የነበሩ ሲሆን ፦

✍️ነገር ግን ዛሬ ደግሞ የወሎ ህዝብ በይበልጥ ከለውጡ ማግስት በማንቻውም የሀገሪቱ ክፍል በሚደርሱ ግጭቶች ፣ ረብሻዎች ፣ ጦርነት እና የዘር ማጥፋት ተግባራት የገፈቱ ቀማሽ እርሱ እና እርሱ ብቻ ነው።

✍️ በዚህ 4 ዓመት ውስጥ በመቶ ሺዎች የሚጠጉ የማህበረሰባችን ክፍሎች ከሶማልያ ፣ ከኦሮምያ ፣ ከደቡብ እና ከትግራይ ተፈናቅለው ሲገኙ ይህን የማህበረሰብ ክፍል በስሙ ለምኖ የግል ኪሱን እና ስልጣኑን ያራዘመ እንጅ አንድም የጠየቀው መንግስት የለም።

✍️ሩቅ ሳንሄድ በህወሀት ወረ ራ ሰሞን የወሎ ህዝብ ሙሉ ንብረቱ ተዘርፏል ፣ ወድሟል ፣ ተቃጥሏል። ይህን ውድመት ለሀገር የተከፈለ መስዋትነት ነው ብሎ ድጋፍ ያደረገ አንድም የክልልሞ ሆነ የፌደራል መንግስት እንድሁም NGO የለም።

ይህነንም ተከትሎ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተፈናቅሎ የመጣው ማህበረሰብ ፣ በጦርነት ንብረቱ የተዘረፈበት ፣ የተቃጠለበት ማህበረሰብ ያለ ማንም ጠያቂ ሜዳ ላይ ቀርቷል

በሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር ኢትዮጵያዊቷ ሀሴት ደረጄ 2ኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀቀች*************************በህንድ በተካሄደው 72ኛው ሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር ኢትዮጵያ...
31/05/2025

በሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር ኢትዮጵያዊቷ ሀሴት ደረጄ 2ኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቀቀች
*************************

በህንድ በተካሄደው 72ኛው ሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር ኢትዮጵያን የወከለችው ሀሴት ደረጄ ሁለተኛ ደረጃን ይዘ አጠናቃለች።

ሀሴት ደረጄ ከአፍሪካ ቀዳሚ በመሆን ነው ለፍጻሜው ውድድር የደረሰችው።

በውድድሩ ከእስያ ታይላንዳዊቷ ኦፓል ሱቻታ ውድድሩን አንደኛ በመሆን አጠናቃ ሚስ ወርልድ 2025 አሸናፊ ሆናለች።

ከአውሮፓ ፖላንዳዊቷ ማጃ ክላጅዳ እና ከአሜሪካ እና ካረቢያን ሀገራት የማረንቲክ ተወላጇ ኦራሊ ጆአኪም 3ተኛ እና 4ተኛ የወጡ ተወዳዳሪዎች መሆናቸውን ከሚስ ወርልድ ድረገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
page

በኢትዮጵያ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ብርቅዬ የተባለውን  ሰማያዊ ላቫ አመነጨ  | የኢትዮጵያ እሳተ ገሞራዎች ውስጥ እጅግ ብርቅዬ የሚባለውን ሰማያዊ ላቫ እየፈነጠቀ መሆኑ  እንደ ክስተት እየታየ...
28/05/2025

በኢትዮጵያ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ብርቅዬ የተባለውን ሰማያዊ ላቫ አመነጨ

| የኢትዮጵያ እሳተ ገሞራዎች ውስጥ እጅግ ብርቅዬ የሚባለውን ሰማያዊ ላቫ እየፈነጠቀ መሆኑ እንደ ክስተት እየታየ ይገኛል። ከኢንዶኔዢያ ጃቫ ግዛት ካዋ ኢጄን እሳተ ገሞራ ጋር ተመሳሳይነት አለው የተባለው ሰማያዊ ላቫው በመጀመሪያ እይታ ላቫው ከተራራው ላይ እየፈሰሰ ይመስላል፣ ነገር ግን ይህ ያልተለመደ ፍካት እንደሚታሰበው አይደለም።

"ሰማያዊ እሳት" እየተባለ የሚጠራው ይህ ክስተት በላቫ የተፈጠረ ሳይሆን ከእሳተ ገሞራው ስንጥቆች በሚወጡት የሚቃጠሉ የሰልፈር ጋዞች የሚመጣ መሆኑ ተገልጿል።

እስከ 600°C (1,100°F) የሚደርስ ሙቀት ያላቸው ትኩስ ጋዞች በአየር ውስጥ ከሚገኘው ኦክሲጅን ጋር ሲገናኙ፣ በእሳት ተያይዘው ደማቅ ሰማያዊ ነበልባል ይፈጥራሉ።

በካዋህ ኢጄን ያለው ትክክለኛው ላቫ እንደ አብዛኞቹ እሳተ ገሞራዎች የተለመደው ቀይ-ብርቱካናማ ቀለም ያለው ቢሆንም፣ የሚቃጠለው ሰልፈር ነበልባል የሚያብረቀርቅ ሰማያዊ ላቫ ምስልን የሚፈጥር ሲሆን በሌሊት ብቻ የሚታይ አስደናቂ ትዕይንት ነው ተብሏል፡፡
news media #

ሚሌ ደርሳለች19/09/2017
27/05/2025

ሚሌ ደርሳለች
19/09/2017

ክብር ለአባቶች                                                         ታላቁ ሩሲያዊ ደራሲ ፊዮዶር ዶስቶቭስኪ: እንዲህ ይላል:እናቴ ሁሌም ምትለኝ፡- አባትህ...
27/05/2025

ክብር ለአባቶች ታላቁ ሩሲያዊ ደራሲ ፊዮዶር ዶስቶቭስኪ: እንዲህ ይላል:

እናቴ ሁሌም ምትለኝ፡-
አባትህ ወደ ቤት ሲመጣ ስቀህ ተቀበለው፣ ከቤት ውጪ ያለው አለም የብቸኝነት ነው አባቶችን ያደክማል።😊 ***

በእናት እና በአባት መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው???
#እናትህ ለ9 ወር በማህፀኗ ውስጥ ተሸክምሀለች...
#አባትህ ቀሪው ህይወትህ ሁሉ ይሸከምሀል.. (አስተዋልክ) 💙
እናትህ እንዳትራብ ታደርግሀለች...
አባትህ እንዳትራብ ያስተምርሀል.. (አትገነዘብም) 💙
እናትህ በደረቷ ታቅፍሀለች...
አባትህ ደግሞ በጀርባው ያዝልሀል.. (አታዩትም) 💙
የእናት #ፍቅር ከተወለደክ ጀምሮ ታውቀዋለህ...
የአባት ፍቅር አባት ስትሆን ነው የምታውቀው.. (ታገስ ጥሩ ነው) 💙
እናት... በዋጋ ልትተመን እትችልም💙
አባት..... በጊዜ ብዛት አይደገምም 💙

መቅደላ ወሎ አብባ ውላለች የተሠሩ የልማት ስራዎችን አስጎበኝተዋል
25/05/2025

መቅደላ ወሎ አብባ ውላለች
የተሠሩ የልማት ስራዎችን አስጎበኝተዋል

ዛሬ ከተሰሙ ዜናዎች ሁሉ ልቤን የሰበረው ..ዶ/ር ኣላእ ነጃር በናስር ሆስፒታል የሕፃናት ሐኪም ናት። ከቤተሰብ ርቃ፣ ቤቷን ትታ .. ሰው ለማዳን ብላ ሆስፒታልን ቤቷ ካደረገች ሰነበተች። ዛ...
25/05/2025

ዛሬ ከተሰሙ ዜናዎች ሁሉ ልቤን የሰበረው ..

ዶ/ር ኣላእ ነጃር በናስር ሆስፒታል የሕፃናት ሐኪም ናት። ከቤተሰብ ርቃ፣ ቤቷን ትታ .. ሰው ለማዳን ብላ ሆስፒታልን ቤቷ ካደረገች ሰነበተች።
ዛሬ ሥራ ላይ እያለች ድንገት ልብን ቀጥ የሚያረግ አደጋ ገጠማት። የትኛዋም እናት የማትቋቋመው ከባድ ህመም። ቤታቸው በኢስራኤል የጦር ጀቶች ተደብድቦ ሰባት ልጆቿ
1- የሕያ ሐምዲ ነጃር
2- ረካን ሐምዲ ነጃር
3- ረስላን ሐምዲ ነጃር
4- ጁብራን ሐምዲ ነጃር
5- ኢይፍ ሐምዲ ነጃር
6- ሪፋን ሐምዲ ነጃር
7- ሲዳን ሐምዲ ነጃር
ሆስፒታል ከመጡት ሰማእታት ውስጥ ሆነው አገኘቻቸው ። ከዚህም ሌላ እንደሞቱ የሚገመቱት ከፍርስራሽ ሥር ያልወጡ
8- ሉቅማን ሐምዲ ነጃር
9- ሲዳር ሐምዲ ነጃር ገና ዓመት ያልሞላው አሉበት።

በአንድ ጊዜ በሕይወት ዘመኗ ያፈራቻቸውን ዘጠኝ ልጆቿን ሁሉ አጣች :: አስረኛው ልጅ አደም ቆስሎ በሆስፒታል እያገገመ ነው::
የሌሎችን ልጆች ስታክም፣ የወላጆቻቸውን ህመም ስትታመም እሷም ተራዋ ደረሠ። ተጎድተው ለመጡ ልጆች ልድረስላቸው ብላ የተሸፈኑበትን ሸራ ገለጥ ስታደርግ የገዛ ልጆቿ ሆነው አገኘቻቸው ።

ሰው እንዲህ ከሆነም በኋላ በሁለት እግሩ ቆሞ ይሄዳል ። ምን ዓይነት ኢማን፣ ምን ዓይነት ፅናት ነው በረቢ!!
እንዲም አለ ወዳጄ።
ጌታዬ ያፅናት። ትልቁ ሶብር ያንቧቧባት።

እኛስ ሶብርና ኢማናችን ምን ድረስ ነው።
ዱንያ።
Muhammed Seid Abx

Address

Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo news media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share