Wollo news media

Wollo news media news on wollo

ስለ ወሎ ያልተነገሩ እውነቶች" በአማራ ክልል አካባቢወች ውስጥ የኤሌክትሪክና ስልክ አገልግሎትን ቀድሞ በማግኘት ወሎ ቀዳሚው ነው። ደሴ ከተማ ከክልሉ ከተሞች ውስጥ ስልክ እና የኤሌክትሪክ አ...
04/09/2025

ስለ ወሎ ያልተነገሩ እውነቶች

" በአማራ ክልል አካባቢወች ውስጥ የኤሌክትሪክና ስልክ አገልግሎትን ቀድሞ በማግኘት ወሎ ቀዳሚው ነው። ደሴ ከተማ ከክልሉ ከተሞች ውስጥ ስልክ እና የኤሌክትሪክ አገልግሎት በማግኘት ቀዳሚዋ ነች።

ባቲ፣ ትዝታ፣ አንቺ ሆዬ እና አምባሰል የሚባሉት አራቱ የኢትዮጲያ የሙዚቃ ቅኝቶች መሰረታቸው ወሎ ነው (ሌሎች ኢትዮጲያውያን ወገኖቻችን ደስ እንዲሰኙባቸው ምክንያት መሆናችን ደስ አሰኝቶናል)።

"በአማራ ክልል ውስጥ ቀዳሚው ዘመናዊ ትምህርት ቤት የተጀመረው ወሎ ደሴ ላይ ነው።

" በኢትዮጲያ እስልምና ታሪክ ውስጥ ስማቸው ገናና ሆኖ የሚታወቁት እነደ ዳና፣ ጥሩ ሲና፣ ሾንኬ፣ ጫሊ፣ ገታ፣ ደገር ወዘተ አይነት መድረሳወች የሚገኙት ወሎ ውስጥ ነው።

"ኢትዮጲያዊ የሆነው መንዙማ የተጀመረው በወሎ ነው

"በአማራ ክልል ከሚገኙ ጥንታዊ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ እጅግ ጥንታዊ የሆነችው እና ቀደምቷ ተድባበ ማርያም የምትገኘው በወሎ ነው።

" አማራ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ከ1000 ዓመት በላይ እድሜ ካስቆጠሩ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ በግርድፉ ከ70% በላይ የሚሆኑት የሚገኙት በወሎ ውስጥ ነው።

"የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ አማኞች በታላቅ ክብር ከተለያየ የኢትዮጲያ ክፍልና ከአለም ተሰባስበው ለሃይማኖታዊ የሚታደሙባቸው ግሸን ደብረ ከርቤ እና ቅዱስ ላሊበላ የሚገኙት በወሎ ነው።

"ኢትዮጲያን ለዘመናት የገዟት የዛጉዌ፣ የሰሎሞናዊ፣ የወረሴህ እና የማመዶች ሥርወ መንግስታት የተመሰረቱት በወሎ ነው። መራ ተክለ ሃይማኖት፣ ዓጤ ይኩኖ አምላክ ፣ አባ ሴሩ ጓንጉል፣ አባ ጂቦ መሀመድ አሊ የተሰኙት የእነዚህ ሥርወ መንግስታት መስራቾች ከዚሁ ከወሎ ምድር የተፈጠሩ ናቸው።

" የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የአገው እና የአርጎባ ህዝቦች በወሎ ውስጥ ይገኛሉ ።

" በዘመናዊ የኢትዮጲያ ታሪክ ውስጥ የወሎየወች ከፍታ የሚባለው አቤቶ እያሱ ስልጣን ሲወርሱ አባታቸው ሚካኤል ዓሊ ንጉሠ ጽዮን ተብለው የወሎ፣ የጎንደር ፣ የትግሬና የጎጃም የበላይ ገዥ ሲባሉ ነው።

" ከአማራ ክልል አካባቢወች ግንባር ቀደም በመሆን የአክስዮን ማህበር ያቋቋሙት ወሎየወች ናቸው። የወሎ ፈረስ ትራንስፖርት አክስዮን ማህበርን በእነ ፊታውራሪ አመዴ ለማ አማካኝነት በግንባር ቀደምነት ተመስርቷል።

" ወሎ የበርካታ ማዕድኖች መገኛ እንደሆነ ይነገራል። የብረት፣ የድንጋይ ክሰል ፣ የነዳጅ ፣ የወርቅ ፣ የከበሩ ድንጊያወችና ላይም ስቶን ወዘተ እምቅ ሀብት አለው።

"የተከዜ ወንዝ መነሻ ወሎ ውስጥ ነው። ለአባይ ገባር የሆነው ታላቁ በሽሎ እና የአዋሽ ገባር የሆነው ቦርከናም ከወሎ የተለያዩ አካባቢወች የሚነሱ ናቸው።

አድሱ የደመወዝ ማሻሻያ ከ2018 ዓ.ም    ጀምሮ
19/08/2025

አድሱ የደመወዝ ማሻሻያ ከ2018 ዓ.ም
ጀምሮ

15/08/2025
ወሎየነት
15/08/2025

ወሎየነት

አሳዛኝ ዜና  #በደሴ ከተማ ጠቅላላ ሀኪም የሆነችው ወጣቷ ዶክተር  #አስረበብ አበበ ተሰማ በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይታናለች    በደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል  በጠቅላላ ሀኪ...
13/08/2025

አሳዛኝ ዜና

#በደሴ ከተማ ጠቅላላ ሀኪም የሆነችው ወጣቷ ዶክተር #አስረበብ አበበ ተሰማ በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይታናለች

በደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በጠቅላላ ሀኪምነት ላለፈው አንድ አመት በሆስፒታሉ ስታገለግል የቆየችው ወጣት ዶ/ር አስረበብ አበበ ትላንት በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይታለች

የወጣት ዶ/ር አስረበብ ድንገተኛ ሞት ብዙዎችን አሳዝኗል አስለቅሷል
ወጣት ሀኪም ዶ/ር አስረበብ አበበ ስራዋን አክባሪ በታካሚዎቿና በስራ ባልደረቦቿ የምትወደድና የምትመሰገን ተስፋ የተጣለባት ጠቅላላ ሀኪም ነበረች

ወጣቷ ዶ/ር በ2014 ከጎንደር ዩኒቨርስቲ በከፍተኛ ማዕረግ በዶክትሬት ተመርቃ አንድ አመት በመካነ ሰላም ጠቅላላ ሆስፒታል ሰርታ ወደ ደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዛሬ አመት በዝውውር በመምጣት ህይወቷ እስከ አለፈበት ትላንት ድረስ በሆስፒታሉ በጠቅላላ ሀኪምነት ስታገለግል ነበር

ለቤተሰቦቿ ለወዳጅ ዘመዶቿ እና ለስራ ባልደረቦቿ መጽናናትን እንመኛለን



#ምንጭ፦ ደሴ ጠቅላላ ሆስፒታል

ዘንድሮ 8ኛ ክፍል ፈተና ላይ የመጣ ጥያቄ ነው አሉ 🤣የእሼቱ ጎብየ ጥያቄ አይነት
11/06/2025

ዘንድሮ 8ኛ ክፍል ፈተና ላይ የመጣ ጥያቄ ነው አሉ 🤣
የእሼቱ ጎብየ ጥያቄ አይነት

በዚህ ሠአት የአማራ ክልልን ፖለቲካ ከያዘው በሽታ  እንዲያገግም ለማድረግ   መታዘዝ ያለበት ትክክለኛ መድሀኒት የወሎ የፖለቲካ ስነልቦና ነው።   በአማራ ክልል ፖለቲካ ውስጥ ደግሞ ወሎን ከ...
03/06/2025

በዚህ ሠአት የአማራ ክልልን ፖለቲካ ከያዘው በሽታ እንዲያገግም ለማድረግ መታዘዝ ያለበት ትክክለኛ መድሀኒት የወሎ የፖለቲካ ስነልቦና ነው።

በአማራ ክልል ፖለቲካ ውስጥ ደግሞ ወሎን ከያዘው የአጨብጫቢነት በሽታ አገግሞ በራሱ ፀንቶ እንዲቆምና ተፎካካሪ እንዲሆን ለማድረግ ሊታዘዝለት የሚገባው መድሀኒት የጎጃም የፖለቲካ ንቃት እንዲሁም የወሎ ኮምቦልቻ ከተማ አካታች ስርአት (Inclusive system ) ነው።

በእያንዳንዳችን ውስጥ ያለውን በሽታ በመፈራራት ጭንብል ከላይ ከላይ እያስመሠሉ በመሸፋፈን ከበሽታው ማገገም አንችልም።

በሽታችንን ያለምንም ፍርሃትና መሸማቀቅ ፈንቅለን በማውጣት መነጋገር መቻል አለብን።

በእያንዳንዳችን ውስጥ ላለው የበሽታ አይነት ትክክለኛ መድሀኒት ካልታዘዘ በስተቀር ከያዘን የውስጥ ህመም በቀላሉ አገግመን መዳን አንችልም።‼️

የደሴ ልጅ በመሆኔ ኩራት እንዲሰማኝ ከሚያደርጉኝ "የደሴ ልጆች" መሀል ዛሬ አንዱን ላስተዋውቃችሁ 💚💛❤️ዛሬ ጁመኣ ነው። እጅግ በጣም ስለማደንቃቸው እና ከእርሳቸው ጋር አንድ ሀገር በመወለዴ...
03/06/2025

የደሴ ልጅ በመሆኔ ኩራት እንዲሰማኝ ከሚያደርጉኝ "የደሴ ልጆች" መሀል ዛሬ አንዱን ላስተዋውቃችሁ 💚💛❤️
ዛሬ ጁመኣ ነው። እጅግ በጣም ስለማደንቃቸው እና ከእርሳቸው ጋር አንድ ሀገር በመወለዴ ከምኮራባቸው የደሴ ልጆች መሀል አንዱን ላስተዋውቃችሁ። (ዩኒቨርሲቲ እያለን እኔና መሰል የደሴ ልጆች የደሴው በላይ ዘለቀ) እያልን ነበር የምንጠራቸው) ሼህ ሰዒድ ሙሐመድ ሷዲቅ 💚💛❤️ ስለ ሼህ ሰዒድ ሙሐመድ የኢትዮጵያ ዝነኛ ደራሲያን ብዙ ፅፈዋል። ከበዓሉ ግርማ እስከ ስብሃት ገ/እግዚአብሔር፣ ከጳውሎስ ኞኞ እስከ ፀጋዬ ገ/ መድን ሼህ ሰዒድን አድንቆ ያልፃፈ የለም። ለመሆኑ ሼህ ሰዒድ ሙሐመድ ማን ናቸው ?
የሼህ ሰዒድ እናት ዘምዘም ሰዒድ ከእትየ መነን አስፋው ዓሊ ቦሩ ጋር በእኩል እርቀት ላይ የሚገኝ ዝምድና ነበራቸው፡፡ ዘምዘም የድንቂቱ ቦሩ የልጅ ልጅ ሲሆኑ ልዕልት መነን ደግሞ የአሊ ቦሩ የልጅ ልጅ ነበሩ። ይህም ማለት ዘምዘምና ልዕልት መነን የእህትና የወንድም የልጅ ልጆች ነበሩ ማለት ነው።
አባታቸው ደግሞ ሼህ ሙሐመድ ሷዲቅ ናቸው፡፡ በ1842 - 1901 በዘመናዊ ተቋማት ሳይተኩ ከከሰሙት ጥንታዊ የትምህርትና የባህል ማዕከሎች አንዱ ተደርጎ የሚወሰድ ማዕከል የመሰረቱ ታላቅ መምህር ነበሩ። በዚሁ ማዕከላቸው ውስጥም በአንድ ጊዜ ከ500 እስከ 800 ያስተናግዱበት ነበር፡፡ ፕ/ር ሁሴን አህመድ "lslamic Literature and religious revival in Ethiopia" ባሉት መፅሐፋቸው ላይ "ይህ ማዕከላቸው በተለይ ሰማንያ ስመ ጥር መምህራን ስለማፍራቱ ይነግሩናል" በረጅሙ የእስልምና ታሪክ ወስጥ አራት መዝሃቦች (school of thoughts) ገዥ ሆነው ዘልቀዋል፡፡ ከአራቱ መዝሃቦች ውስጥ አንዱ እና አገራችንን ጨምሮ በመላው ሙስሊም አለም ዘንድ ሰፊ ተከታይ ያፈራው በኢማም አሽ- ሻፊኢይ (767-820) የተመሰረተውና በስማቸው የተጠራው የሻፊኢይ መዝሃብ ነው፡፡ ማርታ ቶርሲኒ ክሮዝ የተባሉ ፀሐፊ "state and religion in the constitution፡ politics of Ethiopia" በተሰኜ ድንቅ መፅሐፋቸው "ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው የዚህ መዝሃብ ሊቃውንቶች መካከል ሼህ ሙሐመድ ሷዲቅ ግንባር ቀደም ሆነው የሚጠቀሱ ናቸው፡፡" ይሉናል፡፡ ዶ/ር አህመድ ሐሰን ኡመር ደግሞ "በብዙ የኢትዮጵያ ሙስሊም ምሁራን ዘንድ "ሁለተኛው ሻፊኢይ" የሚል ቅፅል ስም ወጥቶላቸው እንደነበር "A preliminary note on religions in Ethiopia" ባሉት መፅሐፍ ላይ ጠቀስ ያረጉታል፡፡
እንግዲህ የኔ ናፍቆት ከእመት ዘምዘም ሰዒድና ከሼህ ሙሐመድ ሷዲቅ ደሴ ከተማ ሜጠሮ ሰፈር ላይ ነው የተወለዱት። በነገራችን ላይ ሼህ ሰዒድ ሙሐመድ ሷዲቅ በተወለዱበት ደሴ ከተማ ላይ በ1943 ዓ.ም አገር ጉድ ባሰኜ በደመቀ ሰርግ ከዘይነብ አብደላ ጋር ትዳር የመሰረቱ ጊዜ ጣሊያን ጥሎት የሄደው 13 ክፍሎች ያሉት ትልቅ መኖርያ ቤታቸውን አንድ ቀን ለማስቃኜት እሞክራለሁ!)
ሼህ ሰዒድ ሙሐመድ የጳውሎስ ኞኞ፣ የስብሐት ገ/ እግዚአብሔር፣ የበዓሉ ግርማ እና የሌሎች ስመ ጥር ደራስያት አስተማሪ እንደነበሩ፡፡ እራሱ ጳውሎስ ኞኞ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከመፃፉም በላይ ዘነበ ወላ የተባለው ደራሲ "ማስታዎሻ" ሲል በፃፈው የጋሽ ስብሃትን ታሪክ በሚተርከው በፅሀፉ ላይ ስብሃት ለሼህ ሰዒድ የነበራቸውን አድናቆት ፅፏል። እንዳለጌታ ከበደ የተባለው ደራሲም የበዓሉ ግርማ ህይወትና ስራዎች በተሰኜው መፅሀፉ ላይ "እውቀት ሞልቶ የፈሰሰባቸው" ሲል ሼህ ሰዒድ ሷዲቅ ስም ጠርቶ ጠቅሷል።
ሼህ ሰዒድ ሷዲቅ ከንጉሱ ጋር በነበረ

 # የወሎከብዙ ጥቂቶቹ  ጥያቄዎች ከታች ተዘርዝረውልካል አንብብና የት ደረሱ ብለህ ጠይቅ። #ወሎ ብለውም ለወጥራት ተጠይፈውህ ነበር ሪፈር አድርግ።የወሎ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች ትላንትና ዛ...
31/05/2025

# የወሎከብዙ ጥቂቶቹ ጥያቄዎች ከታች ተዘርዝረውልካል አንብብና የት ደረሱ ብለህ ጠይቅ።
#ወሎ ብለውም ለወጥራት ተጠይፈውህ ነበር ሪፈር አድርግ።
የወሎ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች ትላንትና ዛሬ ‼️
*********
እንደሚታወቀው ወሎ የቀደምት ስልጣኔ ባለቤት ፣ የአለማቀፋዊ ቅርስ ባለቤት ፣ የታላላቅ ሀይማኖታዊ እና ታሪካዊ ቦታዎች ባለቤት እንድሁም በሀገራችን አንቱ የተባሉ የሀይማኖር አባቶች እና የሀይማኖት ትምህርት ምንጭ መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው።

✍️ሆኖም ግን በዚህ ህዝብ ላይ በሚከሰቱ ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች እና አደጋዎች እንድሁም መንግስት መር መዋቅራዊ ( ክልላዊ እና ፌደራላዊ ) ደባ እና ሸፍጥ ህዝቡ አካባቢውን ለቆ እንዲሰደት፣ በአካባቢው እንዳያለማ ፣ እንዳይማር ፣ እንዳይነቃ ፣ እንዳይደራጅ ፣ አንድ እንዳይሆን በሁለቱ ምክኒያቶች ተሰርቶበታል።

✍️ይህነንም ተከትሎ ወሎ የነበረውን ከፍታ ፣ ወግ ፣ እሴት ፣ ባህል ፣ ማንነት ፣ ታሪክ ፣ ኢኮኖሚው እና የፖለቲካውን ልዕልና እንዲያጣ ሆኗል።

✍️ ወሎ በአጼው ዘመነ መንግስት የሀገሪቱ ዋና መናገሻ የነበረች ፣ እንድሁም ትልቅ የፖለቲካ ማዕከል የነበረ ሲሆን በቅርቡ እንኳን በሃገራችን #ከመርካቶ በመቀጠል ትልቁ የንግድ ማዕከል ወሎ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው።

✍️ ወደ ዋናው ጉዳየ ስገባ የወሎ ህዝብ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር በመሆን ያን አፋኝ የህወሃት ስርዓት ግንባር ቀደም ሆኖ ለህዝቡ እኩል ተጠቃሚነት ፣ ማህበራዊ ፍትህ ፣ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ፣ እኩል የመልማት እና የማደግ መሰረታዊ እና አንኳር ጥያቄዎችን በማንገብ መላው የሀገራችን ህዝቦች ጋር በመሆን በመታገል ህወሃትን የመጨረሻ ቀብ- ሯን ወልድያ ላይ በማድረግ ለውጡ እንድመታ አስችሏል።

✍️ይህም ሲሆን ማህበረሰቡ ከለውጡ በፊት እና ቡሃላ ይዟቸው የነበሩ ጥያቄዎች የመሰረተ ልማት ፣ የትምህርት ፣ የጤና ፣ የመንገድ ፣ መብራት እና ሌሎች ጥያቄዎች ነበሩ። ከነዙህም ውስጥ ዋና ዋና ወቹ

🌴 የወሎ ተሪሸሪ እና ኬር ሆስፒታል

🌴 የኮምቦልቻ ሃራ ገቢያ ባቡር ፕሮጀክት

🌴የደሴ ኮምቦልቻ ሽንቁር መንገድ ፕሮጀክት

🌴 የመካነ ሰላም አየር መንገድ ፕሮጀክት

🌴የዋግ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ

🌴የቆቦ ጊራና ውሃ ፕሮጀክት

🌴 የወሎ ህዝብ የመብራት ሀይል አቅርቦት ችግር

🌴የመርሳ ቆዳ እና ሌጦ ፋብሪካ መቆም

🌴 የሰቆጣ አስፋልት ስራ

🌴የወሎ ሀይቆች ልማት ፕሮጀክት

🌴 የነ ጊሸን ማርያም አስፋልት ስራ

🌴የወሎ ዞኖች እና ወረዳዎች በጀት ጉዳይ

🌴እና ሌሎች መሰረታዊ ጥያቄ የነበሩ ሲሆን ፦

✍️ነገር ግን ዛሬ ደግሞ የወሎ ህዝብ በይበልጥ ከለውጡ ማግስት በማንቻውም የሀገሪቱ ክፍል በሚደርሱ ግጭቶች ፣ ረብሻዎች ፣ ጦርነት እና የዘር ማጥፋት ተግባራት የገፈቱ ቀማሽ እርሱ እና እርሱ ብቻ ነው።

✍️ በዚህ 4 ዓመት ውስጥ በመቶ ሺዎች የሚጠጉ የማህበረሰባችን ክፍሎች ከሶማልያ ፣ ከኦሮምያ ፣ ከደቡብ እና ከትግራይ ተፈናቅለው ሲገኙ ይህን የማህበረሰብ ክፍል በስሙ ለምኖ የግል ኪሱን እና ስልጣኑን ያራዘመ እንጅ አንድም የጠየቀው መንግስት የለም።

✍️ሩቅ ሳንሄድ በህወሀት ወረ ራ ሰሞን የወሎ ህዝብ ሙሉ ንብረቱ ተዘርፏል ፣ ወድሟል ፣ ተቃጥሏል። ይህን ውድመት ለሀገር የተከፈለ መስዋትነት ነው ብሎ ድጋፍ ያደረገ አንድም የክልልሞ ሆነ የፌደራል መንግስት እንድሁም NGO የለም።

ይህነንም ተከትሎ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተፈናቅሎ የመጣው ማህበረሰብ ፣ በጦርነት ንብረቱ የተዘረፈበት ፣ የተቃጠለበት ማህበረሰብ ያለ ማንም ጠያቂ ሜዳ ላይ ቀርቷል

31/05/2025

# የወሎከብዙ ጥቂቶቹ ጥያቄዎች ከታች ተዘርዝረውልካል አንብብና የት ደረሱ ብለህ ጠይቅ።
#ወሎ ብለውም ለወጥራት ተጠይፈውህ ነበር ሪፈር አድርግ።
የወሎ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች ትላንትና ዛሬ ‼️
*********
እንደሚታወቀው ወሎ የቀደምት ስልጣኔ ባለቤት ፣ የአለማቀፋዊ ቅርስ ባለቤት ፣ የታላላቅ ሀይማኖታዊ እና ታሪካዊ ቦታዎች ባለቤት እንድሁም በሀገራችን አንቱ የተባሉ የሀይማኖር አባቶች እና የሀይማኖት ትምህርት ምንጭ መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው።

✍️ሆኖም ግን በዚህ ህዝብ ላይ በሚከሰቱ ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች እና አደጋዎች እንድሁም መንግስት መር መዋቅራዊ ( ክልላዊ እና ፌደራላዊ ) ደባ እና ሸፍጥ ህዝቡ አካባቢውን ለቆ እንዲሰደት፣ በአካባቢው እንዳያለማ ፣ እንዳይማር ፣ እንዳይነቃ ፣ እንዳይደራጅ ፣ አንድ እንዳይሆን በሁለቱ ምክኒያቶች ተሰርቶበታል።

✍️ይህነንም ተከትሎ ወሎ የነበረውን ከፍታ ፣ ወግ ፣ እሴት ፣ ባህል ፣ ማንነት ፣ ታሪክ ፣ ኢኮኖሚው እና የፖለቲካውን ልዕልና እንዲያጣ ሆኗል።

✍️ ወሎ በአጼው ዘመነ መንግስት የሀገሪቱ ዋና መናገሻ የነበረች ፣ እንድሁም ትልቅ የፖለቲካ ማዕከል የነበረ ሲሆን በቅርቡ እንኳን በሃገራችን #ከመርካቶ በመቀጠል ትልቁ የንግድ ማዕከል ወሎ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው።

✍️ ወደ ዋናው ጉዳየ ስገባ የወሎ ህዝብ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር በመሆን ያን አፋኝ የህወሃት ስርዓት ግንባር ቀደም ሆኖ ለህዝቡ እኩል ተጠቃሚነት ፣ ማህበራዊ ፍትህ ፣ ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ፣ እኩል የመልማት እና የማደግ መሰረታዊ እና አንኳር ጥያቄዎችን በማንገብ መላው የሀገራችን ህዝቦች ጋር በመሆን በመታገል ህወሃትን የመጨረሻ ቀብ- ሯን ወልድያ ላይ በማድረግ ለውጡ እንድመታ አስችሏል።

✍️ይህም ሲሆን ማህበረሰቡ ከለውጡ በፊት እና ቡሃላ ይዟቸው የነበሩ ጥያቄዎች የመሰረተ ልማት ፣ የትምህርት ፣ የጤና ፣ የመንገድ ፣ መብራት እና ሌሎች ጥያቄዎች ነበሩ። ከነዙህም ውስጥ ዋና ዋና ወቹ

🌴 የወሎ ተሪሸሪ እና ኬር ሆስፒታል

🌴 የኮምቦልቻ ሃራ ገቢያ ባቡር ፕሮጀክት

🌴የደሴ ኮምቦልቻ ሽንቁር መንገድ ፕሮጀክት

🌴 የመካነ ሰላም አየር መንገድ ፕሮጀክት

🌴የዋግ ዩኒቨርሲቲ ግንባታ

🌴የቆቦ ጊራና ውሃ ፕሮጀክት

🌴 የወሎ ህዝብ የመብራት ሀይል አቅርቦት ችግር

🌴የመርሳ ቆዳ እና ሌጦ ፋብሪካ መቆም

🌴 የሰቆጣ አስፋልት ስራ

🌴የወሎ ሀይቆች ልማት ፕሮጀክት

🌴 የነ ጊሸን ማርያም አስፋልት ስራ

🌴የወሎ ዞኖች እና ወረዳዎች በጀት ጉዳይ

🌴እና ሌሎች መሰረታዊ ጥያቄ የነበሩ ሲሆን ፦

✍️ነገር ግን ዛሬ ደግሞ የወሎ ህዝብ በይበልጥ ከለውጡ ማግስት በማንቻውም የሀገሪቱ ክፍል በሚደርሱ ግጭቶች ፣ ረብሻዎች ፣ ጦርነት እና የዘር ማጥፋት ተግባራት የገፈቱ ቀማሽ እርሱ እና እርሱ ብቻ ነው።

✍️ በዚህ 4 ዓመት ውስጥ በመቶ ሺዎች የሚጠጉ የማህበረሰባችን ክፍሎች ከሶማልያ ፣ ከኦሮምያ ፣ ከደቡብ እና ከትግራይ ተፈናቅለው ሲገኙ ይህን የማህበረሰብ ክፍል በስሙ ለምኖ የግል ኪሱን እና ስልጣኑን ያራዘመ እንጅ አንድም የጠየቀው መንግስት የለም።

✍️ሩቅ ሳንሄድ በህወሀት ወረ ራ ሰሞን የወሎ ህዝብ ሙሉ ንብረቱ ተዘርፏል ፣ ወድሟል ፣ ተቃጥሏል። ይህን ውድመት ለሀገር የተከፈለ መስዋትነት ነው ብሎ ድጋፍ ያደረገ አንድም የክልልሞ ሆነ የፌደራል መንግስት እንድሁም NGO የለም።

ይህነንም ተከትሎ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተፈናቅሎ የመጣው ማህበረሰብ ፣ በጦርነት ንብረቱ የተዘረፈበት ፣ የተቃጠለበት ማህበረሰብ ያለ ማንም ጠያቂ ሜዳ ላይ ቀርቷል

Address

Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo news media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share