Wollo news media

Wollo news media news on wollo

ስለ ወሎ ያልተነገሩ እውነቶች" በአማራ ክልል አካባቢወች ውስጥ የኤሌክትሪክና ስልክ አገልግሎትን ቀድሞ በማግኘት ወሎ ቀዳሚው ነው። ደሴ ከተማ ከክልሉ ከተሞች ውስጥ ስልክ እና የኤሌክትሪክ አ...
04/09/2025

ስለ ወሎ ያልተነገሩ እውነቶች

" በአማራ ክልል አካባቢወች ውስጥ የኤሌክትሪክና ስልክ አገልግሎትን ቀድሞ በማግኘት ወሎ ቀዳሚው ነው። ደሴ ከተማ ከክልሉ ከተሞች ውስጥ ስልክ እና የኤሌክትሪክ አገልግሎት በማግኘት ቀዳሚዋ ነች።

ባቲ፣ ትዝታ፣ አንቺ ሆዬ እና አምባሰል የሚባሉት አራቱ የኢትዮጲያ የሙዚቃ ቅኝቶች መሰረታቸው ወሎ ነው (ሌሎች ኢትዮጲያውያን ወገኖቻችን ደስ እንዲሰኙባቸው ምክንያት መሆናችን ደስ አሰኝቶናል)።

"በአማራ ክልል ውስጥ ቀዳሚው ዘመናዊ ትምህርት ቤት የተጀመረው ወሎ ደሴ ላይ ነው።

" በኢትዮጲያ እስልምና ታሪክ ውስጥ ስማቸው ገናና ሆኖ የሚታወቁት እነደ ዳና፣ ጥሩ ሲና፣ ሾንኬ፣ ጫሊ፣ ገታ፣ ደገር ወዘተ አይነት መድረሳወች የሚገኙት ወሎ ውስጥ ነው።

"ኢትዮጲያዊ የሆነው መንዙማ የተጀመረው በወሎ ነው

"በአማራ ክልል ከሚገኙ ጥንታዊ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ እጅግ ጥንታዊ የሆነችው እና ቀደምቷ ተድባበ ማርያም የምትገኘው በወሎ ነው።

" አማራ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ከ1000 ዓመት በላይ እድሜ ካስቆጠሩ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ በግርድፉ ከ70% በላይ የሚሆኑት የሚገኙት በወሎ ውስጥ ነው።

"የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ አማኞች በታላቅ ክብር ከተለያየ የኢትዮጲያ ክፍልና ከአለም ተሰባስበው ለሃይማኖታዊ የሚታደሙባቸው ግሸን ደብረ ከርቤ እና ቅዱስ ላሊበላ የሚገኙት በወሎ ነው።

"ኢትዮጲያን ለዘመናት የገዟት የዛጉዌ፣ የሰሎሞናዊ፣ የወረሴህ እና የማመዶች ሥርወ መንግስታት የተመሰረቱት በወሎ ነው። መራ ተክለ ሃይማኖት፣ ዓጤ ይኩኖ አምላክ ፣ አባ ሴሩ ጓንጉል፣ አባ ጂቦ መሀመድ አሊ የተሰኙት የእነዚህ ሥርወ መንግስታት መስራቾች ከዚሁ ከወሎ ምድር የተፈጠሩ ናቸው።

" የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የአገው እና የአርጎባ ህዝቦች በወሎ ውስጥ ይገኛሉ ።

" በዘመናዊ የኢትዮጲያ ታሪክ ውስጥ የወሎየወች ከፍታ የሚባለው አቤቶ እያሱ ስልጣን ሲወርሱ አባታቸው ሚካኤል ዓሊ ንጉሠ ጽዮን ተብለው የወሎ፣ የጎንደር ፣ የትግሬና የጎጃም የበላይ ገዥ ሲባሉ ነው።

" ከአማራ ክልል አካባቢወች ግንባር ቀደም በመሆን የአክስዮን ማህበር ያቋቋሙት ወሎየወች ናቸው። የወሎ ፈረስ ትራንስፖርት አክስዮን ማህበርን በእነ ፊታውራሪ አመዴ ለማ አማካኝነት በግንባር ቀደምነት ተመስርቷል።

" ወሎ የበርካታ ማዕድኖች መገኛ እንደሆነ ይነገራል። የብረት፣ የድንጋይ ክሰል ፣ የነዳጅ ፣ የወርቅ ፣ የከበሩ ድንጊያወችና ላይም ስቶን ወዘተ እምቅ ሀብት አለው።

"የተከዜ ወንዝ መነሻ ወሎ ውስጥ ነው። ለአባይ ገባር የሆነው ታላቁ በሽሎ እና የአዋሽ ገባር የሆነው ቦርከናም ከወሎ የተለያዩ አካባቢወች የሚነሱ ናቸው።

አድሱ የደመወዝ ማሻሻያ ከ2018 ዓ.ም    ጀምሮ
19/08/2025

አድሱ የደመወዝ ማሻሻያ ከ2018 ዓ.ም
ጀምሮ

15/08/2025
ወሎየነት
15/08/2025

ወሎየነት

አሳዛኝ ዜና  #በደሴ ከተማ ጠቅላላ ሀኪም የሆነችው ወጣቷ ዶክተር  #አስረበብ አበበ ተሰማ በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይታናለች    በደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል  በጠቅላላ ሀኪ...
13/08/2025

አሳዛኝ ዜና

#በደሴ ከተማ ጠቅላላ ሀኪም የሆነችው ወጣቷ ዶክተር #አስረበብ አበበ ተሰማ በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይታናለች

በደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በጠቅላላ ሀኪምነት ላለፈው አንድ አመት በሆስፒታሉ ስታገለግል የቆየችው ወጣት ዶ/ር አስረበብ አበበ ትላንት በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይታለች

የወጣት ዶ/ር አስረበብ ድንገተኛ ሞት ብዙዎችን አሳዝኗል አስለቅሷል
ወጣት ሀኪም ዶ/ር አስረበብ አበበ ስራዋን አክባሪ በታካሚዎቿና በስራ ባልደረቦቿ የምትወደድና የምትመሰገን ተስፋ የተጣለባት ጠቅላላ ሀኪም ነበረች

ወጣቷ ዶ/ር በ2014 ከጎንደር ዩኒቨርስቲ በከፍተኛ ማዕረግ በዶክትሬት ተመርቃ አንድ አመት በመካነ ሰላም ጠቅላላ ሆስፒታል ሰርታ ወደ ደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዛሬ አመት በዝውውር በመምጣት ህይወቷ እስከ አለፈበት ትላንት ድረስ በሆስፒታሉ በጠቅላላ ሀኪምነት ስታገለግል ነበር

ለቤተሰቦቿ ለወዳጅ ዘመዶቿ እና ለስራ ባልደረቦቿ መጽናናትን እንመኛለን



#ምንጭ፦ ደሴ ጠቅላላ ሆስፒታል

Address

Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo news media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share