Deribe Jino

Deribe Jino This is my official page. https://t.me/DeribeJinoofficial

የጌዴኦ ብሔር ዘመን መለወጫ ''ዳራሮ''በዓል በውጭ ሀገራት በድምቀት ለማክበር አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ Ethiopia||    16/2018ዓ.ምየበዓሉ አከባበርና ዝግጅት በሚመለከት የ...
26/01/2026

የጌዴኦ ብሔር ዘመን መለወጫ ''ዳራሮ''በዓል በውጭ ሀገራት በድምቀት ለማክበር አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ

Ethiopia||

16/2018ዓ.ምየበዓሉ አከባበርና ዝግጅት በሚመለከት የጌዴኦ ዲያስፖራ ማህበር ፕሬዚዳንት ሄኖክ ታደሰ (ዶ/ር) ለተለያዩ ሚዲያዎች መግለጫ ሰጥተዋል።

እንደ ሄኖክ ታደሰ (ዶ/ር) ገለጻ የጌዴኦ ዞን ዳያስፖራ ማህበር በውጪ አገራት ነዋሪ የሆኑ የጌዴኦ ዞን ተወላጆችና ወዳጆችን አቅፎ የምንቀሳቀስ በኢትዮጵያና በአሜሪካ የተመዘገበ ሕጋዊ ተቋም እንደሆነ አንስተዋል።

ማሕበሩ የዞኑን ተወላጆች ያለ ብሔር፣ ሐይማኖትና የፖለቲካ አቋም ልዩነት አቅፎ የምንቀሳቀስ መሆኑንና የዞኑን ባሕልና ቋንቋን ጨምሮ የዞኑ ማሕበራዊና እኮኖሚያዊ ልማት ላይ እንደሚሰራ ነው የተናገሩት።

የጌዴኦ ዞን አስተዳደርና በማሕበሩ የጋራ እቅድ መሰረት የጌዴኦ ብሔር ዘመን መለወጫ ''ዳራሮ'' በዓል በተለያዩ በውጭ ሀገራት በJanuary 31/2026 እንደሚከበር ነው የገለፁት።

በአዲስና በለውጥ አስተሳሰብ በአንድነት እና በጋራ እጅ ለእጅ በመያያዝ የተጀመረው ልማት፣ባህሉን ወደላቀ ደረጀ ለማሸጋገር በጋራ ቃል የሚገባበት ጊዜ እንደምሆን አንስተዋል።

በዓሉ በJanuary 31/2026 በሰሜን አሜሪካ (ዋሽንግተን ዲሲ) በኤምባሲው አደራሽ፣በአውሮፓ(በጀርመን ፍራንክፈርት)- በደቡብ ኢትዮጵያ ልማት ማህበር መሰብሰቢያ አደራሽ እንደሚከበር ጠቁመዋል።

በመካከለኛው ምስራቅ (በሳውዲ አረቢያ) በጂዳ የኢትዮጵያ ቆጽላ ጽ/ቤት በተመሳሳይ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር ነዎ
ሄኖክ ታደሰ (ዶ/ር) ያረጋገጡት።

በበዓሉ የዳራሮን በዓል እሴቶችና መርሆዎች ከክርሰትና እምነት አንፃር በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ የዶክቶራል ተማሪ በሆኑት የዳራሮ ተመራማሪ የውይይት ሀሳብ ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግም ይጠበቃል።

በሌላ ዜና በጌዴኦ ዞንና የዲላ ከተማ የኢንቨስትመንት እድሎችና አማራጮች ላይ በጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪና በዲላ ከተማ የመወያያ ነጥቦች ቀርበው ከመላው ዳያስፖራ አባላት ጋር ውይይት ይደረጋልም ብለዋል።

የዳራሮ በዓል በውጭ ሀገራት የጌዴኦ ተወላጆች ወዳጆች እና ተጋባዥ እንግዶች በተሳተፉበት በተለያዩ በዓላዊ ኩነቶች በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር ይጠበቃል።

ንስርን በተፈጥሮ ከሚገዳደሩት የወፍ ዝርያዎች መካከል አንዱና ዋነኛ የሆነው ቁራ ነው። ቁራ በንስሩ ጀርባ ላይ በመፈናጠጥ የንስሩን አንገቱን እና ጀርባውን መንከስ ይጀምራል።ኢትዮጵያ||  #ጌ...
10/08/2025

ንስርን በተፈጥሮ ከሚገዳደሩት የወፍ ዝርያዎች መካከል አንዱና ዋነኛ የሆነው ቁራ ነው። ቁራ በንስሩ ጀርባ ላይ በመፈናጠጥ የንስሩን አንገቱን እና ጀርባውን መንከስ ይጀምራል።

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

በዚህን ጊዜ ንስሩ ለመከላከል ወይም ከላዩ ላይ ለማስወገድ የሚያደርገው አንዳችም ዓይነት ምላሽ አይኖርም። ጸብ ውስጥም አይገባም፣ ግጭትም አይፈጥርም።

ከቁራው ጋር እየታገለ ምንም ዓይነት ጊዜና ጉልበትንም አያባክንም። ነገር ግን አንድ ነገር ያደርጋል። ይህም ንስሩ ረዣዥም ክንፎቹን በመዘርጋት ከፍ ወዳለው ወደ ሰማየ ሰማያት መወንጨፍ ይጀምራል።

ከፍታው በጨመረ ቁጥር ቁራው አየር ንብረቱን መቋቋም ስለማይችል መተንፈስ አስቸጋሪ ይሆንበታል። በስተመጨረሻም በኦክስጂን እጥረት ምክንያት ቁራው ከጀርባው ላይ ይወድቃል።

ከቁራዎች ጋር ጊዜያችሁን አታባክኑ። ቀጥታ ወደ ከፍታ ውሰዷቸው። የዚያን ጊዜ መተንፈስ ስለማይችሉ አቅም በማጣት ተሸንፈው ይወድቃሉ።

ጊዜያችሁንና ጉልበታችሁን ከደካሞች ጋር በመላፋት አታባክኑ። ከፍታን ምረጡ!!

እናንተ ከፍ ስትሉ ራሳቸው ይወድቃሉ እንጅ እነሱን ለመጣል ምንም ጉልበት አታባክኑ!!!

እንደ ንስር ከፍታችሁን ምረጡ! ቴሌግራም ቻናሉን ለመቀላቀል

+ ለምን ትቀናለህ? +  ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦ በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደ...
27/06/2025

+ ለምን ትቀናለህ? +

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ፡፡

ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉበት፡፡ በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ፡፡ አልተሳካም፡፡ በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም፡፡

አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት፡፡

በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ ‘ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ’ ብዬ ነገርኩትና ወጣሁ፡፡ አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደስታ ጨፈሩ፡፡

ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን ሲገልጸው ‘በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ’ ይለዋል፡፡ ሰይጣን በሰው ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት፡፡ መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::

ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው:: ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡ ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ፡፡

ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር፡፡ አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡

ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም፡፡ እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡ ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል፡፡ ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን ፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡ ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል፡፡ ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ፡፡

ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ ‘ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ’ ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር አስወረወረች፡፡ ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡

የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው፡፡ (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ፡፡ ወዳጄ ቅናት ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል፡፡ የሌላው ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር እየጫርክ ‘እምቢየው አልገባም’ እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ፡፡

ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር፡፡ ጲላጦስ እንኳን ‘በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር’ ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ፡፡

የሰንበት መሻር ፣ ለቄሣር ግብር መከፈል ፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ ‘የቤትህ ቅናት በላኝ’ እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች፡፡

ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ ካንሰር ራስህን አድን፡፡

ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም፡፡ ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር፡፡

ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው፡፡ ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ፡፡ መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ አንተን ሁን፡፡

በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው፡፡ ከወደድሃቸው ‘ፍቅር አይቀናም’ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ‘ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ’ ብለህ ለምነው፡፡

‘በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን’ ሮሜ 13፡13

/// " የነጠፈ ብዕር "///ብዕር ወዙን አጥቶ ቀለሙ ነጠፈጥበብ ማማጥ ትቶ በዘር ተለከፈቅኔን አፍልቅ ቢሉት  ደም እየሰበከከመንደር ሳይወጣ ግፍ እየታከከወረቀቱን ሁሉ በክሎ ጨረሰውባለቅኔ ...
21/06/2025

/// " የነጠፈ ብዕር "///
ብዕር ወዙን አጥቶ ቀለሙ ነጠፈ
ጥበብ ማማጥ ትቶ በዘር ተለከፈ
ቅኔን አፍልቅ ቢሉት ደም እየሰበከ
ከመንደር ሳይወጣ ግፍ እየታከከ
ወረቀቱን ሁሉ በክሎ ጨረሰው
ባለቅኔ መጥቶ እንዳይጠቀመው
የነጠፈ ብዕር ድርቀት ያደረቀው
ቢጽፍ አያምርበት ጽፎ መደለዝ ነው።
/// ስንታየሁ ሀብታሙ ///
02/04/2016 ዓ.ም ተጻፈ ///

አዲስ አዋጅ የአንድ ብሩን ፕላስቲክ ከረጢት ከ2,000 እስከ 5,000 ብር ያስቀጣል! የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባጸደቀው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ መሰረት፣ ለአንድ ...
04/06/2025

አዲስ አዋጅ

የአንድ ብሩን ፕላስቲክ ከረጢት
ከ2,000 እስከ 5,000 ብር ያስቀጣል!

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባጸደቀው የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ መሰረት፣ ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ከረጢቶችን ይዞ መገኘት ከ2,000 እስከ 5,000 ብር ያስቀጣል።

ይህ አዋጅ የአካባቢን ንፅህና ለመጠበቅ ያለመ ሲሆን፣ የፕላስቲክ ከረጢቶች በአካባቢያችን ላይ የሚያደርሱትን ጉዳት ለመቀነስ ይረዳል።

ማወቅ ያለብዎት ዋና ዋና ነጥቦች:

1. ማንኛውንም አንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል ፕላስቲክ ይዞ መገኘት ቅጣት ያስከትላል።

2. አዋጁ ህብረተሰቡን እንዳይጎዳ ታሳቢ ተደርጎ የቅጣት መጠኑ ዝቅተኛው 2,000 ብር እንዲሆን ተደርጓል።

3. አዋጁ የፕላስቲክ ጫማዎችን፣ የውሃ ኮዳዎችን እና ወፍራም የፕላስቲክ ውጤቶችን አይጨምርም።

4. ፕላስቲክ የሚያመርቱ፣ የሚያስገቡ፣ የሚሸጡ ወይም ለንግድ ዓላማ የሚያከማቹ ግለሰቦች ከ50,000 እስከ 200,000 ብር ቅጣት እና እስከ 5 ዓመት ፅኑ እስራት ሊቀጡ ይችላሉ።

5. ከመጪው ሐሙስ ጀምሮ የግንዛቤ
ማስጨበጫ መርሃግብር ይካሄዳል።

ተፈጻሚነቱ ደሞ:- አዋጁ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ ተፈጻሚ ይሆናል።

የአዕምሮ ስሪትና የማረፊያ ጥበብ•••ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦ አዕምሮ በሳይኮሎጂስቶች፣ በባህላዊ አባቶች፣ በግለሰቡ እንዲሁም በተለያዩ ጠቢባን፣ በሃይማኖት አባቶች፣ በኪነ ጥበብ በጥልቅ ትገለጻለ...
28/04/2025

የአዕምሮ ስሪትና የማረፊያ ጥበብ•••

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

አዕምሮ በሳይኮሎጂስቶች፣ በባህላዊ አባቶች፣ በግለሰቡ እንዲሁም በተለያዩ ጠቢባን፣ በሃይማኖት አባቶች፣ በኪነ ጥበብ በጥልቅ ትገለጻለች።

ዊኪፒዲያ እንዲህ ይላል•••
አዕምሮ የአንድ ሰው ንቃተ ህሊና አካል ሲሆን በ"ማሰቡ"፣ በ"መረዳቱ"፣ ትዝታን በመፍጠሩ፣ ስሜትን በመረዳቱ፣ በመፍቀዱ እንዲሁም ወደፊት በመመልከቱ የሚገለጽ ነው። በአንዳንድ ፍልስፍናወች አዕምሮ ከአንጎል ይለያል። አዕምሮ እንደ አንጎል ከቁስ ነገር የተሰራ ሳይሆን በምናቡ አለም የተንሰራፋ ነው፡፡ ስለሆነም አዕምሮ ከሞላ ጎደል የማይታይና የማይጨበጥ "ሃሳብ" ስብስብ ነው።

ውስብስብ ከሚያደርጉ ነገሮች መካከል የሰው ልጅ ሲፈጠር በርካታ ሀሳቦች አሉት። ለመረዳት ይከብዳል። ጊዜ ሰቶ ያስባል፣ ያወጣል፣ ያወርዳል ያደላስላል ነገር ግን ከግሉ ጉዳይ ጋር ካያያዘው ውድቀቱ ከባድ ነው።

አዕምሮ የማረፊያ ስፍራውን ካወቀ፣ የተሰጠውን እንደይሁዳ ለዲያቢሎስና ለዲያቢሎሳዊያን ካላከራየ ለራሱ ቀዳሚ ተጠቃሚ ነው። ሌሊት ተነስቶ ዝናብ ሲዘንብ እያየ ተፈጥሮን ከረገመ፣ ቀኑን ለራሱ እንዲመች ካላደረገ አንድም ስኬት የለውም።

ተከፋይ አዕምሮ ሁሉም በፈጣሪ ፍቃድ ለራሱ፣ ለሰው እንዲሁም ለሌሎች እንዲሆን የተሰራ ነው። ለድሃ ማሰብ በጎነት ነው። ድሃውን ግን ማመናጨቅና መመጻደቅ ለክፋት የተከፈለው አዕምሮ ማለት ነው። አንተ እንድትሰጥ ፈጣሪ በቃሉ "ለድሃ የሰጠ ለፈጣሪው አበደረ" ብሎ ሲናገር እግዚአብሔር ይስጥህ ማለት ላይህ አልፈልግም ማለት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ለድሃው ዝም ብለህ ስታልፍ ፈጣሪ ያንተን የገዘፈ ጥያቄ የሚመልስ እንዳይመስልህ። ቃሉ እንዲህ ይላልና•••

“አእምሮ የሌለው ክቡር ሰው እንደሚጠፋ እንስሶች መሰለ።”
መዝሙር 49፥20

ጉንዳን 30ኛ ፎቅ ላይ ወታ ወደ መሬት ብትከሰከስ የሚሰበረው ቅስሟ እንጂ አጥንቷ አይደለም። የብዙ ሰው ሞራል ይነካ ይሆናል። ሞራል የሚነካው በሰው ልጅ አዕምሮ ነው።

አዕምሮ የተሰጠውን ኃላፊነት ካልተወጣ ክፋት፣ ምቀኝነት፣ ትላንት ውስጥ የሚዋኝ ሰውነት፣ ለነገ ትውልድ የማያስብ፣ ባገኘው እና በተመለከተው እየተነሳ የሚያጓራ ከሆነ አዕምሮ ስራ አቁሟል ማለት ነው።

አዕምሮ ለመልካም ተሰርቷል። ክርስቶስ የይሁዳ እግሮች ያመራው፣ ያመላከተው፣ ያቀናጀው፣ ያሰለጠነው ለአገልግሎት ነበር። ነገር ግን የትንቢት መፈፀሚያ ሆኖ አምላኩ፣ የፈጠረው ጌታ እንዲሰቀል፣ ለፍርድ እንዲቀርብ አድርጎታል።

የኛ አዕምሮ ማረፊያው የት ነው? ምን ይመክራል? ለማን ይመክራል? ወዴት ያመራል? በቀን ማንን ስንት ጊዜ ይገላል? ለማን ይገዛል? ከይሁዳ ጋር ስንቴ ይውላል? ከጴጥሮስ ጋር ስንቴ ይመክራል? ከጥጦስና ዳክርስ ጋር መክሮ ከማን ጋር ውሏል?

ጥያቄው እራስን ለማየት ይረዳ ይሆናል። ለህዝብ የሚጠቅም ጥበብ እንዲገለፅ ያደርግ ይሆናል። መስከንን ያመላክት ይሆናል። እውነት መገለጫዋ የት እንደሆነ ይመሰክር፣ የናገር፣ ያስተምር ሊሆን ይችላል።

ከፈጣሪ የምትሸሽ አዕምሮ ባካኘ ናት። ከሰው የምትሸሸግ አዕምሮ ደግሞ በሻማ፣ በብርሃን፣ በጨረቃ፣ በከዋክብት ብርሃን፣ በኤሌክትሪክ ትጋለጣለች። በዚሀ መጋለጥ ውስጥ ማን ይወቀስ ይሁን? አዕምሮ፣ የአዕምሮ ባለቤት፣ የአዕምሮ ተከራይ፣ የአዕምሮ ደላላ?

ፈጣሪ በፈጠረው ለምለም መሬት ላይ ጥላቻ፣ ክፈት፣ ስድብ፣ መርገምት እና አስከፊ የትውልድ ሳንካ የተከለ እና ሌሎችም የፍርዱ መዶሻና ደወል ድምፅ ተቀባይ ሳይሆኑ አይቀሩም።

ፍርድ ግን ከአዕምሮ ፈጣሪው ነው!

በጉንዳን የሚታከመው ቁራ ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦቁራ ሲታመም ጉዳን በሚገኝበት አካባቢ ሄዶ ይቀመጣል። ከዚያም ክንፉን በመዘርጋት ጉንዳኖቹ ሰውነቱን እንዲወሩትና እንዲነክሱት ይፈቅዳል። ቁራዎች ...
27/04/2025

በጉንዳን የሚታከመው ቁራ

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

ቁራ ሲታመም ጉዳን በሚገኝበት አካባቢ ሄዶ ይቀመጣል። ከዚያም ክንፉን በመዘርጋት ጉንዳኖቹ ሰውነቱን እንዲወሩትና እንዲነክሱት ይፈቅዳል።

ቁራዎች ይህንን የሚያደርጉበት አስገራሚ ምክንያት አላቸው ። ጉንዳኖች ሰውነታቸው "ፎርሚክ አሲድ" የተባለ የተፈጥሮ ፀረ-ተባይ ንጥረ ነገር ይረጫል ። ይህ አሲድ ቁራው ፈንገሶችን፣ ባክቴሪያዎችን እና ጥገኛ ተህዋሲያንን ከሰውነቱ ላይ እንዲያስወግድ ይረዳዋል ። ይህም ህክምና ሳያስፈልገው እንዲያገግም ያስችለዋል።

ይህ ባህሪ "አንቲንግ" ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በተለያዩ የአእዋፍ ዝርያዎች ላይ ተስተውሏል። ይህ የእንሰሳት ራስን የማከም ጥበብ ግሩም ምሳሌ ነው።

ዘወትር ማዕዷን ዘርግታ ለምትመግበን ስንዱ እመቤት አብረን እንስራ!የፍቅርና የበረከት ጥሪ  #ከወናጎ  #ደብረጽዮን  #ቅድስት  #ማርያም ቤተክርስቲያን ምዕመናንና አገልጋይ ካህናት አቅርበውላ...
20/03/2025

ዘወትር ማዕዷን ዘርግታ ለምትመግበን ስንዱ እመቤት አብረን እንስራ!

የፍቅርና የበረከት ጥሪ #ከወናጎ #ደብረጽዮን #ቅድስት #ማርያም ቤተክርስቲያን ምዕመናንና አገልጋይ ካህናት አቅርበውላችኋል።

#ነቢዩ አሞጽ ያስተላለፈውን ጥሪ እስቲ በጥሞና እናንብብ።

" በዚያ ቀን የወደቀችውን የዳዊትን ድንኳን አነሣለሁ፥ የተናደውንም ቅጥርዋን እጠግናለሁ፤ የፈረሰውንም አድሳለሁ፥ እንደ ቀደመውም ዘመን እሠራታለሁ፤ "
ትንቢተ አሞጽ ፱:፲፩

#ወናጎ ደብረጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተክህነት ሥር የሚገኝ ሲሆን ጥንታዊና ታሪካዊ ስዕለት ሰሚ ቤተክርስቲያን ነች።

#ቤተክርስቲያኗ አሁን ጣራው በማፍሰሱ ምክንያት እድሳት ላይ በመሆኗ ነቢዩ አሞጽ እንዳለው የፈረሰውን አድሳለሁ እንደ ቀደመውም ዘመን እሠራታለሁ ስለሚል ቃሉ በሀገር ውስጥ ያላችሁ የእመቤታችን ወዳጆች ከአዲስአበባ ፣ሀዋሳ ፣አዳማ፣ ቢሾፍቱ.... በመላው ሀገሪቱ የምትኖሩ በሙሉ #በውጭ ሀገር በዓርብ ሀገራት በዱባይ ፣ በሳውዲ፣በኩዌት ፣በአሜሪካ ፣በአውሮፓ፣ በአውስትራሊያ ...እስከ ምድር ጫፍ በተለያዩ ሁኔታ ከሀገራችሁ ወጥታችሁ የምትገኙ ሁሉ ዛሬ ጽዮን እናታችን ቅ/ማርያም ልጆቼ ድረሱልኝ በማለት ጥሪዋን እያስተላለፈች ነው።

#ገንዘባችሁን በመለገስ በአጭር ጊዜ ታድሶ ወደ ቀደመ መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠት ይቻል ዘንድ ልግስናችሁ የግድ አስፈልጓል።ለምን ቢባል ታቦታቱ ወጥተው የሚገኙት በቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ተዳብለው ነውና።

#የገንዘብ ልገሳችሁን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለወናጎ ደብረጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በማለት ያስገባችሁበት ስሊፕ ስክሪን ሹት በማድረግ በኢንቦክስ ብትሉኩልን ሌላው እንዲለግስ ያነሳሳል።

#➽1000167792905 የባንክ አካውንት ቁጥር

#የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ የእግዚአብሔር ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ ህብረት፤

#የቅድስተ ቅዱሳን የድንግል ማርያም አማላጅነት የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ አማላጅነት አይለየን አሜን

የታገዱ የምግብ ጨው ምርቶችን ከገበያ ለማስወጣት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸአዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የታገዱ የምግብ ጨው ምርቶችን ከገበያ ለማስወጣ...
18/03/2025

የታገዱ የምግብ ጨው ምርቶችን ከገበያ ለማስወጣት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የታገዱ የምግብ ጨው ምርቶችን ከገበያ ለማስወጣት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

ባለስልጣኑ ባደረገው የገበያ ቅኝት በሕገ-ወጥ መንገድ በገበያ ላይ የነበሩ 49 የገበታ ጨው ምርቶችን ሕብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ማገዱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

የታገዱት የገበታ ጨው ምርቶች ደህንነታቸውና ጥራታቸው ሳይረጋገጥ እንዲሁም የሀገሪቱን አስገዳጅ ብሔራዊ ደረጃ ሳያሟሉ ለገበያ የቀረቡ መሆናቸው ነው የተገለጸው፡፡

በባለስልጣኑ የእንስሳት ተዋጽኦና አልሚ ምግብ ዴስክ ሃላፊ መሃመድ ሁሴን ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የታገዱ የምግብ ጨው ምርቶችን ከገበያ ለማስወጣት እየተሰራ ነው፡፡

ምርቶቹን ከገበያ ለመሰብሰብ እንዲቻል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴርን ጨምሮ ለሚመለከታቸው ተቋማት በደብዳቤ የማሳወቅ ሥራ መከናወኑን አንስተዋል፡፡

በምርት ደረጃ፣ በናሙና እና በገበያ ቅኝት የምርቶችን ደረጃ በየጊዜው ክትትል እንደሚደረግ ገልጸው÷ከገበያ እንዲወጡ ሲደረጉ የንግድ ስም (ብራንድ) እየቀያየሩ ወደ ገበያ የሚመለሱበት ሁኔታ በመኖሩ ጥብቅ ክትትል እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

ባለስልጣኑ በየጊዜው ከሚያካሂደው የገበያ ቅኝት በተጨማሪ ከሕብረተሰቡ በሚደርሰው ጥቆማ መሰረት የጥራት ማረጋገጫ ሳያገኙ በድብቅ ጨው የሚያመርቱ አካላት ላይ ሕጋዊ ርምጃ እየወሰደ መሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡

FBC

ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በጌዴኦ ዞን ተመረቁኢትዮጵያ||  #ጌዴኦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጌዴኦ ዞን፣ ዲላ እና ገደብ ከተሞች ከግማሽ ቢ...
04/03/2025

ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በጌዴኦ ዞን ተመረቁ

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጌዴኦ ዞን፣ ዲላ እና ገደብ ከተሞች ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎች የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት ስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶቹ ከ525 ሚሊዮን ብር በላይ በላይ ወጪ የተደረገባቸው ሲሆን፤ ከ233 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ዳራሮን በዋሽንግተን ዲሲ•••ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦ ዳያስፖራዎቻችን የጌዴኦ ማህበረሰብ ዘመን መለወጫ የዳራሮ በዓል በዲሲ ይከበራል።የጌዴኦ ዞን ተወላጆች፣ ኢትዮጵያዊያን ዳራሮን ለማክበር ቅድመ...
29/12/2024

ዳራሮን በዋሽንግተን ዲሲ•••

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

ዳያስፖራዎቻችን የጌዴኦ ማህበረሰብ ዘመን መለወጫ የዳራሮ በዓል በዲሲ ይከበራል።

የጌዴኦ ዞን ተወላጆች፣ ኢትዮጵያዊያን ዳራሮን ለማክበር ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ዞኑን የማስተዋወቅ ስራ ለመስራት ማቀዳቸውም ተሰምቷል።

የጌዴኦ ማህበረሰብ ፈጣሪውን ሲያመሰግን ምስጋና ድንበር የለውምና በአካል ባንገናኝም ባለንበት እንጋራለን በማለት መነሳሳትን ደጥረዋል ተብሏል።

የባለ ልዩ ጣዕም የጌዴኦ ይርጋ ጨፌ ቡና አምራች የሆነው የሆነው ማህበረሰብ ባህሉ፣ ትውፊቱ፣ ወጉ፣ ልማዱ፣ ታሪኩ እና ቋንቋው እንዲያድግ ለማድረግ ሚና አለው ተብሏል።

ዳያስፖራው አካባቢን ከማስተዋወቅ አልፎ በኢንቨስትመንት እንዲሳተፍ ያደርገዋል የተባለ ሲሆን ሌሎች ዳያስፖራዎች እንዲሳተፉ ዕድል ይሰጣል።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ እንደገለፁት ዳያስፖራው ዳራሮን ከማክበር ባለፈ ለዞኑ ልማትና ዕድገት የዳያስፖራው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው በዞኑ የተጀመሩ ልማቶችን ለማጠናከር ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ አስረድተዋል።

በቱሪዝም ሀብት ልማት ቱሪስቶች አካባቢውን እንዲጎበኙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የተናገሩት አቶ ደርቤ ጅኖ የዳራሮ በዓል በውጪ አገራት መከበሩ ባህሉን በማስተዋወቅ ቱሪስቶችን ያነቃቃል ብለዋል።

ወ/ሮ ሠላም ዋቆ ከቲሞቻቸው ጋር በመሆን እንዳስረዱት በዓሉ እንዲከበር በውጪ የሚገኙ ዳያስፖራዎች ኃላፊነት ወስደው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን አስረድተው በዞኑ ለሚካሄደው ልማት የዳራሮ በዓል መከበሩ አዎንታዊ ምላሽ ያመጣል ብለዋል።

አገር ወዳድ ዳያስፖራዎች በዓሉ በድምቀት እንዲከበር ከማህበሩ ጎን በመሆን ማበረታታት ይገባል ተብሏል።

በአፍሪካ ፕላስቲክ ሊያስወግድ የሚችል ምርምር እያከናወኑ መሆናቸውን ተመራማሪዎች ገለጹ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦህዳር 04 2017| -በአፍሪካ ፕላስቲክን የሚመገብ የትል ዝ...
13/11/2024

በአፍሪካ ፕላስቲክ ሊያስወግድ የሚችል ምርምር እያከናወኑ መሆናቸውን ተመራማሪዎች ገለጹ
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

ህዳር 04 2017| -በአፍሪካ ፕላስቲክን የሚመገብ የትል ዝርያ መገኘቱ የተሰማ ሲሆን ተመራማሪዎቹ ዛሬ ባወጡት መግለጫቸው ለፕላስቲክ ብክለት የመፍትሔ ፍንጭ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡

ፕላስቲክን ይመገባል የተባለለት የትል ዝርያ የመጀመርያ መገኛው በአፍሪካ ሲሆን አሁን ግን በየትኛውም የዓለም ክፍል እንደሚገኝ ነው የተገለጸው፡፡

የአሁኑ የተመራማሪዎቹ ግኝት የፕላስቲክ ብክለት በከፍተኛ ደረጃ ላይ የእስያ እና የአፍሪካ አህጉራት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑ ተነግሯል፡፡

እንደ ዓለም የጤና ድርጅት ማብራሪያ በዓለም የፕላስቲክ ብክለት አንደኛ የእስያ አሕጉር ሲሆን ሁለተኛ ደግሞ የአፍሪካ አሕጉር ነው፡፡ዘገባው የግሪክ ሪፖርተር ድረ ገጽ ነው፡፡

NBC

Address

Gedeo
Dila
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Deribe Jino posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share