Deribe Jino

Deribe Jino This is my official page. https://t.me/DeribeJinoofficial

የአዕምሮ ስሪትና የማረፊያ ጥበብ•••ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦ አዕምሮ በሳይኮሎጂስቶች፣ በባህላዊ አባቶች፣ በግለሰቡ እንዲሁም በተለያዩ ጠቢባን፣ በሃይማኖት አባቶች፣ በኪነ ጥበብ በጥልቅ ትገለጻለ...
28/04/2025

የአዕምሮ ስሪትና የማረፊያ ጥበብ•••

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

አዕምሮ በሳይኮሎጂስቶች፣ በባህላዊ አባቶች፣ በግለሰቡ እንዲሁም በተለያዩ ጠቢባን፣ በሃይማኖት አባቶች፣ በኪነ ጥበብ በጥልቅ ትገለጻለች።

ዊኪፒዲያ እንዲህ ይላል•••
አዕምሮ የአንድ ሰው ንቃተ ህሊና አካል ሲሆን በ"ማሰቡ"፣ በ"መረዳቱ"፣ ትዝታን በመፍጠሩ፣ ስሜትን በመረዳቱ፣ በመፍቀዱ እንዲሁም ወደፊት በመመልከቱ የሚገለጽ ነው። በአንዳንድ ፍልስፍናወች አዕምሮ ከአንጎል ይለያል። አዕምሮ እንደ አንጎል ከቁስ ነገር የተሰራ ሳይሆን በምናቡ አለም የተንሰራፋ ነው፡፡ ስለሆነም አዕምሮ ከሞላ ጎደል የማይታይና የማይጨበጥ "ሃሳብ" ስብስብ ነው።

ውስብስብ ከሚያደርጉ ነገሮች መካከል የሰው ልጅ ሲፈጠር በርካታ ሀሳቦች አሉት። ለመረዳት ይከብዳል። ጊዜ ሰቶ ያስባል፣ ያወጣል፣ ያወርዳል ያደላስላል ነገር ግን ከግሉ ጉዳይ ጋር ካያያዘው ውድቀቱ ከባድ ነው።

አዕምሮ የማረፊያ ስፍራውን ካወቀ፣ የተሰጠውን እንደይሁዳ ለዲያቢሎስና ለዲያቢሎሳዊያን ካላከራየ ለራሱ ቀዳሚ ተጠቃሚ ነው። ሌሊት ተነስቶ ዝናብ ሲዘንብ እያየ ተፈጥሮን ከረገመ፣ ቀኑን ለራሱ እንዲመች ካላደረገ አንድም ስኬት የለውም።

ተከፋይ አዕምሮ ሁሉም በፈጣሪ ፍቃድ ለራሱ፣ ለሰው እንዲሁም ለሌሎች እንዲሆን የተሰራ ነው። ለድሃ ማሰብ በጎነት ነው። ድሃውን ግን ማመናጨቅና መመጻደቅ ለክፋት የተከፈለው አዕምሮ ማለት ነው። አንተ እንድትሰጥ ፈጣሪ በቃሉ "ለድሃ የሰጠ ለፈጣሪው አበደረ" ብሎ ሲናገር እግዚአብሔር ይስጥህ ማለት ላይህ አልፈልግም ማለት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ለድሃው ዝም ብለህ ስታልፍ ፈጣሪ ያንተን የገዘፈ ጥያቄ የሚመልስ እንዳይመስልህ። ቃሉ እንዲህ ይላልና•••

“አእምሮ የሌለው ክቡር ሰው እንደሚጠፋ እንስሶች መሰለ።”
መዝሙር 49፥20

ጉንዳን 30ኛ ፎቅ ላይ ወታ ወደ መሬት ብትከሰከስ የሚሰበረው ቅስሟ እንጂ አጥንቷ አይደለም። የብዙ ሰው ሞራል ይነካ ይሆናል። ሞራል የሚነካው በሰው ልጅ አዕምሮ ነው።

አዕምሮ የተሰጠውን ኃላፊነት ካልተወጣ ክፋት፣ ምቀኝነት፣ ትላንት ውስጥ የሚዋኝ ሰውነት፣ ለነገ ትውልድ የማያስብ፣ ባገኘው እና በተመለከተው እየተነሳ የሚያጓራ ከሆነ አዕምሮ ስራ አቁሟል ማለት ነው።

አዕምሮ ለመልካም ተሰርቷል። ክርስቶስ የይሁዳ እግሮች ያመራው፣ ያመላከተው፣ ያቀናጀው፣ ያሰለጠነው ለአገልግሎት ነበር። ነገር ግን የትንቢት መፈፀሚያ ሆኖ አምላኩ፣ የፈጠረው ጌታ እንዲሰቀል፣ ለፍርድ እንዲቀርብ አድርጎታል።

የኛ አዕምሮ ማረፊያው የት ነው? ምን ይመክራል? ለማን ይመክራል? ወዴት ያመራል? በቀን ማንን ስንት ጊዜ ይገላል? ለማን ይገዛል? ከይሁዳ ጋር ስንቴ ይውላል? ከጴጥሮስ ጋር ስንቴ ይመክራል? ከጥጦስና ዳክርስ ጋር መክሮ ከማን ጋር ውሏል?

ጥያቄው እራስን ለማየት ይረዳ ይሆናል። ለህዝብ የሚጠቅም ጥበብ እንዲገለፅ ያደርግ ይሆናል። መስከንን ያመላክት ይሆናል። እውነት መገለጫዋ የት እንደሆነ ይመሰክር፣ የናገር፣ ያስተምር ሊሆን ይችላል።

ከፈጣሪ የምትሸሽ አዕምሮ ባካኘ ናት። ከሰው የምትሸሸግ አዕምሮ ደግሞ በሻማ፣ በብርሃን፣ በጨረቃ፣ በከዋክብት ብርሃን፣ በኤሌክትሪክ ትጋለጣለች። በዚሀ መጋለጥ ውስጥ ማን ይወቀስ ይሁን? አዕምሮ፣ የአዕምሮ ባለቤት፣ የአዕምሮ ተከራይ፣ የአዕምሮ ደላላ?

ፈጣሪ በፈጠረው ለምለም መሬት ላይ ጥላቻ፣ ክፈት፣ ስድብ፣ መርገምት እና አስከፊ የትውልድ ሳንካ የተከለ እና ሌሎችም የፍርዱ መዶሻና ደወል ድምፅ ተቀባይ ሳይሆኑ አይቀሩም።

ፍርድ ግን ከአዕምሮ ፈጣሪው ነው!

በጉንዳን የሚታከመው ቁራ ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦቁራ ሲታመም ጉዳን በሚገኝበት አካባቢ ሄዶ ይቀመጣል። ከዚያም ክንፉን በመዘርጋት ጉንዳኖቹ ሰውነቱን እንዲወሩትና እንዲነክሱት ይፈቅዳል። ቁራዎች ...
27/04/2025

በጉንዳን የሚታከመው ቁራ

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

ቁራ ሲታመም ጉዳን በሚገኝበት አካባቢ ሄዶ ይቀመጣል። ከዚያም ክንፉን በመዘርጋት ጉንዳኖቹ ሰውነቱን እንዲወሩትና እንዲነክሱት ይፈቅዳል።

ቁራዎች ይህንን የሚያደርጉበት አስገራሚ ምክንያት አላቸው ። ጉንዳኖች ሰውነታቸው "ፎርሚክ አሲድ" የተባለ የተፈጥሮ ፀረ-ተባይ ንጥረ ነገር ይረጫል ። ይህ አሲድ ቁራው ፈንገሶችን፣ ባክቴሪያዎችን እና ጥገኛ ተህዋሲያንን ከሰውነቱ ላይ እንዲያስወግድ ይረዳዋል ። ይህም ህክምና ሳያስፈልገው እንዲያገግም ያስችለዋል።

ይህ ባህሪ "አንቲንግ" ተብሎ የሚጠራ ሲሆን በተለያዩ የአእዋፍ ዝርያዎች ላይ ተስተውሏል። ይህ የእንሰሳት ራስን የማከም ጥበብ ግሩም ምሳሌ ነው።

ዘወትር ማዕዷን ዘርግታ ለምትመግበን ስንዱ እመቤት አብረን እንስራ!የፍቅርና የበረከት ጥሪ  #ከወናጎ  #ደብረጽዮን  #ቅድስት  #ማርያም ቤተክርስቲያን ምዕመናንና አገልጋይ ካህናት አቅርበውላ...
20/03/2025

ዘወትር ማዕዷን ዘርግታ ለምትመግበን ስንዱ እመቤት አብረን እንስራ!

የፍቅርና የበረከት ጥሪ #ከወናጎ #ደብረጽዮን #ቅድስት #ማርያም ቤተክርስቲያን ምዕመናንና አገልጋይ ካህናት አቅርበውላችኋል።

#ነቢዩ አሞጽ ያስተላለፈውን ጥሪ እስቲ በጥሞና እናንብብ።

" በዚያ ቀን የወደቀችውን የዳዊትን ድንኳን አነሣለሁ፥ የተናደውንም ቅጥርዋን እጠግናለሁ፤ የፈረሰውንም አድሳለሁ፥ እንደ ቀደመውም ዘመን እሠራታለሁ፤ "
ትንቢተ አሞጽ ፱:፲፩

#ወናጎ ደብረጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተክህነት ሥር የሚገኝ ሲሆን ጥንታዊና ታሪካዊ ስዕለት ሰሚ ቤተክርስቲያን ነች።

#ቤተክርስቲያኗ አሁን ጣራው በማፍሰሱ ምክንያት እድሳት ላይ በመሆኗ ነቢዩ አሞጽ እንዳለው የፈረሰውን አድሳለሁ እንደ ቀደመውም ዘመን እሠራታለሁ ስለሚል ቃሉ በሀገር ውስጥ ያላችሁ የእመቤታችን ወዳጆች ከአዲስአበባ ፣ሀዋሳ ፣አዳማ፣ ቢሾፍቱ.... በመላው ሀገሪቱ የምትኖሩ በሙሉ #በውጭ ሀገር በዓርብ ሀገራት በዱባይ ፣ በሳውዲ፣በኩዌት ፣በአሜሪካ ፣በአውሮፓ፣ በአውስትራሊያ ...እስከ ምድር ጫፍ በተለያዩ ሁኔታ ከሀገራችሁ ወጥታችሁ የምትገኙ ሁሉ ዛሬ ጽዮን እናታችን ቅ/ማርያም ልጆቼ ድረሱልኝ በማለት ጥሪዋን እያስተላለፈች ነው።

#ገንዘባችሁን በመለገስ በአጭር ጊዜ ታድሶ ወደ ቀደመ መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠት ይቻል ዘንድ ልግስናችሁ የግድ አስፈልጓል።ለምን ቢባል ታቦታቱ ወጥተው የሚገኙት በቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ተዳብለው ነውና።

#የገንዘብ ልገሳችሁን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለወናጎ ደብረጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በማለት ያስገባችሁበት ስሊፕ ስክሪን ሹት በማድረግ በኢንቦክስ ብትሉኩልን ሌላው እንዲለግስ ያነሳሳል።

#➽1000167792905 የባንክ አካውንት ቁጥር

#የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ የእግዚአብሔር ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ ህብረት፤

#የቅድስተ ቅዱሳን የድንግል ማርያም አማላጅነት የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ አማላጅነት አይለየን አሜን

የታገዱ የምግብ ጨው ምርቶችን ከገበያ ለማስወጣት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸአዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የታገዱ የምግብ ጨው ምርቶችን ከገበያ ለማስወጣ...
18/03/2025

የታገዱ የምግብ ጨው ምርቶችን ከገበያ ለማስወጣት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የታገዱ የምግብ ጨው ምርቶችን ከገበያ ለማስወጣት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

ባለስልጣኑ ባደረገው የገበያ ቅኝት በሕገ-ወጥ መንገድ በገበያ ላይ የነበሩ 49 የገበታ ጨው ምርቶችን ሕብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ማገዱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

የታገዱት የገበታ ጨው ምርቶች ደህንነታቸውና ጥራታቸው ሳይረጋገጥ እንዲሁም የሀገሪቱን አስገዳጅ ብሔራዊ ደረጃ ሳያሟሉ ለገበያ የቀረቡ መሆናቸው ነው የተገለጸው፡፡

በባለስልጣኑ የእንስሳት ተዋጽኦና አልሚ ምግብ ዴስክ ሃላፊ መሃመድ ሁሴን ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የታገዱ የምግብ ጨው ምርቶችን ከገበያ ለማስወጣት እየተሰራ ነው፡፡

ምርቶቹን ከገበያ ለመሰብሰብ እንዲቻል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴርን ጨምሮ ለሚመለከታቸው ተቋማት በደብዳቤ የማሳወቅ ሥራ መከናወኑን አንስተዋል፡፡

በምርት ደረጃ፣ በናሙና እና በገበያ ቅኝት የምርቶችን ደረጃ በየጊዜው ክትትል እንደሚደረግ ገልጸው÷ከገበያ እንዲወጡ ሲደረጉ የንግድ ስም (ብራንድ) እየቀያየሩ ወደ ገበያ የሚመለሱበት ሁኔታ በመኖሩ ጥብቅ ክትትል እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

ባለስልጣኑ በየጊዜው ከሚያካሂደው የገበያ ቅኝት በተጨማሪ ከሕብረተሰቡ በሚደርሰው ጥቆማ መሰረት የጥራት ማረጋገጫ ሳያገኙ በድብቅ ጨው የሚያመርቱ አካላት ላይ ሕጋዊ ርምጃ እየወሰደ መሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡

FBC

ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በጌዴኦ ዞን ተመረቁኢትዮጵያ||  #ጌዴኦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጌዴኦ ዞን፣ ዲላ እና ገደብ ከተሞች ከግማሽ ቢ...
04/03/2025

ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በጌዴኦ ዞን ተመረቁ

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጌዴኦ ዞን፣ ዲላ እና ገደብ ከተሞች ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና ሌሎች የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት ስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶቹ ከ525 ሚሊዮን ብር በላይ በላይ ወጪ የተደረገባቸው ሲሆን፤ ከ233 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ዳራሮን በዋሽንግተን ዲሲ•••ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦ ዳያስፖራዎቻችን የጌዴኦ ማህበረሰብ ዘመን መለወጫ የዳራሮ በዓል በዲሲ ይከበራል።የጌዴኦ ዞን ተወላጆች፣ ኢትዮጵያዊያን ዳራሮን ለማክበር ቅድመ...
29/12/2024

ዳራሮን በዋሽንግተን ዲሲ•••

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

ዳያስፖራዎቻችን የጌዴኦ ማህበረሰብ ዘመን መለወጫ የዳራሮ በዓል በዲሲ ይከበራል።

የጌዴኦ ዞን ተወላጆች፣ ኢትዮጵያዊያን ዳራሮን ለማክበር ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ዞኑን የማስተዋወቅ ስራ ለመስራት ማቀዳቸውም ተሰምቷል።

የጌዴኦ ማህበረሰብ ፈጣሪውን ሲያመሰግን ምስጋና ድንበር የለውምና በአካል ባንገናኝም ባለንበት እንጋራለን በማለት መነሳሳትን ደጥረዋል ተብሏል።

የባለ ልዩ ጣዕም የጌዴኦ ይርጋ ጨፌ ቡና አምራች የሆነው የሆነው ማህበረሰብ ባህሉ፣ ትውፊቱ፣ ወጉ፣ ልማዱ፣ ታሪኩ እና ቋንቋው እንዲያድግ ለማድረግ ሚና አለው ተብሏል።

ዳያስፖራው አካባቢን ከማስተዋወቅ አልፎ በኢንቨስትመንት እንዲሳተፍ ያደርገዋል የተባለ ሲሆን ሌሎች ዳያስፖራዎች እንዲሳተፉ ዕድል ይሰጣል።

የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ እንደገለፁት ዳያስፖራው ዳራሮን ከማክበር ባለፈ ለዞኑ ልማትና ዕድገት የዳያስፖራው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው በዞኑ የተጀመሩ ልማቶችን ለማጠናከር ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ አስረድተዋል።

በቱሪዝም ሀብት ልማት ቱሪስቶች አካባቢውን እንዲጎበኙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የተናገሩት አቶ ደርቤ ጅኖ የዳራሮ በዓል በውጪ አገራት መከበሩ ባህሉን በማስተዋወቅ ቱሪስቶችን ያነቃቃል ብለዋል።

ወ/ሮ ሠላም ዋቆ ከቲሞቻቸው ጋር በመሆን እንዳስረዱት በዓሉ እንዲከበር በውጪ የሚገኙ ዳያስፖራዎች ኃላፊነት ወስደው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን አስረድተው በዞኑ ለሚካሄደው ልማት የዳራሮ በዓል መከበሩ አዎንታዊ ምላሽ ያመጣል ብለዋል።

አገር ወዳድ ዳያስፖራዎች በዓሉ በድምቀት እንዲከበር ከማህበሩ ጎን በመሆን ማበረታታት ይገባል ተብሏል።

በአፍሪካ ፕላስቲክ ሊያስወግድ የሚችል ምርምር እያከናወኑ መሆናቸውን ተመራማሪዎች ገለጹ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦህዳር 04 2017| -በአፍሪካ ፕላስቲክን የሚመገብ የትል ዝ...
13/11/2024

በአፍሪካ ፕላስቲክ ሊያስወግድ የሚችል ምርምር እያከናወኑ መሆናቸውን ተመራማሪዎች ገለጹ
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

ህዳር 04 2017| -በአፍሪካ ፕላስቲክን የሚመገብ የትል ዝርያ መገኘቱ የተሰማ ሲሆን ተመራማሪዎቹ ዛሬ ባወጡት መግለጫቸው ለፕላስቲክ ብክለት የመፍትሔ ፍንጭ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡

ፕላስቲክን ይመገባል የተባለለት የትል ዝርያ የመጀመርያ መገኛው በአፍሪካ ሲሆን አሁን ግን በየትኛውም የዓለም ክፍል እንደሚገኝ ነው የተገለጸው፡፡

የአሁኑ የተመራማሪዎቹ ግኝት የፕላስቲክ ብክለት በከፍተኛ ደረጃ ላይ የእስያ እና የአፍሪካ አህጉራት ጠቀሜታው የጎላ መሆኑ ተነግሯል፡፡

እንደ ዓለም የጤና ድርጅት ማብራሪያ በዓለም የፕላስቲክ ብክለት አንደኛ የእስያ አሕጉር ሲሆን ሁለተኛ ደግሞ የአፍሪካ አሕጉር ነው፡፡ዘገባው የግሪክ ሪፖርተር ድረ ገጽ ነው፡፡

NBC

እንግዶቻችን እንኳን ደህና መጣችሁ!!ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦለምለሚቷን፣ ሻላይቱ  #ጌዴኦን ለመጎብኘት እና ለማስተዋወቅ ስለመጣችሁ እናመሰግናለን!!
10/11/2024

እንግዶቻችን እንኳን ደህና መጣችሁ!!

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

ለምለሚቷን፣ ሻላይቱ #ጌዴኦን ለመጎብኘት እና ለማስተዋወቅ ስለመጣችሁ እናመሰግናለን!!

ሀሰተኛ  የገንንዘብ ኖቶችን ሲጠቀሙ እና ሲያዘዋውሩ የተገኘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የዲላ ከተማ ፖሊስ አስታወቀኢትዮጵያ||  #ጌዴኦዲላ ጥቅምት 30/2017 ዓ/ም...
09/11/2024

ሀሰተኛ የገንንዘብ ኖቶችን ሲጠቀሙ እና ሲያዘዋውሩ የተገኘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የዲላ ከተማ ፖሊስ አስታወቀ

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

ዲላ ጥቅምት 30/2017 ዓ/ም
20 ሺህ 400 ሀሰተኛ ባለ 2 መቶ የብር ኖት ይዞ ስጠቀምና ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰብ በፖሊስና ህብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር መዋሉን የዲላ ከተማ ፖሊስ አስታወቀ።

ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር የዋለው በዲላ ከተማ ሀሮ ወላቡ በቀሌ ሀርሱ ቀጠና ቀራ አገልግሎት የሚሰጠበት አካባቢ መሆኑ ተገልጿል።

የዲላ ከተማ የወንጀልና የትራፊክ አደጋ ማስተባበሪያ ኃላፊ ረ/ኢንስፔክተር ይጨነቁ ጀቦ ግለሰቡ ሃሰተኛ ገንዘቡን ወደ ማህበረሰቡ በማሰራጨትና በአቋራጭ ለመበልጸግ በማሰብ ከግለሰቦች የእርድ ከብት ገዝቶ ለቀብድ የከፈለው 20 ሽህ ብር ሀሰተኛ ኖት መሆኑን የተጠራጠሩት የአከባቢው ማህበረሰብ ለፖሊስ በሰጠው ጥቆማ ግለሰቡ ቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጿል።

ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ ቦታው ላይ ደርሶ ተጠርጣሪው ሲፈተሽ ተጨማሪ 400 ሀሰተኛ ባለ 2 መቶ የብር ኖት እጅ ከፍንጅ እንደተያዘ ገልጿል።

ግለሰቡ አስፈላጊውን ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ የገለጹት ረ/ኢንስፔክተር ይጨነቁ ሃሰተኛ የገንዘብ ዝውውር በማህበረሰቡ ብሎም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚስከትል በመሆኑ በእንደዚህ አይነት ህገ ወጥ ተግባር ላይ የሚሳተፍ ግለሰቦችን በመከላከልና በመቆጣጠሩ በኩል ህብረተሰቡ እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።

ህብረተሰቡ ግብይት ሲፈፅም ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል ያሉት ኃላፊዉ ሃሰተኛ የብር ኖቶችን የሚጠቀሙ ወንጀለኞች ሲያጋጥመው በፍጥነት ማሳወቅ እንዳለበት ፖሊስ መምሪያው መልእክቱን አስተላልፏል ስል የዘገበው የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ነው ።

አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈኢትዮጵያ||  #ጌዴኦ በቫሌንሺያ በተካሄደው የዓለም የግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ማሸነፉ...
27/10/2024

አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር አሸነፈ

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

በቫሌንሺያ በተካሄደው የዓለም የግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ማሸነፉን የዓለም አትሌቲክስ ዘግቧል።

ዮሚፍ ርቀቱን በ57 ደቂቃ ከ30 ሰከንድ በማጠናቀቅ በኡጋንዳዊው አትሌት ጃኮብ ኪፕሊሞ ተይዞ የቆየውን ክብረ ወሰን በአንድ ሰከንድ አሻሽሏል።

የአዕምሮ ኪራይ…. ኢትዮጵያ||  #ጌዴኦ አዕምሮ በአሳቢነቱ፣ ልብ በአስተውሎቱ፣ ዐይን በዕይታው፣ ጆሮ በአድምጦቱ ተዋህደው ቅንነት እና ለሰው ልጅ መልካም መሆን የማይችሉ ከሆነ ፍርደ ገምድል...
27/10/2024

የአዕምሮ ኪራይ….

ኢትዮጵያ|| #ጌዴኦ

አዕምሮ በአሳቢነቱ፣ ልብ በአስተውሎቱ፣ ዐይን በዕይታው፣ ጆሮ በአድምጦቱ ተዋህደው ቅንነት እና ለሰው ልጅ መልካም መሆን የማይችሉ ከሆነ ፍርደ ገምድልነታቸው ውሎ ሳያድር የክፋት ይሆናል፡፡

አዕምሮን ተከራይተው የወንጀል፣ የክፋ፣ የአሳዳጅነት እና የገዳይነት ውል ተዋውለው ከግለሰብ አልፎ ህዝብ ላይ ተጭነው የጨፍላቂነት ሸክም ተሸክሞ በደል ለመስራ ዕቅድ አውጥቶ፣ አዕምሮአቸውን የተከራያቸውን ሰዎች መድቦ፣ አዕምሮውን አከራይቱ ከእራሱ ዕይታ ውጪ የቡድን እና የግልሰብ የሸፍጥ ሀሳቦችን ተሸክሞ አዕምሮውን ለዲያቢሎስ ያከራያል፡፡

ማንኛውም ሰው የራሱ ዕድል አለው፡፡ የአንድ ሰው ዕድል ግን የሌላው ሊሆን አይችልም፣ ምናልባት የተሰጠውን ዕድል መጠቀም የማይችል በማንኪያ አጉርሱኝ የሚል ደግሞ አይጠፋም፡፡

ዲያቢሎስ በማህበርም ይንቀሳቀስ በግል ዓላመው የሰው ልጆችን ማሳት፣ ዓላማ ማደናቀፍ፣ ማሰናከል እና ከማይደረስበት የሰው ልጆች አበሳ ውስጥ መጣል ነው፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ ጠላቱን እንጂ ወዳጁን ተጠንቅቆት አያውቅም፡፡ ብዙውን ጊዜ ለአባቶቻችን ጆሮ መስጠት ትተን ነው እንጂ እንዲህ ሲሉ ይፀልያሉ “አቤቱ ጌታ ሆይ! ጠላቶቼን እኔ ጠብቃለሁ ወዳጆቼን ግን አንተ ጠብቅልኝ” ታዲያ ይህ ፀሎት ለሚያስተውል ይገባዋል፣ ይገርመዋል ሲረዳው መፀለዩ አይቀሬ ነው፡፡

ይሁዳ ጌታውን በሰላሳ ዲናር እንዲሸጠው ዲያቢሎስ የይሁዳን አዕምሮ ተከራይቶ ነበር፡፡ ወዳጅ መስሎ አቅፎ ደግፎ በእርኩስ ከንፈሩ ስሞት ለካህናት አለቆች አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ ይሁዳ ከተመረጡ ሐዋሪያት መካከል አንዱ ነው፣ ለመልካም እና ለበጎነት፣ ለሰማያዊ አገልግሎት የመረጠው ነበር ግን እሱ የፈጠረውን አምላክ አሳልፎ ሽጦታል፡፡

ሌላኛዋ የአዕምሮ ኪራይዋን ለዲያቢሎስ ያከራየች ደግሞ የትዕግስተኛው፣ የወረደበትን ፈተና ችሎ፣ ፈጣሪውን ዘወትር የሚያመሰግን መከራን መሸከም የቻለው የእዮብ ባለቤት ናት፡፡ የእዩብ ባለቤት ዘወትር የሚታያት የወደሙ ንብረቶች፣ የሞቱባት ልጆቿ እና የእዮብ ቁስል ብቻ ስለነበር እዮብ ጌታውን ሰድቦት እንዲሞት አዕምሮዋን የተከራየው ዲያቢሎስ በውስጧ ሆኖ ይናገርና ያናግራት ነበር፡፡

አሁን ባለንበት በዚህ ስልጣኔ አለበት በሚባልበት ዘመን ዲያቢሎስ የብዙ ሰዎችን አዕምሮ ተከራይቶ ያሳማል፣ ያሰድባል፣ ለግድያ በማህበር ያደራጃል፣ አስቀምጦ ያስመክራል፣ ለመመገብ ባርከው የጀመሩትን ምግብ እያስወራ ወደ ሰው ልጆች ስጋ መብላት ውስጥ ያስገባቸዋል፡፡

ክፋት፣ አሳዳጅነት፣ ደም አፍሳሽነት፣ ምቀኝነት፣ አድመኝነት፣ ሐሜተኝነት እና ሐሰት ዲያቢሎስ በሰው ልጆች አዕምሮ ውስጥ የሚገኙ ክፍሎችን የሚከራይላቸው የጥፋት ሴራዎች ናቸው፡፡

ማንኛውም ነገር ተሰጥቶህ ይሆናል፡፡ ከተሰጠህ በኋላ አጠቃቀም እና ውጤታማነት የራስ ተጠያቂነት ይሆናል እንጂ የተሰጠኝም ተወሰደብኝ፣ የጠበኩት አልተሰጠኝም ብሎ በዲያቢሎስ የአዕምሮ ኪራይ ስሌት ግን ማግኘት አይቻልም፡፡ በጩኸት የሚገኝ ምንም ዓይነት ነገር አይኖርም፡፡ ከበስተኋላ ያለውን የግልም ይሁን የቡድን ታሪኮችን መርምሮ ወደ ዋናው ሐዲድ ውስጥ መግባት አማራጭ የሌለው ምርጫ ነው፡፡

በአገራችን ውስጥ የትኛውንም አካባቢ በአትኩሮት ማየት እና ማስተዋል ከተቻለ የሰው ልጆችን፣ የህዝብን ፍላጎቶች ዲያቢሎስ የሰውን አዕምሮ ተከራይቶ ሙሉ ልብሱን በከረባት ሽክ! አድርጎ በማህበር እየተንቀሳቀሰ ያለ ይመስላል፡፡
ከብዙ ዓመታት የክፉ ስራዎች መካከል ከትቤ ካኖርኩት ውስጥ ይህንን ጻፍኩት
መስከረም 12/2010 ዓ.ም
ከትዝብት ማህደሬ

የዲላ መካከለኛ አግሮ ኢንዲስትሪ ፓርክ ለመጀመሪያ ጊዜ 22 ሺህ ሊትር የአቮካዶ ዘይት ለውጭ ገበያ አቀረበኢትዮጵያ||  #ዲላጥቅምት 16፣ 2017 (ዲዩ ኤፍኤም 89.0) የዲላ መካከለኛ አግ...
26/10/2024

የዲላ መካከለኛ አግሮ ኢንዲስትሪ ፓርክ ለመጀመሪያ ጊዜ 22 ሺህ ሊትር የአቮካዶ ዘይት ለውጭ ገበያ አቀረበ

ኢትዮጵያ|| #ዲላ

ጥቅምት 16፣ 2017 (ዲዩ ኤፍኤም 89.0) የዲላ መካከለኛ አግሮ ኢንዲስትሪ ፓርክ ለመጀመሪያ ጊዜ ያመረተውን 22 ሺህ ሊትር የአቮካዶ ዘይት ምርት ለውጭ ገበያ ማቅረቡን ገለጸ።

በኢንዱስትሪ ፓርኩ የሲይዝ አግሮ ኢንዱስትሪ ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ጌቱ ፥ በአንድ ፈረቃ የተመረተ 22 ሺህ ሊትር የአቮካዶ ዘይት ለመጀመሪያ ጊዜ ለውጭ ገበያ መቅረቡን ገልጸዋል፡፡

በቀጣይ የሚመረትበትን ፈረቃ በማሳደግ በዓመት ለአራት ጊዜ የአቮካዶ ዘይት ለአውሮፓ እና ለአሜሪካ ገበያዎች ለማቅረብ የሚያስችል ትስስር እየተፈጠረ መሆኑንም ተናግረዋል።

ከአቮካዶ ዘይት ምርት በተጨማሪ ቡናን እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ ለማቅረብና ከአቮካዶ ተረፈ ምርት የእንስሳት መኖ ለማምረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ምርቱ ለውጭ ገበያ መቅረቡ በቀጣይ የፓርኩን ምርታማነትና ተወዳዳሪነት ከማሳደግ ባለፈ በሀገሪቱ ላሉ መሰል ፓርኮች መነሳሳት እንደሚፈጥርም ተገልጿል፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ በበኩላቸው ፥ ፓርኩ ቴክኖሎጂ በማሸጋገርና በሥራ ዕድል ፈጠራ ካለው አስተዋጾ ባለፈ የአቮካዶ ዘይት ምርት ለውጭ ገበያ ማቅረብ መጀመሩ በእድገትና ሽግግር ምዕራፍ ላይ እንዲሚገኝ አመላካች ነው ብለዋል።

በቀጣይ አቅሙን በማጠናከር በዓመት ከ130 ቶን በላይ የአቮካዶ ዘይት ምርት ለውጭ ገበያ ለማቅረብ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም አመልክተዋል።

ፓርኩ በውስጥ ከፈጠረው የሥራ እድል ባለፈ በግብዓት አቅርቦት ትስስር ከ3 ሺህ በላይ የአካባቢውን አርሶ አደሮች ተጠቃሚ ማድረጉን የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡

Address

Gedeo
Dila
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Deribe Jino posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share