26/01/2026
የጌዴኦ ብሔር ዘመን መለወጫ ''ዳራሮ''በዓል በውጭ ሀገራት በድምቀት ለማክበር አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ
Ethiopia||
16/2018ዓ.ምየበዓሉ አከባበርና ዝግጅት በሚመለከት የጌዴኦ ዲያስፖራ ማህበር ፕሬዚዳንት ሄኖክ ታደሰ (ዶ/ር) ለተለያዩ ሚዲያዎች መግለጫ ሰጥተዋል።
እንደ ሄኖክ ታደሰ (ዶ/ር) ገለጻ የጌዴኦ ዞን ዳያስፖራ ማህበር በውጪ አገራት ነዋሪ የሆኑ የጌዴኦ ዞን ተወላጆችና ወዳጆችን አቅፎ የምንቀሳቀስ በኢትዮጵያና በአሜሪካ የተመዘገበ ሕጋዊ ተቋም እንደሆነ አንስተዋል።
ማሕበሩ የዞኑን ተወላጆች ያለ ብሔር፣ ሐይማኖትና የፖለቲካ አቋም ልዩነት አቅፎ የምንቀሳቀስ መሆኑንና የዞኑን ባሕልና ቋንቋን ጨምሮ የዞኑ ማሕበራዊና እኮኖሚያዊ ልማት ላይ እንደሚሰራ ነው የተናገሩት።
የጌዴኦ ዞን አስተዳደርና በማሕበሩ የጋራ እቅድ መሰረት የጌዴኦ ብሔር ዘመን መለወጫ ''ዳራሮ'' በዓል በተለያዩ በውጭ ሀገራት በJanuary 31/2026 እንደሚከበር ነው የገለፁት።
በአዲስና በለውጥ አስተሳሰብ በአንድነት እና በጋራ እጅ ለእጅ በመያያዝ የተጀመረው ልማት፣ባህሉን ወደላቀ ደረጀ ለማሸጋገር በጋራ ቃል የሚገባበት ጊዜ እንደምሆን አንስተዋል።
በዓሉ በJanuary 31/2026 በሰሜን አሜሪካ (ዋሽንግተን ዲሲ) በኤምባሲው አደራሽ፣በአውሮፓ(በጀርመን ፍራንክፈርት)- በደቡብ ኢትዮጵያ ልማት ማህበር መሰብሰቢያ አደራሽ እንደሚከበር ጠቁመዋል።
በመካከለኛው ምስራቅ (በሳውዲ አረቢያ) በጂዳ የኢትዮጵያ ቆጽላ ጽ/ቤት በተመሳሳይ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር ነዎ
ሄኖክ ታደሰ (ዶ/ር) ያረጋገጡት።
በበዓሉ የዳራሮን በዓል እሴቶችና መርሆዎች ከክርሰትና እምነት አንፃር በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ የዶክቶራል ተማሪ በሆኑት የዳራሮ ተመራማሪ የውይይት ሀሳብ ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግም ይጠበቃል።
በሌላ ዜና በጌዴኦ ዞንና የዲላ ከተማ የኢንቨስትመንት እድሎችና አማራጮች ላይ በጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪና በዲላ ከተማ የመወያያ ነጥቦች ቀርበው ከመላው ዳያስፖራ አባላት ጋር ውይይት ይደረጋልም ብለዋል።
የዳራሮ በዓል በውጭ ሀገራት የጌዴኦ ተወላጆች ወዳጆች እና ተጋባዥ እንግዶች በተሳተፉበት በተለያዩ በዓላዊ ኩነቶች በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር ይጠበቃል።