Gedeo TV

Gedeo TV ይህ የጌዴኦ ቴሌቪዥን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ፣ ሼርና ኮሜንት በማድረግ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን በየዕለቱ ይከታተሉ! t.me/gedeotvofficial

የተፈጥሮ ፀጋ ጌዴኦ _ራጴ ወረዳ
20/10/2025

የተፈጥሮ ፀጋ ጌዴኦ _ራጴ ወረዳ

ምክክርና ውይይት  የችገሮች መፍቻ ቀዳሚ አማራጭ እና ባህል እንዲሆኑ ሊሰራ ይገባል ተባለዲላ:- ጥቅምት 9/2018(ጌዴኦ ቴለቪዥን)በሀገራችን ላለፉት በርካታ ዓመታት በተፈጠሩ ግጭቶች ብዙ ው...
19/10/2025

ምክክርና ውይይት የችገሮች መፍቻ ቀዳሚ አማራጭ እና ባህል እንዲሆኑ ሊሰራ ይገባል ተባለ

ዲላ:- ጥቅምት 9/2018(ጌዴኦ ቴለቪዥን)

በሀገራችን ላለፉት በርካታ ዓመታት በተፈጠሩ ግጭቶች ብዙ ውድመቶች በመድረሳቸው ለብዙ ጉዳት ተዳርገናል ብለዋል በወላይታ ሶዶ ከተማ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያዘጋጀው የውይይት መድረክ ተሳታፍዎች።

በውይይቱም ከባለፈው በመማርና ለቀጣዩ ትውልድ በማሰብ የትኛውንም የሀሳብ ልዩነቶች በምክክር እና ውይይት ብቻ ለመፍታት መስራት እንደምገባም አስገንዝበዋል።

የሴቶች የወጣቶችና አካል ጉዳተኞች ሚና ለሀገራዊ ምክክር የተመለከተ እና በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም ዞኖች የተወጣጡ ተሳታፊዎች በተገኙበት በወላይታ ሶዶ ከተማ ለሁለት ቀናት ስካሄድ የነበረው ውይይት ምክክር ለሀገር ዕድገት ያለውን ሚና እንዲሁም የወጣቶች ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ሚና ጉልህ መሆኑን ከመግባባት ላይ በመድረስ ተጠናቋል።

ኢትዮጵያ አሰብና ቀይ ባሕርን ያጣችበት ሂደት በአሻጥር የተቀነበበ እንጅ  ሕጋዊ መሠረት የለውም ዲላ :-ጥቅምት 9/2018(ጌዴኦ ቴሌቪዥን )፡- ኢትዮጵያ አሰብንና ቀይ ባሕርን ያጣችበት መን...
19/10/2025

ኢትዮጵያ አሰብና ቀይ ባሕርን ያጣችበት ሂደት በአሻጥር የተቀነበበ እንጅ ሕጋዊ መሠረት የለውም

ዲላ :-ጥቅምት 9/2018(ጌዴኦ ቴሌቪዥን )፡-

ኢትዮጵያ አሰብንና ቀይ ባሕርን ያጣችበት መንገድ በዓለም አቀፍ ሕግ ተቀባይነት እንደሌለው የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተመራማሪ ገለጹ።

የቀይ ባሕር ባለቤት የነበረችው ኢትዮጵያ በመስመሩ ተጽዕኖ ፈጣሪ እንደነበረችና በወቅቱም ከዓለም ትላልቅ ስልጣኔዎች እና ንግድ ጋር ከፍተኛ ትስስር እንደነበራት በአምቦ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህርና ተመራማሪ ሴነሳ ደምሴ ገልጸዋል።

ኤርትራ ተገንጥላ ሀገር ስትሆን በተወሳሰበ ተንኮልና አሻጥር ኢትዮጵያ ደካማ እንድትሆን በሚፈልጉ ኃይሎች ጭምር ጫና ተደርጎባት የባሕር በሯን እንድታጣ መደረጉንም አውስተዋል።

ሆኖም የ30 ዓመታት ታሪክ ከዚያ በፊት ከነበሩት አያሌ ዓመታት ባለቤትነት እንደማይበልጥ ገልጸዋል።

እንዲሁም ከነበረው ትስስር አንጻር ስለ አሰብና ቀይ ባሕር ስናነሳ ከኢትዮጵያ ነጥለን ማንሳት አይቻልም ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ ለቀይ ባሕር ቅርብ መሆኗ እየታወቀ፤ ሌሎች ሀገራት በርካታ ማይሎችን ተጉዘው ቀይ ባሕርን እንዳሻቸው ሲጠቀሙ፣ ጭራሽ እንደከልካይ፣ ፈቃጅ እና ተቆጣጣሪ ሲያደርጋቸው እየታዘብን ነው ብለዋል።

እዚህ አካባቢ ያሉ ባለድርሻ አካላት ነን ባዮች ከሩቅ ሀገር መጥተው እንደፈለጉ የሚሆኑትን ሳይጠይቁ ኢትዮጵያ ልጠቀም ስትል ግን እንዳይሳካ ለማድረግ ምን ያህል አሻጥርና ተንኮል እንደሚተበትቡ መታዘባቸውንም አንስተዋል።

በአጠቃላይ ኢትዮጵያ አሰብን እና ቀይ ባሕርን ያጣችበት መንገድ በዓለም አቀፍ ሕግ ተቀባይነት የሌለው መሆኑንም አሥረድተዋል።

ለዚህም በምክንያትነት ከሚነሱት መካከል፤በወቅቱ የነበረው የሽግግር መንግሥት መሆኑ ነው ያሉት ተመራማሪው፤ ሙሉ በሙሉ በሕዝብ ይሁንታ መንግሥትነትን ያላገኘ አካል ይህን የማድረግ ሥልጣንም ሆነ ኃላፊነት የለውም ብለዋል።

ወደቡን አሳልፎ የሰጠው የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ አለመሆኑ ደግሞ በዓለም አቀፍ ሕግና ደንቦች መነጽር ሲታይ ወደቡን ማጣቷ ትክክል እንዳይሆን ያደርገዋል ነው ያሉት።

ስለዚህ መንግሥት አሁን ኢትዮጵያ ወደብ እንደሚገባት መጠየቁ ትክክለኛ ነው፤እንዲያውም ከለውጡ በፊት በነበሩት መንግሥታት መነሳት እና መመለስ የነበረበት ነው ሲሉ አመላክተዋል።

#ኢዜአ

18/10/2025

በቅርብ ቀን

ለውጤታማ ሀገራዊ ምክክር የሴቶች ፣የወጣቶችና አካል ጉዳተኞች ሚናና አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸዲላ፦ ጥቅምት 08/2018ዓ.ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን) የሴቶች ወጣቶችና አካል ጉዳተኞችን ሚና ላ...
18/10/2025

ለውጤታማ ሀገራዊ ምክክር የሴቶች ፣የወጣቶችና አካል ጉዳተኞች ሚናና አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

ዲላ፦ ጥቅምት 08/2018ዓ.ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

የሴቶች ወጣቶችና አካል ጉዳተኞችን ሚና ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት እየተካሄደ ነው።

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ብሌን ገ/መድህን እንዳሉት የምክክር ኮሚሽኑ ባለፉት ግዜያት በሁሉም የሀገርቱ አካባቢዎች ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍሎችን ያሳተፈ እና ፍትሃዊ የሆነ ስሰራ መቆዬቱን ገልፀዋል።

በሀገርቱ ያለውን ሁለንተናው ብዝሃነት ያመከለ ውይይትን በባለቤትነት በመደገፍና በመሳተፍ ውጤታማ የሆነ ምክክር በማድረግ ዘላቂ መፍትሔ ለሀገራችን እውን ማድረግ እንደምገባ አንስተዋል።

ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ከክልሉ ሁሉም ዜኖች ከተወጣጡ ባለድርሻ አከላት ጋር በወላይታ ሶዶ ከተማ የሴቶች የወጣቶችና የአካል ጉዳተኞች አስተዋጽኦ ለሀገራዊ ምክክር የተሰኘ ውይይት በማካሄድ ላይ ይገኛል።

ዲላ፣ቡሌና ሐሮ ዋጩ የአስፓልት መንገድ ግንባታን በተመለከተ በጌዴኦ ዞን መንገዱ አቋርጦ በሚያልፍበት አካባቢ  ያሉ ስራዎች በአብይ ኮሚቴ   ተገመገመ ዲላ፦ ጥቅምት 07/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ...
17/10/2025

ዲላ፣ቡሌና ሐሮ ዋጩ የአስፓልት መንገድ ግንባታን በተመለከተ በጌዴኦ ዞን መንገዱ አቋርጦ በሚያልፍበት አካባቢ ያሉ ስራዎች በአብይ ኮሚቴ ተገመገመ

ዲላ፦ ጥቅምት 07/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

ዲላ፣ቡሌና ሐሮ ዋጩ የአስፓልት መንገድ ግንባታን በተመለከተ በጌዴኦ ዞን መንገዱ አቋርጦ በሚያልፍበት አካባቢ ያሉ ስራዎች በአብይ ኮሚቴ ተገምግመዋል፡፡

ለረጅም ጊዜ የመልካም አሰተዳደር ችግረ ሆኖ የቆየው ዲላ፣ ቡሌና ሀሮ ዋጩ መንገድ አሰፓልት እንዲሆን ተወሰነው ግንባታ መጀመሩ ይታወቃል።

መንገዱ ዲላ ከተማን ጨምሮ ዲላ ዙሪያ ፣ቡሌ ወረዳና ከተማ አሰተዳደር አርቋጦ የሚያልፍ ሲሆን ፕሮጀክቱ አሁን ያለበትን ደረጃ በሚመልከት አብይ ኮሚቴው ገምግሟል፡፡

የጌዴኦ ዞን ዋና አሰተዳደር ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) የኮሚቴው ሰብሳብ ለፕሮጀክቱ ትግበራ አሰፈላጊ የሆኑ ቀሪ ሰራዎች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ አሳስበዋል ።

አብይ ኮሚቴው የተለያዩ ባለሙያዎችን ያቀፈ ሲሆን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪን ጨምሮ የዞኑ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያና የተጠቀሱ ወረዳዎች አሰተባባሪ አካላት ተሳትፈዋል።

በይልማ አበበ

‎በገጠር መሬት መጠቀሚያ ግብር አፈፃፀም እና በቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ ‎‎ዲላ፦ ጥቅምንት  7/2018 ዓ.ም (ጌዴኦ ቴሌቭዥን)‎‎የይርጋጨፌ ወረዳ ገቢዎች ጽ...
17/10/2025

‎በገጠር መሬት መጠቀሚያ ግብር አፈፃፀም እና በቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ

‎ዲላ፦ ጥቅምንት 7/2018 ዓ.ም (ጌዴኦ ቴሌቭዥን)

‎የይርጋጨፌ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት የ2017 ዓ.ም የገጠር መሬት መጠቀምያ ግብር አፈፃፀም ግምገማ እና የ2018 ዓ.ም የግብር አሰባሰብ ዙርያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል ።

‎በንቅናቄ መድረክ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የይርጋጨፌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡነ በንግግራቸው የገጠር መሬት መጠቀሚያ ግብር ከማህበረሰቡ በአግባቡ በመሰብሰብ ከህብረተሰቡ የሚነሳው የልማት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል ተግባር በመሆኑ የሁሉም ባለድርሻዎች ጥረት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል ።

‎በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከዕቅድ በላይ መሰብሰቡን ገልጸው ከዞኑ አንደኛ ደረጃ በመያዝ ወረዳው በገቢ አሰባሰብ የዋንጫ ተሸላሚ ለመሆን መቻላቸውን አክለዋል፡፡

‎የይርጋጨፌ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን አስፋ በበኩላቸው ገቢን ማሰባሰብ የልማት ማረጋገጫ ስለሆነ ከገጠር መሬት ገቢውን በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

‎አያይዘውም የ2018 ዓ.ም ገቢ በተሻለ ሁኔታ እንዲሰበሰብ ሁሉም ባለድርሻዎች እንዲወጣ ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ለመድረክ ተሳታፊዎች አብራርተዋል ።

‎በመድረኩ የ2017 ዓ.ም የአፈፃፀም ላይ የነበረውን ክፍተት በመገምገም ለቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች በማስቀመጥ በተደረጉ በገብ ማሰባሰብ ዙርያ ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ ተቋማትንና ባለድርሻ አካላት የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ።

‎ በመድረኩ የይርጋጨፌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡነ ፣ የይርጋጨፌ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ናዝሬት ዘክዮስ ፣የይርጋጨፌ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘሪሁን አስፋ፣ ከሁሉም ቀበሌ የተወጣጡ አካላት እና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዎል ።


‎በደፋር ገመዴ

በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ የገቢ አሰባሰብና የማህበረሰበ አቀፍ  ጤና መድህን የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሄደ‎‎ዲላ፦ጥቅምት 7/2018 ዓ/ (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)‎‎በጌዴኦ ዞ...
17/10/2025

በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ የገቢ አሰባሰብና የማህበረሰበ አቀፍ ጤና መድህን የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሄደ

‎ዲላ፦ጥቅምት 7/2018 ዓ/ (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

‎በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ የገቢ አሰባሰብና የማህበረሰብ ዓለም አቀፍ ጤና መድህን የንቅናቄ መድረክ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል

‎የጤና መድህን የ2017 ዓ/ም የነበረው አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት ከተደረገ ቦኃላ የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን በማረታታት ደካም ያሉ ጉዳዮችንም ለማረም በትኩረት እንደሚሠራ ነው በንቅናቄ መድረኩ የተገለጸው ።

‎የገደብ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ምትኩ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ለማፋጠን ገቢ አሟጠው መሰብሰብ ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም በጋራ ተቀናጅተው እንደሠራ አቅጣጫ መቀመጡን አንስተዋል። ።

‎በጤና መድህን ሥራዎች ላይም አምና የነበረውን ጥሩ አፈፃፀም ለማስቀጠል በላቀ ሁኔታ ለመሥራት ከባለድርሻ አካላት ጋር መግግባት ተፈጥራል ብለዋል።

‎በተለይ በ "ሐ "ግብር ከፋዮች ያሳየነው የላቀ አፈፃፀም በመሬት መጠቀሚያ ግብር ላይ ለመድገም የመክፈያ ጊዜ ገደብ አሰቀምጠው በቁርጠኝ እየሠሩ መሆናቸውን አቶ ሳሙኤል አስረድተዋል ።

‎የገደብ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከበደ ገራ በበኩላቸው የጤና መድህንና የ ገቢ ሀብት አሰባሰቢ ላይ ንቅናቄ መድረክ በማካሄድ መላ ፈጥረን በፍጥነት መፈፀም ይገባናል ብለዋል።

‎አቅሞቻችን ሰብሰብንና ተቀናጅተን የጤና መድህንና ገቢ አሰባሰብ ላይ በትኩረት ይሠራል ያሉት ኃላፊ የ2018 ዓ/ም ዕቅድን ለማሳካት ከወዲሁ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማርቆስ ጠገኖ በበኩላቸው በ2018 ዓ/ም የ1ኛ ሩቢ ዓመት ገቢ የተሻለው አፈፃፀም መኖሩን ጠቁመው፣ የመሬት መጠቀሚያ ግብር ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ ተናግረዋል።

‎የገደብ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ሽፈራው ባለፈው ዓመት በጤና መድህን ዘርፍ ወረዳ ከዞኑ ግንባር ቀደም መሆኑን ተናግረው በ2018 በላቀ ሁኔታ ለመፈጸም ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ተቀናጅተው እየሠሩ መሆናቸውን አስረድተዋል።

‎የንቅናቄ መድረኩ ተሳተፊዎችም የሁሉቱን ገቢ በማሰባሰብ የሚጠበቅባቸው ማህበራዊ ኃላፊነት እንደሚወጡ ተናግረዋል

‎በተስፋዬ ጎበና

17/10/2025

Shiqoxxe yannan

ዕቅዱን መነሻ ያደረጉ ተግባራት በማከናወን የህብረተሰብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ልሰራ እንደሚገባ ተገለፀዲላ፦ ጥቅምት 7/2018 ዓ.ም (ጌዴኦ ቴለቪዥን)የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት የ2017...
17/10/2025

ዕቅዱን መነሻ ያደረጉ ተግባራት በማከናወን የህብረተሰብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ልሰራ እንደሚገባ ተገለፀ

ዲላ፦ ጥቅምት 7/2018 ዓ.ም (ጌዴኦ ቴለቪዥን)

የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት የ2017 ዕቅድ አፈፃፀምና 2018 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ ዙሪያ በዲላ ከተማ መድረክ አካሂደዋል።

የዞኑ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ሮቤ እንዳሉት፦ የዞኑ መንግሥት ከህብረተሰቡ ዘንድ የሚነሱትን የመልካም አስተዳደርና የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ለመፍታትት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል ።

ኃላፊው አክለውም በአከባቢው ያሉትን ፀጋዎችን በአግባቡ በመጠቀም የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል ።

የመንግሥት ተቋማት ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ በትኩረት ልሰራ እንደሚገባ ተገልጿል።

በመድረኩም በ2018 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ ላይ የግብ ስምምነት በመፈራረም በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ መዋቅሮች የማበረታቻ እና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።

በማሙሽ ኢሳያስ

‎የእንዱስትሪ ዞን ልማት ተግባርን በተለየ በመምራት የከተማውን የመልማት አቅም በተሻለ ማሳደግ ይገባል; ዶክተር ቦጋለ ቦሼ‎‎ጥቅምት :- 7/2018 ዓ.ም. (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)‎‎በከተሞች የእ...
17/10/2025

‎የእንዱስትሪ ዞን ልማት ተግባርን በተለየ በመምራት የከተማውን የመልማት አቅም በተሻለ ማሳደግ ይገባል; ዶክተር ቦጋለ ቦሼ

‎ጥቅምት :- 7/2018 ዓ.ም. (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

‎በከተሞች የእንዱስትሪ ዞኖችን ልማት ማስፋፋት አስፈላጊነት አስመልክቶ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ቦጋለ ቦሼ የተመራ ልኡክ ከዲለ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ምክክር አካህዷል።

‎በምክክሩ የተገኙት የቢሮ ሀላፊው እንደተናገሩት በከተሞች የእንዱስትሪ ዞኖችን ልማት በአግባቡ በማልማት የከተማውን ዕድገት ማፋጠን እንደሚገባ ገልጸዋል።

‎በእንዱስትሪ ዞኑ ዋነኛ የመሬት ምድብ በጥናት ለይቶ በመያዝና የመሰረተ ልማት አውታሮች በአግባቡ በመዘርጋት ከየትኛውም የመሬት ፕላን ንክኪ ነጻ ማድረግ እንደሚገባ ተገልጿል።

‎ጤናማ የመሰረተ ልማት ዝርጋታን በማፋጠን በተለይም
‎የመሬት ብክነት በመቀነስና አላስፈላጊ የአከባቢ ብክለት ችግሮች ለመቀነስ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ተብሏል።

‎የዲላ ከተማ ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶክተር) በበኩላቸው የእንዱስትሪ ዞን ልማት ስራውን በአግባቡ ተግባራዊ በማድረግ እውነተኛ አልሚዎች ወደ አከባቢው እንዲፈልሱ በማድረግ ለከተማው ልማት መፍጠን አስተዋጽኦውን ማጉላት ተጠባቂ ተግባር ነው ተብሏል።

‎ለእንድስትሪ ዞኑ ልማት የመሬት አቅርቦትን በተገቢው በማዘጋጀት መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በመስጠት የመሠረተ ልማት አቅርቦት በማዘጋጀትና በመለየት የልማት ተነሺዎችም ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሁኔታ ማመቻቸት እንደሚገባ ተገልጿል።

‎እንዱስትሪ ዞኖችን ለይቶ በማካለል እና ከይገባኛል ነጻ በማድረግ ለልማቱ መጠናከር እንደሚሠራ ከንቲባው ጠቅሰዋል።

‎በፕላን የተመሰረተ የከተማ ኢንዱስትሪ ዞን ልማት በማሳደግ ተወዳዳሪ የሆነ የከተሞች ልማት ስራ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ዶ/ር መስፍን ገልጸዋል።

‎የዲላ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ስራ አስኪያጅ አቶ ማዘንጊያ አያቶ የእንዱስትሪ ዞን ልማትን ለማጠናከር አከባቢውን ከመለየት ባለፈ ከየትኛውም ይገባኛል ጥያቄዎችን ነጻ የማድረግ ተገቢነቱን ገልጸዋል።

‎ተፈጥሮን መሠረት አድርጎ የእንዱስትሪ ዞን ስፊራውን ከመለየት ባለፈ ከንፋስ አቅጣጫ እንዲሁም የህብረተሰቡ ማህበራዊ መስተጋብር ጋር በማይቃረን መልኩ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግሯል።

‎የከተሞችን መዘመን ተከትሎ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት የከተሞችን ልማት ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የእንዱስትሪ ዞን ልማቱ የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ እንደሆነ ተብራርቷል ።

‎ከተማው ካለበት የመሬት ጥበት አኳያ ዘርፉ የሚጠይቀው መሠረታዊ መስፈርት መነሻ በማድረግ ‎ቀጣይ ስራዎችን ደረጃ በደረጃ ወደ ተግባር ለማስገባት አመራሩ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ተገልጿል።

‎በምክክሩ የከተማው አስተባባሪ አካላትና የመንግስት የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተውበታል።‎

ዘገባው የዲላ ከተማ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

የጌዴኦ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች  የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ‎‎ዲላ፦ ጥቅምት 7/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን )‎‎የጌዴኦ ዞን ሠራተኛና...
17/10/2025

የጌዴኦ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

‎ዲላ፦ ጥቅምት 7/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን )

‎የጌዴኦ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የክራንች ድጋፍ አደርገዋል።

‎በመርሃ ግብሩ ንግግር ያደረጉት የገደብ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታሪኩ ሮበ ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የአርባ ምንጭ ተሃድሶ ማዕከል ላደረገው ድጋፍ አመስግነው ድጋፉ አካል ጉዳተኝነት ሳይበገራችሁ ሥራ እንዲሠሩ እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል።

‎ በማህበራዊ ችግር ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተደረገ ያለውን ድጋፍ ማዕከሉ አጠናክሮ እንዲቀጥል ከንቲባው አሳስበዋል ።

‎የገደብ ወረዳ አሰተዳደሪ አቶ ሳሙኤል ምትኩ በበኩላቸው ተጋላጭ ለሆኑ የማህበር ክፍሎች በጀት መድቦ የተለያዩ ድጋፎችን እያደረጉ መሆናቸውን አስረድተዋል።

‎በቀጣይም ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎች የሚደረጉ ድጋፎች በትኩረት እነደሚሠራም አሰተዳዳሪው‎ አክለዋል

‎በዞኑ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ማህበር ክፍሎች ከአርባ ምንጭ ተሃድሶ ማዕከል የተገኘውን የክራንች ድጋፍ በገደብ ወረዳና ከተማ አስተዳደር ለሚገኙ ተጋላጭ ወገኖች ማድረጋቸውን የጌዴኦ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ፍሬነሽ ሮባ ገልጸዋል ።

‎አካል ጉዳት ማለት ሥራ አለመቻል መሆኑን የገለጹት ኃላፊዋ አካል ጉዳተኛ ሆነው እየሠሩ ለተለያዩ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠሩ አካል ጉዳተኞች እንዳሉም አንስተዋል።

‎በቀጣይም በደረሰባቸው አካል ጉዳት እንቅስቃሴ ማድረግ ለማይችሉ የህብረተሰብ ክፍሎችም ማዕከሉ ልከት ወሰደው በቀጠሮ ውልቸር ሰርተው እንደሚሰጣቸው ነው ወ/ሮ ፍሬነሽ የተናገሩት።

‎በተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት አካል ጉዳት እንደሚከሰት በመግለጽ የተለያዩ ችግር ያለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን ማህበረሰቡ እንዲያስመዝቡ መልዕክት አሰተላልፈዋል።

‎ ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ያነጋገርናቸው የማህበረሰብ ክልሎችም ለተደረገላቸው ድጋፍ አመስግነው መሰል ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

‎በተሰፋዬ ጎበና




Address

Gedeo
Dila
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gedeo TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share