Gedeo TV

Gedeo TV ይህ የጌዴኦ ቴሌቪዥን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ፣ ሼርና ኮሜንት በማድረግ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን በየዕለቱ ይከታተሉ! t.me/gedeotvofficial

እንደ ሀገር በትምህርት ዘርፍ የገጠመውን ስብራት ለመጠገን በሚደረገው ርብርብ የግብረሰናይ ድርጅት ሚና ከፍተኛ ነው ፦ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ (ዲላ ሰኔ 27/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) በሀገር ደረጃ...
04/07/2025

እንደ ሀገር በትምህርት ዘርፍ የገጠመውን ስብራት ለመጠገን በሚደረገው ርብርብ የግብረሰናይ ድርጅት ሚና ከፍተኛ ነው ፦ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ

(ዲላ ሰኔ 27/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) በሀገር ደረጃ በትምህርት ዘርፍ የገጠመውን ስብራት ለመጠገን በሚደረገው ርብርብ የግብረሰናይ ድርጅት ሚና ከፍተኛ ነው ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ ገልጸዋል ።

ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስቴር እና ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተወጣጣ ልኡክ በጌዴኦ ዞን እየተተገበረ የሚገኘውን "እማጅን ዋን ደይ" ኮስታ ፋውንደሽን ታርል ፕሮግራምን ጉብኝት በማድረግ የእስካሁኑ አፈፃፀም ገምግሟል ።

"እማጅን ዋን ደይ" የተሰኘው ግብረሰናይ ድርጅት ከኮስታ ፋውንዴሽን ታር ፕሮግራም ጋር በመሆን በጌዴኦ ዞን በሶስት ወረዳዎች ተማሪዎች የንባብና የማስላት ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ ፕሮጀክት ነው ።

በወቅቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳ እንደገለጹት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሀገራችን ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፍ የገጠመው ችግር ስር እንዳይሰድ መንግስት ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል ።

መንግስት እያከናወነ ካለው ስራዎች ጎን ለጎን ከባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር በመዘርጋት ቀጣይነት ያለው ውጤት እንዲመዘገብ በተለይም ከአጋር ድርጅቶች ጋር በቅርበት እየተሰራ ስለመሆኑ አብራርተዋል ።

ለአብነትም እንደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብቻ 39 አጋር ድርጅቶች የትምህርት ዘርፉን በማገዝ ላይ እንደሚገኝ ወ/ሮ ፀሐይ ጠቁመው ለዚህም በክልሉ መንግስት እና በተማሪዎች ስም አመስግነዋል ።

በዘርፉ አሁን ላይ እየመጣ ያለውን መነቃቃት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን በመሆን የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል ።

በትምህርት ሚንስቴር መሪ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ሙሉቀን ንጋቱ(ዶ/ር) በበኩላቸው በዞኑ በግብረሰናይ ድርጅት እየተተገበረ የሚገኘው ተግባር ውጤታማ እንደሆነ በመግለጽ በቀጣይ ወደ ሌሎች ሀገሪቱ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል ።

እንደ ሀገር መንግስት የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል ያሉት ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ሁሉም የሚጠበቅበትን በመወጣት ሀገሪቷን የተሻለ ደረጃ ላይ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል ።

የእማጅን ዋን ደይ (I1d) ዳይሬክተር አቶ ኡመር ሊሙ በወቅቱ እንዳነሱት ከሌሎች አጋር ድርጅት ጋር በመሆን የተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል እና የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ያለው ፕሮግራም መሆኑን አብራርተዋል ።

በፕሮግራሙ እየተተገበረ የሚገኘው ስራዎችን ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስትር እና ከክልል ትምህርት ቢሮ መጎበኘቱ ለቀጣይ ስራዎች የሚያበረታታ እና ክፍተቶችን ለማረም የሚያስችል ነው ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የእማጅን ዋን ደይ ዳይሬክተር አቶ አማኑኤል ኩሼታ ተናግረዋል ።

የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍለ በበኩላቸው በዞኑ የትምህርት ስብራትን ለመጠገን እና ጠንካራ የትምህርት ስርዓትን ለመዘርጋት ስር ነቀል ተግባራት እየተከናወነ እንደሚገኝ በመግለጽ ይህም በግብረሰናይ ድርጅት እየተተገበረ የሚገኘው ስራ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል ።

@ጌዴኦ ቴሌቪዥን

በዞኑ በ"እማጅን ዋን ደይ" ፕሮግራም እየተከናወነ የሚገኘው የትምህርት ስራ አበርታች ውጤት አስመዝግቧል ተባለ (ዲላ ሰኔ 27/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) በጌዴኦ ዞን በ"እማጅን ዋን ደይ" ፕሮግ...
03/07/2025

በዞኑ በ"እማጅን ዋን ደይ" ፕሮግራም እየተከናወነ የሚገኘው የትምህርት ስራ አበርታች ውጤት አስመዝግቧል ተባለ

(ዲላ ሰኔ 27/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) በጌዴኦ ዞን በ"እማጅን ዋን ደይ" ፕሮግራም እየተከናወነ የሚገኘው የትምህርት ስራ አበርታች ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ተገልጿል ።

በዞኑ በ"እማጅን ዋን ደይ" ኮስታ ፋውንዴሽን ታር ፕሮግራም እየተከናወነ የሚገኘው የትምህርት ስራ ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስቴር እና ከክልሉ ትምህርት ቢሮ በተወጣጣ ልኡክ ጉብኝት ተደርጓል ።

ጉብኝቱ በፕሮግራሙ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ የሚያስችል ነው ተብሏል ።

ኮስታ ፋውንዴሽን በዞኑ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከመንግስት ጎን በመሆን በተለያዩ ወረዳዎች አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አስገንብቶ አስረክቧል ።

ፋውንዴሽኑ በግንባታው ብቻ ሳያበቃ ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ተማሪዎች ከቅድመ መደበኛ ትምህርት ክፍል ጀምሮ መሠረታዊ ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲማሩ በተግባር ትምህርት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ስለመሆኑ ተጠቅሷል ።

ትግበራው ይርጋጨፌ፣ ቡሌ እና ኮቾሬ ወረዳዎች ከሚገኙ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለተወጣጡ ከ3 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የንባብና የማስላት ክህሎት ከወዲሁ እንዲያደብሩ ያለመ ነው ።

እንደ ዞኑ ተግባሩ ጥሩ ደረጃ እንደሚገኝ የተገለጸ ሲሆን በቀጣይ ሌለሎች አከባቢዎችም ተሞክሮ በሚሆን መልኩ ውጤት ማስመዝገቡ ተመልክቷል ።

የእስካሁኑ አፈፃፀም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በነገው ዕለትም ይገምገማል ተብሏል ።

በጉብኝቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳን ጨምሮ የፌዴራል ፣ የክልል እና የዞን ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።

@ጌዴኦ ቴሌቪዥን

ግብርን በታማኝነት መክፈል ለሀገር እና ለከተማው  እድገት ትልቅ ፋይዳ አለዉ ተባለ(ዲላ ሰኔ 27/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) የገደብ ከተማ አስተዳደር ከ "ሐ" ግብር ከፋዮች ጋር የ2017 ግብር...
03/07/2025

ግብርን በታማኝነት መክፈል ለሀገር እና ለከተማው እድገት ትልቅ ፋይዳ አለዉ ተባለ

(ዲላ ሰኔ 27/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) የገደብ ከተማ አስተዳደር ከ "ሐ" ግብር ከፋዮች ጋር የ2017 ግብር ዘመን እና የ2018 ዘመን የንግድ ስራ ፈቃድ እድሳት ማስጀመሪያ በተመለከተ ፍሬያማው ዉይይት አካሄደዋል።

የገደብ ከተማ የንግዱ ማህበረሰብ በባለፈው የግብር አመት በታማኝነት ግብራቸውን በመክፍል ተሸላሚ የነበረው ስሆን በዘንድሮው የግብር አመት የላቀ ታማንነታቸዉን እንድያስጠብቁ የከተማው ከንቲባ አቶ ታርኩ ሮቤ አሳስበዋል።

መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና የከተማ ልማት ለማስፋፋት የንግዱ ማህረሰብ በተሰማሩበት የሙያ ዘርፍ ጠንክሮ በመስራት ግብሩን በታማንኘት እንድከፈል የገደብ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ዋና ተጠሪና የብጽልግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን በርሶ ገልጸዋል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የገደብ ከተማ የገብዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካዮ ፈለቀ ግብር በትክከል እና በታማኝነት ማሰባሰብ ካልተቻሌ የሕዝብን ጥያቄዎች መመለስ ስለማይችል የንግዱ ማህበረሰብ በታማኝነት ግብሩን መክፈል አለበት በማለት አሳስበዋል።

በመድረኩ ላይ የተሳተፉት የ"ሐ" ግብር ከፈዮች በባለፈው የግብር አመት በታማኝነት ግብራችንን በመክፍል ተሸላሚ የነበርን ስለሆነን በዘንድሮው የግብር አመት በላቀ ታማንኘት እንከፍላለን በማለት አስታይታቸዉን ገልጸዋል።

@ጌዴኦ ቴሌቪዥን

ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስቴር እና ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተወጣጣ ልኡክ በጌዴኦ ዞን እየተተገበረ የሚገኘውን "እማጅን ዋን ደይ" ኮስታ ፋውንደሽን ታር ፕሮግራምን ጉብኝት በማድረግ ላይ ነው (...
03/07/2025

ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስቴር እና ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተወጣጣ ልኡክ በጌዴኦ ዞን እየተተገበረ የሚገኘውን "እማጅን ዋን ደይ" ኮስታ ፋውንደሽን ታር ፕሮግራምን ጉብኝት በማድረግ ላይ ነው

(ዲላ ሰኔ 27/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ)ከኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስቴር እና ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተወጣጣ ልኡክ በጌዴኦ ዞን እየተተገበረ የሚገኘውን "እማጅን ዋን ደይ" ኮስታ ፋውንደሽን ታር ፕሮግራምን ጉብኝት በማድረግ ላይ ይገኛል ።

ፕሮግራሙ በዞኑ በሶስት ወረዳዎች ተግባራዊ እየተደረገ ያለው ሲሆን የእስካሁኑ አፈፃፀም ግምገማ እንደሚደረግም ተጠቅሷል ።

በጉብኝቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወራሳን ጨምሮ የፌዴራል ፣ የክልል እና የዞን ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።

@ጌዴኦ ቴሌቪዥን

በከተማዋ የ2017 የግብር ዘመን የግብረ ክፊያና የ2018 የንግድ ስራዎች ፈቃድ እድሳት ማስጀመሪያ  የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነዉ(ዲላ ሰኔ 26/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) የ2017 የግብር ...
03/07/2025

በከተማዋ የ2017 የግብር ዘመን የግብረ ክፊያና የ2018 የንግድ ስራዎች ፈቃድ እድሳት ማስጀመሪያ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነዉ

(ዲላ ሰኔ 26/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) የ2017 የግብር ዘመን፣ የግብረ ክፊያ የ2018 የንግድ ስራዎች ፊቃድ እድሳት ማስጀመሪያ የንቅናቄ መድረክ በጌዴኦ ዞን በገደብ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ የገደብ ከተማ ከንቲባ አቶ ታርኩ ሮቤ፣ አቶ ካሳሁን በርሶ የገደብ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፖርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊው፣ አቶ ካዮ ፈለቀ የገደብ ከተማ አስተዳደር የገብዎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ጨምሮ የንግዱ ማህበረሰብ፣ የሐይማኖት አባቶችን እና የተለያዩ የባለድርሻ አካላት ተገንተዋል።

@ጌዴኦ ቴሌቪዥን

የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ከሁሉም ሴቶች አደረጃጀት የተወጣጡ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በይርጋጨፌ ከተማ ለጓሮ አትክልትና ለግብርና ሰብሎች በተዘጋጀው መሬት ላይ...
02/07/2025

የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ከሁሉም ሴቶች አደረጃጀት የተወጣጡ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በይርጋጨፌ ከተማ ለጓሮ አትክልትና ለግብርና ሰብሎች በተዘጋጀው መሬት ላይ የዘር ማፊሰስ ስራ አካሄዱ

(ዲላ ሰኔ 25/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) የዘር ማፈሰስ ሂደቱ ላይ የክልል የዞንና የሁሉም መዋቅሮች የሴቶች ክንፍ እና አደረጃጀቶች ተሳትፈዋል ።

በይርጋጨፌ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሴቶች ክንፍ አባላት 11 በቤተሰብ የተደራጁ ለጓሮ አትክልትና ለግብርና ሰብሎች ባዘጋጁት ከ150 መደቦች ላይ የዘር የማፊሰስ ስራ አካሂደዋል።

በወቅቱ የተገኙ እንግዶች በሴቶች እየተሰሩ ያሉ የግብርና ስራዎች ይበል የሚያሰኝ መሆኑን ገልፀው የሴቶች አደረጃጀቶች በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለባቸው ተመላክቷል ።

@ጌዴኦ ቴሌቪዥን

ሴቶች በተለያዩ ዘርፎች ጠንክሮ በመስራት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እንዲለወጡ ለማድረግ እየተሰራ ነው ተባለ (ዲላ ሰኔ 25/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) "እኔ እያለሁ ባሌ ስንዴ የሚሰፈርለት አይ...
02/07/2025

ሴቶች በተለያዩ ዘርፎች ጠንክሮ በመስራት ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እንዲለወጡ ለማድረግ እየተሰራ ነው ተባለ

(ዲላ ሰኔ 25/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) "እኔ እያለሁ ባሌ ስንዴ የሚሰፈርለት አይሆንም" በሚል መሪ ቃል የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶ ክንፍ ከሴቶች አደረጃጀት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የንቅናቄ መደረክ በጌዴኦ ዞን በይርጋጨፌ ከተማ ተካሄደዋል።

የደቡብ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊና የፌዴራል የሴቶች ስራ አስፈፃሚ ክንፍ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን እንደገለጹት በክልሉ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎን በማሳደግ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መንግስት እየሰራ ይገኛል ብለዋል ።

ለዚህም ስኬት በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ኃላፊነት በመወጣት የሚፈለገው ውጤት እንዲመዘገብ ማድረግ አለባቸው ሲሉ ወ/ሮ ሰናይት አሳስበዋል ።

ሴቶች በልማት ፣ በፖለቲካ በኢኮኖሚ እና በሌሎችም ዘርፍ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ያነሱት የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ሮቤ ይህንን በማጠናከር ግንባር ቀደም እንዲሰለፉ በትኩረት እየተሰራ ስለመሆኑ አብራርተዋል ።

የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ነፃነት በቀለ በበኩላቸው መድረኩ ሴቶች ከተረጅነት አስተሳሰብ እንዲወጡ እና በራሳቸው ኃይል እንዲቆሙ አቅማቸውን ለመገንባት የታሰበ እንደሆነ ገልጸዋል።

ሴቶች እርሻን ጨምሮ በንግድና በተለያዩ ዘርፎች ጠንክሮ በመስራት የራሳቸውን ኑሮ እንዲያሻሽሉ እና የገቢ ምንጭ እንዲፈጥሩ የሚያስችላቸውን እንቅስቃሴ ማሳደግ እንዳለባቸውም ወ/ሮ ነፃነት ጠቁመዋል ።

ሴቶች የራሳቸውን አቅም በመጠቀም፣ በህብረተሰቡ ዉስጥ ተፅእኖ መፍጠር እንዲችሉ፣ በኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እንዲሳተፉ ማንቃትን ጨምሮ ምርትን ምርታማነት እንዲያሳድጉ፣ ከተረጅነት ሐሳብ እንድዉጡ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የምጠበቅበትን መስራት እንዳለባቸው የይርጋጨፌ ከተማ ከንቲባ አቶ ታደለ ጥላሁን ጥሪ አቅርበዋል ።

ሴቶች የምለሚኑ ሳይሆኑ ተፈጥሮ በሰጣቸው ፀጋ እና መንግስት በመመቻቸዉ የልማት ስራ ተሳታፊ በመሆን እራሳቸውን እና ሌሎችንም ተጠቃሚ ከማድረግ አንፃር መስራት እንዳለባቸው የመድረኩ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

በመድረኩ የደቡብ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊና የፌዴራል የሴቶች ስራ አስፈፃሚ ክንፍ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን፣ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ሮቤ ፣ የይርጋጨፌ ከተማ ከንቲባ አቶ ታደለ ጥላሁንን ጨምሮ የዞን እና የሁሉም መዋቅር ሴቶች ክንፍ እና አደረጃጀቶች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳትፏል።

@ጌዴኦ ቴሌቪዥን

"እኔ እያለሁ ባሌ ስንዴ የሚሰፈርለት አይሆንም" በሚል መሪ ቃል የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ክንፍ ከሴቶች አደረጃጀት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የንቅናቄ መደረክ እየተካሄ ነዉ(ዲላ ሰኔ 25/2017...
02/07/2025

"እኔ እያለሁ ባሌ ስንዴ የሚሰፈርለት አይሆንም" በሚል መሪ ቃል የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ክንፍ ከሴቶች አደረጃጀት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የንቅናቄ መደረክ እየተካሄ ነዉ

(ዲላ ሰኔ 25/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) "እኔ እያለሁ ባሌ ስንዴ የሚሰፈርለት አይሆንም" በሚል መሪ ቃል የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ክንፍ ከሴቶች አደረጃጀት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የንቅናቄ መደረክ በጌዴኦ ዞን በይርጋጨፌ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ የደቡብ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊና የፌዴራል የሴቶች ስራ አስፈፃሚ ክንፍ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን፣ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ሮቤ ፣ የይርጋጨፌ ከተማ ከንቲባ አቶ ታደለ ጥላሁንን ጨምሮ የዞን እና የሁሉም መዋቅር ሴቶች ክንፍ እና አደረጃጀቶች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ ።

@ጌዴኦ ቴሌቪዥን

በክልሉ እየተደረገ ያለው የአንድነት መድረክ ልምድ የሚወሰድበት ነዉ ፦ አቶ አደም ፋራህ ሰኔ 24/2017 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ያለው  የሠላም፣ የአን...
01/07/2025

በክልሉ እየተደረገ ያለው የአንድነት መድረክ ልምድ የሚወሰድበት ነዉ ፦ አቶ አደም ፋራህ

ሰኔ 24/2017 ዓ.ም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ያለው የሠላም፣ የአንድነት እና የልማት ጉባኤ ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።

በወቅቱ የተገኙት የኢፌድሪ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ፣ክልሉ በታሪክ በባህልና በተፈጥሮ ፀጋ የታደለ መሆኑን ገልጸዋል ።

ኢትዮጵያ ብዝሃ ማንነት የሚኖሩባት መሆኑን የገለፁት አቶ አደም ፋራህ ፣በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙት ብሔር ፣ብሔረሰቦች ይህንኑ የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

በክልሉ 32 ብሔሮች ፣ብሔረሰቦች እንደሚገኙ የገለፁት አቶ አደም ፋራህ ክልሉ ፣በተመሰረተ አጭር ጊዜ ውስጥ፣ ከነባር ክልሎች ጋር መሰለፍ መቻሉን ገልጸዋል ።

በዚህም ፣በክልሉ እየተከናወኑ ያሉት የልማት ስራዎች ዉጤት ማስመዝገብ መቻሉን አቶ አደም ፋራህ ጠቁመዋል ።

በኢትዮጵያ ህብረ ብሔራዊ አንድነት ለማጠናከር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሰረት ነዉ ያሉት አቶ አደም ፋራህ ፣በቀጣይም በክልሉ ህዝብ ዘንድ ያለዉን አብሮነት በዘላቂነት ለማስቀጠል መስራት እንደሚገባም አስረድተዋል ።

በክልሉ ያሉት የጋራ ማንነትቶች እንዲጎለብቱ የተጀመሩት ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸውም የኢፌድሪ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ጠቁመዋል ።

በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ (ዶ/ር) የተጀመረው የመደመር ፍልፍስና ዉጤት በሀገሪቱ ሁለንታዊ ብልጽግና እንዲረጋገጥ ስለማስቻሉ ፕሬዝዳንቱ አስገንዝበዋል ።

በክልሉ ወንድማማቾችና እህትማማችነት የተጀመሩ የገዢ ትርክት ዕሳቤዎች እንዲጠናከሩ የኢፌድሪ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል ።

በቀጣይ በክልሉ ያለዉን ታሪክ ባህልና ቋንቋ እንዲሁም የተፈጥሮ ፀጋ ለጋራ ብልጽግና መጠቀም እንደሚገባም አስረድተዋል ።

ጉባዔው ''ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል ነዉ እየተካሄደ እንደሚገኝ ይታወቃል።

በጉባኤው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ በተጨማሪ ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደን ጨምሮ ሌሎች የፌደራልና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ።፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት አባቶች ተሳታፊ ሆነዋል ።

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ለጌዴኦ ዞን ከ1ሺ 200 በላይ መፃሀፍቶች ድጋፍ አደረገየኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት  ለጌዴኦ ዞን ከ1ሺ 280 አጋዥና ል...
01/07/2025

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ለጌዴኦ ዞን ከ1ሺ 200 በላይ መፃሀፍቶች ድጋፍ አደረገ

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ለጌዴኦ ዞን ከ1ሺ 280 አጋዥና ልዩ ልዩ መፃሐፍቶችን ድጋፍ አድርጓል።

ድጋፉን የተረከቡት የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍሌ መምሪያው የመጽሐፍ እጥረት ላለባቸዉ ት/ቤቶች መጽሐፍትን ለማዳረስ ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከዚህ በፊትም ለ10 ትምህርት ቤቶች 1ሽህ 800 በላይ መጸሐፍቶችን ድጋፍ ማድረጉንና ለተጨማሪ ድጋፍ ቃል ገብተዉ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ዘማች ቃላቸው አክብረው ላደረጉት ድጋፍ በዞኑ መንግስት ስም አመስግነዋል።

በት/ቤቶች በመጽሐፍ አጠቃቀም ላይ ከፍተኛ ክፍተት ይስተዋላል ያሉት አቶ ዘማች ተማሪዎችና ት/ቤቶች መጽሐፍቶቹ እድሜ የሚያሳጥር አጠቃቀምን በመከላከልና መጽሐፍ እንዳይባከን በተገቢ፣ ጥንቃቄና በንጽሕና መጠቀም እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ተወካይ አቶ ደጀን ታደሴ አገልግሎቱ የንባብ ባህልን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥተዉ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው ለዚህም በሀገር ደረጃ በተለያዩ አከባቢዎች የመጽሐፍት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

አገልግሎቱ ከዚህ በፊትም በዲላ ከተማ ለሚገኙ ት/ቤቶች የመጽሐፍ ድጋፍ አድረገው ለተጨማሪ ድጋፍ ቃል በገባው መሠረት 530 ሽህ ብር ወጭ የተደረገባቸውን 1 ሽህ 280 አጋዥና ልዩ ልዩ መጽሐፍቶችን ለጌዴኦ ዞን ማስረከቡን ገልጿል።

ተማሪዎች የነገ ሀገር ተረካቢዎች መሆናቸዉን ተገንዝበዉ ነገ የተሻለ ደረጃ ለመድረስ በተገቢው ማንበብና ማጥናት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

@የጌዴኦ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን

አቶ አደም ፋራህ በተገኙበት ክልል ዓቀፍ የሰላም፤ የልማትና የአንድነት ህዝባዊ ኮንፍራንስ 2ኛ ቀን  ቀጥሎ በመካሄድ ላይ ነው (ዲላ ሰኔ 24/2017 ዓ/ም ጌ ቲቪ) ክቡር አቶ አደም ፋራህ ...
01/07/2025

አቶ አደም ፋራህ በተገኙበት ክልል ዓቀፍ የሰላም፤ የልማትና የአንድነት ህዝባዊ ኮንፍራንስ 2ኛ ቀን ቀጥሎ በመካሄድ ላይ ነው

(ዲላ ሰኔ 24/2017 ዓ/ም ጌ ቲቪ) ክቡር አቶ አደም ፋራህ በም/ጠ/ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት እንዲሁም ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ታሪካዊው የክልሉ ሕዝቦች የሰላም፣ የልማትና የአንድነት የማጠቃለያ ኮንፍራንስ ሁለተኛ ቀን በወላይታ ሶዶ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

"ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በመካሄድ ላይ በሚገኘው ክልላዊ የማጠቃለያ ኮንፍራንሱ ከሁሉም ዞኖች የተውጣጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተካተቱበት ከ1ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡

Gedeo TV

የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ለስራ ጉዳይ ወላይታ ሶዶ ከተማ ገቡ (ሰኔ 23/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
30/06/2025

የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ለስራ ጉዳይ ወላይታ ሶዶ ከተማ ገቡ

(ሰኔ 23/2017 ዓ.ም ጌ ቲቪ) የብልፅግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ለስራ ጉዳይ ወላይታ ሶዶ ከተማ ገብተዋል።

አቶ አደም ፋራህ ወላይታ ሶዶ ስገቡ፣ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርጎላቸዋል።

ፕረዚደንቱ በቆይታቸው "ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚገኘው ክልላዊ ጉባኤ ይታደማሉ ተብለዉ ይጠበቃል።

Address

Gedeo
Dila
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gedeo TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share