
30/07/2025
በነገው ዕለት በዞኑ በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃግብር ሁሉም በነቅስ ወጥቶ የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪው ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ
(ዲላ ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም ) በነገው ዕለት በዞኑ በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃግብር ሁሉም በነቅስ ወጥቶ የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪው ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ጥሪ አቅርበዋል ።
እንደ አስተዳዳሪው ገለፃ ነገ ሐምሌ 24 ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ጀምበር እስክትጠልቅ ድረስ በዞኑ ደረጃ ብቻ ከ4 ሚሊዮን በላይ ችግኝ ይተከላል ።
ለዚህም በዞኑ በሚገኙ በሁሉም መዋቅሮች አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ነው ዝናቡ(ዶ/ር) የጠቆሙት ።
በጠቅላይ ሚንስቴር አብይ አህመድ(ዶ/ር) የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያ ስም ገኖ እንዲነሳ እና ሌሎች ሀገራትም ጭምር ምሳሌ እንዲትሆን ማድረጉን ነው አስተዳዳሪው የተናገሩት ።
የጌዴኦ ህዝብ ደግሞ በጥምር እርሻ የሚታወቅ እና በዩኒስኮ ሁሉ ሳይቀር ጥምር እርሻውን አስመዝግቦ የሚኖር ኩሩ ህዝብ መሆኑን አንስቶ የአሁኑ ትውልድም ይህንን ድል እንደሚደግም እምነታቸው ጽኑ እንደሆነ ተናግረዋል ።
አስተዳዳሪው በመጨረሻም በነገው ዕለት በዞኑ በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃግብር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በነቅስ ወጥቶ የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍ ጥሪ አቅርበዋል ።
Gedeo TV