Gedeo TV

Gedeo TV ይህ የጌዴኦ ቴሌቪዥን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ፣ ሼርና ኮሜንት በማድረግ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን በየዕለቱ ይከታተሉ! t.me/gedeotvofficial

በነገው ዕለት በዞኑ በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃግብር ሁሉም በነቅስ ወጥቶ የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪው ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ (ዲላ ሐምሌ 23/2...
30/07/2025

በነገው ዕለት በዞኑ በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃግብር ሁሉም በነቅስ ወጥቶ የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪው ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ

(ዲላ ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም ) በነገው ዕለት በዞኑ በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃግብር ሁሉም በነቅስ ወጥቶ የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪው ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ጥሪ አቅርበዋል ።

እንደ አስተዳዳሪው ገለፃ ነገ ሐምሌ 24 ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ጀምበር እስክትጠልቅ ድረስ በዞኑ ደረጃ ብቻ ከ4 ሚሊዮን በላይ ችግኝ ይተከላል ።

ለዚህም በዞኑ በሚገኙ በሁሉም መዋቅሮች አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ነው ዝናቡ(ዶ/ር) የጠቆሙት ።

በጠቅላይ ሚንስቴር አብይ አህመድ(ዶ/ር) የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያ ስም ገኖ እንዲነሳ እና ሌሎች ሀገራትም ጭምር ምሳሌ እንዲትሆን ማድረጉን ነው አስተዳዳሪው የተናገሩት ።

የጌዴኦ ህዝብ ደግሞ በጥምር እርሻ የሚታወቅ እና በዩኒስኮ ሁሉ ሳይቀር ጥምር እርሻውን አስመዝግቦ የሚኖር ኩሩ ህዝብ መሆኑን አንስቶ የአሁኑ ትውልድም ይህንን ድል እንደሚደግም እምነታቸው ጽኑ እንደሆነ ተናግረዋል ።

አስተዳዳሪው በመጨረሻም በነገው ዕለት በዞኑ በሚካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃግብር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በነቅስ ወጥቶ የበኩሉን አሻራ እንዲያሳርፍ ጥሪ አቅርበዋል ።

Gedeo TV

የተረከብናቸውን ችግኞች በመትከል አሻራችንን ለማኖር ተዘጋጀትናል :- የዲላ ከተማ ነዋሪዎች ( ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም ) የዲላ ከተማ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ ብዙ ጠቄሜታ ያላቸውን ችግ...
30/07/2025

የተረከብናቸውን ችግኞች በመትከል አሻራችንን ለማኖር ተዘጋጀትናል :- የዲላ ከተማ ነዋሪዎች

( ሐምሌ 23/2017 ዓ.ም ) የዲላ ከተማ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን

ዘርፍ ብዙ ጠቄሜታ ያላቸውን ችግኞች በመትከል አሻራቸውን ለማኖር መዘጋጀታቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዲላ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ገለጹ።

በክልሉ ለአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ የጉርጓድ ቁፋሮቻ የችግኝ ስርጭት መጠናቀቁም ተመላክቷል።

አስተያየታቸውን የሰጡት የዲላ ከተማ የጪጩ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ታሪካየው ሃይለማርያም በቀጠናቸው ላዘጋጁት ከ2 ሺህ በላይ ጉርጓዶች የሚሆን ዘርፍ ብዙ ጠቄሜተ ያላቸውን ችግኞች መረከባቸውን ጠቅስዋል።

በተለይ ለምግብነትና ለአከባቢ ጥበቃ የሚሆኑ የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት ማግኝታቸውን አንስተው ነገ በሌሊት በመውጣት በመትከል አሻራቸውን ለማኖር መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

ይህም የአካባቢያቸውን ከጽታ ከመቀየር በተጨማሪ ለምግብ ዋስትና መረጋገት ድርሻው የጎላ በመሆኑ ተከባክበው ለማሳደግ በቅንጀት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ዞኑ የሚታወቅበትን የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ባህልን የሚያጠናከር ነው ያሉት ደግሞ ሌለኛዋ አስተያየት ሰጭ ወይዘሮ ዝናሽ ብርሃኑ ናቸው።

በተለይ ለልጆቻችን ሚቹ አከባቢ ለማውረስ መትከል እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው በነገው የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ በነቂስ ለመሳተፍ ዝግጅት ማድረጋቸውን አንስተዋል።

ሌላቸው አቶ ፍላጎት ወልደሰንበት በበኩላቸው ዘርፍ ብዙ ጠቄሜታ ያላቸውን ችግኞች በመትከል አሻራቸውን ለማኖር መዘጋጀታቸውን ገለጸዋል።

ለዚህም ችግኝ ማግኝታቸውን ጠቅሰው በጓሯቸው እንዲሁም በጋራ መትከያ ስፍራ በማሌዳ ተነስተው እንደሚተክሉ ገልጸዋል።

በከተማው የጎላ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ሃይሉ ሻንቆ በበኩላቸው ለአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ የሚሆን ችግኝ በእጃቸው መግባቱን ነው ያነሱት።

የተረከባቸውን ችግኞች በጓሯቸውንና በቀበሌው በተለዩ የወል መሬቶች በመትከል አሻራቸውን ለማኖር መዘጋጀታቸውን ጠቅሰዋል።

በተለይ የፍራፍሬ ችግኞች መውሰዳቸው ለጥምር ግብርና ባህላቸውን ከማጎልበት ባለፍ በቀጣይ የገቢ ምንጭ መሆኑንም ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጱያ ክልል ደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ግዛቴ ግጄ በበኩላቸው በክልል ለተከላ ከተለዩ 973 ስፍራዎች ውስጥ 891 በቀጥታ ለብሔረዊ የመረጃ ቋት የሚገቡ ናቸው ብለዋል።

ለነገ የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላም የጎርጓድ ቁፋሮና የችግኝ ስርጭት መጠናቀቁን ነው ያነሱት።

በዚህም ለምግብነት የሚሆኑ የፍራፍሬ፣ የጥምር ግብርና፣ የደንና የኢንዱስትሪ ችግኞች በስፋት እንደሚተከሉም ተናግረዋል።

የአረንጓዴ አሻራ በክልሉ የተራቁ አካባቢዎችን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የግብርና ምርታማነትን ማሳደጉን ጠቅሰው በነቃ የህብረተሰብ ተሳትፎ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ዘገባው የዲላ ከተማ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ነው።

Baabo kaansso!!Haanjinne bogiinka Heqqino!!
30/07/2025

Baabo kaansso!!
Haanjinne bogiinka Heqqino!!

Nage'a Saamantto!!!ሠላምን እንሻማ!!!  TV
30/07/2025

Nage'a Saamantto!!!
ሠላምን እንሻማ!!!
TV

እንደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአንድ ጀምበር 60 ሚሊዮን የአረንጓዴ ዐሻራ የማስጀመሪያ መርሀ-ግብር በምደረግበት በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ድባንድቤ ቀበሌ ተገኝተው ቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ አሁን...
30/07/2025

እንደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአንድ ጀምበር 60 ሚሊዮን የአረንጓዴ ዐሻራ የማስጀመሪያ መርሀ-ግብር በምደረግበት በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ድባንድቤ ቀበሌ ተገኝተው ቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ አሁን የደረሰበትን ደረጃ የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ምልከታ አደረጉ ።

‎ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም ) ዲላ

‎የአረንጓዴ ዐሻራ ቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ አሁን የደረሰበትን ደረጃ የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ተመስገን ጥላሁን እና የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ እና የመንግሥት ረዳት ተጠሪ አቶ ተገኝ ታደሴ ጨምሮ የወረዳ አስተባባሪ አካላት ምልከታ አደረገዋል ።

‎በተደረገ ምልከታም የጉድጓድ ዝግጅት፣ከችግኝ አቅርቦት ዝግጅት አንፃር በበቅ ሁኔታ መዘጋጀቱን እና በዕሌቱ ወደ ምተከልበት ቦታ ሁሉም ችግኞች በየቦታቸው የማድረሱ ዝግጅት እና ዕእንግዶችን ለመቀበል እየተደረገ ያለው ሁኔታ የተሻሌ ደረጃ መሆኑን ተገለፀዋል።

‎እንዴ ወረዳው በአጠቃልያ በአንድ ጀምበር 625,500 ችግኝ ለመትከል የሁሉም ቦታዎች የ XYZ coordinations ተወስደው ሁሉም ማህበረሰብ ዕለቱን እየተጠባበቁ ያለበት ደረጃ ያለ መሆኑን ተጠቁመዋል

‎ #በአንድ ጀምበር፦
‎ እንደ ሀገር 700 ሚሊዮን
‎እንደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 60 ሚሊዮን
‎እንደ ጌዴኦ ዞን 4 ሚሊዮን
‎እንደ ጮርሶ ወረዳ 625,500 ሺህ
‎ዝግጅቶቻችን እያለቁ ነው 2 ቀን ብቻ ይቀረናል።

‎ዘገባው :-የጮርሶ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ነው

Gede'iinxe zoone giddo afendaaxxa songuwwa jabeessatee gargar hexxeexxi hujuwwa hujemate'n iima hexxeen፦ Abba Gada Biifo...
29/07/2025

Gede'iinxe zoone giddo afendaaxxa songuwwa jabeessatee gargar hexxeexxi hujuwwa hujemate'n iima hexxeen፦ Abba Gada Biifoom Waaqo

(Dilla, Hageyya 22/2017 G.W) Abba Gada Biifoom Waaqo Gede'iinxe zoone'n coorsoke roga'n Geesheke loola'n afendaxxe songo'n afemeexxi looliinxe hayyoolenninaa hedhdhalluwwik welt mari'e assine'en.

Tenne yanna'n Abba Gada Biifoom Waaqo hineeshsha Gede'iinki ardi olminaa'n safeexxi aadatike galdumin ege'nemeeke arda kadeexxa hassonne'en.

Kunni ardiink galdum ilatibaa'n ilatibaa foofaashsha assatee aadatixxi geedhe mi'lachchot hujate'n iima hexxeexxa Abba Gada Biifoom ifinse'en.

Abba Gada lenbexxi gargarxe songuwwa'n uwwenda'neexxi ergachcho seera Gede'iinka waaldebaangi kaddaashsha assatee jabaxxi huje safendeexxanna eere'en.

Gede'iinxe Zoone Aadanna Daa'unsot akeeki sooreessi Aaddi Derbe Jinno Zoonetishsha aada, laagadanna daa'unso uuddaaxxinni ba'laxxi huje hujemate'n iima hexxeexxa ege'nishshe'en.

Zoonetishsha afendaxxi duuchchiinxi songuwwa heqendashsha mootummati darrenaa'n aadatixxe geedhenni mitteba weli qabati mi'lachchoti hujenda'neexxa Aaddi Derbe haassonne'en.

Coorsoke rogi illichchi galchalli aaddi Birhaanu Mekkonninni insa'ne darree'n hineeshsha roginsha aadate'n safendexxi huje eloxxe kaddeexxa ifinse'en.

Coorsoke rogishsha 47 kaddaaxxa songuwwa haaroonsateenna hasissaaka kipha assatee rogiinxi mootumma qurxeeffachchot hujaaxxa haassonne'en.

Gedeo TV

የቶምቦላ ሎተሪ እድለኛው አቶ ቶምቦላ ወልደ ሥላሴ**************************በቅርቡ በወጣው የቶምቦላ ሎተሪ የ2ኛው እጣ አሸናፊ የሆነው አቶ ቶምቦላ ወልደ ሥላሴ ስሙ እና እድለ...
29/07/2025

የቶምቦላ ሎተሪ እድለኛው አቶ ቶምቦላ ወልደ ሥላሴ
**************************

በቅርቡ በወጣው የቶምቦላ ሎተሪ የ2ኛው እጣ አሸናፊ የሆነው አቶ ቶምቦላ ወልደ ሥላሴ ስሙ እና እድለኝነቱ መገጣጠሙ ብዙዎችን አስገርሟል።

አቶ ቶምቦላ ወልደ ስላሴ በ1984 ዓ/ም በይርጋጨፌ ወረዳ ሃሩ ቀበሌ ነው የተወለደው።

ቶምቦላ የተባለበት ምክያትንም ሲያስታውስ፤ እናቱ እሱን ለመውለድ ለረጅም ቀናት ምጥ ይዟቸው እንደቆዩ እና ቡና ነጋዴ አባታቸውም በዚህ ምክንያት ሥራቸውን ትተው ከእናታቸው ጋር እንደነበሩ ይገልጻል።

በዚህ መካከል አባታቸው የሚነግዱት ቡና ቢዘረፍም ባለቤታቸው ከአስጨናቂ ምጥ በኋላ ወንድ ልጅ ስለወለዱላቸው፤ ሀብት ነገ ይተካል እኔ ልጄ ሎተሪ ሆኖልኛል ብለው ቶምቦላ ብለው ስም ያወጡለታል።

አቶ ቶምቦላ አባታቸው ለረጅም ጊዜ ሎተሪ ይቆርጡ እንደነበርም ያስታውሳል። በተለይም በጊዜው በኢትዮጵያ ሬዲዮ የአሸናፊ እጣ ቁጥሮች ሲነገሩ በጉጉት ጠብቀው ያዳምጡ እንደነበርም ይገልጻል።

እርሱም ሎተሪ መቁረጥን ከአባቱ አይቶ እንደጀመረ ገልጾ፤ የረጅም ጊዜ የሎተሪ ደንበኛ እንደሆነ ለኢቢሲ በሰጠው ቃል ገልጿል።

በቅርቡ የውጣው ቶምብላ ሎተሪ ሁለኛ እጣ የባለሁለት መኝታ መኖሪያ ቤት እና 40 ሺህ በየወሩ ለሁለት ዓመት አሸናፊ የሆነበትን እጣ እንዴት እንደቆረጠ ሲያስታውስም፤ በሃሩ ቀበሌ ለምትገኘው ሱቁ አንዳንድ እቃዎች ለማሟላት ከባለቤቱ ጋር ወደ ይርጋጨፌ በመጣበት ወቅት እንደቆረጠ ገልጿል።

እጣው እንደወጣ ለ3 ቀናት አካባቢ ሳያስታውስ ቆይቶ፤ ከ3 ቀን በኋላ ምሽት ላይ አረፍ ብሎ በማሕበራዊ ትስስር ገጽ የእጣ ውጤቱን ሲፈልግ 2ኛ እጣ እንደወጣላት እንደተመለከተም ነው የተናገረው።

ከ12 ዓመት በላይ በየገጠመኙ ሎተሪ ይቆርጥ እንደነበርም አቶ ቶምቦላ ወልደ ሥላሴ ተናግሯል።

በብሩክታዊት አስራት

ህብረተሰቡ ከተረጂነት ለማላቀቅ በንቅናቄ ወደ ሥራ ተገብቷል፦ የጌዴኦ ዞን ግብርና መምሪያ ‎‎( #ዲላ 22-2017 ዓ/ም) "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለሃገር ሉዓላዊነትና ለተሟላ ክብር" በ...
29/07/2025

ህብረተሰቡ ከተረጂነት ለማላቀቅ በንቅናቄ ወደ ሥራ ተገብቷል፦ የጌዴኦ ዞን ግብርና መምሪያ

‎( #ዲላ 22-2017 ዓ/ም) "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለሃገር ሉዓላዊነትና ለተሟላ ክብር" በሚል መር ቃል በሚካሄደው ተግባር ብቻ በመኸር ወቅት ከ500 ሄክታር መሬት በላይ በተለያዩ አዝርዕት ለመሸፈን ታቅደው በሁሉም መዋቅሮች የመሬት ዝግጀት በንቅናቄ መጀመሩን መምሪያው አስታውቋል።

‎የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ ታጠቅ ዶሪ(እጩ ዶ/ር) ጨምሮ የዞኑ የዘርፉ ኃላፊዎችና ጨምሮ የወረዳ አመራሮች "ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለሃገር ሉዓላዊነትና ለተሟላ ክብር" በሚል መር ቃል በይርጋጨፌ ወረዳ በቱቲቲ ቀበሌ በመኸር 2017/2018 ምርት ዘመን በወረዳ አቅም ለሚመረት ስንዴ የማሳ ዝግጅት ምልከታ አድረገዋል።

‎የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ኃላፊ ታጠቅ ዶሪ(እጩ ዶ/ር) የእርዳታ እጁ በመላቀቅ እርስበርስ በመደጋገፍ በጋራ በመሆን ለመቻል ተግባራት ተጀምረዋል።

‎በህብረት ተቀናጅተን ባለነው መሬት አቅሙ የፈቀደውን ሁሉ በማድረግ ከተጠናከርን ከድህነትና ከልመና መወጣት የሚያዳግት ጉዳይ የለም ብለዋል ኃላፊው።

‎ህብረተሰቡ በየአካባቢው የተጀመረው የመኽር ሥራዎች አጠናክሮ እንዲያስቀጥሉ ኃላፊው አሳስበዋል።

‎የይረጋጨፌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክፍሌ ጅግሶ ልመና ውርደት ነው፦ ከተረጂነት ለመውጣት በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

‎የመሬቱ ባለቤት የሆኑት አቶ ንጋቱ መንገሻ 10 ሄክታር መሬት በህመም ምክንያት ማረስ ባለመቻላቸው ወረዳው ወስደው እንዲያለማ በፍቃዳቸው ሰጥተው ወደ ሥራ መግባታቸውን ኃላፊው ገልጿል።

‎የአከባቢ አርሶአደሮች ከተረጂነት ለመውጣት የተጀመረውን ሥራ በግቢ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

‎@የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን።

''የተራቡትን ማብላት የደከሙትን ማበረታታት እንደ ሕብረተሰብ ባሕል ያደረግን ሕዝቦች ነን" አቶ ዳዊት ቡኔ ‎(ዲላ ሐምሌ 21/22017 ዓ/ም)‎''በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል...
28/07/2025

''የተራቡትን ማብላት የደከሙትን ማበረታታት እንደ ሕብረተሰብ ባሕል ያደረግን ሕዝቦች ነን" አቶ ዳዊት ቡኔ

(ዲላ ሐምሌ 21/22017 ዓ/ም)‎''በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ የተጀመረው የክረምት በጎ አድራጎት ዛሬ በይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳደር በሀሩ ቀበሌ መክፈቻ መድረክ ተካሂዷል ።

‎በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡኔ እንደተናገሩት ''የተራቡትን ማብላት የደከሙትን ማበረታታት እንደ ሕብረተሰብ ባሕል ያደረግን ሕዝቦች ነን '' በዚህ መንግስት አብሮ በመስራቱ መልካም ዉጤት እየታዬ መምጣቱን ተናግረዋል ።

‎እንዲሁም በዘንድሮው የክረምት በጎ አገልገሎት በይጋጨፈ ወረዳ 700 ቤቶችን ለመገንባት እንደታቀደ ተናግረው ከዚህም 420 አድስ ቤት እና 280 ያረጁ ቤቶችን መሆናቸው ገልጸዋል ።

‎እንዲሁም የጌዴኦ ዞን የወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳንኤል ታደሰ እንደተናገሩት በጌዴኦ ዞን በክረምት በጎ ሥራ በ15ቱ የትኩረት አቅጣጫዎች መልካም ዉጤት እየታየ መሆኑን ተናግረው ።

በዘንድሮው 4390 ቤቶችን ለመገንባት መታቀዱን እንዲሁም በነሐሴ 12 ላይ በአንጅ ጀንበር 2000 ቤቶችን እና በሐምሌ 24 1,5 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል መታቀዱን ተናግረዋል ።

‎የይሪጋጨፌ ወረዳ ወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አለማየሁ አየለ መልካም ስራ ለአእምሮ እርካታ የምሰራ መሆኑን ተናግረው ወጣቱ አብሮ በመስራት ከጎናቸው እንድቆም ጥሪ አቅርበዋል ።

‎በዕለቱ ለአቅሜ ደካሞች ቤት መገንባት፤ የክረምት ትምህርት ማስጀመሪያ እና የአሩጋዴ አሻራ ችግኝ የመትከል እንዲሁም የደም ልገሳ መርሐግብር ተካሂዷል ።

‎'

በክረምት ወራት ለመሰረታዊ ማህበራዊ ችግር ተጋላጭ የሆኑትን ህብረተሰብ ከችግራቸው ለማላቀቅ በትኩረት ይሰራል፦ የገደብ ከተማ አስተዳደር‎‎( #ዲላ 21-2017 ዓ/ም) ከተማ አስተዳደሩ "በጎ...
28/07/2025

በክረምት ወራት ለመሰረታዊ ማህበራዊ ችግር ተጋላጭ የሆኑትን ህብረተሰብ ከችግራቸው ለማላቀቅ በትኩረት ይሰራል፦ የገደብ ከተማ አስተዳደር

‎( #ዲላ 21-2017 ዓ/ም) ከተማ አስተዳደሩ "በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል ለሁለት ወራት የሚከናወነው የ2017 ዓ/ም የወጣቶች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የቤት ግንባታና ማጠናከሪያ ትምህርት በማስጀመር፣ በደም ልገሳና በአረንጓዴ አሻራ ተከላ አስጀምረዋል።

‎የገደብ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታርኩ ሮቤ በ2016 ክረምት በጎ ፍቃድ ሥራ የተከማ ህብረተሰብ በማስተባበር 120 የአቅም ደካሞች ቤቶች መስራት ተችሎዋል።

‎ወጣቶች፣ ባለሃብቶችና የከተማ ነዋሪዎች ለተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ለተጋለጡት ህብረተሰብ ክፍል በበጎ ፍቃዳቸው በገንዘብና በጉልበት በመደገፍ ከፍተኛ አስታውጾ አበርክቷል ከንቲባው።

‎የከተማ ወጣቶች በከተማ ጽዳት፣ ደም በመለገስ፣ በትምህርት፣ በመንገድ ደህንነትና በከተማ ሰላምና ፀጥታ እና በሌሎች ማህበራዊ ዘርፎች እየተወጡ ላሉት አስታውጾ ከንቲባው ምስጋና አቀርበዋል።

‎የጌዴኦ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደግነት ኃይሉ በዞኑ"በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መር ቃል በሚካሄደው ተግባር በርካታ ውጤቶች ተመዝግቧል፤ በርካታ የህብረተሰብ ክፍል የአገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል።

‎የክረምት የወጣቶ በጎ ፍቃድ አገልገሎት ግልጋሎት ከወጣቶች አልፈው በሁሉም ዘርፎች እያደገ መጥተዋል፣ በክረምት ወራት በግብርና፣ በማህበረሰብ ግንባታና በጤና ላይ በትኩረት ይሰራል ብለዋል ኃላፊው።

‎በዞን ደረጃ በነሐሴ ወር በአንድ ጀንበር 2 ሺህ የአቅም ደካሞች ቤት ለመገንባት ቅድመ ዝግጀት እየተደረገ ነው፦ለዚህም ሁሉ ህብረተሰብ ክፍል ባለቸው አቅም ሁሉ የበኩላቸውን በማድረግ እንዲወጡ አቶ ደግነት ጥሪ አቀርበዋል።

‎የገደብ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አረጋኃን ነጋሽ በከተማው በ2017 ዓ/ም የወጣቶች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በ15 ዘርፎች ከሰባት ሺህ በላይ ወጣቶች በማሳተፍ ከ40 ሺህ በላይ ህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

‎ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው አረጋውያን፣ የመከላከያ ሠራዊት ቤተሰቦቾና ለአካል ጉዳተኞችን ጨምሮ ለከፍተኛ ማህበራዊ ችግሮች ተጋላጭ ህብረተሰብ ክፍል ከችግራቸው ማላቀቅ ተችለዋል ብለዋል።

‎በዘንድሮው ክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በ15ቱ ዘርፎች የሚከናወኑ ተግባራት በገንዘብ ሲተመን ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት ኃላፊው ገልጸዋል።

‎የእረፍት ግዜያቸውን ግዜ በመስጠት በገልበት፣ በገንዘብና በሌሎች አስፈላጊ ጉዳዮች ተሳትፎ በማድረግ የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ያነጋገርናቸው የከተማ ወጣቶች ተናግረዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በስድስቱ ማዕከላት ለሚገነባ የህንፃ ግንባታ ስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በድስቱ ማዕከላት ለቢሮ እ...
28/07/2025

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በስድስቱ ማዕከላት ለሚገነባ የህንፃ ግንባታ ስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት በድስቱ ማዕከላት ለቢሮ እና ሌሎች አገልግሎቶች ለሚውሉ የህንፃ ግንባታ ስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ተካሄዷል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመርሃ ግብሩ በሁሉም የክልሉ ማዕከላት ሊገነቡ ለታሰቡ የተቋማት ህንፃ ግንባታ ቀድሞ የተጀመሩ ስራዎች የደረሱበትን ደረጃ በተለያየ ጊዜ በመገምገም፤ ግንባታውን በሁሉም ማዕከላት በፍጥነት በመጀመር ባጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ የሚያስችል ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ የቀደምት ታሪካቸውን በመገምገም በግዜ እና በጥራት ሰርተው የሚያጠናቅቁ በክልሉ የሚገኙ 8 ተቋራጮች የመንግስት የግዥ ህግን በመከተል መመረጣቸውንም አስረድተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ ተቋራጮቹ ፕሮጀክቱን በተያዘለት የግዜ ገደብ እና የጥራት ደረጃ እንዲሁም በሚፈለገው የአገልግሎት እሳቤ ፈጥኖ መጨረስ ይገባቸዋል ሲሉም አሳስበዋል።

አክለው ፕሮጀክቱ ትልቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለስኬታማ አፈጻጸሙ አስፈላጊው ክትትል፣ ቁጥጥር እና ድጋፍ ለዚሁ ዓላማ በተዋቀረ ኮሚቴ የሚደረግ መሆኑንም ተናግረዋል።

በመጨረሻም ርዕሰ መስተዳድሩ በተገኙበት በስድስቱም ማዕከላት ለሚገነቡ የተቋማት የህንፃ ግንባታ ስራው ከየተቋሙ አስተባባሪዎች ጋር የውል ስምምነት ተፈርሟል።

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

የገደብ ከተማ አስተዳደር የ2017 ዓ/ም የወጣቶች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ እየተካሄደ ነው‎‎ ( #ዲላ ሐምሌ 2017 ዓ/ም) "በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ  ከፍታ" በሚል...
28/07/2025

የገደብ ከተማ አስተዳደር የ2017 ዓ/ም የወጣቶች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ እየተካሄደ ነው

‎ ( #ዲላ ሐምሌ 2017 ዓ/ም) "በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል ለሁለት ወራት የሚከናወነው የ2017 ዓ/ም የወጣቶች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በጌዴኦ ዞን የገደብ ከተማ አስተዳደር ማስጀመሪያ እያካሄደ ይገኛል።

‎በማስጀመሪያ መርሃግብር የገደብ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታርኩ ሮቤ፣ የጌዴኦ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደግነት ኃይሉ፣ የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ዜና ማሞ፣ አቶ ካሳሁን በርሶ የገደብ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የገደብ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አረጋኃን ነጋሽጨምሮ የከተማ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የሃገር ሽማግሌዎችና የከተማ ወጣቶች ተሳትፈዋል።

@የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን።

Address

Gedeo
Dila
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gedeo TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share