Gedeo TV

Gedeo TV ይህ የጌዴኦ ቴሌቪዥን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ፣ ሼርና ኮሜንት በማድረግ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን በየዕለቱ ይከታተሉ! t.me/gedeotvofficial
(1)

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፍዎች ለይፋዊ  የስራ ጉብኝት ዲላ ከተማ ገቡዲላ ፦ ሴነ 03/2018 ዓ.ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)‎በነገው ዕለት የሚመረቀውን የዲ...
10/06/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፍዎች ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዲላ ከተማ ገቡ

ዲላ ፦ ሴነ 03/2018 ዓ.ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

በነገው ዕለት የሚመረቀውን የዲላ ከተማ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ህንፃ ምክኒያት በማድረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ዲላ ከተማ ገብተዋል።

በሀገር በቀል ዕሳቤ የተጀመረው መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በክልሉ ከተሞች ተመርቀው አገልግሎት ወደ መስጠት እየገቡ ሲሆን በቅርቡም የአርባምንጭ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል።

በነገው ዕለትም የሚመረቀው የዲላ ከተማ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የበርካታ ተገልጋይ ህብረተሰብ የአገልግሎት የሚያሳልጥና በተገልጋይ ዕርካታ አይነተኛ ሚና እንደሚኖረው ይታመናል።

በአብነት አበበ
ፎቶ ፦ሔኖክ ሽፈራው

‎በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ሀገር አቀፍ ፈተና የተሻለ ዉጤት ለማምጣት ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን የዲላ  2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ገለፁ‎‎ዲላ ፦ ሰኔ 03/2018 ዓ/ም ( ጌዴ...
10/06/2026

‎በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ሀገር አቀፍ ፈተና የተሻለ ዉጤት ለማምጣት ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን የዲላ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ገለፁ

‎ዲላ ፦ ሰኔ 03/2018 ዓ/ም ( ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

‎በ2018 የትምርት ዘመን በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ጥሩ ውጤት ለማምጣት ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ነው የዲላ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የገለፁት ።

‎ተማሪዎች በብሄራዊ ፈተናው ጥሩ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ለማድረግ ከኮምፒውተር ስልጠና ጀምሮ የተለያዩ አጋዥ ሥራዎች ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ።

‎የዲላ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች እንደገለፁት
‎ሀገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ጠቅሰው ፈተናው በኦንላይን የሚሰጥ በመሆኑ ከት/ቤቱ የኮምፒውተር ስልጠና እየተሰጣቸው እንደሆነም ተናግረዋል ።

‎ፈተናው ሁሉን አቀፍ እንደመሆኑ ዘንድሮ በተሻለ መልኩ የድጋፍ ትምህርት ማግኘታቸውን የገለፁት ተማሪዎቹ
‎ሁሉም ተማሪ ያለውን ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም በፈተናው የተሻለ ውጤት ለማምጣት የራሳቸውን ዝግጅት ማድረግ አለባቸው ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

‎ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ፈተና ጥሩ ውጤት እንዲያመጡ የድጋፍ ትምህርት በመስጠት እራሳቸውን ለፈተናው ዝግጁ እንዲያደርጉ ያለፋ አመታትን የፈተና ወረቀቶችን በጋራ በመስራት ለብሔራዊ ፈተና የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ለማድረግ እንደተሰራ የት/ቤቱ መምህራን ተናግረዋል ።

‎በሥነልቦና ጎልብተው በፈተናው ጥሩ ውጤት እንዲያመጡ የሚያስችል ሥራዎች መከናወኑን የጠቆሙት መምህራኖቹ ያላቸውን ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም በፈተናው ጥሩ ውጤት ለማምጣት ተግቶ ማንበብ አለባቸው ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል ።

‎የዲላ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ዋና ርዕሰ መምህር አቶ ደሳለኝ ታፈሰ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እንዲወስዱ ለማድረግ ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረው መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት በማጠናቀቅ የማጠናከሪያ ትምህርት እንደተሰጠም አስረድተዋል ።

‎ፈተናው የሚሰጠው በኦንላይን በመሆኑ ከቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋም ጋር በመሆን ተማሪዎች የኮምፒውተር ትምህርት ልምምድ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረው ተማሪዎች እራሳቸውን በሥነ ልቦና ዝግጁ በማድረግ ያላቸውን ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም ጥሩ ውጤት እንዲያመጡ መዘጋጀት አለባቸው ሲሉ አሳስበዋል ።

‎የዲላ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ ኡዊዩ ሃይሉ በበኩላቸው በተለይ ተማሪዎች ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የማጠናከሪያ ትምህርት ሲሰጥ መቆየቱን በመጥቀስ ተማሪዎች በሥነልቦና ዝግጁ እንዲሆኑ ለማድረግ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል ።

‎እንደ ዲላ ከተማ ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የዲጂታል ፈተና አሰጣጥን መሰረት ባደረገ መልኩ በተመረጡ የፈተና ማዕከላት ላይ ለማስፈተን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን በመግለፅ ተማሪዎች ያላቸውን ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም በፈተናው ጥሩ ውጤት ለማምጣት እራሳቸውን ዝግጁ ማድረግ እንዳለባቸው ም/ኃላፊው አክለዋል ።


‎ዘጋቢ በሰኒያ መሀመድ
‎ፎቶግራፍ ፦ኤልሳ ውብሸት
‎ይህንንና ሌሎችን ዘገባዎች ለመከታተል በነዝህ ድህረ ገጾች ይከታተላሉ
‎ ዩቱብ https://youtube.com/?feature=shared

‎ቴሌግራም https://t.me/gedeotvofficial

‎ቲክቶክ https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-96GXGnq7yeD

10/06/2026

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የሚዲያ ጥቆማ፣ቅሬታ ማቅረቢያ እና መከታተያ (Mobile Application) በቅርቡ ተግባራዊ በማድረግ ወደ ስራ ማስገባቱ ይታወቃል።

መተግበሪያውን ከPlay Store ወይም ከApp Store በስልክዎ ላይ በመጫን (Install በማድረግ)፣ የተቀናጀ የሚዲያ ሬጉላቶሪና አስተዳደር ሥርዓት አገልግሎቶችን በቀላሉ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

መተግበሪያውን በመጠቀም በዲጂታልም ሆነ በመደበኛ የሚዲያ አውታሮች ላይ የሚፈፀም የህግ ጥሰት፣ የሙያ ስነ-ምግባር ግድፈት፣ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃዎችን ሲመለከቱ በነፃ የጥሪ ማዕከል 9192 ጥቆማ ማቅረቢያ በተጨማሪ በእጅ ስልክዎ ፣ በዴስክቶፕ ኮምፕዩተሮች፣ በላፕቶፖች እና በሁሉም አማራጮች ለባለሥልጣኑ በማሳወቅ ሀገራዊ ግዴታዎን ይወጡ!!

https://play.google.com/store/apps/details?id=et.aii.mediacomplanitapp



የክልሉ 3ኛ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል በነገው ዕለት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዲላ ከተማ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናልዲላ:- ሰኔ 3/2018(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)ማዕከሉ ...
10/06/2026

የክልሉ 3ኛ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል በነገው ዕለት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዲላ ከተማ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል

ዲላ:- ሰኔ 3/2018(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

ማዕከሉ አሰልቺ የእንግልት አሰራር የሚያስቀር ቢሮ ለቢሮ መንከራተትን በማስቀረት፣ቀልጣፋ አገልግሎቶችን በአጭር ጊዜ የሚሰጥ ይሆናል።

በተለይም አዲስ የንግድ ፈቃድ ማውጣት፣ማደስ እና የንግድ ስም ምዝገባ፤ የወጣቶች ስራ ፈጠራ ድጋፎች፣ የምዝገባ እና የቦታ አሰጣጥ፤ ያለምንም እንግልትና ወረፋ ግብር የሚከፈልበት አሰራር፤ የልደት፣ የጋብቻ የምስክር ወረቀቶች እና የነዋሪነት መታወቂያ፤እንዲሁም የቁጠባና የብድር አቅርቦቶችን ሌሎችን በአንድ ላይ ማግኘት የሚችሉበትን ዕድል ያመቻቻል።

የማዕከሉ ዋና ዓላማ የህዝባችንን ጊዜና ጉልበት በመቆጠብ፣የሙስና እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሰብሮ በአንድ ጣራ ስር ቀልጣፋና ዘመናዊ መስተንግዶ ማቅረብ ነው።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 3ኛ የሆነው የዲላ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል፤ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም የመሶብ አንድ ማዕከል ቦርድ ሰብሳቢ፣ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በነገው ዕለት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል።

የማዕከሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን አማካኝነት የተከናወነ ሲሆን፣የደቡብ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት ደግሞ የማማከር ስራውን በጥራት መሥራቱን ለማረጋገጥ ተችሏል።

ዘገባው የዲላ ከተማ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ነው።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ማናጅመንት አባላቶች በጌዴኦ ዞን ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት በመገኘት ድጋፍና ክትትል እያከናወነ ይገኛል ‎‎ዲላ፦ ሰኔ 03-2018 ዓ/ም(ጌዴኦ ቴሌቪ...
10/06/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ማናጅመንት አባላቶች በጌዴኦ ዞን ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት በመገኘት ድጋፍና ክትትል እያከናወነ ይገኛል

‎ዲላ፦ ሰኔ 03-2018 ዓ/ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን(

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ማናጅመንት አባላቶች በጌዴኦ ዞን ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት በመገኘት ድጋፍና ክትትል እያከናወነ ነዉ።

‎የድጋፍና ክትትል ቡድኑ በዞኑ በሚገኙ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የድጋፍና የክትትል ስራ በማከናወን ላይ ይገኛሉ ።

‎የክልሉ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን የክትትል ቡድኑ በዞኑ በሚኖራቸው የስራ ቆይታ በመዋቅሩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች የስራ እንቅስቃሴዎች ፣አዳዲስ ፕሮጀክት የስራ ሁኔታ እና ባጋጠሙ ችግሮች ዙሪያ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ይጠበቃል ።

‎በድጋፍና ክትትሉም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ወ/ሮ አፀደ አይዛን ጨምሮ የክልሉ ማናጅመንት አካላቶች እየተሳተፉ ይገኛል ።

‎ዘገባው የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ነው።

በ2018 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ላይ ጥሩ ዉጤት ለማስመዘገብ በትጋት እየሰሩ መሆናቸዉን በገደብ ወረዳ የባንቆ ጎቲት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ገለጹ‎‎ዲላ ፦...
10/06/2026

በ2018 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ላይ ጥሩ ዉጤት ለማስመዘገብ በትጋት እየሰሩ መሆናቸዉን በገደብ ወረዳ የባንቆ ጎቲት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ገለጹ

‎ዲላ ፦ ሰኔ 03/2018 ዓ/ም ( ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

‎በ2018 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ላይ ጥሩ ዉጤት ለማስመዘገብ በትጋት እየሰሩ መሆናቸዉን በገደብ ወረዳ የባንቆ ጎቲት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ገልጸዋል ።

‎በብሔራዊ ፈተና ላይ የተሻለ ውጤት ለማስመዘገብ የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወኑ መቆየታቸውን ትምህርት ቤቱ አስታዉቋል ።

‎በፊት የነበራቸዉን ክፍተቶችን ለመሙላት በ2018 የትምህርት ዘመን ለሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ልዩ ዝግጅት ማድረጋቸዉን የትምህርት ቤቱ ተፈታኝ ተማሪዎች ተናግረዋል ።

‎በፈተና ጥሩ ዉጤት ለማስመዘገብ ትምህርት ቤቱ ባዘጋጀዉ ማጠናከሪያ ትምህርቶችና በግል ጥረት ታግዞ እየተዘጋጅ መሆናቸዉን ነዉ የገለፁት ።

‎ከባለፈዉ አመት በተሻለ ተማሪዎችን ለማሳለፍ የፈተና ሺቶችን በትጋት እየሰሩ መሆናቸዉን የተናገሩት የትምህርት ቤቱ መምህራን ተማሪዎቹ ዉጤታማ እንዲሆኑ የቻልነውን ሁሉ እያደረግነዉ ብለዋል ።

‎ተማሪዎቹ የቀሩት ጥቂት ጊዜያት በጥናትና ጥያቄዎችን በመስራት ማሳለፍ አለባቸዉ ስሉም መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል ።

‎እንደ ትምህርት ቤት ከዚህ በፊት የነበሩ ክፍተቶችን ለመሙላት ለተማሪዎች የተሻለ የጥናት ወረቀቶችን በማዘጋጀትና መምህራን በእቅዳቸዉ መነሻ በጊዜ መማሪያ መፅሕፍትን አጠናቀው የባለፈው አመት የፈተና ወረቀቶችን በመስራት ለብሔራዊ ፈተና የተሻለ ዝግጅት እንዳደረጉ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ተናግረዋል ።

‎ባደረጉት ዝግጅት መነሻ በዘንድሮ የትምህርት ዘመን የተሻለ ዉጤት ለማስመዘገብ ተግተው እየሠሩ መቆየታቸውን ርዕሰ መምህሩ አክለዋል ።

‎በበረከት ጅግሶ
‎ፎቶ ፦ ሄኖክ ሽፈራው

‎ይህንንና ሌሎችን ዘገባዎች ለመከታተል በነዝህ ድህረ ገጾች ይከታተላሉ
‎ ዩቱብ https://youtube.com/?feature=shared

‎ቴሌግራም https://t.me/gedeotvofficial

‎ቲክቶክ https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-96GXGnq7yeD

ክልላዊ ፈተና ድህንነት በተጠበቀ መልኩ ከመስጠት ባሻገር ለፈተናው ምቹ አካባቢ መፍጠር ያስፈልጋል ፦ ዝናቡ ወልዴ ( ዶ/ር )‎‎ዲላ ፦ ሰኔ 3/2018 ዓ/ም ( ጌዴኦ ቴሌቪዥን )‎‎ክልላዊ ...
10/06/2026

ክልላዊ ፈተና ድህንነት በተጠበቀ መልኩ ከመስጠት ባሻገር ለፈተናው ምቹ አካባቢ መፍጠር ያስፈልጋል ፦ ዝናቡ ወልዴ ( ዶ/ር )

‎ዲላ ፦ ሰኔ 3/2018 ዓ/ም ( ጌዴኦ ቴሌቪዥን )

‎ክልላዊ ፈተና ድህንነት በተጠበቀ መልኩ ከመስጠት ባሻገር ለፈተናው ምቹ አካባቢ መፍጠር እንደሚያስፈልግ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ ( ዶ/ር ) ገልጸዋል ።

‎በጌዴኦ ዞን በክልል ደረጃ በሚሰጠው የ6ኛ እኛ የ8ኛ ክፍል ፈተና ማስፈፀሚያ ዕቅድ ላይ ውይይት በመካሄድ ላይ ነው ።

‎በ2018 ትምህርት ዘመን ለ6ኛ እኛ ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በሚሰጠው ክልላዊ ፈተና የማስፈፀሚያ እቅድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶክተር ዝናቡ ወልዴ በተገኙበት በዲላ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል ።

‎በዞኑ በ2018 ትምህርት ዘመን 15 ሺህ 556 የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች እንዲሁም 9 ሺህ 555 ደግሞ የስምንተኛ ክፍል ተፈታኞች መሆናቸውን ነው የተገለጸው ።

‎በዞኑ በተያዘው 2018 ትምህርት ዘመን ክልላዊም ሆነ ሀገራዊ ፈተና በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ስሰራ መቆየቱን የጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዘማች ክፍሌ ጠቅሰዋል።

‎በክልላዊ ፈተና ከኩረጃ የፀዳ እንዲሆን ለማስቻል በተያዘው ትምህርት ዘመን ለተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት ስሰጥ መቆየቱን ኃላፊው ገልጸዋል ።

‎በመድረኩም በዞኑ የሁሉም መዋቅሮች የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል ።

‎በማሙሽ ኢሳያስ
‎ፎቶ ፦ ብሩክ ተስፋዬ

‎ይህንንና ሌሎችን ዘገባዎች ለመከታተል በነዝህ ድህረ ገጾች ይከታተላሉ
‎ ዩቱብ https://youtube.com/?feature=shared

‎ቴሌግራም https://t.me/gedeotvofficial

‎ቲክቶክ https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-96GXGnq7yeD


‎ለአየር ንብረት ለውጥ ጥበቃ ተገቢው እርምጃ ካልተወሰደ ዓለማችን አስከፊ አደጋ ልያጋጥማት እንደምችል ተገለፀ ‎‎ዲላ:- ሰኔ 3/2018 ዓ.ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)‎‎ለአየር ንብረት ለውጥ ጥበቃ...
10/06/2026

‎ለአየር ንብረት ለውጥ ጥበቃ ተገቢው እርምጃ ካልተወሰደ ዓለማችን አስከፊ አደጋ ልያጋጥማት እንደምችል ተገለፀ

‎ዲላ:- ሰኔ 3/2018 ዓ.ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

‎ለአየር ንብረት ለውጥ ጥበቃ ተገቢው እርምጃ ካልተወሰደ ዓለማችን አስከፊ አደጋ ልያጋጥማት እንደምችል የተገለጸው የ2018 ዓለምአቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ቀን በዲላ ከተማ ስከበር ነው።

የመልዕክቱ ‎ዋናው ዓላማውም የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ የሚያስከትለውን ጉዳት ህዝቡ ባለመገንዘብ እየደረሰ ካለው ጥፋት የራሱን የማስተካከያ የአጸፋ እርምጃ እንድወስድ ለማስቻል እንደሆነም ነው የተመላከተው።

ዕለቱ ስከበር ‎ሰዎች ለአካባቢ ፣ ለደን ጥበቃ፣ ለውሃ እና አየር ንፅህና ከመገንዘብ ባለፈ ወደ ተግባር እንድገቡ ለማስቻል ያለመ ነው ተብሏል።

‎የደን እና የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራ ከባቢ አየር እንድሁም የመሬት መራቆት እና በረሃማነትን በመከለል ምቹ ስነምህዳር ከመፍጠር ዋነኛ ሞቶር እንደሆነ የተናገሩት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) ናቸው።

‎በከተሞች ከኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ ተገቢው የኬሚካል ማስወገጃ ሁኔታን ያለመከተል ችግር እና በማህበረሰቡ ዘንድ ዘመናዊነትን ያልተከተለ የቆሻሻ አወጋገድ ስረዓት የሚስተዋል በመሆኑ በዓለማችን እየተፈጠረ ያለውን ችግር በመገንዘብ አሰፈላጊ ጥንቃቄ ለአካባቢ ጥበቃ እንድደረግ ጠይቀዋል ዋና አስተዳዳሪው።

‎የዲላ ከተማ ከንቲባ መስፍን ደምሴ(ዶ/ር) ጽዳት እና ውቤትን ባህል በማድረግ ከብክለት የጸዳ አካባቢን ፣የደንና የብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ስራ የመንግስት ተቋማትና ዜጎች በልዩ እይታ ተገቢውን እንክብካቤ እንድያደረጉ እየተሰራ መሆኑን በመግለጽ በታዳሽ ኃይል የታገዘ የኃይል አጠቃቀም ተግባራዊ እንድደረግ እየተሰራ እንደሆነ አንስተዋል ።።

‎ ለሰው ልጅና ለብዝሀ ሕይወት የተሻለ ጥበቃን በማድረግ አስተማማኝ ሀገርን መገንባት ልዩ ትኩረት የሚሻው ጉዳይ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ከልል የአካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቴ ግጄ ናቸው ።

‎የካረቤን ልቀትን በመቀነስ ታዳሽ ኃይልን በመጠቀም ፣የደን ጭፍጨፋና የአየር ንብረት ለውጥ በዓለም ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደሩ በመሆናቸው ህብረተሰቡ አካባቢን በመንከባከብ ተፈጥሮን ለትውልድ የማስቀጠል ጉዳይ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት እንደሆነም አሳስበዋል።

‎የአካባቢ ብክለት ለሁሉ ዓቀፍ ጉዳት የሚዳርግ በመሆኑ ብክለትን ለመከላከልና ምድርን ለትውልድ ለመጠበቅ ዘላቂ አሰራር፣ የህብረተሰቡ ግንዛቤ እና ህጋዊ አሰራሮችን በመዘርጋት ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ እንደሚገባ ነው በመድረኩ የተገለጸው።


‎ዘጋቢ ይልማ አበበ
‎ፎቶግራፍ ፦ሄኖክ ሽፈራው

10/06/2026

በምክክር ሀገር እናፅና!!
ምክክርን ባህል እናድርግ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን!!

"ምድራችንን ለማዳን አሁኑኑ እርምጃ እንውሰድ '' የሚል መሪ ሀሳብ ያነገበው የዜንድሮ የአለም አከባቢ ጥበቃ ቀን በተለያዩ ኩኔቶች ለማክበር ያለመ መርሃግብር በዲላ ከተማ ልጀመር ነው‎‎ዲላ:...
10/06/2026

"ምድራችንን ለማዳን አሁኑኑ እርምጃ እንውሰድ '' የሚል መሪ ሀሳብ ያነገበው የዜንድሮ የአለም አከባቢ ጥበቃ ቀን በተለያዩ ኩኔቶች ለማክበር ያለመ መርሃግብር በዲላ ከተማ ልጀመር ነው

‎ዲላ:- ሰኔ 3/2018 ዓ.ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

"‎ምድራችንን ለማዳን አሁኑኑ እርምጃ እንውሰድ '' የሚል መሪ ሀሳብ ያነገበው የዜንድሮ የአለም አከባቢ ጥበቃ ቀን በተለያዩ ኩኔቶች ለማክበር ያለመ መርሃግብር በዲላ ከተማ ልጀመር ነው።

‎የአለም አካባቢ ጥበቃ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲከበር፣ አካባቢን ከብክለትና ከደን ጭፍጨፋ ለመታደግ የሁሉም ዜጎች ተሳትፎና ትብብር አስፈላጊ ‎እንደሆነ በመገንዘብ ስሆን ሀገራችን ኢትዮጵያ ለ33ኛ ጊዜ እያከበረች ትገኛለች ።

‎በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስተባባሪነት በየዓመቱ እኤአ ሰኔ ወር ላይ የሚከበረው የአለምአቀፍ የአካባቢ ቀን ( World Environment Day) በዲላ ከተማ በመካሄድ ላይ የሚገኝ ስሆን በአረንጓዴ አሻራ እና በጽዳት ስራ የተለያዩ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛል ።

ከማለዳው 12፡30 ጀምሮ በከተማዋ እየተካሄደ የሚገኘው የጽዳት እና የችግኝ ተከላ መርሃግብር ህብረተሰቡ በአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ላይ ተገቢውን እርምጃ መወሰድ እንድጀምር ለማስቻል ያለመ ነውም ተብለዋል።

‎መርሃግብሩ ክልል አቀፍ እንደሆነም የተገለፀ ስሆን የቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ባህልን ማጠናከር ለችግሮቹ ከሚወሰዱ መፍትሔዎች መካከል ናቸው።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የዲላ ክላስተር አስተባባሪ ዶ/ር መርሁን ፍቅሩ ፣የዲላ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር መስፍን ደምሴ እንድሁም የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ እና
‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የአካባቢ ጥበቃና የአየር ለውጥ ባለስልጣን አቶ ግዛቴ ጊጄን ጨምሮ የዲላ ከተማ ነዋሪዎች እና የክልሉ የዲላ ክላስተር ተቋማት ሰራተኞችና ኃላፍዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል ።

‎ዛሬ የሚተከለው ዛፍ፣ በምጠብቀው ውሃ እና ከብክለት በጸዳ አለም የነገን ትውልድ መታደግ እንድቻልም ጭምር ታስቦ እየተከናወነ የሚገኝ ነው ተብለዋል ፡፡

‎2018 ወይም 2026 የአለም አቀፍ የአካባቢ ቀን!

‎ይልማ አበበ
‎ፎቶግራፍ ፦ሄኖክ ሽፈራው






Address

Gedeo
Dila
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gedeo TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share