10/06/2026
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፍዎች ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዲላ ከተማ ገቡ
ዲላ ፦ ሴነ 03/2018 ዓ.ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)
በነገው ዕለት የሚመረቀውን የዲላ ከተማ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ህንፃ ምክኒያት በማድረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ዲላ ከተማ ገብተዋል።
በሀገር በቀል ዕሳቤ የተጀመረው መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት በክልሉ ከተሞች ተመርቀው አገልግሎት ወደ መስጠት እየገቡ ሲሆን በቅርቡም የአርባምንጭ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል።
በነገው ዕለትም የሚመረቀው የዲላ ከተማ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የበርካታ ተገልጋይ ህብረተሰብ የአገልግሎት የሚያሳልጥና በተገልጋይ ዕርካታ አይነተኛ ሚና እንደሚኖረው ይታመናል።
በአብነት አበበ
ፎቶ ፦ሔኖክ ሽፈራው