Gedeo TV

Gedeo TV ይህ የጌዴኦ ቴሌቪዥን ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው። ገፁን ላይክ ፣ ሼርና ኮሜንት በማድረግ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን በየዕለቱ ይከታተሉ! t.me/gedeotvofficial
(1)

በጌዴኦ ዞን ላለፉት ሁለት ቀናት ስካሄድ የቆየው የ2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ እና የአመራር ምዘና መድረክ ተጠናቋልዲላ ፦ ነሐሴ 6/2018 ዓ/ም(ጌዴ...
12/08/2026

በጌዴኦ ዞን ላለፉት ሁለት ቀናት ስካሄድ የቆየው የ2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ እና የአመራር ምዘና መድረክ ተጠናቋል

ዲላ ፦ ነሐሴ 6/2018 ዓ/ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

በጌዴኦ ዞን ላለፉት ሁለት ቀናት ስካሄድ የቆየው የ2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ እና የአመራር ምዘና መድረክ ተጠናቋል።

ያሳለፍነው በጀት ዓመት ትልቅ ሀገራዊ ተልዕኮ የተሳካበት ከመሆኑም ባለፍ በምርጫው ፓርቲያችን የበላይነትን የተጎናጸፈበት እንደመሆኑ የተገኘውን ‎የህዝብ አመኔታ ማስቀጠል ህዝቡ ለፓርቲው ያሳየውን ከፍተኛ ቁርጠኝነት እና አጋርነት እንደ ትልቅ ጥንካሬ በመውሰድ ይህንኑ ወጥ በሆነ መልኩ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ መግባባት ተፈጥሯል።

‎በየተቋሙ የተመዘገቡ በጎ ተግባራቶችን እና መልካም የአሰራር ልምዶችን የራሳችን በማድረግ ለቀጣይ ስራዎች መነሻ ግበዓቶቻችን ማድረግ መውሰድ እንደሚያስፈልግም በመድረኩ በአጽንኦት ተነስቷል።

‎​አሁን ያለንበት ወቅት የዝግጅት ምዕራፍ በመሆኑ፣ እያንዳንዱ ተቋም ግልጽ፣ የሚጨበጥ እና ጥራት ያለው ዕቅድ ለማዘጋጀት ከመድረኩ የተገኙ ነጥቦች ግብዓት ሆኖ እንደሚያገለግል ነው መግባባት የተቻለው።

‎​በፓርቲ እይታ ተጨማሪ የተካተቱ ስትራቴጂካዊ ነጥቦች
‎​የአመራሩ የፖለቲካዊ ዝግጁነት የዝግጅት ምዕራፉን በብቃት ለመወጣት አመራሩ በፖለቲካዊ አስተሳሰብ እና በህዝባዊ ወገንተኝነት ሙሉ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

‎​በተቋማት መካከል የሚኖረውን ቅንጅት በማጠናከር፣ የፓርቲውን ራዕይና ግብ በተሳለጠ መልኩ ወደ መሬት ማውረድ እንዲሁም በመዋቅሮች ወጥነት ያለውን አፈጻጸም በማስፈን የተፈለገ ውጤት እንዲመዘገብ አመራሩ ሚናውን መወጣት እንዳለበት በቁርጠኝነት ተወስዷል።

‎​የተዘጋጁ ዕቅዶችን ወደ ተግባር በሚቀየሩበት ወቅት ህዝባዊ ጥያቄዎችን በፍጥነት እና በጥራት ለመመለስ የሚያስችል የክትትልና ግምገማ ስርዓት በመዘርጋት እስትራቴጂካዊ ራዕይ እንዲሳካ መስራት ቀዳሚ አጀንዳ እንደሚሆንም በመድረኩ ተደምድሟል።

በተቀመጠ ግብ መሠረት የተሳካ የአመራር ምዘና የተካሄደ ሲሆን መርህንና ተግባርን ብቻ መሠረት ባደረገ መልኩ በአመቱ አፈጻጸም መነሻ የተደረገ ምዘና ሲሆን በተዋረድ በሚገኙ መዋቅሮችም ተመሳሳይ ሂደት ያለው መድረክ እንዲካሄድ አስፈላጊ ማስፈጸሚያ ሰነድ ተዘጋጅቶ ወርዷል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሀልጌዮ ጅሎ የዲላ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የስራ እንቅስቃሴ ጎበኙ‎‎ዲላ ፦ ነሐሴ  6/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቴለቪዥን )...
12/08/2026

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሀልጌዮ ጅሎ የዲላ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት የስራ እንቅስቃሴ ጎበኙ

‎ዲላ ፦ ነሐሴ 6/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቴለቪዥን )

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሀልጌዮ ጅሎ የዲላ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የስራ እንቅስቃሴ ጉብኝት አድርገዋል ።

‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ታልሞ ከተቋቋሙት የመሶብ አንድ ማዕከላት መካከል በቅርቡ ወደ ስራ የገባው የዲላ ማዕከል አንዱ ነው ።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሀልጌዮ ጅሎ ተቋሙ ስራውን ከጀመረ ወዲህ ያለውን ሂደት ተዘዋውረው ጎብኝቷል ።

‎በጉብኝታቸውም በተቋሙ ያለውን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ የተመለከቱ ሲሆን ማዕከሉ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለተገልጋዩ በሚሰጠው አገልግሎቶች ዙሪያ ከባለሙያዎችና ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርገዋል ።

‎በክልሉ ሥራ የጀመሩ ዲላ ፣ አርባምንጭ እና ወላይታ ሶዶ የመሶብ አንድ አገልግሎት ማዕከላት ላይ የተገልጋይ ዕርካታው 99 ከመቶ መድረሱን ያነሱት ኮሚሽነሩ ለዲላ ማዕከል ስራውን አቀናጅቶ ውጤታማ ለማድረግ ስራ አስኪያጅ መመደቡ በቀጣይ አገልግሎቱንም ለማስፋት ያለመ ነው ብለዋል ።

‎በዲላ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከሚሰጠው ስምንት የአገልግሎት ተቋማት መካከል የንግድ ባንክ ፣ ኢምግሬሽን ፣ ገቢዎች እና ንግድና ኢንዱስትሪ ይገኙ በታል ።

‎የህዝብን አገልግሎት ለማርካት መንግስት ዲጂታል የአገልግሎት አሰጣጥ ዕውን እንድሆን እየሰራ መሆኑን የተናገሩት የማዕከሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ረድኤት ክፍሌ ማዕከሉ በ2 ወር 2 ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች አገልግሎት መስጠቱን አስረድተዋል ።

‎በቀጣይም የሌሎችን ተቋማት አገልግሎት ወደ ማዕከሉ
‎ለማምጣት እየተሰራ ይገኛልም አስኪያጁ ብለዋል ።

‎የገቢዎች ሰራተኛ የሆኑ ወ/ሮ ወይንሸት በቀለ ቀደም ስል በማኑዋል አሰራር የተገልጋዮች የመረጃ አደረጃጀትና በተራ የማስተናገዱ ሁኔታዎች አጨቃጫቂ እንደነበሩ በማንሳት የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎቱ ይህንን በማስቀረት በተሰጠው ደቂቃ ሰራው እንዲጠናቀቅ በማስቻል በአገልጋይ እና ተገልጋይ መካከል መተማመን የፈጠረ እንደሆነ አብራርተዋል ።

‎በትስስር የተለያዩ ተቋማት ስራዎቻቸውን ዜጎች ያለ እንግልት በዲጂታል የታገዘ ቀልጣፋ አገልግሎት እያገኙ መሆናቸውን ተገልጋዮች ተናግረዋል ።

‎በማዕከሉ ከነበሩት ተገልጋዮች መካከል ወ/ሮ ምህረት አህመድ እና ወ/ሮ ማርታ መምህሩ በዲጂታል የታገዘው የማዕከሉ አገልግሎት ከጊዜና ወጪ ብክነት እንደታደጋቸው ጠቁመዋል ።

‎ምቹ ሁኔታን ከመፍጠር ረገድ የህጻናት ማቆያ ጭምር መዘጋጀቱን የገለጹት ተገልጋዮቹ የዜጎችን ዕርካታ የሚያረጋግጥ አገልግሎት እንደሆነም አስረድተዋል ።

‎በይልማ አበበ
‎ፎቶ ፦እስራኤል አድማሱ


‎ይህንንና ሌሎችን ዘገባዎች ለመከታተል በነዚህ ድህረ ገጾች ይከታተላሉ
‎ ዩቱብ https://youtube.com/?feature=shared

‎ቴሌግራም https://t.me/gedeotvofficial

‎ቲክቶክ https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-96GXGnq7yeD




ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት የልዩ ልዩ የስፖርት ሻምፒዮና ማካሄድ ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑ ተገለፀ‎ዲላ፦ ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም ( ጌዴኦ ቴሌቪዥን)በጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ የክረምት እ...
11/08/2026

ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት የልዩ ልዩ የስፖርት ሻምፒዮና ማካሄድ ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑ ተገለፀ

‎ዲላ፦ ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም ( ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

በጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ የክረምት እግር ኳስ ስፖርት ሻምፒዮና የመክፈቻ መረሃ ግብር ተደርጓል።

በውድድሩ በተለያዩ ሻምፒዮና የሚሳተፉ ስፖርተኞችን ከመምረጥ ባለፈ በቡድን ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ተተኪዎችን ለማፍራት እየተሠራ መሆኑን ተመላክቷል።

የዲላ ዙሪያ ወረዳ ባህልና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ተመስገን ሽፈራዉ እንደገለፁት በእግር ኳስ ወረዳን የሚወክሉ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማግኘት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።

ውድድሩ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማግኘት ካለው ፋይዳ በተጨማሪ የህዝብ ለሕዝብ ትስስር ለማጠናከር እንደሚረዳ ኃላፊው ገልፀዋል።

በውድድሩ ይሳተፋሉ ተብሎ ከታቀዱ 14 ቀበሌያት መካከል 9 ቀበሌያት ብቻ መሳተፋቸውን የጠቆሙት ኃላፊው፣ ውድድሩም በቀጣይ ከዞን አልፎ በክልል ደረጃ ለሚዘጋጀው ውድድሮች ብቁ ተወዳዳሪዎችን ለማቅረብ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።

ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት የልዩ ልዩ የስፖርት ሻምፒዮና ማካሄድ ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑን አቶ ተመስገን ገልፀዋል።

በወረዳው ባህልና ስፖርት ጽ/ቤት ትምህርትና ሥልጠና ሥራ ሂደት ሥራ አስተባባሪ አቶ ተመስገን ደጎማ፣ በወረዳው በሎጂስቲክ እጥረት ምክንያት ሁሉንም ቀበሌ ማሳተፍ አለመቻሉን ጠቁመው በቀጣይ ውድድር ዘመን ይህ ችግር እንዳይደገም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ አስረድተዋል።

በጽ/ቤቱ የስፖርት ማዘወተሪያና ማስፋፊያ ባለሙያ ወ/ሮ ክብነሽ ወጠሾ በወረዳው ያሉ የስፖርት ማዘወተሪያ ችግር በመቋቋም ባሉ ውስን ቦታዎች ላይ ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራት ጥረት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።

የውድድሩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ውድድሩ አልባሌ ቦታ ከማሳለፍ ጊዘያቸውን በአግባቡ በመጠቀም የተሻለ ብቃት እንዲያሳዩ እንደረዳቸው ገልፀዋል።

ዘጋቢ፦ በረከት ጅግሶ
‎ፎቶግራፍ፦ ባምላኩ ተፈራ

ይህንንና ሌሎችን ዘገባዎች ለመከታተል በነዚህ ድህረ ገጾች ይከታተላሉ
‎ ዩቱብ https://youtube.com/?feature=shared

‎ቴሌግራም https://t.me/gedeotvofficial

‎ቲክቶክ https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-96GXGnq7yeD

የሃይማኖት ጉዳዮች እና የሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ተመካካሪዎች ባቀረቧቸው ምክረ ሃሳቦቻቸው መግባባት ላይ ደረሱነሐሴ 5/2018 ዓ.ምየኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8/2018 ዓ....
11/08/2026

የሃይማኖት ጉዳዮች እና የሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ተመካካሪዎች ባቀረቧቸው ምክረ ሃሳቦቻቸው መግባባት ላይ ደረሱ

ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8/2018 ዓ.ም ጀምሮ እያካሄደ ባለው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በኮሚሽኑ ምክር ቤት በተለዩ ስምንት አጀንዳዎች ላይ ምክክር እየተደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡

አጀንዳዎቹ 500 አባላት ባሏቸው ስምንት የስራ ቡድኖች ምክክር እየተደረገባቸው ይገኛሉ፡፡ በኮሚሽኑ የአሰራር ሥነ-ዘዴ መሰረት 500 አባላት ያሉት አንድ ቡድን በአንድ አጀንዳ ላይ እየተመካካረ ይገኛል፡፡

በዚህም በሃይማኖት ጉዳዮች እና በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ለይ ሲመካካሩ የቆዩት ሁለት ቡድኖች ዛሬ ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም በተጠናቀሩ ምክረ ሃሳቦቻቸው ላይ ተስማማተው በተዘጋጀው ቃለ ጉባኤ ላይ ተፈራርመዋል፡፡

የሌሎች አጀንዳዎች ተመካካሪዎችም በቀጣይ ቀናት በተመሳሳይ መልኩ የአጀንዳ ሃሳቦቻቸውን የጋራ አድርገው በቃለ ጉባኤዎቻቸው ላይ በመፈራረም እንደሚስማሙ ይጠበቃል፡፡

የዲላ ዩኒቨርስቲ የመማር ማስተማር ስራን ከቴክኖሎጂው ጋር በማስተሳሰር ብቁ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት ተግተው እየሠራ መሆኑን ገለጸ‎‎ዲላ፦ ነሐሴ 05/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)‎‎ይህም ...
11/08/2026

የዲላ ዩኒቨርስቲ የመማር ማስተማር ስራን ከቴክኖሎጂው ጋር በማስተሳሰር ብቁ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት ተግተው እየሠራ መሆኑን ገለጸ

‎ዲላ፦ ነሐሴ 05/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

‎ይህም የተገለጸው ዩኒቨርሲቲው የ2018 ዓ/ም የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 ዓ/ም ዕቅድ ዙሪያ ውይይት ባካሄደበት ወቅት ነው ።

‎በውይይቱ የዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ዘርፎች ኃላፊዎች በ2018 ዓ/ም የተከናወኑ ሥራዎችን፣ የተገኙ ውጤቶችን፣ ያጋጠሙ ችግሮችንና በቀጣይ ሊከናወኑ የታቀዱ ተግባራትን በሪፖርት አቅርበዋል ።

‎የዲላ ዩኒቨርስቲ የማስተማሪያና የህክምና ሆስፒታል በፍጥነት ተጠናቆ ስራ ይጀምራል ያሉት የዲላ ዩኒቨርስቲ ፕረዚዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) ሁሉንም አገልግሎቶች ከወረቀት ነፃ ለማድረግ የዲጅታላይዜሽን ስራ ተጠናክሮ ይሰራል ብለዋል ።

‎በዩኒቨርስቲው የመማር ማስተማር ስራ ከቴክኖሎጂው ጋር በማስተሳሰር ብቁ ዜጋን ለማፍራት ተግቶ እንደሚሰራ አክለዋል ።

‎የዲላ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕረዚዳንት ታምራት በየነ ( ዶ/ር ) በ2018 ዓ/ም በዓለም አቀፍና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተለያዩ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ በመማር ማስተማር ዘርፍ የተሻለ የሥራ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል ።

‎በመደበኛ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከ90 በመቶ በላይ ተማሪዎች ማለፍ መቻላቸውን የጠቆሙት ዶክተር ታምራት ፣ የተማሪዎች ፈተና ከወረቀት ነጻ ሆኖ በበይነ መረብ እንዲካሄድ ሰፊ ሥራዎች መሰራታቸውንም አስታውቀዋል ።

‎በተጨማሪም የድህረ ምረቃና የዶክትሬት ፕሮግራሞችን የማጽደቅና የትምህርት ፕሮግራሞችን እውቅና የማሰጠት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል ።

‎የዲላ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር እና ልማት ምክትል ፕረዚዳንት ማቴዎስ ሀብተ ( ዶ/ር ) በ2018 ዓ/ም ዩኒቨርሲቲው ዲጂታል ኢትዮጵያን ከማሳካት አንጻር የተለያዩ ዕቅዶችን በመንደፍ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡን ገልጸዋል።

‎በውሃ አቅርቦት ረገድም ከዲላ ከተማ ውሃ ልማት ጋር በመቀናጀት ችግሩን ለመቅረፍ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመው ፣ መማሪያ ክፍሎችን ከማዘመን አንጻር ሰፊ ሥራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል ።

‎የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ግንዛቤ እጥረት ግን በዩኒቨርሲቲው ከገጠሙ ተግዳሮቶች መካከል አንዱ መሆኑን ማቴዎስ (ዶ/ር ) ገልጸዋል።

‎በሌላ በኩል የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሕክምና ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ትዝአለኝ በ2018 ዓ.ም. ሆስፒታሉ በሀገር አቀፍና በአፍሪካ ደረጃ እውቅና ማግኘቱን ገልጸዋል።

‎ሆስፒታሉ በመድኃኒት አቅርቦትና በአጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ያስመዘገባቸው ውጤቶች በመኖራቸው የእውቅና ሰርተፊኬትና ዋንጫ ሽልማት ማግኘቱን አስታውቀዋል ።

‎በክረምት ወቅትም ለሕብረተሰቡ ነጻ የምርመራና የሕክምና አገልግሎት መሰጠቱን ገልጸው እንዲሁም በሆስፒታሉ የዲጂታል ሥርዓት አጠቃቀምን ለማስፋፋት ሥራዎች መከናወናቸውን፣ በወረቀት ይከናወኑ የነበሩ ሥራዎችም በኮምፒውተር እንዲከናወኑ መደረጉንም ጠቁመዋል።

‎የ2019 ዓ/ም ዋና ዕቅድ ደግሞ በመጠናቀቅ ላይ ለሚገኘው የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ሕክምና ሆስፒታል አስፈላጊ የሕክምና ቁሳቁሶችን በግዢና በተለያዩ የድጋፍ አማራጮች ማሟላት መሆኑን ገልጸዋል።

‎በዚህም ሕብረተሰቡና ሌሎች ተቋማት ለሆስፒታሉ የሚያደርጉትን ትብብርና ድጋፍ እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል ።

‎በመርሃ ግብሩ የ2018 ዓ/ም የሥራ አፈጻጸም በየዘርፉ ቀርቦ የተገመገመ ሲሆን፣ የ2019 ዓ/ም ዕቅድም በቀጣይ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትና ግቦች ላይ ተመስርቶ ቀርቧል።

‎በዳኛቸው ሳሙኤል
‎ፎቶ ፦ሄኖክ ሽፈራው

‎ይህንንና ሌሎችን ዘገባዎች ለመከታተል በነዚህ ድህረ ገጾች ይከታተላሉ
‎ ዩቱብ https://youtube.com/?feature=shared

‎ቴሌግራም https://t.me/gedeotvofficial

‎ቲክቶክ https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-96GXGnq7yeD


የ 2018 የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በጌዴኦ ዞን መካሄድ ጀመረዲላ ፦ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)በጌዴኦ ዞን የ 2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመን...
11/08/2026

የ 2018 የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በጌዴኦ ዞን መካሄድ ጀመረ

ዲላ ፦ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

በጌዴኦ ዞን የ 2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ እና የአመራር ምዘና መድረክ በዲላ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

መድረኩ ባለፉት ጊዜያት የተመዘገቡ ጥንካሬዎችን ለማስፋት፣ ተሞክሮዎችን ለመቀመር እንዲሁም የተስተዋሉ ድክመቶችን ለማረም ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በዞኑ በ2018 የበጀት ዓመት በፓርቲ እና በመንግስት የተከናወኑ ተግባራትን በመፈተሽ አመራሩን ለቀጣይ ተልዕኮ የማዘጋጀት ዓላማ ያለው መድረክ እንደሆነም ተጠቁሟል።

መድረኩን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መሬት አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰብስበ ቡናቤ እና የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) በጋራ የሚመሩት ሲሆን ዞናዊ የአፈጻጸም ሪፖርት የያዘ ሰነድ የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ኢንጂነር ተመስገን ጥላሁን እያቀረቡ ይገኛሉ።

የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) እንደ ጌዴኦ ዞን በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡ ሲሆን በሀገር እና በክልል ደረጃ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን በአመለካከትና በተግባር የላቀ አፈፃፀም ያላቸዉን አመራሮች ለመፍጠር እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የግምገማ መድረኩ በፓርቲው መርህ መሠረት በበጀት ዓመቱ ሁለተኛ ግማሽ ዓመት በጥንካሬ የተለዩትን ይበልጥ ለማጠናከር፣ ጉድለት የታየባቸውን ደግሞ ለማረም ዓላማ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የ2018 በጀት ዓመት ለአጠቃላይ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የተቀመጡ መንቲያ ግቦች የተሳኩበትና በመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ረገድም አመርቂ ድሎች መመዝገባቸው ተጠቅሷል።

በተለይም በ 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የተገኘው ስኬት "ከምርጫ ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው መድረክ በጥልቀት መገምገሙ ተመላክቷል።

መድረኩ በቀጣይ በወረዳና ከተማ አስተዳደሮች በመቀጠል ኃይል የሚሰባሰብበት ሲሆን ጠንካራ አቅጣጫዎች የሚቀመጡበት መሆኑም ተመላክቷል።

በመድረኩ ከሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደሮች አስተባባሪ አካላት፣ የዞን ማዕከል አጠቃላይ አመራሮ በመሳተፍ ላይ ናቸው።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ/ም ሥራ አፈፃፀም ግምገማና  የ2019 ዓ/ም እቅድ ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ነው‎‎ዲላ፦ ነሐሴ 05/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)‎‎የዲላ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ...
11/08/2026

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ/ም ሥራ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 ዓ/ም እቅድ ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ነው

‎ዲላ፦ ነሐሴ 05/2018 ዓ/ም (ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

‎የዲላ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ/ም ሥራ አፈፃፀም ግምገማ ና የ2019 ዓ/ም.እቅድ ዙሪያ ውይይት በማካሄድ ላይ ይገኛል ።

‎ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ መማር ማስተማር ላይና በሌሎች ዘርፎች በሰራቸው ሥራዎች ዙሪያና በቀጣይ በሚተገብራቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት ዙሪያ እየመከረም ነው ።

‎በመርሃ ግብሩ በአሁን ወቅት በዩኒቨርሲቲው የተከናወኑ ተግባራት ሪፖርት እየቀረበ ሲሆን በ2018 ዓ.ም. የተከናወኑ ተግባራትን፣ የተገኙ ውጤቶችንና ያጋጠሙሙ ችግሮችን በመለየት በቀጣይ ዩኒቨርስቲው የያዛቸውን ግቦች ከግብ ለማድረስ መነሻ የሚሆኑ እቅዶች ይቀርባሉ ተብሎም ይጠበቃል።

‎በዳኛቸው ሳሙኤል
‎ፎቶ ፦ ሄኖክ ሽፈራው

‎ይህንንና ሌሎችን ዘገባዎች ለመከታተል በነዚህ ድህረ ገጾች ይከታተላሉ
‎ ዩቱብ https://youtube.com/?feature=shared

‎ቴሌግራም https://t.me/gedeotvofficial

‎ቲክቶክ https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-96GXGnq7yeD



የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) የምክክር ጉባዔውን አሁናዊ ሒደት አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-👉 በሀገራዊ ምክክር ሒደቱ ከስልታዊ...
10/08/2026

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) የምክክር ጉባዔውን አሁናዊ ሒደት አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

👉 በሀገራዊ ምክክር ሒደቱ ከስልታዊ ቡድኖች የቀረቡ የአጀንዳ ምክረ ሀሳቦች ተቀናጅተው 500 አባላት ላሏቸው 8 የስራ ቡድኖች መቅረብ ጀምረዋል።

👉 የ250 አባላት ያሏቸው ሁለት ስልታዊ ቡድኖች በአንድ አጀንዳ ላይ የተነጋገሩበትን ሀሳቦች በማጠናቀር እና በመሰነድ ለ500 አባላት ላሏቸው ቡድኖች እያቀረቡ ይገኛሉ።

👉 500 አባላት ያሏቸው ቡድኖች የቀረቡላቸውን ሀሳቦች በማዳመጥ መካተት ያለበትን እና ሊካተት የሚገባውን ሃሳብ በጥልቅ ውይይት እያዳበሩ ነው።

👉 የሥራ ሒደቱን ጨርሰው ለ500 ቡድናቸው ያቀረቡ እንዳሉ ሁሉ፣ ያላጠናቀቁት ደግሞ ስራቸውን አጠናቅቀው ሲጨርሱ ለቀጣዩ ቡድን ያስረክባሉ።

👉 የምክክር ሒደቱ የመጀመሪያ ምዕራፎች በባህሪያቸው ብዙ አለመግባባቶች፣ የስሜት ጫናዎች እና ክርክሮች የሚታዩባቸው ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

👉 አለመግባባቶች የሚፈጠሩት የራስን ምክረ ሀሳብ ወደፊት ለማስቀደም ካለው ፍላጎት እና ለዘመናት ሲጠየቁ የነበሩ የአካባቢ ጥያቄዎችን ለማንጸባረቅ ካለ እምነት የተነሳ ነው።

👉 የሰዎችን ሀሳብ መደፍጠጥ፣ ማሸማቀቅ እና ማሳፈር በስብሰባው የሥነ ምግባር ደንብ ጭራሽ የማይፈቀድ እና ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው።

👉 ወሳኝ መርሆች በሆኑት መከባበር፣ መደማመጥ እና ወደ መሀል መምጣት በነጻነት ተነጋግሮ እና ተደማምጦ ወደጋራ ሀሳብ መድረስ ይገባል።

👉 ሀገርን ማዕከል በማድረግ ከየአካባቢው ይዞ የተመጣውን ጥያቄ ብቻ ለመመለስ ሳይሆን ሀገራችን ኢትዮጵያን ማዕከል አድርጎ መንቀሳቀስ ተገቢ ነው፡፡

👉 በምክክር ሒደቱ እስካሁን ድረስ በአንድም አጀንዳ ላይ የተሰጠ ምንም አይነት ውሳኔ የለም፤ ወደፊትም ቢሆን ውሳኔ አይሰጥም።

👉 የጉባዔው ዋና ተግባር ምክረ ሀሳብ ማዘጋጀት ሲሆን፣ ከጉባዔው መጠናቀቅ በኋላ የተዘጋጁት ምክረ ሀሳቦች ለሕግ አውጪው፣ ለህግ አስፈጻሚው፣ ለሕግ ተርጓሚው እና ለሚመለከታቸው አካላት ይተላለፋሉ።

ዘገባው የኤፍ ኤም ሲ ነው።

በጌዴኦ ዞን በሁሉም አካባቢ የሰላምና ደህንነት ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠሉ ረገድ ከፍ ባለ መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል።ዲላ:- ነሐሴ 04/2018 ዓ/ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)የማህበረሰ...
10/08/2026

በጌዴኦ ዞን በሁሉም አካባቢ የሰላምና ደህንነት ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠሉ ረገድ ከፍ ባለ መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል።

ዲላ:- ነሐሴ 04/2018 ዓ/ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)

የማህበረሰቡን ሰላምና መረጋጋት በዘላቂነት ለማስቀጠል አጠቃላይ በዞኑ ያሉት የጸጥታ አካላት ወታደራዊ ትዕዛዝን በመቀበል እየፈጸሙ እንደሚገኝ ይታወቃል።

ይህንንም ሰላም የማስጠበቅ ስራን የዞኑ አጠቃላይ የጸጥታ መዋቅር እንዲሁም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ አድማ በታኝ ኃይል ጋር በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል።

ሰላምን ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ አካላትን በመለየት ህግ የማስከበር ስራን ለመስራት ሁሉም የጸጥታ አካላት ከመቼዉም ግዜ በበለጠ በቅንጅት እና በቅርበት እየተሰራ ነዉ

የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያም በዞኑ በሁሉም አካባቢ ሰላም እንዲሆን ከፍተኛ ስራን በአጽንዎት እየሰራ ሲሆን ለዚህም ተግባር የማህበረሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ እንደሆነና የህብረተሰቡን ትብብርም ተጠይቋል።

በዛሬዉ ዕለትም አጠቃላይ ጥምር የጸጥታ አካላት ጸጥታ በማስከበር ስራ ዙሪያ የስራ መመሪያ የጌዴኦ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ብሩ ማርቆስ መመሪያ ሰጥተዋል።

ይህንን ተልዕኮ የሚተገብሩ ጥምር የጸጥታ አካላትን የይርጋጨፌ ወረዳ እና የይርጋጨፌ ከተማ የፊት አመራሮች ተገኝተዉ እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት በፍቅር ተቀብለዋል።

በመጨረሻም በዞኑ በሁሉም የፖሊስ ተቋሞች የዘዉትር ሰኞ ተግባር የሆነዉ ሳምንታዊ ቡና ጠጡ ፕሮግራም በይርጋጨፌ ወረዳ እና ይርጋጨፌ ከተማ ፖሊስ አዘጋጅነት በደመቀ መልኩ ተከብሯል።
ዘገባው የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምርያ ነው።

Lame weli duuka barruwwa Dilli qachcha'n me'ate'n hedhemmaki 4xxe dowweek 29sok deettichch ya'i muuxeme'en.Dilla:- Oriit...
09/08/2026

Lame weli duuka barruwwa Dilli qachcha'n me'ate'n hedhemmaki 4xxe dowweek 29sok deettichch ya'i muuxeme'en.

Dilla:- Oriito 3/2018 G.W (Gede'o Televizhiine)

Gede'inxe zoone illicho galchallo Zinaabuu Wolde (Dr) afemmeeba lame weli duuka barruwwa Dilli qachcha'n me'ate'n hedhemmaki Gede'inxe zooneki 4xxe dowweeke 29sok deettichch ya'i muuxeme'en.

Ya'inke muuxama'ninna gede'inxe zoone'n hujenda'neexxa duuchcha hujuwwa ardi sholla garinni alfa dande'axx haarooxxi webisayite Gede'inxe zoone sayinsenna inoveshine akeeki darree'n shiqqe'en.

Saxxeexxe onde wogguwwa'a mari'eti minixxe unoole kadati ergatta'n turteexxe ardiinxe tukkanuwwa'a galateeffachchonna hooqubiink badhaasi uwweme'en.

Eerallo: Bereket Jisso
Foto: Meeroon Niguse

ይህንንና ሌሎችን ዘገባዎች ለመከታተል በነዚህ ድህረ ገጾች ይከታተላሉ
‎ ዩቱብ https://youtube.com/?feature=shared

‎ቴሌግራም https://t.me/gedeotvofficial

‎ቲክቶክ https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZS-96GXGnq7yeD

Address

Gedeo
Dila
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gedeo TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share