12/08/2026
በጌዴኦ ዞን ላለፉት ሁለት ቀናት ስካሄድ የቆየው የ2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ እና የአመራር ምዘና መድረክ ተጠናቋል
ዲላ ፦ ነሐሴ 6/2018 ዓ/ም(ጌዴኦ ቴሌቪዥን)
በጌዴኦ ዞን ላለፉት ሁለት ቀናት ስካሄድ የቆየው የ2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ እና የአመራር ምዘና መድረክ ተጠናቋል።
ያሳለፍነው በጀት ዓመት ትልቅ ሀገራዊ ተልዕኮ የተሳካበት ከመሆኑም ባለፍ በምርጫው ፓርቲያችን የበላይነትን የተጎናጸፈበት እንደመሆኑ የተገኘውን የህዝብ አመኔታ ማስቀጠል ህዝቡ ለፓርቲው ያሳየውን ከፍተኛ ቁርጠኝነት እና አጋርነት እንደ ትልቅ ጥንካሬ በመውሰድ ይህንኑ ወጥ በሆነ መልኩ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ መግባባት ተፈጥሯል።
በየተቋሙ የተመዘገቡ በጎ ተግባራቶችን እና መልካም የአሰራር ልምዶችን የራሳችን በማድረግ ለቀጣይ ስራዎች መነሻ ግበዓቶቻችን ማድረግ መውሰድ እንደሚያስፈልግም በመድረኩ በአጽንኦት ተነስቷል።
አሁን ያለንበት ወቅት የዝግጅት ምዕራፍ በመሆኑ፣ እያንዳንዱ ተቋም ግልጽ፣ የሚጨበጥ እና ጥራት ያለው ዕቅድ ለማዘጋጀት ከመድረኩ የተገኙ ነጥቦች ግብዓት ሆኖ እንደሚያገለግል ነው መግባባት የተቻለው።
በፓርቲ እይታ ተጨማሪ የተካተቱ ስትራቴጂካዊ ነጥቦች
የአመራሩ የፖለቲካዊ ዝግጁነት የዝግጅት ምዕራፉን በብቃት ለመወጣት አመራሩ በፖለቲካዊ አስተሳሰብ እና በህዝባዊ ወገንተኝነት ሙሉ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ ተጠቁሟል።
በተቋማት መካከል የሚኖረውን ቅንጅት በማጠናከር፣ የፓርቲውን ራዕይና ግብ በተሳለጠ መልኩ ወደ መሬት ማውረድ እንዲሁም በመዋቅሮች ወጥነት ያለውን አፈጻጸም በማስፈን የተፈለገ ውጤት እንዲመዘገብ አመራሩ ሚናውን መወጣት እንዳለበት በቁርጠኝነት ተወስዷል።
የተዘጋጁ ዕቅዶችን ወደ ተግባር በሚቀየሩበት ወቅት ህዝባዊ ጥያቄዎችን በፍጥነት እና በጥራት ለመመለስ የሚያስችል የክትትልና ግምገማ ስርዓት በመዘርጋት እስትራቴጂካዊ ራዕይ እንዲሳካ መስራት ቀዳሚ አጀንዳ እንደሚሆንም በመድረኩ ተደምድሟል።
በተቀመጠ ግብ መሠረት የተሳካ የአመራር ምዘና የተካሄደ ሲሆን መርህንና ተግባርን ብቻ መሠረት ባደረገ መልኩ በአመቱ አፈጻጸም መነሻ የተደረገ ምዘና ሲሆን በተዋረድ በሚገኙ መዋቅሮችም ተመሳሳይ ሂደት ያለው መድረክ እንዲካሄድ አስፈላጊ ማስፈጸሚያ ሰነድ ተዘጋጅቶ ወርዷል።