31/10/2025
ሞተ ተብሎ የለቅሶ ፕሮግራም እየተደረገ ባለበት አለሁ ብሎ ደወለ
አክሊሉ ሊሰንሶ ይበላል በደምቦያ ወረዳ የሄጎ ቀበሌ ተወላጅ ሲሆን ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ መንገድ ወጥቶ ነበር እና የጉዞው ደላላ መንገድ ላይ በወባ በሽታ መታመሙንና በበሽታው መሞቱን ከባድ የሀዘን መርዶ ለቤተሰቦቹ ያረዳል።
ቤተሰቦቹም ሀዘናቸው ከፍተኛ ሆኖ በጣም አዝነው እራሳቸውን ጎድተው በለቅሶ ስነስርዓት ሦስት ቀን ተቀምጠው ሦስተኛው ቀን ላይ የቀብር ስነስርዓት ለመፈጸም አስከሬን ስላልመጣ በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ሆነው የለቅሶ ስነ-ስርዓት ዘመድ አዝማድ በተገኙበት እየተከናወነ እያለ ስልክ ከደቡብ አፍሪካ ካሉ ወንድሞቹ ይደወላል በዚያው ስልክም ወንድማቸው በህይወት መኖሩን ያረጋግጣሉ።
ቤተሰብም ለማመን የልጁን የዛምቢያ ስልክ ወስደው ደውለው እራሱን በአካል አግኝተው የነበረው የለቅሶ ፕሮግራም ወደ ሰርግ የነበረው ሀዘን ወደ ደስታ ተቀይሯል እና እንኳን ደስ አላችሁ ቤተሰቦች እኛም ሞታ ስባል ሀዘናችንን ገልፀን ነበር አሁን ደግሞ የደስታ ብስራት ማድረስ ያስፈልጋል እና እንኳን ደስ አለን አላችሁ!!!
የናንተም ሞተ የተባለው እንዲህ ህይወት ያግኝ!!
አለቀ በተባለው ይድረስላችሁ!!
ሀዘናችሁ በደስታ ይቀየር!!
እግዚአብሔር ስለሁሉ የተመሰገነ ይሁን !