Kembata TV

Kembata TV "በሁሉም፤ ከሁሉም ተመራጭ!!"

 የከምባታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ተመስገን አማረ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 10ሺ ብር አበርክተዋል። ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻች...
26/06/2025


የከምባታ ዞን ፕላንና ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ተመስገን አማረ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 10ሺ ብር አበርክተዋል።

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

------------------
በተጨማሪም

በቴሌግራም: https://t.me/KembataTelevision

በፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/161AHqus1c/

በዩቱብ: https://youtube.com/?si=8XWuS98JRIlvDDrgg
ይከታተሉን።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በፍራፍሬ ልማት ኢኒሼቲቭ ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧልበማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው የ30-40-30 የተቀናጀ የፍራፍሬ ልማ...
26/06/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በፍራፍሬ ልማት ኢኒሼቲቭ ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቧል

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው የ30-40-30 የተቀናጀ የፍራፍሬ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ ተግባራት ተከናውኗል አለ የክልሉ ግብርና ቢሮ።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ አቶ ኡስማን ሱሩር ኢኒሼቲቩ ለኅብረተሰቡ በተለይም ለወጣቶች ሰርተው የሚለወጡበትን እድል በመፍጠር ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል።

በኢንሼቲቩ ሦስት ጉዳዮችን ትኩረት አድርገን ሥራውን ጀምረናል ያሉት አቶ ኡስማን እነዚህም የምግብና ምግብ ዋስትናን በቤተሰብ ደረጃ ማረጋገጥ፣ የገቢ ምርትን በመተካት ለኢንዱስትሪ ግብዓት ማቅረብ እንዲሁም በሒደት የወጪ ምርትን ማሳደግ መሆናቸውን አብራርተዋል።

በዚህም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ማንጎ ፍራፍሬዎች በክልሉ በሚገኙ 53 ወረዳዎች እንደየአካባቢው አየር ሁኔታ መብቀል የሚችሉበትን ቦታዎች የመለየት ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡

በተሰራው ሥራም 44 አቮካዶ፣ 24 ፓፓያ፣ 16 አፕል፣ 40 ማንጎ እና 32 ሙዝ ማምረት የሚችሉ ወረዳዎችን መለየት መቻሉን አስረድተዋል።

በዚህም ፍራፍሬዎቹን አምርተው በማያውቁ አካባቢዎች ጭምር ሀሳቡን በመተግበር በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎች አምርተው መጠቀም፣ የተፈጠረውን ፍላጎት መነሻ በማድረግ ችግኞችን አብዝቶ በመሸጥ የሥራ ዕድል መፍጠር መቻሉን አስረድተዋል፡፡

ኢኒሼቲቩ በአካባቢዎቹ አዲስ ዕይታ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ የአመራረት ሥርዓት እና አዳዲስ ውጤቶችን ይዞ መምጣቱን አቶ ኡስማን ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል።

በተጨማሪም የፍራፍሬ ምርቶቹ ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የሥራ ዕድል ፈጠራና የገቢ ምንጭ እንዲሆን ለማስቻል ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱንና ውጤታማነቱ እየተረጋገጠ መሆኑንም አመልክተዋል። ኤፍ ኤም ሲ

 የከምባታ ዞን ትምህርት መምሪያ የሥራ ባልደረባ አቶ ኤሊያስ ሉቃስ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 777 ብር አበርክተዋል። ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድር...
26/06/2025


የከምባታ ዞን ትምህርት መምሪያ የሥራ ባልደረባ አቶ ኤሊያስ ሉቃስ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 777 ብር አበርክተዋል።

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

------------------
በተጨማሪም

በቴሌግራም: https://t.me/KembataTelevision

በፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/161AHqus1c/

በዩቱብ: https://youtube.com/?si=8XWuS98JRIlvDDrgg
ይከታተሉን።

 የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ዱራሜ ካምፓስ መምህርና ተመራማሪ ኢንጂነር ዓለማየሁ ለተሞ (ዶ/ር) ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 2,777 ብር አበርክተዋል። ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባ...
26/06/2025


የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ዱራሜ ካምፓስ መምህርና ተመራማሪ ኢንጂነር ዓለማየሁ ለተሞ (ዶ/ር) ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 2,777 ብር አበርክተዋል።

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

------------------
በተጨማሪም

በቴሌግራም: https://t.me/KembataTelevision

በፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/161AHqus1c/

በዩቱብ: https://youtube.com/?si=8XWuS98JRIlvDDrgg
ይከታተሉን።

 አቶ ነጋልኝ ሉቢሶ ከደቡብ አፍሪካ በመዓዛ ተሾመ በኩል ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 5,040 ብር አበርክተዋል። ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን ...
26/06/2025


አቶ ነጋልኝ ሉቢሶ ከደቡብ አፍሪካ በመዓዛ ተሾመ በኩል ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 5,040 ብር አበርክተዋል።

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

------------------
በተጨማሪም

በቴሌግራም: https://t.me/KembataTelevision

በፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/161AHqus1c/

በዩቱብ: https://youtube.com/?si=8XWuS98JRIlvDDrgg
ይከታተሉን።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምርጥ ዘር አቅርቦት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሄደ። በመድረኩ በምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ለታቀፉ ወረዳዎች የግብርና ጽ/ቤት ኃ...
26/06/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምርጥ ዘር አቅርቦት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሄደ።

በመድረኩ በምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ለታቀፉ ወረዳዎች የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና በዘር ብዜት ለተሰማሩ የኢንተርፕራይዝ ቡድን መሪዎች በዘር አመራረት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የምርጥ ዘር ድርጀት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ተክሌ ባህሩ መድረኩን ሲከፍቱ ባስተላለፉት መልዕክት በግብርና ሴክተር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የሴክተሩን ምሶሶዎች ለማሳከት ቁልፉ ጉዳይ የምርጥ ዘር አቅርቦት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በምርጥ ዘር አቅርቦት የሚስተዋሉ ማነቆዎችን ለመፍታት ከተለያዩ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ያሉት ዋና ሥራ አስኪያጁ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) የዘርፉን ክፍተት በበሙላት ከፍተኛ እገዛ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በምርጥ ዘር ብዜት በተሰሩ ስራዎች የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና ጉድለቶችን ለማረም ዓላማ ያደረገ መድረክ መሆኑንም የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ተክሌ ባህሩ አስረድተዋል፡፡

በክልሉ ግብርና ቢሮ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ማናጀር አቶ ከድር መሐመድ በበኩላቸው ፕሮግራሙ በክልሉ በአራት ዞኖች ውስጥ በሚገኙ 10 ወረዳዎች በ289 ቀበሌያት ቀጥተኛ በሆነ መንገድ ለ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን የህብረተሰብ ተጠቃሚዎችን የሚደግፍ እንዲሁም ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ የክልሉን ህብረተሰብ በስልጠናና ምርጥ ልምምዶችንና ተሞክሮዎችን በመቀመር ወደ ሌሎች በማድረስ ሰፊ እገዛ እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡

የፕሮግራሙ ዋና ዓላማ ግብርናን ትራንስፎርም ማድረግ ነው ያሉት አቶ ከድር ወደ ብልፅግና የሚደረገውን ጉዞ ለማፋጠን በግብርና ሴክተር የተነደፉ ኢኒሼቲቮችን ወደ አርሶአደሩ እንዲደርሱና እንዲተገበሩ ማድረግና የባለሞያውንም ሆነ የአርሶአደሩን የአቅም ክፍተት በስልጠና መደገፍ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡

ፕሮግራሙ የምርጥ ዘር ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም በዘር ብዜትና ማምረት የተሰማሩ አካላትን የአቅም ክፍተት በመሸፍንና የገበያ ትስስር በመፍጠር ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

የግብርና ምርታማነት 50 በመቶው በምርጥ ዘር ላይ የተመሰረተ ነው ያሉት አቶ ከድር አርሶአደሩ ምንጩ የሚታወቀውን ዘር መጠቀም እንደሚገባም አስገንዝበዋል፡፡

በዘርፉ የተሰማሩ አካላት በገቡት ውል መሰረት ዘር ያለማቅረብና አላስፈላጊ ዋጋ የመጨመር ሁኔታዎች እንደነበሩ አንስተው ለቀጣይ መታረም እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡

በመድረኩም የክልሉ ምርጥ ዘር ድርጅትና የምግብ ሰርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ በፕሮግራሙ ከታቀፉ ወረዳዎች የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና በዘር ብዜት የተሰማሩ ኢንተርፕራይዝ ቡድን መሪዎች ተገኝተዋል፡፡

መድረኩ የክልሉ ምርጥ ዘር ድርጅት ከክልሉ ግብርና ቢሮ የምግብ ሥርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም (FSRP) ጋር በመተባበር ያዘጋጀው መሆኑን ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
------------------
በተጨማሪም

በቴሌግራም: https://t.me/KembataTelevision

በፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/161AHqus1c/

በዩቱብ: https://youtube.com/?si=8XWuS98JRIlvDDrgg
ይከታተሉን።

 የከምባታ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ሾፌር አቶ መሀመድ አያሌው ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 5,777 ብር አበርክተዋል። ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ...
26/06/2025


የከምባታ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ሾፌር አቶ መሀመድ አያሌው ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 5,777 ብር አበርክተዋል።

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

------------------
በተጨማሪም

በቴሌግራም: https://t.me/KembataTelevision

በፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/161AHqus1c/

በዩቱብ: https://youtube.com/?si=8XWuS98JRIlvDDrgg
ይከታተሉን።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የእግር ኳስ ክለብ የሁለተኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእግር ኳስ ክለቦች ሻንፒዮና ውድድር አሸናፊ ሆነ።በሆሳዕና ከተማ አቢዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ሁለገብ ስቴድየም...
26/06/2025

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የእግር ኳስ ክለብ የሁለተኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእግር ኳስ ክለቦች ሻንፒዮና ውድድር አሸናፊ ሆነ።

በሆሳዕና ከተማ አቢዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ሁለገብ ስቴድየም ለ15 ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

በሆሳዕና እና በወራቤ ከተሞች እግር ኳስ ክለቦች መካከል በተደረገው የፍፃሜ ጨዋታ ሆሳዕና ከተማ ተጋጣሚውን 1 ለባዶ በመርታት የዋንጫ ባለቤት ለመሆን ችሏል።

በሻምፒዮናው የመዝጊያ መርሀ ግብር ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾ ስፖርት ለማህበራዊ እድገትና ልማት የላቀ ሚና አለው ብለዋል።

በስፖርቱ ዘርፍ የሚፈለገውን ውጤት ማስመዘገብ እንዲቻል ወቅታዊና በአዲስ አስተሳሰብ ዘርፉን መምራትና ህዝባዊ መሠረት እንዲኖረው ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በውድድሩ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴቶችና ስፖርታዊ ጨዋነት ጎልብተው የታዩበት መሆኑንም አቶ ጌታቸው ገልፀዋል።

የክልሉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ሠርካለም ሳሙኤል በበኩላቸው ሻምፒዮናው የእርስ በርስ ወዳጅነት የተጠናከረበትና ጠንካራ የእግር ኳስ ተጫዋቾችን ማየት የተቻለበት መሆኑን ጠቁመዋል።

ዘርፉን ለማሳደግ ከባለሀብቱና የስፖርቱ ቤተሰብ ጋር በመቀራረብ የሚሰራ ስለመሆኑም ተናግረዋል።

የእግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር በአማረ መልኩ እንዲጠናቀቅ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትና የስፖርቱ ቤተሰብ ፕሬዚዳንቷ ምስጋና አቅርበዋል።

የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች የወራቤ ከተማ አስተዳደር እግር ኳስ ክለብ ተጫዋች ፉአድ ሙስጠፋ፣ ኮከብ ግብ አግቢ የእንድግኝ ወረዳ እግር ኳስ ክልብ ተጫዋች ደሳለኝ ተስፋዬ፣ ኮከብ ግብ ጠባቂ አምሳሉ ዲላሞ ከሆሳዕና እንዲሁም የእለቱ ኮከብ ከሆሳዕና ከተማ አስተዳደር እግር ኳስ ክለብ ተጫዋች መንታ በቀለ ሆነዋል።

የውድድሩ የፀባይ ተሸላሚ የእንደጋኝ ወረዳ ሲሆን፣ ኮከብ ዋና ዳኛ ሲሳይ ካባሞ፣ ኮከብ ረዳት ዳኛ ተከተል በቀለ በመሆን የዋንጫና የሰርተፊኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በሁለተኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ሆሳዕና ከተማ አስተዳደርን በመከተል ወራቤ ከተማ አስተዳደር እና እንደጋኝ ወረዳ 2ኛ እና 3ኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቅቀዋል።

 የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ዳምቦያ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተጠጋኝ ደስታ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 2,777 ብር አበርክተዋል። ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳ...
26/06/2025


የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ዳምቦያ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተጠጋኝ ደስታ ለሀምበሪቾ 777 ተጨማሪ ሥራዎች ፕሮጀክት 2,777 ብር አበርክተዋል።

ሁላችንም ከታች በተጠቀሱት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የድርሻችንን እያበረከትን ታሪክ እንሥራ፤ እናኑር ዐሻራ!!

• የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000702856292
SWIFT code: CBETETAA
• አዋሽ ባንክ - 013201588434000
SWIFT code: AWINETAA
• ዳሽን ባንክ - 5351865591021
SWIFT code: DASHETAA

------------------
በተጨማሪም

በቴሌግራም: https://t.me/KembataTelevision

በፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/161AHqus1c/

በዩቱብ: https://youtube.com/?si=8XWuS98JRIlvDDrgg
ይከታተሉን።

የኦሮሚያ ክልል የመላው ኢትዮጵያ ጨዋታዎች አጠቃላይ አሸናፊ ሆነበ26 የስፖርት አይነቶች ሲካሄድ የቆየው 6ኛው የመላው ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ውድድር በኦሮሚያ ክልል አሸናፊነት ተጠናቅቋል።በውድድ...
26/06/2025

የኦሮሚያ ክልል የመላው ኢትዮጵያ ጨዋታዎች አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ

በ26 የስፖርት አይነቶች ሲካሄድ የቆየው 6ኛው የመላው ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ውድድር በኦሮሚያ ክልል አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

በውድድሩ ከ5 ሺህ በላይ ስፖርተኞች የተሳተፉ ሲሆን በወንዶች የእግር ኳስ የፍፃሜ ጨዋታ ኦሮሚያ ክልል ደቡብ ኢትዮጵያን 2 ለ 1 በማሸነፍ የወርቅ ሜዳሊያ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

በተመሳሳይ የሴቶች እግር ኳስ ኦሮሚያ ደቡብ ኢትዮጵያን 1 ለ 0 በመርታት የወርቅ ሜዳሊያ እና የዋንጫ ተሸልሟል።

ከሰኔ 10 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በጅማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የመላ ኢትዮጵያ ሻምፒዮና ዛሬ ፍፃሜውን ሲያገኝ ኦሮሚያ ክልል የአጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል።

225 ሜዳሊያዎችን የሰበሰበው ኦሮሚያ ክልል 1ኛ ደረጃን ይዞ ሲያጠናቅቅ አዲስ አበባ ከተማ በ220 ሜዳሊያዎችን በማግኘት ሁለተኛ እንዲሁም አማራ ክልል 143 ሜዳሊያዎችን በማግኘት 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።

በውድድሩ ኦሮሚያን ተከትሎ በአጠቃላይ ውድድር 2ኛ ደረጃን ይዞ የጨረሰው አዲስ አበባ ከተማ የፀባይ ዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል። ኤፍ ኤም ሲ

ሁለተኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር የመዝጊያ መርሀ ግብር በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ በአቢዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ሁለ ገብ ስታድየም እየተካሔደ ነው። በመዝ...
26/06/2025

ሁለተኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር የመዝጊያ መርሀ ግብር በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ በአቢዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ሁለ ገብ ስታድየም እየተካሔደ ነው።

በመዝጊያ በመርሀ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ሌሊሾ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ሠርካለም ሳሙኤል፣ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የእግር ኳስ ስፖርት ቤተሰቦች ታዳሚ ሆነዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን

Address

Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kembata TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category