Kembata TV

Kembata TV "በሁሉም፤ ከሁሉም ተመራጭ!!"

27/09/2025

መስቀል በጽናትና በትጋት ተፈልጎ እንደተገኘ፤ ሁሉም በየደረጃው በሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት ተገለፀ።

------------------
በተጨማሪም

በቴሌግራም: https://t.me/KembataTelevision

በፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/161AHqus1c/

በዩቱብ: https://youtube.com/?si=8XWuS98JRIlvDDrgg
ይከታተሉን።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )የመስቀል ፌስቲቫል ዐውደ-ርዕይ በወልቂጤ ከተማ መርቀው ከፈቱ   በጉራጌ እና በምስራቅ ጉራጌ ዞኖች፣ በጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር እና በወልቂጤ ዩ...
27/09/2025

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )የመስቀል ፌስቲቫል ዐውደ-ርዕይ በወልቂጤ ከተማ መርቀው ከፈቱ

በጉራጌ እና በምስራቅ ጉራጌ ዞኖች፣ በጉራጌ ልማትና ባህል ማህበር እና በወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ትብብር በቸሃ ወረዳ የፈረዝየ ቀበሌ የተዘጋጀው የዘንድሮው የመስቀል ፌስቲቫል ዐውደ -ርዕይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር በክቡር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ተመርቆ ለዕይታ ክፍት ሆኗል።

የመስቀል ደመራ በዓል አንድነትና ፍቅር የሚገለፅበት ለሰው ልጆች ሁሉ ተምሳሌት ነው - ክቡር ከንቲባ አቶ ታረቀኝ ተስፋዬ!!በዱራሜ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራ በዓል የኦርቶዶክስ እምነት...
26/09/2025

የመስቀል ደመራ በዓል አንድነትና ፍቅር የሚገለፅበት ለሰው ልጆች ሁሉ ተምሳሌት ነው - ክቡር ከንቲባ አቶ ታረቀኝ ተስፋዬ!!

በዱራሜ ከተማ አስተዳደር የመስቀል ደመራ በዓል የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በተለያዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች የእምነቱ ተከታዮችና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተከበሯል።

በሥፍራው በመገኘት መልዕክት ያስላለፉት የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ታረቀኝ ተስፋዬ የመስቀል ደመራ በዓል አንድነትና ፍቅር የሚገለፅበት ለሰው ልጆች ሁሉ ተምሳሌት ነው ብለዋል።

በሀገራችን ብሎም በከተማችን ከሚከበሩ ሃይማኖታዊ የአደባባይ በዓላት የጥምቀትና የደመራ በዓል ከሃይማኖታዊ ዐዓል ባሻገር የሁሉም ቤተ እምነቶች የጋራ በዓል በሚመስል መልኩ በአንድነትና በጋራ ያለ አንዳች ልዩነት ፍጹም ፍቅር በተሞላበት ሁኔታ የሚከበር መሆኑ ልዩ መገለጫ እንደሆነም ገልፀዋል።

የእንጨቱ መሰብሰብና የደመራው መደመር በአንድ ሀሳብ ለፀሎት፣ ለፍቅር፣ ለልማት፣ ለሰላምና ለአንድነት መትጋት እንዳለብን የሚያስተምር ነው ያሉት ክቡር ከንቲባ ሁላችን በመገንዘብ ለጋራ አላማ በጋራ መቆም አለብን ብለዋል።

በመርሐ-ግብሩም የከምባታ ጠምባሮና ሀላባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ቆሞስ አባ ሚካኤል ታደሰ፣ የቤተ እምነቱ መሪዎችን ጨምሮ መላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን የተለያዩ የኃይማኖቱ ክዋኖች በማድረግ ተጠናቅቋል።

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ የ2018 ዓ/ም የደመራና የመስቀል በዓልን አስመልክቶ ያስተላላፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!Eman Masaali Ayyaanii x...
26/09/2025

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ የ2018 ዓ/ም የደመራና የመስቀል በዓልን አስመልክቶ ያስተላላፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!

Eman Masaali Ayyaanii xummiin iillishshonne iillishsho'nne.

አምላክ ለሰው ልጆች ያለውን ፍፁም ፍቅር የገለፀበትን፣ የሰው ልጆችን ከዘላለማዊ ሞት ዘላለማዊ ህይወትን፣ ምህረትንና ድህነትን በክርስቶስ ሞት ያገኘንበትን እንዲሁም ክርስቶስ ስለ ሰው ልጅ መዳን ብሎ የተሰቀለበት መስቀል በአይሁዶች ከተደበቀበት በተዓምር ከብዙ አመታት በኃላ የተገኘበት መታሰቢያ ብስራት በየአመቱ ይከበራል ይዘከራል።

የተከበራችሁ በመላው ዓለም ላይ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የምትኖሩ የዞናችን ተወላጆች፣ ምሁራን፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ነጋዴዎች፣ አርሶ አደሮችና መላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን በከምባታ ብሔረሰብ ዘንድ በድምቀት ለሚከበረው የከምባታ ብሔር ዘመን መለወጫ መሳላ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! እያልኩ በራሴና በዞኑ ህዝብ ስም መልካም ምኞቴን መግለፅ እወዳለሁ።

'መሳላ' በዓል በከምባታ ብሔር ዘንድ ከክብረ በዓልነቱም ባሻገር ከብሔረሰቡ ባህል ታሪክና እምነት የዘመን አቆጣጠር ቀመር ጋር የተሳሰረ በከፍተኛ ድምቀትና ልዩ ዝግጅት የሚከበር የብሔሩ የዘመን መለወጫ አውራ በዓል መሆኑ ይታወቃል።

የተከበራችሁ በሀገር ውስጥና ባህር ማዶ የሚትገኙ የመሳላ በዓልን የምታከብሩ የዘንድሮውን የመሳላ በዓል ልዩ የሚያደርገው በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የሚገኙ ልማት ወዳድ ህብረተሰባችንን ከምንጊዜውም በበለጠ በጋራ በመቆም ለዞናችን ዕድገት እየሠራን ያለንበት ከመሆኑም ባሻገር በመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረት የተገነባው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ በተመረቀበት ወቅት የሚከበር በዓል መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

በመሳላ በዓል በከምባታ ብሔር ዘንድ በሥራ ምክንያት ዓመቱን ሙሉ ተለያይተው የቆዩ ቤተሰቦች የሚሰባሰቡበት፣ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ ወዳጅ ዘመድ የሚጠያየቅበት እና የተለያዩ ባህላዊና ማህበራዊ ክዋኔዎች የሚፈፀሙበት ከትውልድ ትውልድ ከዘመን ዘመን ሲሸጋገር የመጣ ድንቅ ባህላዊ ታሪካዊና ሀይማኖታዊ በዓል እንደሆነም ይታወቃል።

የመሳላ በዓል ወዳጅ ዘመድ ተሰባስቦ ጎረቤት ተጠራርቶ ህፃን አዋቂው ወንድ ሴቱ እና ወጣት አዛውንቱ በየአቻቸውና በጋራ በመሆን በልዩ ደስታ እየበሉና እየጠጡ የተለያዩ ባህላዊ ጨዋታዎችን እየተጫወቱ የሚያከብሩት በዓል በመሆኑ ከዓመት ዓመት በታላቅ ጉጉትና ናፍቆት የሚጠበቅ ተናፋቂ በዓል እንደሆነም እሙን ነው።

የመሳላ ዝግጅቱም በአባቶች፣ በእናቶች፣ በወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች እና በህፃናት በኩል የሚደረግ ሲሆን ሁሉም በየፊናቸው ዝግጅቱን የሚጀምሩ ሲሆን በብሔሩ ዘንድ ልዩ ባህላዊና ታሪካዊ ይዘትን ተላብሶ የሚከበር በዓል በመሆኑ የመሳላ በዓል ቅድመ ዝግጅት የሚደረገው ዓመቱን ሙሉ ነው።

አባቶች ስለ መሳላ የሼማታ ዝግጅት እናቶች ደግሞ ስለ ቆጮና አተካና እየተገናኙ ይመክራሉ በጋራም ይዘጋጃሉ። ይህም የከምባታ ብሔርን ለማንኛውም ጉዳይ መመካከርን መዘየድን ቀድሞ ማሰብንና መዘጋጀትን ባህል ማድረጉን ያሳያል።

አባወራዎች በሼማታ ሰንጋ መግዣ ብር በመቆጠብ ያዘጋጃሉ ከሼማታው መሀል ገንዘብ ያጠረው አልያም የቸገረው ካለ ለሱም በጋራ መፍትሔ ይፈልጋሉ ያበድራሉ በጥጋብ እንዲያሳልፍ ይተባበራሉ ይረዳዳሉ።

እናቶችም እንዲሁ የመሳላ እና የአተካና ቆጮ በጋራ/በጌጃ ይፍቃሉ የአተካና መስሪያ የወተትና ቅቤ ዊጆ/እቁብ /ይገባሉ።

ወጣት ወንዶችም የመሳላ ማገዶ እንጨት ከሰፈር አቻዎቻቸው ጋር በመተባበር ፈልጠው በየበራፉ ይከምራሉ።

ይህ የመሳላ ቅድመ ዝግጅት ተግባር በአብዛኛው በጋራና በመተባበር የሚከናወን መሆኑ የከምባታ ብሔርን የቆየ የመተጋገዝ የመረዳዳትና በጋራ የመቆም ባህልን የሚያሳይ ነው።

ክቡራን የዞናች ነዋሪዎች የዘንድሮ ዓመት የመሳላ በዓልን ስናከብር እንደቀድሞው ሁሉ በነበረን ባለንና ወደፊትም በሚኖረን የመረዳዳት የመከባበርና የአብሮነት ባህላችን ያለው ለሌለው በመስጠት ብርቱው ደካማውን በማገዝ በፍፁም ወንድማማችነትና በጽኑ መተሳሰብ ወዳጅ ዘመድ ተሰባስበን በነበረን በከምባታ ወግና ባህላችን እንዲሆን መልእክቴን አስተላልፋለሁ።

በመጨረሻም መላው ኢትዮጵያውያንና የከምባታ ዞን ህዝቦች እንኳን ለከምባታ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ ለሆነው የመሳላ በዓልና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ በልዩ ድምቀት ለሚከበረው ለደመራ ሥነ ስርዓት በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።

በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድነትና የብልፅግና ይሁንልን!

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን የከምባታ፣ ጠምባሮና ሀላባ እንዲሁም የዳውሮና ኮንታ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁ...
26/09/2025

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን የከምባታ፣ ጠምባሮና ሀላባ እንዲሁም የዳውሮና ኮንታ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ በተገኙበት የ2018 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓል በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል።

ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ያስመዘገበችው የመጀመሪያው የማይዳሰስ ቅርስ - የመስቀል በዓልኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሣይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ካስመዘገበቻቸው 6 የማይዳሰ...
26/09/2025

ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ያስመዘገበችው የመጀመሪያው የማይዳሰስ ቅርስ - የመስቀል በዓል

ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሣይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ካስመዘገበቻቸው 6 የማይዳሰሱ ቅርሶች መካከል የመጀመሪያው የመስቀል በዓል ነው፡፡

የመስቀል በዓል በኢትዮጵያ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በተለይም በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በድምቀት የሚከበር የአደባባይ በዓል ነው።

በየዓመቱ መስከረም 17 ቀን የሚከበረው በዓሉ፣ በበርካታ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በዋዜማው ደመራ በመደመር እና በማብራት በተለያዩ የሃይማኖቱ ሥርዓቶች የሚከበር ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ደመራው በዕለቱ ይበራል፡፡

በዓሉ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ የመጣ፣ በሀገሪቱ ማኅበራዊ አንድነትን እና የእርስ በርስ ትስስርን የሚፈጥር ሃይማኖታዊና ባህላዊ ትውፊቶችን የያዘ ነው።

የመስቀል በዓል ለረጅም ጊዜ ተለያይተው የቆዩ ቤተሰቦች የሚገናኙበት፣ ከሀገራቸው ውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር የሚመለሱበት፣ የተጣሉ የሚታረቁበት እና ሁሉም በአንድነት የሚሰባሰቡበት ነው፡፡

በ2006 ዓ.ም በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ባህላዊ ቅርስነት በተመዘገበው በዚህ በዓል ላይ ለመታደም ከተለያዩ የውጭ ሀገራት በርካታ ጎብኝዎች ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ፡፡

Ethiopian Broadcasting Corporation

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለመስቀል በዓል ያስተላለፉት መልዕክት -እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ! እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ! አደረሰ...
26/09/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ለመስቀል በዓል ያስተላለፉት መልዕክት -

እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ!

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ! አደረሰን! እያልኩ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ፣

ባለብዙ ቀለም፣ መስኩ ለምለም፣ ዜጎች ለአዳዲስ ሰኬቶች የሚነሳሱበት የተስፋና የብርሃን ወቅት በሆነው ወርሃ መስከረም የሚከበረው የመስቀል በዓል ልዩ ድምቀት ያለውና በሃይማኖታዊና ማህራዊ እሴቶችና ትሩፋቶች የታጀበ ነው።

ተፈጥሮ ምድርን ደማቅና ውብ አድርጎ በሚያሸበርቅበት፣ የአዲስ ዓመት ማግስት የሚከበረው የመስቀል በዓል ሃይማኖታዊ አስተምህሮውና ማህበራዊ ትውፊቶቹ ለአዳዲስ ሰኬቶች የሚያነሳሱ ናቸው።

በዓሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም ከሃይማኖታዊ እሴቶቹ ባሻገር ማህበራዊ ትሩፋቶቹ በርካታ ናቸው። ተራርቀው የሠነበቱ ቤተሰቦች ተገናኝተው ቤተሰባዊ ፍቅራቸውን የሚወጡበት፣ ሐሴታቸውን የሚገልፁበት ነው።

የተስፋ ብርሃን፣ የፅናት፣ የአሸናፊነትና የመስዋዕትነት ምልክት የሆነው የመስቀል በዓል የአብሮነት፣ የተስፋና የትጋት እሴቶችን እንድናጠናክር የሚያግዝ ነው።

በዓሉ የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበት፣ ለሠላምና ለልማት ግንባታ በአጠቃላይ ለሁለንተናዊ ብልጽግና በጋራ ለመትጋት የምንነሳሰበት እንዲሆን እመኛለሁ ።

መልካም የመስቀል በዓል!

አመሠግናለሁ !

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት -እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ!የመስቀል በዓል ሲታሰብ እውነት ተቀብራ እንደማትቀር እናስባለን። መስቀሉ የተቀበረበት ቦታ ተራራ ሠርቶ...
26/09/2025

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት -

እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ!

የመስቀል በዓል ሲታሰብ እውነት ተቀብራ እንደማትቀር እናስባለን። መስቀሉ የተቀበረበት ቦታ ተራራ ሠርቶ ነበር። የቀበሩት ሰዎች ከዚህ በኋላ እንደማይወጣ ደምድመው ነበር። አንዳንድ አማኞችም ተስፋ ቆርጠው ነበር።

ጊዜው በረዘመ ቁጥር ቀባሪዎቹ ያሸነፉ መስሏቸው ተደሰቱ። የተቀበረው መስቀልም ታሪክ የሆነ መሰለ።

ብርቱ ሰዎች፣ እውነት ፈላጊ ሰዎች፣ አቧራውን የሚገልጡ፣ ቆሻሻውን የሚያነሡ ሰዎች፣ ሲመጡ ግን መስቀሉ ከተቀበረበት ወጣ።

እውነት አይቀበርም። ጊዜው ሲደርስ አቧራውን አንሥቶ ዐሻራውን ያሳያል። ሐሰቱን እንደ ጉም አትንኖ፣ ሐቁን እንደ ዐለት አግንኖ ያሳያል።

የኢትዮጵያም እውነት እንደዚሁ ነው። የአውራ ዶሮዎች ጩኸት የፀሐይን መውጣት አያስቀረውም። የሌሊት ወፎች ክንፍ የፀሐይን ንጋት አያግደውም። በዚህም ተባለ በዚያ ፀሐይ ትወጣለች።

የኢትዮጵያ እውነት እንደ መስቀሉ ሁሉ አቧራውን ጥሶ፣ አፈሩን አፍልሶ፣ ቆሻሻውን ደርምሶ ይገለጣል። የወጓት ያዩዋታል። ከላይ ሆነው እንዳዩዋት ሁሉ፣ ከታች ሆነው ይገረሙባታል።

በመደመር ደመራ እየተመራን፣ በትጋት እየቆፈርን፣ የኢትዮጵያን ብልጽግና እናወጣዋለን። ይህ ዓመት የኢትዮጵያ ብርሃን ሲወጣ የምናይበት ይሆናል።

በድጋሚ መልካም የደመራና የመስቀል በዓል ይሁንልን።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ።ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በኢትዮጵያ የኑክሌር ኃይል ማመን...
25/09/2025

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኑክሌር ልማት ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረሙ።

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በኢትዮጵያ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ልማት ዙሪያ በሮሳቶም እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን መካከል የድርጊት መርሀ ግብር ተፈራረመዋል።

በኢትዮጵያ የሩሲያ ኤምባሲ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው የሮሳቶም ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሌክሲ ሊካቼቭ እና የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ፣ ቭላድሚር ፑቲን እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት የተፈረመውን ሰነድ ተለዋውጠዋል።

የፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ በሩሲያው መሪ እና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መካከል የተደረገው የውይይት አካል ነው።

Office of the Prime Minister-Ethiopia

በሁሉም ዘርፍ የሚሰጠውን አገልግሎት በማዘመን ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ከብልሹ አሰራር የጸዳ እና  በእርካታ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን መስራት ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )...
25/09/2025

በሁሉም ዘርፍ የሚሰጠውን አገልግሎት በማዘመን ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ፣ከብልሹ አሰራር የጸዳ እና በእርካታ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን መስራት ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመርቆ ስራ ጀመረ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) እንደገለጹት በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋ፣ ከብልሹ አሰራር የጸዳ፣ የህብረተሰቡን እርካታ ያረጋገጠ እንዲሁም የአገልጋይነት መንፈስ የተላበሰ እንዲሆን ያስችላል ብለዋል።

በክልሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ተገንብቶ ስራ የጀመረው የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአጭር ጊዜ አገልግሎት መለየት፣ ማኑዋል ማዘጋጀት፣ቢሮን መገንባትና ማደስ፣ሰራተኛ መረጣ እና የቴክኖሎጂ አቅርቦት ስራ ማከናወን መቻሉን አብራርተዋል።

በክልሉ በዛሬው እለት ከተመረቀው ፕሮጀክት ልምድ በመውሰድ በወራቤ፣ በቡታጅራ፣ በወልቂጤ፣ በሳጃ፣ በዱራሜ፣ በቁሊቶ ከተሞች በ2018 ማጠቃለያ ላይ ሰባት መሶብ የአንድ ማዕከላት እንደሚኖሩ ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በ2018 በጀት አመት በሀገሪቱ እና በክልሉ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

ማዕከሉ ተገንብቶ ወደ ተግባር እንዲገባ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አመራሮች ለፌደራል እና ለክልል ተቋማት ርዕሰ መስተዳድሩ ምስጋና አቅርበዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በበኩላቸው የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ የተንዛዛ፣ የግልጸኝነት ጉድለት ያለው ለብልሹ አሰራር የተጋለጠ እንግልት የበዛበት እና ተገልጋይ ተኮር ያለመሆኑ በመንግስት እና በፓርቲ ከግንዛቤ ውስጥ ገብቷል ብለዋል።

በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታየው ክፍተት በህዝብ ዘንድ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ ስለመስተዋሉም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

በሁሉም ዘርፍ የሚስተዋለውን የአገልግሎት አሰጣጥ እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ (ዶ/ር ) አቅጣጫ ማስቀመጣቸውን ተከትሎ በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እውን ማድረግ መቻሉን አቶ አንተነህ ጠቁመዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለዜጎች የተደራጀ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

በክልሉ በዛሬው እለት ተመርቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ክቡር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ኮሚቴ በማቋቋም ለስራው ልዩ ትኩረት በመስጠታቸው ፕሮጀክቱ ስኬታማ እንዲሆን አስችሎታል ሲሉም አቶ አንተነህ ጠቁመዋል።

ማዕከሉ ዜጎች የተሟላ የዲጂታል አማራጮችን በመጠቀም የፌደራል እና የክልል ተቋማትን አገልግሎት ማግኘት እንደሚያስችላቸው የተናገሩት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ የተገልጋዮችን እንግልት እና ከወረቀት ጋር ተዛማጅ የሆኑ አሰራሮችን የሚያስቀር ነው ብለዋል።

ማዕከሉ በሰባት የፌደራል እና የክልል ተቋማት 20 አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረግ የሚያስችል ስለመሆኑም አቶ አንተነህ በንግግራቸው አመላክተዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የፕሮጀክቶች አስተባባሪ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ብርሀኑ ተስፋዬ እንደገለጹት የክልሉ መንግስት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተገንብቶ ለውጤት እንዲበቃ በማድረጉ ምስጋና አቅርበዋል።

የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩን ተልዕኮ ከማሳካት አንጻር በሀገሪቱ ሰባት ማዕከላት ለምረቃ መብቃታቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን ጨምሮ ስድስት ማዕከላት እየተመረቁ ነው ብለዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሀገሪቱ የአገልግሎት አሰጣጡን ተደራሽነትና ግልጸኝነትን ከማሳደግ አንጻር ወደ አንድ ደረጃ እንደሚያሳድገውም አብራርተዋል።

በህዳሴ ግድብ ግንባታ፣ በቱሪዝም መዳረሻ ልማት፣ በከተማ እና በገጠር ኮሪደር፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በሌማት ትሩፋት፣ በስንዴ ልማት እንዲሁም የማዕድን ልማት የኢትዮጵያ ማንሰራራት መገለጫዎች ናቸው ሲሉም ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል።

በመርሐ ግብሩ ለፕሮጀክቱ ስኬታማነት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ተሰጥቷቸዋል።

25/09/2025

ፀጋዎችን መሰረት ያደረገ የግብርና ልማት ተግባራትን በማከናወን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ አበርክቶ የላቀ መሆኑ ተገለፀ።

------------------
በተጨማሪም

በቴሌግራም: https://t.me/KembataTelevision

በፌስቡክ: https://www.facebook.com/share/161AHqus1c/

በዩቱብ: https://youtube.com/?si=8XWuS98JRIlvDDrgg
ይከታተሉን።

የዱራሜ ከተማ ቦቦዳ (የመሳላ) ገበያ የቀንድ ከብት ግብይት በምስል
25/09/2025

የዱራሜ ከተማ ቦቦዳ (የመሳላ) ገበያ የቀንድ ከብት ግብይት በምስል

Address

Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kembata TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category