Kembata TV

Kembata TV "በሁሉም፤ ከሁሉም ተመራጭ!!"
(1)

የ2026 የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት  የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ 4:00 ላይ ይጀምራል። ሜክሲኮ እና ደቡብ አፍሪካ ከሚያደርጉት ጨዋታ በፊት በታሪካዊው አዝትካ ስታዲየም የመክፈቻ ስነ...
11/06/2026

የ2026 የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት

የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ 4:00 ላይ ይጀምራል።

ሜክሲኮ እና ደቡብ አፍሪካ ከሚያደርጉት ጨዋታ በፊት በታሪካዊው አዝትካ ስታዲየም የመክፈቻ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል።

በአሁኑ ሰዓት ሻኪራን ጨምሮ የተመረጡ ሙዚቀኞች ዝግጅታቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ።

ደህንነቱ የተጠበቀ የፈተና አስተዳደር ስርዓት በመገንባት ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎች ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ ነው - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ...
11/06/2026

ደህንነቱ የተጠበቀ የፈተና አስተዳደር ስርዓት በመገንባት ብቁና ተወዳዳሪ ዜጎች ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ ነው - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው የትምህርት ዘመን ከሰኔ 8 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ባሉት ቀናት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ይሰጣል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በጽ/ቤታቸው ለመገናኛ ብዙሀን በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት በተያዘው የትምህርት ዘመን ከሰኔ 8 እስከ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ባሉት ቀናት የ6ኛ እና የ8 ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ይሰጣል ብለዋል።

በክልሉ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 እስከ 9 እንዲሁም የ8 ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ደግሞ ከሰኔ 11 እስከ 12/2018 እንደሚሰጥ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አስታውቀዋል።

በክልሉ በ2018 የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን ብቁና ተወዳዳሪ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራ ተግባራዊ ስለመደረጉም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በመግለጫቸው አብራርተዋል።

በክልሉ በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የትምህርት ይዘታቸውን በጊዜ እንዲያጠናቅቁ መደረጉን አቶ አንተነህ ጠቁመዋል።

ተማሪዎች ብቃታቸውን እንዲፈትሹ ሞዴል ፈተናዎችን በማዘጋጀት ወደ ተግባር መገባቱን ኃላፊው ተናግረዋል።

በተለይ ለ8 ኛ ክፍል ተማሪዎች በሆሳዕና ትምህርት ኮሌጅ እና በሌሎችም ትምህርት ቤቶች የማጠናከሪያ ትምህርት መሰጠቱን አስረድተዋል።

በተያዘው የትምህርት ዘመን በክልሉ 46ሺ 151 ወንዶች እንዲሁም 45ሺ 767 በድምሩ 91ሺ 918 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ክልል አቀፍ ፈተና ይወስዳሉ ሲሉም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።

በተመሳሳይ 44ሺ 370 ወንዶች እና 43ሺ 506 ሴቶች በድምሩ 87ሺ 876 ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ለመፈተን ዝግጁ ስለመሆናቸውም አቶ አንተነህ ጠቁመዋል።

ባለፉት አመታት አዲሱ የትምህርት እና ስልጠና ፖሊሲ ተግባራዊ ከተደረገ ወዲህ ተማሪዎች ከኩረጃ በጸዳ መልኩ እንዲፈተኑ ዘርፈ ብዙ ጥረት ስለመደረጉም አብራርተዋል።

የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በክላስተር በጉድኝት ማዕከላት እንዲፈተኑ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል ሲሉም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

የፈተና አስተዳደሩ በጥብቅ ዲሲፕሊን እንዲመራ ተደርጓል ያሉት ኃላፊው በተለይ የትምህርት ማህበረሰቡ ኩረጃን የተጸየፈ ዜጋ ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት የላቀ አበርክቶ እንደነበረው በአብነት ጠቅሰዋል።

ለዘንድሮው ክልል አቀፍ ፈተና ጠንካራ ፈታኞች፣ ሱፐር ቫይዘሮች እና ሌሎች የዘርፉ ባለሙያዎች ተመድበው ዝግጁ መሆናቸውን ኃላፊው አስታውቀዋል።

የፈተና አሰጣጡ ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን ከጸጥታ አካላት፣ ከፖሊስ መዋቅሩ፣ ከትምህርት አመራሩ እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመመካከር የጋራ ተግባቦት መፈጠሩን አስረድተዋል።

Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau

497 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውጤት ወደ ማዕከል ደርሷል - ምርጫ ቦርድየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተረጋገጡ የምርጫ ውጤቶችን በይፋ እየተቀበለ መሆኑን የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃ...
11/06/2026

497 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውጤት ወደ ማዕከል ደርሷል - ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተረጋገጡ የምርጫ ውጤቶችን በይፋ እየተቀበለ መሆኑን የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አስታውቀዋል።

ሰብሳቢዋ እንደገለጹት፣ የቦርዱ ሠራተኞች ሂደቱን በስኬት ለማጠናቀቅ የማጣራት ሥራዎችን ቀንና ሌሊት በከፍተኛ ትጋትና በቅንጅት እያከናወኑ ይገኛሉ።

እስካሁን ባለው ሂደት 497 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውጤት ወደ ማዕከል መድረሱን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።

በተጨማሪም 634 የክልል ምክር ቤት የምርጫ ውጤት ወደ ማዕከል መድረሳቸውን ጠቅሰዋል።

በአጠቃላይ 1 ሺህ 131 የምርጫ ውጤቶች ወደ ማዕከል መድረሳቸውንም አረጋግጠዋል።

በተያያዘም ቅሬታ የቀረበባቸው የምርጫ ክልል ውጤቶች በጥንቃቄ እየታዩ መሆኑን ተናግረዋል።

የክርክሩ ሂደት ሕጋዊ ፍጻሜ እስኪያገኝ ድረስ የእነዚህ አካባቢዎች ውጤት ይፋ እንደማይደረግ ገልጸዋል።

በማጣራት ሂደቱ የምስክሮች በትክክል አለመቅረብ በሥራው ላይ መጠነኛ መዘግየት እየፈጠረ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

ክልሉ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በሳይንስ፣ በፈጠራ እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ ነው - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይ...
11/06/2026

ክልሉ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በሳይንስ፣ በፈጠራ እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ ነው - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች ውድድር አውደ ርዕይ እና የፓናል ውይይት ከሰኔ 5 እስከ 6 ቀን 2018 በቡታጅራ ከተማ ይካሔዳል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ ለመገናኛ ብዙኃን በጽ/ቤታቸው በሰጡት መግለጫ ክልሉ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በሳይንስ፣ በፈጠራ እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ለአንድ ሀገር ብልፅግና መረጋገጥ ወሳኝ ናቸው ሲሉም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

"ክልሉን የሳይንስ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ!" በሚል መሪ ሀሳብ ለሁለት ተከታታይ ዓመታት የፈጠራ ሥራ ውድድር ዐውደ ርዕይ መካሔዱን አስታውቀዋል።

በክልሉ የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች ውድድር አውደ ርዕይ እና የፓናል ውይይት ከሰኔ 5 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ/ም በቡታጅራ ከተማ እንደሚካሔድ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በመግለጫቸው ጠቁመዋል።

በክልሉ በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና፣ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና በሌሎችም የልማት ዘርፎች የሚያጋጥሙ መዋቅራዊ ችግሮችን በሀገር በቀል እውቀት እና በቴክኖሎጂ ለመፍታት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ስለመሆኑም አቶ አንተነህ በአብነት ጠቅሰዋል።

ይህን አላማ ይበልጥ ስኬታማ ለማድረግ በየደረጃው የሚገኙ ተማሪዎችን፣ መምህራንን እንዲሁም ወጣቶችን ለማበረታታት 3ኛ ዙር ክልላዊ የሳይንስና ፈጠራ ውድድር እና ዐውደ ርዕይ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።

ካለፉት ሁለት ዓመታት አንጻር ሲታይ የዘንድሮው የሳይንስ የፈጠራ ውድድር እና ዐውደ ርዕይ ልዩ ገጽታ እንዳለውም አመላክተዋል።

በመርሀ ግብሩ ሰፊ የምርምር ስራዎች ስብጥር እንደሚታይበት የገለጹት ኃላፊው 146 የፈጠራ ስራዎች እና ቴክኖሎጂዎች ለውድድር እንደሚቀርቡም ጠቁመዋል።

በመርሐ ግብሩ 8 የተለዩ የውድድር ዘርፎች የሚኖሩ ሲሆኑ ከ7ኛ እስከ 8 ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች፣ ከ9ኛ እስከ 10ኛ፣ከ11ኛ እስከ 12 ኛ ክፍል ተማሪዎች፣የመካከለኛ ደረጃ የ7ኛ እና የ8ኛ ክፍል መምህራን፣ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚያስተምሩ መምህራን፣ ኢንተር ፕራይዞች፣ በግል የፈጠራ ውድድር እንዲሁም የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የፈጠራ ስራዎቻቸውን አቅርበው የሚወዳደሩበት ምድብ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።

ዘንድሮ ለውድድሩ የተለየ ትኩረት በመስጠት እና ፍትሀዊ እና ሚስጥራዊ እንዲሆን ጥረት መደረጉን የተናገሩት ኃላፊው ለዚህም የዋቸሞ፣የወልቂጤ እና የወራቤ ዩኒቨርሲቲ መምህራን እንዲሁም የፖሊቴክኒክ ኮሌጆች መምህራን በዳኝነት እንደሚሳተፉም አስታውቀዋል።

ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ለወጡ ተወዳዳሪዎች ልዩ ሽልማት ይበረከትላቸዋል ያሉት አቶ አንተነህ በዚህ አውደ ርዕይ እና የፈጠራ ስራዎች ውድድር ላይ የቀረቡ ስራዎች ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ እንዲሸጋገሩ ይሰራል ብለዋል።

የተሻለ የፈጠራ ስራዎችን ያቀረቡ ተወዳዳሪዎች ችግር ፈቺ መሆናቸው ተረጋግጦ ወደ ምርት መግባት እንዲችሉ የገበያ ትስስር ይፈጠራል ያሉት ኃላፊው በፈጠራ ስራቸው የአእምሯዊ ንብረት ባለቤትነት ማግኘት እንዲችሉ ልዩ ድጋፍ እንደሚደረግም አቶ አንተነህ አስታውቀዋል።

የክልሉ ህዝብ፣ ባለሀብቶች፣ ተመራማሪዎች፣ ወጣቶች የሚዲያ አካላት የክልሉን የፈጠራ አቅም እንዲመለከቱ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች ውድድር አውደ ርዕይ እና የፓናል ውይይት የክልሉ ትምህርት ቢሮ፣ የሳይንስ ኢንፎርሜሽን እና ቴክኖሎጂ ቢሮ፣የስራ እድል ፈጠራ እና ኢንተር ፕራይዝ ልማት ቢሮ እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ በትብብር ማዘጋጀታቸውን አቶ አንተነህ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።

Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau

የከምባታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሕንፃ ግንባታ የመጨረሻው ወለል ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል።የከምባታ ዞን ፖሊስ መምሪያ/Kembata Zone Police Department
11/06/2026

የከምባታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሕንፃ ግንባታ የመጨረሻው ወለል ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል።

የከምባታ ዞን ፖሊስ መምሪያ/Kembata Zone Police Department

11/06/2026
በከምባታ ዞን ዶዮገና ከተማ አስተዳደር የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በንቅናቄ ተጠናክሮ ቀጥሏል‎በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች፣ በቀበሌ ለሚገኙ አርሶ አደሮ...
11/06/2026

በከምባታ ዞን ዶዮገና ከተማ አስተዳደር የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በንቅናቄ ተጠናክሮ ቀጥሏል

በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች፣ በቀበሌ ለሚገኙ አርሶ አደሮችና አጠቀላይ ነዋሪዎች የዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥና ዘመናዊ አሰራርን ለመዘርጋት የተጀመረው የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በከፍተኛ ሕዝባዊ ንቅናቄ እየተከናወነ ይገኛል።

‎ማህበረሰብን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ከፍ ለማድረግ እየተደረገ ያለው ርብርብ የሚበረታታ መሆኑንና ምዝገባው ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ተገቢው ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተመላክቷል።

‎የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያው ዘመናዊ፣ ፈጣንና አስተማማኝ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማስፈን ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ እስካሁን ያልተመዘገቡ የከተማችን ነዋሪዎች በየምዝገባ ማዕከላት በመገኘት ምዝገባ እንዲያካሂዱ ጥሪ ተላልፏል።

ዶዮገና ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

 #ገበታለሀምበሪቾ በኢፌዴሪ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ከፈለች ደምቦባ ለሀምበሪቾ የኢትዮጵያዊያን መንደር ግንባታ ፕሮጀክት 20,000 ብር አ...
10/06/2026

#ገበታለሀምበሪቾ

በኢፌዴሪ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ከፈለች ደምቦባ ለሀምበሪቾ የኢትዮጵያዊያን መንደር ግንባታ ፕሮጀክት 20,000 ብር አበርክተዋል።

ገበታ ለሀምበሪቾ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ: 1000746464871
:1000761497848
አዋሽ ባንክ ሂሳብ ቁጥር: 013201588434000
ዳሸን ባንክ ሂሳብ ቁጥር: 5351865591021
ኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ: 1049200203855
ብርሃን ባንክ: 1030986710069

ከላይ የቀረቡ የባንክ ሒሳብ ቁጥር አማራጮችን በመጠቀም "የጋራ ቤትዎን በጋራ ይገንቡ!!"

10/06/2026

የአካባቢ ብክለት በሰው ልጆች ጤና፣ በብዝኀ ህይወት፣ በኢኮ ሲስተም እና አጠቃላይ በስነ ምህዳር ላይ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተጽዕኖ ለመከላከል የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎችን በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ ተገለፀ።

10/06/2026

Address

Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kembata TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category