Kembata TV

Kembata TV "በሁሉም፤ ከሁሉም ተመራጭ!!"
(1)

12/08/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዱራሜ ክላስተር ሴቶች ማህበር ከዱራሜ ከተማ ለተወጣጡ ሴት አረጋውያን እና አቅመ ደካማ ተማሪዎች የዱቄት፣ የዘይትና የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

በ933 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮና ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ተፈረመየውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ...
12/08/2026

በ933 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮና ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ተፈረመ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ከቢጌታ ቢዝነስ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ጋር የ933 ሚሊዮን 609ሺ 566.54 ብር የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮና ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ፈርመዋል።

የፕሮጀክቱ ትግበራ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ከምባታ ዞን አንጋጫ ወረዳ የሚከናወን ሲሆን ወጪውም በመንግሥት በሚመደብ በጀት የሚሸፈን ነው።

በውሉ መሠረት ሥራው በ18 ወራት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ የሲቪል ግንባታ ሥራዎችን ጨምሮ የውሃ ቧንቧዎች፣ መገጣጠሚያዎችና የቫልቭ መለዋወጫዎች አቅርቦት፣ እንዲሁም የኤሌክትሮ-ሜካኒካል መሣሪያዎች ግዥና ተከላ ይካተታሉ።

ፕሮጀክቱ በCR-WASH መርሀ ግብር ሥር የሚተገበር ሲሆን፣ በአካባቢው የውሃ አገልግሎትን ለማስፋፋትና ለማሻሻል ያለመ ነው። በተለይም ለሕብረተሰቡ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን በማሳደግ የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል።

የሥራው ተቋራጭ ቀደም ሲል በተመሳሳይ የውሃ ፕሮጀክቶች ላይ በመሳተፍ የሥራ ልምድ ያካበተ መሆኑ ታውቋል።

በውል ስምምነቱ ወቅት ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ፣ ተቋራጩ የተወሰኑትን የጥራት መስፈርቶች በጥብቅ በመከተል ሥራውን በተያዘለት ጊዜ እንዲያጠናቅቅ አሳስበዋል። ፕሮጀክቱ ለሕዝብ ዘላቂ ጥቅም እንዲያስገኝ በሥራ አፈጻጸሙ ላይ ትኩረት እንዲደረግም ገልጸዋል።

ሚኒስቴሩ በበኩሉ የፕሮጀክቱን አፈጻጸም በቅርበት በመከታተል ሥራው በውሉ መሠረት እንዲከናወን እንደሚያደርግ ገልጿል።

የሥራው ተቋራጭም ለተሰጠው የሥራ ዕድል ምስጋና በማቅረብ፣ ፕሮጀክቱን በተወሰነው የጊዜ ገደብ ውስጥ፣ የጥራት መስፈርቶችን በማሟላት ለማጠናቀቅና ለማስረከብ ቃል ገብቷል።

Ministry of Water and Energy - Ethiopia

የከምባታ ዞን አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በቀዲዳ ጋሜላ እና ቃጫ ቢራ ወረዳዎች እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ልማት ሥራዎችን ጎበኙበከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ የተመራው...
12/08/2026

የከምባታ ዞን አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በቀዲዳ ጋሜላ እና ቃጫ ቢራ ወረዳዎች እየተከናወኑ ያሉ የግብርና ልማት ሥራዎችን ጎበኙ

በከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ የተመራው የዞኑ አስተባባሪ ኮሚቴ በቀዲዳ ጋሜላ እና በቃጫ ቢራ ወረዳዎች እየተከናወኑ የሚገኙትን የግብርና የልማት ሥራዎችና የፍራፍሬ ልማት ኢኒሼቲቮችን በመስክ ተዘዋውሮ ጎብኝቷል።

የልማት ምልከታው በዋናነት የመሬትን ሥነ-ምህዳርና ለምነት በከፍተኛ ሁኔታ በሚጎዳው የባህር ዛፍ ተክል ምትክ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸውንና የተሻሻሉ የአቮካዶ ዝርያዎችን በመትከል የአርሶ አደሩን ኑሮ በማሻሻል፣ እንዲሁም የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ስለመሆኑም ተመላክቷል።

ምልከታ ከተደረገባቸው አካባቢዎች አንዱ በሆነው ቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ጆሬ ቀበሌ አርሶ አደሩን በዘላቂነት ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመው የብሔራዊ አቮካዶ ልማት ፕሮግራም ኢኒሼቲቭ በተግባር ሲተረጎም ታይቷል።

በዚህም በወረዳው በአጠቃላይ 7ሺ የተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 3ሺ 704 የሚሆኑት በጆሬ ቀበሌ ቀሪዎቹ ደግሞ በአዜ ዶቦኦ ቀበሌ መተከላቸው ተገልጿል።

የፍራፍሬ ልማት ኢኒሼቲቭ አርሶ አደሩ ከባህላዊ አሰራር ወጥቶ በአጭር ጊዜ ምርት ወደሚሰጡና ዓለም አቀፍ የገበያ ተፈላጊነት ወዳላቸው የፍራፍሬ ዝርያዎች እንዲሸጋገር የሚያስችል የግብርና ትራንስፎርሜሽን ማሳያ መሆኑ በጉብኝቱ ወቅት ተብራርቷል።

በመስክ ምልከታው በቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ የተጀመረው የገጠር ኮሪደር ልማት አፈጻጸም ትኩረት የተሰጠው ሲሆን የክኮሪደር ልማቱን ከጥምር ግብርና ጋር አቀናጅቶ ማስኬድ የላቀ ውጤት እንደሚያስገኝም አቅጣጫ ተቀምጧል።

የዞኑ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ምልከታ ባደረጉባቸው ቀበሌያት ከአርሶ አደሮቹ ጋር በማሳ ውስጥ ውይይት ያደረጉ ሲሆን አርሶ አደሩ በማሳው ላይ የሚገኙ ቀሪ የባህር ዛፎችን በማስወገድ፣ በምትኩ ለተተከሉ ዘመናዊ የአቮካዶ ችግኞች ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ አሁን የጀመረውን ተስፋ ሰጪ የለውጥ ጉዞ አጠናክሮ እንዲያስቀጥል መክረዋል።

በተመሳሳይ በቃጫ ቢራ ወረዳ በተደረገው የመስክ ምልከታ ባህር ዛፍን በዘመናዊ የአቮካዶ ክላስተር የመተካቱ ስኬታማ ሥራ እየተተገበረ መሆኑ ተረጋግጧል።

በወረዳው በሚገኙ የመሳፌ፣ የቃጫቢራ፣ የዌሬራማ እና የገመሻ ቀበሌያት የፍራፍሬ መንደሮች በአጠቃላይ 18ሺ 519 የተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ተደርገው እንዲተከሉ መደረጉ ተገልጿል።

እነዚህ የተሻሻሉ የአቮካዶ ዝርያዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ፍሬ በመስጠት የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ አቅም በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድጉ በመሆናቸው፣ ችግኞቹ ጸድቀው ወደ ምርት እስኪሸጋገሩ ድረስ ሙያዊ ክትትልና እንክብካቤ ሊደረግላቸው እንደሚገባ በምልከታው ወቅት አጽንኦት ተሰጥቷል።

በመስክ ምልከታው የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ፣ የከምባታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ተክሌ ስዩም፣ የከምባታ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተሾመ ሔራሞ፣ የከምባታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ እና የዞኑ ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ወንድሙ ተሰማን ጨምሮ የቀዲዳ ጋሜላ እና የቃጫ ቢራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪዎችና የአስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዱራሜ ክላስተር ሴቶች ማህበር ከዱራሜ ከተማ ለተወጣጡ ሴት አረጋውያን እና አቅመ ደካማ ተማሪዎች የዱቄት፣ የዘይትና የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።‎‎ማ...
12/08/2026

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዱራሜ ክላስተር ሴቶች ማህበር ከዱራሜ ከተማ ለተወጣጡ ሴት አረጋውያን እና አቅመ ደካማ ተማሪዎች የዱቄት፣ የዘይትና የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

‎ማህበሩ "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ መልዕክት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ፣ ማቀጣጠያ እና የ2018 በጀት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ማካሔዱም ተመላክቷል።

‎የማህበሩ አባላት ከመድረኩ ጎን ለጎን የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆኑ የጽዳት እና የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በዱራሜ ከተማ አካሄደዋል።

‎በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ኤጄንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሀሊያ ሽፋ፤ የማህበሩ ዋና ዓላማ ሴቶች መብታቸውን እና ደህንነታቸውን እንዲያስጠብቁ እና ተጠቃሚነታቸውን እንዲያሳድጉ ከማድረግ በሻገር ለሌሎችም መጥቀም የሚችሉበት ደረጃ እንዲደርሱ ማስቻል መሆኑን ገልጸዋል።

‎ማህበሩ ከተቋቋመ በጣም አጭር ጊዜ ቢሆንም አበረታች ውጤቶችን ማስመዝገቡን የጠቆሙት ወ/ሮ ሀሊያ፤ ሴቶች ከተናጠል እንቅስቃሴ ይልቅ በጋራ በመሆን የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ አብራርተዋል።

‎ወይዘሮ ሀሊያ ሽፋ አክለውም የማህበሩን አንድነት በማጠናከር ለህብረተሰቡ መትረፍ መቻል ትልቅ ደስታን የሚፈጥር በመሆኑ፣ ለአረጋውያንና ተማሪዎች ለሚደረጉ መሰል የበጎ አድራጎት ስራዎች ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

‎የዱራሜ ክላስተር የሴቶች ማህበር ሰብሳቢ ወይዘሮ ክብነሽ ዶበሞ መደራጀት የሰው ልጆች መብት በመሆኑ ሴቶች በመደራጀት ጎጂ ልማደዊ ድርጊቶችን ለመከላከል፣ የሴቶች እኩልነት እና ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በማህበር መንቀሳቀስ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

‎ሴቶች በማህበር ተደራጀተው በጋራ በክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት ላይ በንቀት እየተሳተፉ እንደሚገኙ የገለጹት ወይዘሮ ክብነሽ ዶበሞ ዛሬም ከዱራሜ ከተማ ለተወጣጡ 20 አረጋውያን እና ተማሪዎች ድጋፍ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

‎የማህበሩ ምክትል ሰብሳቢ ወ/ሮ ፍሬወርቅ ታምራት በበኩላቸው በጎነት የማህበረሰብ ባህል እየሆኑ መምጣቱን ጠቅሰው በክረምት የበጎ ፈቃድ ተግባራት ሴቶች በማህበርም በግልም እያደረጉት ያለው ተሳትፎ አበረታች መሆኑን ገልፀዋል።

‎በዱራሜ ከተማ በተደረገው የጽዳት መርሀ ግብር እና በዶንግቾ ጤና ጣቢያ ግቢ ውስጥ ችግኝ ተካለ በማካሄዳቸው ለነገ ትውልድ ተስፋ የሚሆን ሥራ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

‎በመርሃ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ታየች ሞላ፣ በሠላም ሚንስቴር የዱራሜ ከተማ የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ ተግባራት አስተባባሪ አቶ ደርቤ አሰፋን ጨምሮ የክልሉ ሴቶች ማህበር አባለት የዱራሜ ከተማ አመራሮች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ለወላጆች!ልጆችዎን ትምህርት ቤት ለማስመዝገብ ፈልገው የፋይዳ ቁጥር አልደረሳቸውም ብለው አይጨነቁ! በቀላሉ በምዝገባ ወቅት በሰጡት ስልክ ወደ *9779 # በመደወል ወይም የፋይዳ ቴሌግራም ቦ...
11/08/2026

ለወላጆች!

ልጆችዎን ትምህርት ቤት ለማስመዝገብ ፈልገው የፋይዳ ቁጥር አልደረሳቸውም ብለው አይጨነቁ!

በቀላሉ በምዝገባ ወቅት በሰጡት ስልክ ወደ *9779 # በመደወል ወይም የፋይዳ ቴሌግራም ቦት https://t.me/FaydaHelpBot በመጠቀም በራስዎ ማስላክ ወይም ምዝገባው ያለበትን ደረጃ ማወቅ ይችላሉ።

የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በሁለቱም ሴክተሮች የተጀመረውን የሪፎርም ስራ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ...
10/08/2026

የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በሁለቱም ሴክተሮች የተጀመረውን የሪፎርም ስራ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ እና የክልሉ የንግድ እና ገበያ ልማት ቢሮ የህገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር፣ ኑሮ ማረጋጋት እና የታክስ ህግ ተገዢነት ለማረጋገጥ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ ተካሂዷል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በምክክር መድረኩ ማጠቃለያ በሰጡት የስራ መመሪያ እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት በክልሉ ይስተዋሉ የነበሩ መሰረታዊ ችግሮችን መፍታት መቻሉን ጠቁመዋል።

በክልሉ ካጋጠሙ ችግሮች ውስጥ በዋናነት የፋይናንስ፣የአፈር ማዳበሪያ፣የህዝብ አንድነት እና ሌሎችም ተጠቃሽ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ያጋጠሙ ፈተናዎችን በመሻገር መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት ጥረት መደረጉን ተናግ ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

ስራን መሰረት ያደረገ የአመራር ስርዓት ተፈጥሯል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ይህም በሁሉም ዘርፍ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚያግዝም አመላክተዋል።

በክልሉ የብልጽግና ፓርቲ እሳቤን መሰረት ያደረገ የስራ መመሪያ ተግባራዊ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በሁሉም መስኮች የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ጀምረናል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

ኮንትሮባንድ፣ግብር መሰወር፣በድርድር ገንዘብ መቀበል፣ያለ አግባብ የምርት ክምችት፣የተሰጠን አቅጣጫ ተቀብሎ ተግባራዊ አለማድረግ፣ስራን በፍላጎት ያለመስራት፣አድርባይነት እና ጠባቂነት ያልተሻገርናቸው ችግሮች ናቸው ብለዋል።

በሁለቱም ሴክተሮች የተጀመረውን የሪፎርም ስራ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

በአግባቡ ማቀድ፣ጸጋችንን መለየት፣ያለውን ምቹ ሁኔታን ያገናዘበ አመራር መፍጠር ይገባል ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በስራ መመሪያቸው ጠቅሰዋል።

ከፈጻሚ አካላት እና ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ተግባቦት መፍጠር ወሳኝ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

ተከታታይ ጠንካራና የማይቋረጥ ክትትል ማድረግ ተገቢ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ህግ የማስከበር ስራ ላይ ማተኮር ወሳኝ ስለመሆኑም ተናግረዋል።

የበቃ አመራር እና ፈጻሚ መፍጠር በሁለቱም ሴክተሮች የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።

ጠንካራ ህግ የማስከበር ስራው በተገልጋዩም ሆነ አገልግሎት በሚሰጠው አካል ላይ ተግባራዊ በማድረግ መስራት ይገባል ብለዋል።

የተገኘ ውጤት እና የተወሰደ እርምጃ ለህብረተሰቡ ማሳወቅ እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ በስራ መመሪያቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቀመረያ ረሻድ በበኩላቸው በ2018 በጀት አመት በገቢ ሴክተሩ ጠንካራ ስራ ተግባራዊ በመደረጉ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው ውጤት እንደተጠበቀ ሆኖ በአፈጻጸም ረገድ የተስተዋሉ ውስንነቶች እንደነበሩም ኃላፊዋ አብራርተዋል።

የታክስ ህግ ከማስከበር ረገድ የተስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት መድረኩ ወሳኝ መሆኑን ወ/ሮ ቀመሪያ ጠቁመዋል።

በክልሉ ታማኝ ግብር ከፋዮች እንዳሉ ሁሉ ግብርን ለመሰወር እና ለማጭበርበር ፍላጎት ያላቸው አካላት መኖራቸውንም ኃላፊዋ ጠቁመዋል።

ግብር ከጥንት ጀምሮ ይከፈላል ያሉት ኃላፊዋ ይህ ባህል ተጠናክሮ አለመቀጠሉን ጠቅሰዋል።

ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ በዘርፉ ግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል።

የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋዬ በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ተግባራዊ እየተደረጉ በነበሩ ስራዎች የተስተዋሉ ውስንነቶችን መፍታት እና በጥንካሬ የተለዩ ጉዳዮችን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጠናከር በዘርፉ ለውጥ ለማምጣት ወሳኝ ነው ሲሉም ጠቁመዋል።

በክልሉ በወቅታዊ የክረምት ስራዎች የንግድ ፈቃድ እድሳት በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ በተደረገ ጥረት ከ40 ሺ በላይ ተግባራዊ ማድረግ ስለመቻሉም ዶ/ር ባዩሽ አስረድተዋል።

ከነዳጅ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ሀብት የሚጠይቅ መሆኑን የተናገሩት ኃላፊዋ ለአዳዲስ ማደያዎች ፈቃድ እየተሰጠ አለመሆኑን አብራርተዋል።

በክልሉ 28 ወረዳዎች የነዳጅ ማደያ የላቸውም ያሉት ኃላፊዋ በዘርፉ እያጋጠመ ያለውን ችግር ለመፍታት እንደ ክልል በልዩ ውሳኔ ተግባራዊ እየተደረገ ነው።

በገቢና ንግድ ዘርፎች ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ለመፍታት በቁርጠኝነት ይሰራል - እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በገቢና ንግድ ሥርዓት ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት አስገዳጅ ሕግ የማስከበር ...
10/08/2026

በገቢና ንግድ ዘርፎች ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ለመፍታት በቁርጠኝነት ይሰራል - እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

በገቢና ንግድ ሥርዓት ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት አስገዳጅ ሕግ የማስከበር ሥራ ላይ ትኩረት ይደረጋል አሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፡፡

በክልሉ ሕገ ወጥ ንግድ ቁጥጥር፣ ኑሮ ማረጋጋት እና የታክስ ህግ ተገዢነትን ለማጠናከር ያለመ ምክክር እየተካሄደ ነው፡፡

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት በገቢና ንግድ ዘርፎች የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን በዘላቂነት ለማስወገድ መወያየትና ለቀጣይ ሥራ ተግባቦት መፍጠር አስፈላጊ ነው፡፡

የታክስ ሕግን በማስከበር ገቢን ለማሳደግ የጋራ ጥረት ይጠይቃል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የገቢ አሰባሰብ ሒደቱ የክልሉ ኢኮኖሚ ከሚያመነጨው ገቢ አንጻር አሁንም ቀሪ ስራ እንዳለ አመላክተዋል።

የገቢ አሰባሰብ ሥርዓት እያደገ ሲሄድ የክልሉን ከተሞች የመሰረተ ልማት ፍላጎት ማሟላት እንደሚያስችል አብራርተዋል።

በየጊዜው እያደገ ለመጣው የሕዝብ የልማት ፍላጎት ምላሽ መስጠት የሚቻለው ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ ሲቻል ብቻ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

በክልሉ የንግድ ሥርዓቱን መቆጣጠር እና መስመር ማስያዝ ይገባል፤ በሀገሪቱ የሚወጡ ደንቦች እና መመሪያዎችን ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

በንግድ እና ገቢ ዘርፎች እያጋጠመ ያለውን ችግር በመፍታት ረገድ የላቀ ቁርጠኝነት እንደሚጠይቅም ርዕሰ መስተዳድሩ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

እያጋጠመ ያለውን የዋጋ ንረት በመቆጣጠር በሕብረተሰቡ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ በትኩረት መስራት ይገባል ማለታቸውንም የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመልክቷል፡፡

የምክክር ሒደቱ ወደ ተስፋ ሰጪ ደረጃ ላይ እየደረሰ ይገኛል - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያእየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሒደት ተጠናክሮ መቀጠሉን እና አበረታች ደረጃ ላይ መድ...
10/08/2026

የምክክር ሒደቱ ወደ ተስፋ ሰጪ ደረጃ ላይ እየደረሰ ይገኛል - ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ

እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሒደት ተጠናክሮ መቀጠሉን እና አበረታች ደረጃ ላይ መድረሱን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አስታውቀዋል።

ዋና ኮሚሽነሩ የምክክር ጉባኤውን ሒደት አስመልክተው በሰጡት መግለጫ እንዳብራሩት፣ በአሁኑ ወቅት 250ዎቹ የምክክር ቡድኖች አጀንዳዎቻቸውን ሁለት ጊዜ በመመልከት እና በማጠናቀር ለ500ዎቹ ቡድኖች እያዘጋጁ ይገኛሉ።

አብዛኛዎቹ ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ ሲሆን፣ አጠቃላይ የ250ዎቹ ቡድኖች የሀሳብ ማጠናቀር ሥራ ዛሬ ማታ ሙሉ በሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ቀጣዩ ሂደት ደግሞ 500ዎቹ ቡድኖች እነዚህን የተሰባሰቡ ሀሳቦች ይበልጥ በማዳበር ለዋናው ጉባኤ የሚያዘጋጁበት እንደሚሆን ፕሮፌሰር መስፍን ጠቁመዋል።

ይህ የሀሳብ ማጠናቀር እና የምክክር ሂደት ቀላል የሚባል እንዳልነበር ያስታወሱት ፕሮፌሰር መስፍን፣ ከ10 ቡድን ጀምሮ በርካታ የሀሳብ ፍጭቶች ሲደረጉባቸው መቆየታቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በመጀመሪያዎቹ ምዕራፎች ላይ ተሳታፊዎች ያመጡት ሀሳብ እንደመጣ እንዲያልፍላቸው ይፈልጉ ስለነበር ከፍተኛ መጨቃጨቆች እና መጎራበጦች ታይተው እንደነበር አልሸሸጉም።

ይሁን እንጂ ኮሚሽኑ ውይይቶቹ በግለሰቦች ላይ ሳይሆን በሀሳብ ላይ ብቻ እንዲያተኩሩ በቅርበት እየተከታተለ እና እየተቆጣጠረ እዚህ በመድረሱ፣ በአሁኑ ወቅት ውይይቱ እየለዘበ መጥቶ ትክክለኛውን የመግባባት መሥመር ሊይዝ መቻሉን ዋና ኮሚሽነሩ አረጋግጠዋል።

"መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለሙስናና ለእንግልት የሚዳርጉ አሠራሮችን ሥር ነቀል በሆነ መንገድ የሚቀይር ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
10/08/2026

"መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለሙስናና ለእንግልት የሚዳርጉ አሠራሮችን ሥር ነቀል በሆነ መንገድ የሚቀይር ነው" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በተከናወነ ጠንካራ ስራ የክልሉን ገቢ የመሰብሰብ አቅም ወደ 35 ቢሊየን ብር ማሳደግ መቻሉ ተገለፀየማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ እና የክልሉ የንግድ እና ገ...
10/08/2026

ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በተከናወነ ጠንካራ ስራ የክልሉን ገቢ የመሰብሰብ አቅም ወደ 35 ቢሊየን ብር ማሳደግ መቻሉ ተገለፀ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ እና የክልሉ የንግድ እና ገበያ ልማት ቢሮ የህገ-ወጥ ንግድ ቁጥጥር፣ ኑሮ ማረጋጋት እና የታክስ ህግ ተገዢነት ለማረጋገጥ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) በመድረኩ መክፈቻ የገቢ እና የንግድና ገበያ ልማት ሴክተሮች በኢኮኖሚ ዘርፍ እና ኑሮን በማረጋጋት ረገድ የላቀ ሚና አላቸው ብለዋል።

ክልሉ ስራ ሲጀምር የገቢ ሴክተሩ የሚያመነጨው ገቢ ከ8 ቢሊየን ብር በላይ እንዳልነበር ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

ባለፉት ተከታታይ ዓመታት ለዘርፉ በተሰጠ ትኩረት ይህን አሀዝ ከ8 ወደ 35 ቢሊየን ብር ማሳደግ ስለመቻሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በንግግራቸው አመላክተዋል።

በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በአመት በአማካይ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን ከ15 እስከ 20 ቢሊየን ብር በማሳደግ የክልሉን ገቢ የማመንጨት አቅም ከ120 ቢሊየን ብር በላይ ከፍ ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል።

የገቢ አቅምን ማሳደግ የከተሞችን ገጽታ መለወጥ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የመሰረተ ልማት ስራን ለማስፋፋት፣ የአርሶ አደሩን ህይወት ለመቀየር የሚደረገውን ጥረት ውጤታማ ለማድረግ አመራሩ፣ ፈጻሚ አካላት፣ የንግዱ ማህበረሰብ እና መላው የክልሉ ህዝብ የድርሻውን እንዲወጣም ርዕሰ መስተዳድሩ ጥሪ አቅርበዋል።

በሌላ በኩል የንግድ ስርዓቱን ለማዘመን የተሳለጠ አሰራር መዘርጋት አስፈላጊ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

በንግድ ስርዓቱ ውስጥ ህገ-ወጥነትን መከላከል፣ የግብይት ማዕከላትን የማስፋፋት፣ ምርትን በበቂ ሁኔታ ማቅረብ፣የዋጋ ንረትን መቆጣጠር፣ የሸማች ማህበራትን ማጠናከር እንዲሁም ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በመግባባት መስራት ተገቢ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በመድረኩ በሁለቱም ሴክተሮች ወቅታዊና አስፈላጊ አጀንዳዎች ላይ በቂ ምክክር በማድረግ በተግባር የሚተረጎሙ አቅጣጫቻዎችን ማስቀመጥ የሚያስችል ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

Address

Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kembata TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category