የዱራሜ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Durame
  • የዱራሜ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የዱራሜ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ✍️ወቅታዊና ተአማኒነት ያለዉን መረጃ ለህብረተሰቡ ተደራሽ እናደርጋለን!
✍️We strive to address the p***c whith reliable and timely information!

በክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አማካሪ በአቶ ይርጋው ሐንዲሶ የተመራ የአመራር ቡድን በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በመገኘት ያደረገዉን ድጋፋዊ ክትትሉን በማጠናቀቅ ክቡር ከንቲባ አቶ አ...
05/11/2025

በክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አማካሪ በአቶ ይርጋው ሐንዲሶ የተመራ የአመራር ቡድን በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በመገኘት ያደረገዉን ድጋፋዊ ክትትሉን በማጠናቀቅ ክቡር ከንቲባ አቶ አክሊሉ አቡቶ እና አስተባባሪዎች በተገኙበት ግብረ መልስ ሰጥተዋል።

ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የተወጣጣ የአመራር ቡድን በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በመገኘት 1ኛ ሩብ ዓመት የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎች አፈፃፀም ተመልክቷል።

ድጋፋዊ ክትትል ቡድኑ በቆይታቸው የቤተሰብ እና ህብረት ያሉበትን ደረጃ እና የአደረጃጀት ሂደቱን በተመለከተ በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ከተማ ቀበሌ በማቅናት የተመለከቱ ሲሆን በማጠቃለያውም የተለያዩ የልማት ሥራዎችን የመስክ መልከታ አድርገዋል።

በቆይታቸዉም በከተማ አስተዳደሩ በሁሉም ዘርፍ ያለዉ ዉጤት እና እንቅስቃሴ አበራታች እንደሆነ በመግለፅ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ እና ቀጣይነት ባለዉ መልኩ እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

በመርሐ-ግብሩም የክልሉ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አማካሪ በአቶ ይርጋው ሐንዲሶ ፣ የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ አክሊሉ አቡቶ ፣ የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙልጌታ ተመስገን ፣ የክልሉ አመራር ፣ የዱራሜ ከተማ አስተባባሪ አካላት እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር  የሰብዓዊ አገልግሎቱን በተገቢ ሁኔታ ተደራሽ እንዲያደርግ  የህዝብ የአባልነት ምጣኔን እና የገቢ አቅሙን ማሳደግ ይገባል ተባለ። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበ...
05/11/2025

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሰብዓዊ አገልግሎቱን በተገቢ ሁኔታ ተደራሽ እንዲያደርግ የህዝብ የአባልነት ምጣኔን እና የገቢ አቅሙን ማሳደግ ይገባል ተባለ።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከምባታ ዞን ቅርንጫ ጽ/ቤት '' ለሰብዓዊነት እንኖረለን በሚል መሪ ቃል'' የአባላት ማበራከትና የገቢ ማሳደጊያ ዞናዊ የንቅናቄ መድረክ በዱራሜ ከተማ አካሂዷል።

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ ደነቀ ደልከሶ ሰብዓዊነትን የተላበሰ የሚረዳዳ ፣ የሚተባበር ፣ ለወገኑ ጉዳት ፈጥኖ የሚደርስና ህዝባዊ መሠረት ያለው ተቋም ለመገንባት በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

ተቋማት በተገቢ ሁኔታ መገንባት የተቋቋሙበትን ዓላማ በአግባቡ እንዲፈጽሙና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንዲያረጋግጡ በንቅናቄ የሚመሩ ሥራዎች ወደ ተግባር መቀየር አለባቸውም ብለዋል።

ቀይ መስቀል ማህበር እንደ ከምባታ ዞን የህዝብ ተጋላጭነትን በመመከት የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን ያብራሩት አቶ ደነቀ ደልከሶ የተቋሙን ሁለንተናዊ አቅም ለማሳደግ ስለ ተቋሙ ተግባራት ለህብረተሰቡ በየደረጃው ግንዛቤ መፍጠርና ማስተባበር ይገባልም ነው ያሉት።

የቀዲዳ ጋሜላ ወረዳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና የማህበሩ ቦርድ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ውባየሁ በቀለ ቀይ መስቀል ተቋም የሰብዓዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋም ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

ማህበሩ በ1985 ዓ/ም ጀምሮ በከምባታ ዞን በማስተባበሪያ ጽ/ቤት ደረጃ ተቋቋሞ አለም አቀፍ የሰብዓዊ አገልግሎት መርሆችን መሠረት ያደረጉ በርካታ የሰብዓዊ ተግባራትን ስፈጽም መቆየቱን የገለፁት የተከበሩ ወ/ሮ ውባየሁ በቀለ በመድኃኒት አቅርቦት፣ በአፈር ጥበቃ፣ በደን ልማት፣ በከተማ ውኃ ዝርጋታ፣ ለአደጋ ተጋላጮች ፈጣን ምላሽ መስጠትና መሰል ተግባራትን እየፈፀመ ይገኛልም ብለዋል።

የተከበሩ ውባየሁ በቀለ አክላውም ተቋሙ ህዝባዊ መሠረት ይዞ ሰብዓዊ አገልግሎቱን በሚገባ ተደራሽ ማድረግ እንዲችል አባላትን በማፊራትና የገቢ አቅሙን ከማጠናከር አኳያ ልዩ ትኩረት በመስጠት በየደረጃው በቅንጅት መሥራትና ውጤታማ እንዲሆን ማስቻል ከሁሉም የሚጠበቅ ኃላፊነት በመሆኑ ጊዜ ልሰጠው አይገባም ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ከምባታ ዞን ቅርንጫ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጥላሁን ወንታሞ ተቋሙ ከአስቸኳይ ጊዜ እርዳታን ተደራሽ ከማድረጉ ባሻገር በተለያዩ የልማት ሥራዎችም ንቁ ተሳትፎ እያደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

የተቋሙ ዋንኛ የገቢ ምንጭ ከአባላት የሚገኝ መዋጮ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ጥላሁን ወንታሞ ነባር አባላት የሚከፍሉ መዋጮዎችን ሳይጠባጠብ በአግባቡ መሥራትና ማስተባበር፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና በጎ ፈቃደኞች አዳዲስ አባላትን በብዛትና በጥራት ማፍራት፣ የተቋሙን አቅም ለማጠናከር ያግዛልም ብለዋል።

እንደዞን ከ36,130 አባላት ብቻ እና ከ2.5 ሚሊየን የማይበልጥ ገቢ በየዓመቱ መሰብሰቡ ሰብዓዊ አገልግሎቱን በአግባቡ ተደራሽ ለማድረግ ተግዳሮት እየፈጠረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በተያዘው በጀት ዓመት የአባላት ቁጥሩን ወደ 138,168 በማሳደግ ከ35.9 ሚሊየን በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ልዩ እቅድ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አቶ ጥላውን ገልፀዋል።

ማህበሩ ሰብዓዊ አገልግሎቱን የበለጠ ተደራሽ እንዲያደርግ ይህ ልዩ እቅድ ስኬታማ እንዲሆን አመራሩና ባለድርሻ አካላት በየደረጃው የተቀናጀ ርብርብ እንዲያደርጉም አቶ ጥላሁን ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

በተዘጋጀው የማህበሩ አባላት እና ገቢ ማሳደጊያ የንቅናቄ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን አመራሩም ማህበሩ ህዝባዊ መሠረት ይዞ የገቢ አቅሙን አሳድጎ ሰብዓዊ ተግባሩን የበለጠ ተደራሽ በማድረግ ከአቻ ዞኖች ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆን የማጠናከር ሥራ ለመስራት የጋራ ተግባቦት ተፈጥሮ መድረኩ ፍፃሜውን አግኝቷል።

በመድረኩ የከምባታ ዞን ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ_ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አስካለ ሰሶ፣ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተወካይና የዞኑ ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ መልካሙ ማቴዎስ፣ የከምባታ ዞን መንግስት ዋና ተጠሪ ተወካይ አቶ ምህረቱ መኬቦን ጨምሮ የሁሉም ወረዳ አስተዳዳሪዎች ፣ ከንቲባዎች፣ የፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊዎችና የማህበሩ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝቷል።

በክልሉ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አማካሪ በአቶ ይርጋው ሐንዲሶ የተመራ የአመራር ቡድን በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በመገኘት የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛሉ፦ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽ...
05/11/2025

በክልሉ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አማካሪ በአቶ ይርጋው ሐንዲሶ የተመራ የአመራር ቡድን በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በመገኘት የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛሉ፦

ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የተወጣጣ የአመራር ቡድን በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በመገኘት 1ኛ ሩብ ዓመት የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎች አፈፃፀም እየተመለከቱ ነዉ።

አንድ ሀገርነት ችግራችን ነው ብለው ወደ ሁለት የመጡ ሀገራት አሉ፡፡ ሁለትነት ግን ከአዙሪቱ አላወጣቸውም፡፡ በአንድ ሀገር የነበረው ችግር በሁለት ሀገር ነው የቀጠለው፡፡ ሐሳብ አልባ ፖለቲካ...
05/11/2025

አንድ ሀገርነት ችግራችን ነው ብለው ወደ ሁለት የመጡ ሀገራት አሉ፡፡ ሁለትነት ግን ከአዙሪቱ አላወጣቸውም፡፡ በአንድ ሀገር የነበረው ችግር በሁለት ሀገር ነው የቀጠለው፡፡ ሐሳብ አልባ ፖለቲካ የታሪክ፣ የፖለቲካ፣ የሃይማኖት፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቅሬታዎችን ከትናንት ስቦ ያመጣል፡፡ በዘመናዊ መሣሪያዎች ኃይል ደግሞ ዛሬ ላይ ያቀጣጥላቸዋል፡፡

የመደመር መንግሥት፣ ገጽ 361፣2018 ዓ.ም

በክልሉ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አማካሪ በአቶ ይርጋው ሐንዲሶ የተመራ የአመራር ቡድን በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በመገኘት የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያ ሩብ አመት የፖርቲና የመንግስት ዋና ዋ...
05/11/2025

በክልሉ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አማካሪ በአቶ ይርጋው ሐንዲሶ የተመራ የአመራር ቡድን በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በመገኘት የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያ ሩብ አመት የፖርቲና የመንግስት ዋና ዋና ስራዎች አፈፃፀም ድጋፋዊ ክትትል እያደረጉ ይገኛሉ።

ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የተወጣጣ የአመራር ቡድን በዱራሜ ከተማ አስተዳደር በመገኘት 1ኛ ሩብ ዓመት የፓርቲና የመንግሥት ሥራዎች አፈፃፀም እየተመለከተ ነዉ።

በዚህ መሠረት የቤተሰብ እና ህብረት ያሉበትን ደረጃ እና የአደረጃጀት ሂደቱን በተመለከተ በከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ከተማ ቀበሌ በመሄድ ድጋፋዊ ክትትል እያደረጉ ይገኛሉ።

በመርሐ-ግብሩም የክልሉ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አማካሪ በአቶ ይርጋው ሐንዲሶ ፣ የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙልጌታ ተመስገን ፣ የክልሉ አመራር ፣ የዱራሜ ከተማ አስተባባሪ አካላት እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ከክልሉ ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ የተወጣጡ የአመራር እና የባለሙያ የድጋፍና የክትትል ቡድን በዱራሜ ከተማ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት በመተግበር ላይ ያሉ የልማት ሥራዎችን ምልከታ በማድ...
04/11/2025

ከክልሉ ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ የተወጣጡ የአመራር እና የባለሙያ የድጋፍና የክትትል ቡድን በዱራሜ ከተማ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት በመተግበር ላይ ያሉ የልማት ሥራዎችን ምልከታ በማድረግ ግብረ መልስ ሰጥቷል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ዘርፍ ሃላፊ በሆኑት ኢንጅነር ዝናቡ ተካበ የተመራ የአመራር እና የባለሙያ የድጋፍና የክትትል ቡድን የመስክ ምልከታዉን በማጠናቀቅ ግብረ መልስ ሰጥቷል።

ቡድኑ በከተማ አስተዳደሩ በአንደኛ ሩብ ዓመት የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን የተመለከተ ሲሆን በሂደቱም ኮሪደር ሥራዎችይ ፣ የፕላን ሥራዎች ፣ የህብረተሰብ መድኃኒት ቤት ግንባታ ያለበት ደረጃ ፣ የክልሉ ቢሮ ህንፃ ግንባታ እና ሌሎችም የልማት ሥራዎችን ተዟዙረዉ ተመልክተዋል።

በከተማ አስተዳደሩ በሁሉም ዘርፍ ያለዉ የልማት እንቅስቃሴ አበራታች እኔደሆነ የተገለፀ ሲሆን የሚሰሩ ሥራዎችም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ ልሰሩ እንደሚገባ ተገልጿል።

በመድረኩም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ዘርፍ ሃላፊ በሆኑት ኢንጅነር ዝናቡ ተካበ ፣ የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ አክሊሉ አቡቶ ፣ የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ ሙልጌታ ተመስገን ፣ የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዲሴ ዳንኤልን ጨምሮ የክልሉ ፣ የዞን አመራሮች እና የዱራሜ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አመራሮች ተገኝተዋል።

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ትውልድ መገንቢያ ማዕከላት ናቸው።በሚል መሪ ሃሳብ የ2018 ዓ/ም የሠልጣኝ ቅበላን አስመልክቶ የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል።በማዕከላዊ  ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ቴክኒክ...
04/11/2025

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ትውልድ መገንቢያ ማዕከላት ናቸው።በሚል መሪ ሃሳብ የ2018 ዓ/ም የሠልጣኝ ቅበላን አስመልክቶ የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ በከምባታ ዞን የዱራሜ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓም ሥልጠና ዘመን የሰልጣኝ ቅበላ የንቅናቄ መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር ማካሄዱን ተመልክቷል ።

የከምባታ ዞን የህዝብ ተወካዮች ምከር ቤት ዋና አፈ _ጉባኤ ክብርት አስካለ ሰሶ በንቅናቄ መድረኩ ተገኝተው እንደተናገሩት ኮሌጁ በየጊዜው አቅሙን እያሳደገ በቴክኖሎጂ እየዘመነ የስልጠና ህደቱንም ውጤታማና ለትውልድ የሚሸጋገር እያደረገው መምጣቱ የሚያስመሰግነው ነው ብለዋል።

ዘሬ በመድረኩ የተገኘን አካላት ባለድርሻ ብቻ ሳንሆን ባለቤት ሆነን ተቀናጅተንና ተባብረን ከሰራን ለቅበላ ከተቀመጠው ዕቅድ በላይ ማሳከት እንችላለን ብለዋል።

በኮሌጁ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም እንዲሁም የትምህርት ቤቶችን ርዕሰ መምህራን ያሉንን ተማሪዎች መረጃ በስም ዝርዝር በማደራጀት ከያዙ ባላድርሻ አካላት ጋር በመሆን እንደ ምክር ቤት የጉባኤ መድረኮችን በመጠቀም የሰልጣኝ ቅበላ አጀንዳ ከሌሎች ተግባራት ጋር እየተገመገመ ከተመራ ለማሳካት እንችላለን ብለዋል።

የከምባታ ዞን የዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ በመድረኩ ተገኝተው እንደገለጹት ኮሌጁ በቴክኖሎጂ፣ በሰው ሀይል ፣ በግብዓት አቅርቦት እና በአመራር ብቃት ላሳየው እምርታ ያላቸውን አድናቆት ገልፀው ኮሌጁ የሕዝብ ሀብት እንደመሆኑ መጠን ሠልጣኞች በአመለካከት ፣ በክህሎትና በእውቀት የበለፀጉ የበቁ እና ተወዳዳሪ ሆነው እንድወጡ በማድረግ ሁሉም የድርሻውን በቅንነትና በመተባበር ማከናወን ይጠበቅብናል ብለዋል።

አሁን የተቀመጠውን የቅበላ ዕቅድ ለማሳካት ሁሉንም አቋሞቻችንን አሟጠን በመጠቀም ያሉንን አደረጃጀቶች እስከ ታችኛው 1ለ10በማነቃነቅ ያላለፉተመሪዎች መቀበያ የሚለውን በማስቀረት ሁሉም ወጣት ገብቶ የተሻለ ሥልጠና አግኝቶ እራሱንና ሀገርን የሚጠቅም ሥራ እንድሰራ እንዲሁም የብልግና ጉዞአችንን እንድያፈጥን የበኩላችንን ማበርከት ይጠበቅብናል ብለዋል።

የግንዛቤ ክፍተቶችን በመቅረፍ መረጃዎችን በአግባቡ በማደራጀት እንድሁም በማዕከሉ ሰልጥነው ውጤታማ የሆኑ ወጣቶችን በሚዲያ ለህብረተሰቡ በማስተዋወቅ ተቋሙ የሚሰጣቸውን ሥልጠናዎች ተደራሽ በማድረግ አሰልጥነው በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የሥራ ዕድል ተሳታፊ እንድሆኑ ጠንካራ ሥራ መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል።

የከምባታ ዞን ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና መምሪያ ሀላፊ አቶ አብርሃም ጳውሎስ እንደተናገሩት የሚበዛ የሚሸጋገር እና ትውልድ የሚቀርጽበት ተቋም በመሆኑ ልዩ ትኩረት ልሰጠው የሚገባ ተቋም መሆኑን ገልጸው ለወጣቶች የሥራ ዕድል እንድፈጠር የኑሮ ውድነት እንድቃለል በወቅቱ ገበያ ተወዳዳሪ የሚሆን ብቁ እና አምራች ዜጋ ለማፍራት እንዲቻል ወጣቶችን ወደ ስልጠና ኮሌጅ እንድመጡ የቅስቀሳ ሥራ መሥራት ይገባል ።

በመሆኑም የሥልጠናውን ዓላማ እና አስፈላጊነት ፋይዳ በህብረተሰባችን ውስጥ በማስረጽ የተዛቡ አመለካከቶችን በመቅረፍ የቅስቀሳ እና የንቅናቄ ሥራዎቻችንን በሚዲያ ፣በሃይማኖት ተቋማት ፣በእድሮች እና በቀበሌ አንድ ለ አሥር ተቀናጅቶ በመሥራት የተቀመጠውን የቅበላ ግብ ማሳካት ያስፈልጋል ተብለዋል ።

የዱራሜ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ዶክተር ግርማ ጌታሁን በበኩላቸው ኮሌጁ ከጊዜ ወደ ጊዜ የተሻለ አፈጻጸም በማስመዝገብ ለበርካቶች በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ የሥራ ዕድል በመፍጠር ፣በቴክኖሎጂ ራሱን በመገንባት የተሻለ ሥልጠና ለተማሪዎች በማቅረብ በISO እስከ መመዝገብ የሚያስችሉ ሥራዎችን በመሥራት ከክልል አልፎ በሀገር ደረጃ ተፎካካሪ ኮሌጅ መሆኑን ገልጸዋል።

አያይዘውም ኮሌጁ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራትና የአሰልጣኝ ቅበላ ማስፈፀሚያ ስነድ በዝርዝር ያቀረቡት ዶክተር ግርማ የ2018 ዓም የተማሪ ቅበላ ዕቅዳችን 680 ሆኖ እየገጠመን ያለውን የቅበላ ተግዳሮት በቅረፍ ከዞን አመራር ጀምሮ እስከ ታችኛው ቀበሌ ድረስ የንቅናቄ ስራዎቻችንን አጠናክረን በመሥራት ከዕቅድ በላይ ማሳከት ይጠበቅብናልም ብለዋል።

ኮሌጁ ባሉት በሁሉም ዘርፎች የደረሰበትን ከፍታና የሚሰጣቸውን የሥልጠና ህደቶች በሚጠበቀው ደረጃ የሚያሳይ የሚዲያ ሥራ ያልተሰራ መሆኑን አንስተው በቀጣይ አሰልጣኞችን የሚስብና የሚያማልል የህዝብ ግኑኝነት ሥራ መሥራት ይገበልም ብለዋል።

እንድሁም አሰራሮቻችን ሁሉም ስስተም ላይ የገቡ በመሆናቸው አሰልጣኝ ምዝገባ የትምህርት ጥራት አጠባበቅ ለድርድር የማይቀርብ እንደሆነ ገልፀው የሥራ ባህላችንን በማሻሻል በህገወጥ ደላሎች የሚደርሰውን ዘረፋና እንግልት ለማስቀረት ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መሥራት የስፈልጋልም ብለዋል ።

በመጨረሻም በንቅናቄ መድረኩ የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አክሊሉ አቡቶን ጨምሮ የዞን ካቢኔ አባላት የሶስቱ ከችመንት መዋቅሮች አስተባባሪ አካላትና የኮሌጁ ማናጅመንት አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።

የ2018 ዓ.ም 1ኛ ሊግ የዉድድር ዘመን ሊጀመር መቃረቡን ተከትሎ ከነገ ጀምሮ ምልመላ እንደሚደረግ ተገለፀ።የዱራሜ ከነማ እግር ኳስ ቡድን በሊጉ የሚሳተፉ ተጨዋቾች ቦርድ ግልፅ በሆነ መልኩ ...
04/11/2025

የ2018 ዓ.ም 1ኛ ሊግ የዉድድር ዘመን ሊጀመር መቃረቡን ተከትሎ ከነገ ጀምሮ ምልመላ እንደሚደረግ ተገለፀ።

የዱራሜ ከነማ እግር ኳስ ቡድን በሊጉ የሚሳተፉ ተጨዋቾች ቦርድ ግልፅ በሆነ መልኩ ምልመላ እንዲደረግ በወሰነው ዉሳኔ መሠረት መሳተፍ የሚፈልጉ ተጨዋቾች በተባለው ቀንና ሰዓት እንዲሳተፉ ከተማ አስተዳደሩ ጥሪ ያቀርባል።

በዱራሜ እና አከባቢዋ የምትገኙ ስፖርተኞች ከነገ 4:00 ሰዓት ጀምራችሁ በዱራሜ ሁለገብ ስታዲየም በመገኘት በመወዳደር እድላችሁን እንድትሞክሩ ሲል ከተማዉ ያሳስባል።

ሴቶች በፖለቲካ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ዘርፎች በራስ የመተማመን አቅማቸዉ እንዲስፋፋ ከማድረግ ረገድ በየደረጃው የሚካሄዱ ስብሰባዎችና ተሳትፎዎች ከፍተኛዉን ስፍራ ይይዛል።የዱራሜ ከተማ የህ...
04/11/2025

ሴቶች በፖለቲካ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ዘርፎች በራስ የመተማመን አቅማቸዉ እንዲስፋፋ ከማድረግ ረገድ በየደረጃው የሚካሄዱ ስብሰባዎችና ተሳትፎዎች ከፍተኛዉን ስፍራ ይይዛል።

የዱራሜ ከተማ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመራጭ ሴት ኮከስ የ2017 በጀት ዓመት ማጠቃለያ እና የ2018 በጀት ዓመት ጠቋሚ እቅድ ላይ ያተኮረ መድረክ ተካሂዷል።

መድረኩን የመሩት የዱራሜ ከተማ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤ እና የተመራጭ ሴቶች ኮከስ ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ አማረች ኬሬቦ ሴቶች በፖለቲካ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ዘርፎች በራስ የመተማመን አቅማቸዉ እንዲስፋፋ ከማድረግ ረገድ በርካታ ሥራዎች እየተሰራ ነዉ ብለዋል።

ለዚህም በየደረጃው የሚካሄዱ ስብሰባዎች ተሳትፎዎች ከፍተኛዉን ስፍራ ይይዛል ያሉት ምክትል አፈጉባኤ ክብርት ወ/ሮ አማረች ኬሬቦ ለዚህም ሴቶች በግንባር ቀደምነት መሳተፍ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

በተለይ ሴቶች የገቢ ምንጫቸውን ለማሳደግ የሚያደርጉትን ርብርብ በማጠናከር በሁሉም ዘርፍ ተወዳዳሪ ልሆኑ እንደሚገባ አሳስበዋል።

አሁን የምንገኝበት ዘመን ሰሴቶች በጣም የተሻዕ እና ጥያቄዎቻቸው ሙሱ በሙሉ ምሳሽ ስያገኘበት ወደ ተሻሰ ተጠቃሚነት እየተሸጋገርን ያሰን ሠቅት ነው:፣ በሀገር አቀፍና በዓሰም አቀፍ ደረጃም በሊቶች ጥያቄ ሳይ ግንዛቢ ለየተያዘና ወደ መግባባት የተደረሰበት ወቅት በመሆኑ ይህንን ሚቹ ሁኔታ ተጠቀም ሁሱም የየበኩሱን ድርሻ መወጣት ግድ ይሳዕ::

በተላይ በሴቷ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት የም/ቤት ተመራጭ ሴቶችና በተለያዩ ቦታ በሀገር ደረጃ ኃላፊነት ድርሻ ሳይ የሚገኙ ሴቶች አሉ ያሉት ኃላፊዋ እነዚህን ያየናቸውን ተሞክሮ በመቀመርና ከራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማገናዘብ የተለያዩ አደረጃጀቶችን ፈጥረን በአካባቢያችንና በሴከተር መ/ቤቶቻችን የሚፈጸሙ ዕቅዶች አፈፃፀሞች የሥርዓተ-ፆታና ዘርፈ ብዙ ተግባራትን መምራት ይጠበቃል ብለዋል።

በመጨረሻም በምክር ቤቱ ቅጥር ገቢ ዉስጥ ባለዉ ባዶ መሬት በኮከሱ አባላት የለመ የኮሮት መሬት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ አለሙ ሙኔ በተገኙበት በማድረግ የመስክ ምልከታ መድረኩ ተጠናቋል።

በዱራሜ ከተማ አስተዳዳር ከክልሉ ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ የተውጣጡ የአመራር እና የባለሙያ የድጋፍና የክትትል ቡድን በመጀመሪያ ሩብ ዓመት በከተማዋ በመተግበር ያሉ የልማት ሥራዎች...
04/11/2025

በዱራሜ ከተማ አስተዳዳር ከክልሉ ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ የተውጣጡ የአመራር እና የባለሙያ የድጋፍና የክትትል ቡድን በመጀመሪያ ሩብ ዓመት በከተማዋ በመተግበር ያሉ የልማት ሥራዎችን ምልከታ እያደረጉ ይገኛሉ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊና የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ዘርፍ ሃላፊ በሆኑት ኢንጅነር ዝናቡ ተካበ የተመራ የአመራር እና የባለሙያ የድጋፍና የክትትል ቡድን የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛሉ።

በዚሁ መነሻ በዱራሜ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት ሥራ-አስኪያጅ በሆኑት በአቶ ጌታቸዉ አቡኬ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የእቅድ አፈፃፀም እና የኢንሼቲቭ ሥራዎች ሪፖርት ክቡር ከንቲባ አቶ አክሊሉ አቡቶ እና አስተባባሪ አካላት በተገኙበት የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት መነሻ የመስክ ምልከታ እየተደረገ ነዉ።

ጥራት ያለው የሰው ሀይል በማፍራት፣ ብቁ እና ተወዳዳሪ ሙያተኞች እንዲሆኑ ለማድረግ በሁሉም አከባቢ ያሉ ሰልጣኞች ወደ ኮሌጅ እንድገቡ እና የኮሌጆች ቅበላ አቅም ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን የከ...
03/11/2025

ጥራት ያለው የሰው ሀይል በማፍራት፣ ብቁ እና ተወዳዳሪ ሙያተኞች እንዲሆኑ ለማድረግ በሁሉም አከባቢ ያሉ ሰልጣኞች ወደ ኮሌጅ እንድገቡ እና የኮሌጆች ቅበላ አቅም ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን የከምባታ ዞን ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና መምሪያ ገለጸ

የከምባታ ዞን ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ እና የ2018 ሩብ ዓመት አፈጻጸም የምክክር መድረክ አካሂዷል።

መድረኩን የመሩት የከምባታ ዞን ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ አቶ አብርሃም ጳውሎስ እንደተናገሩት የሀብት አሰባሰብና የአጠቃቀም ሥርዓትን በማሻሻል ከተቋማት ዉስጥ ገቢ እና ከህብረተሰቡ ተሳትፎ በማጠናከር ምቹ እና ሳቢ የትምህርት ተቋማት እንድኖሩ በማድረግ የተሻሉ ኮሌጆች እና ተመራጭ ለማድረግ መስራት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

አክለውም አቶ አብርሃም ጰውሎስ ተደራሽነትን እና ፍትሃዊነትን በማሻሻል በመደበኛ ስልጠና አዲስ እና ነባር ሰልጣኞች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ታቅዶ አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት ዜጎች በአገር ዉስጥ እና ከሀገር ውጭ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የቴክኖሎጂ ሽግግር ሂደትን ጥቅም ላይ ከማዋል ረገድ የቴክኖሎጂ ማበልፀጊያ ማዕከላትን በማደረጀት የተሻለ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንድኖር እና የተሻለ ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ሥራ ላይ መሠራቱን የተጠቀሱት አቶ አብርሃም ጳውሎስ ኢንተርፕራይዞች ከውጭ ተኪ ምርቶች ላይ ትኩረት በማድረግ እንድሰማሩ ስልጠና እየተሰጠ እንደሆነ ነባርና አዲስ ለሆኑ ኢንተርፕራይዞች የተሟላ የኢንድስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ እንዲያገኙ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ሁሉም ኮሌጆች በአሁኑ ወቅት የተማሪዎች ቅበላ ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው የጠቀሱት የመመሪያው ኃላፊ ሁሉንም የሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም መረጃ ተደራሽ እንዲሆን በማድረግ ግንዛቤ በመፍጠር የቅበላ አቅማችንን ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል።

በመድረኩ የሁሉም ኮሌጅ ዲኖች የከምባታ ዞን ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና መምሪያ ማነጅሜንት አባላት እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል። የከምባታ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ

የዶ/ር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል ዕውቅና አገኘ።የዶ/ር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል (CPD-...
03/11/2025

የዶ/ር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል ዕውቅና አገኘ።

የዶ/ር ቦጋለች ገብሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል (CPD-Center) የዕውቅና ፈቃድ ሰርተፍኬት (CPD Accreditation) ከኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር ማግኘቱን አሳውቋል።

የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማዕከሉ የዕውቅና ፈቃድ ሰርተፍኬት ያገኘዉ ከፌዴራል ጤና ሚነስትር ለCPD ማዕከላት ዕዉቅና የመስጠት (CPD Accreditor) ፈቃድ ባለዉ የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር አማካይነት በተደረገዉ ተከታታይ ምዘና መሰረት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ ማዕከሉ የሚጠበቀዉን እስታንዳርድ ሙሉበሙሉ ማሟላቱን በምዘናዉ የተረጋገጠ መሆኑም ተገልጿል።

የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ደረበ ዮሐንስ በፌዴራል ጤና ሚንስቴር በተረጋገጡና ዕዉቅና በተሰጠባቸዉ ኮርሶች ላይ የተለያዩ የሥልጠና አሰጣጥ ዘዴዎችን በመጠቀም ሠልጣኞች በሥልጠና ወቅት በሚደረገዉ ምዘናና የኮርስ ይዘት በተቀመጠዉ እስታንደርድ መሠረት በተቀናጀዉ የሰዉ ሀብት መረጃ አስተዳደር (i-HRIS) ሥርዓት የክሬዲት የምዘና ሰርተፊኬት በመዉሰድ የሙያ ፈቃዳቸዉን ለማሳደስ መጠቀም የሚችሉ መሆኑ ገልጸዋል፡፡

በዞኑ እና በአጎራባች አከባቢዎች የሚገኙና በጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶች የተሰማሩ የመንግሥትና የግል ተቋማት የተለያዩ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን፤ወርክሾፖችን እና ስብሰባዎችን ለማካሄድ ሲያቅዱ ከሆስፒታሉ የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል (CPD Provider Center) ጋር በቅንጅት ቢሰሩ ይበልጥ ዉጤታማ መሆን ስለሚችሉ በማዕከሉ እንዲገለገሉ ዶ/ር ደረበ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም ዶ/ር ደረበ ዮሐንስ ሆስፒታሉ ለዚህ ስኬት እንዲበቃ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉትን የባለድርሻ አካላት
አመስግነዋል።

!

Address

Durame

Telephone

+251948156400

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የዱራሜ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share