የዱራሜ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Durame
  • የዱራሜ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የዱራሜ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ✍️ወቅታዊና ተአማኒነት ያለዉን መረጃ ለህብረተሰቡ ተደራሽ እናደርጋለን!
✍️We strive to address the p***c whith reliable and timely information!

09/10/2025

የሀምበሪቾ ተራራ ጨዋታ:-

09/10/2025

በትንንሽ ጉዳዮች ከመታሰር...

የሀገሪቱ መንግሥት በግብርናው ዘርፍ የነደፈዉን ፖሊሲ ቀድመዉ በመተግበር ዉጤታማ የሆኑ የዱራሜ ከተማ አርሶ አደር አቶ ስምኦን ያዕቅም፦ ነዋሪነታቸው በዱራሜ ከተማ በላሎ ከተማ ቀበሌ ዌታ መን...
09/10/2025

የሀገሪቱ መንግሥት በግብርናው ዘርፍ የነደፈዉን ፖሊሲ ቀድመዉ በመተግበር ዉጤታማ የሆኑ የዱራሜ ከተማ አርሶ አደር አቶ ስምኦን ያዕቅም፦

ነዋሪነታቸው በዱራሜ ከተማ በላሎ ከተማ ቀበሌ ዌታ መንደር ነዉ አርሶ አደር ስምኦን ያዕቅም።

ጅማሮያቸዉን ምንም እንኳን ትምህርታቸዉን በአግባቡ በመከተል በመንግሥት ሥራ ላይ ቢሰማሩም ከወር እስከ ወር ተጠብቆ የሚገኘዉ ደሞዝ እሳቸው በሚፈልጉት ልክ በሳቸውና በቤተሰባቸው ሕይወት ላይ ተጨባጭ ውጤት ሊያመጠላቸው ባለመቻሉ እና ለዚህም በግብርናው ዘርፍ የተቻላቸውን ሁሉ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው እራሳቸውን በማሳመን ቆርጠዉ በመነሳት የግብርና ሥራ መጀመራቸውን ይናገራሉ።

አርሶ አደሩ የሀገሪቱ መንግሥት በግብርናው ዘርፍ የነደፈውን የግብርና ፖሊሲና ስትራቴጂ ቀድመው በመተግበር በርካታ አመርቂ ዉጤቶችን ማስመዝገባቸው ደግሞ ህያዉ ምስክር ሆኖ በመሬት ላይ ደምቆ፣ ጎልቶ፣ እና በውጤት አሸብርቆ እንዲታይ አድርገዋል።

በዚህም የብልጽግና መንግስት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ የግብርና ፖሊሲዎችን ነድፎ ያስቀምጥ እንጂ እኚህ ምሁር፣ ታታሪና ሞዴል አርስ አደር በአካባቢያቸው ያለውን የመሬት፣ የሰውና መሰል የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ሀብቶችን/ፀጋዎችን በአግባቡ በመጠቀም በቁርጠኝነት ተግባራዊ አድርገዉ የተገኙ መሆናቸውን በቃላቸውና በሠናይ ምግባራቸው ጭምር አብራርተዋል።

የምግብ ዋስትና የሚያረጋግጡ ጥምር ግብርና ላይ ትኩረታቸውን በማድረግም ዉጤታማ የግብርና ሥራ አከናዉነዋል ሞዴል አርሶ አደር ስምኦን ያዕቅም።

በአካባቢው ያለውን ሀብት በመለየት ፣ ጊዜን በአግባቡ በመጠቀምና እና ልዩ ትኩረት በመስጠት ከተሰራ ዉጤታማ መሆን የሚከለክል አንዳች ስንኳን እንደሌላ የሚናገሩት አርሶ አደሩ በዚሁ መነሻ ዉጤታማ የግብርና መንገድ በመከተል ከራሳቸዉ አልፈዉ ለሌሎችም ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል እንደፈጠሩ ይናገራሉ።

ጅምር ላይ አንድ የወተት ላም እንደነበራቸዉ የሚነግሩት ሞዴል አርሶ አደር አቶ ስምኦን ከስኬታማ ወንድ ጀርባ ሁሌም ጠንካራና ታታሪ ሴት አለች እንደሚባለው, ከፀባይ ሠናይ ጠንካራ ሥራ ወዳድና ሰው አክባሪ ከሆኑ ከባለቤታቸው ከገነት ዮናስ ጋር በጋራ በመሆን እየሠሩ ባሉት ጠንካራ ሥራ በአሁን ሰዓት ከ10 በላይ ዘመናዊ የወተት ላሞችን በማድለብ ከእርሻ ሥራቸው ባሻገር ወተት እና የወተት ተዋፅኦ የገቢ ምንጫቸው እንደሆነ በመናገር ልጆቻቸውን በአግባቡ በማስተማር ለቁምነገር እንዲበቁ በማድረግ ሥራ ወዳድ፣ ውጤታማና ሀገር ተረካቢ ዜጋ እንዲሆኑ የወላጅነት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ ይገኛሉ።

የመንግሥት ፖሊሲ እና ስትራቴጂ በመከተል የተለያዩ ለማሳ ለሚነት ጠንቅ የሆኑ እንደ ባህር ዛፍ ያሉ የማይበሉ ዛፎችን በመንቀል የተጎዱ ማሳዎቻቸውን በማከም፣ ወደ እህል፣ ፍራፍሬ ፣ የቡናና መሰል ጠቃሚ ወደ ሆኑ ምርቶች በመቀየር በተላይ መንግስት ያስጀመረውን የሌማት ትሩፋት ኢንሼቲቭ በማሳካት ተጠቃሚነታቸውን በማረጋገጥ ለአካባቢው ፣ ለከተማውና ለሌሎችም አካባቢ አርሶ አደሮች አርአያ የሆኑ ውጤታማ አርሶ አደር መሆናቸውን ከከተማ፣ ከዞን፣ ከክልል፣ ብሎም እስከ ፌድራል ያሉ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ማሳቸውንና መኖሪያ ቤታቸውን በመጎብኘት ምስክርነታቸውን ሰጥቷቸዋል።

አቶ ስምዖን ያዕቅም የዉበት ፣የምግም፣ ኢንቨስትመንት እና አረንጓዴ አከባቢ የመፍጠር ሥራ የመሥራት ተግባራቸውን በማጠናከር ጠንካራ የግብርና ግስጋሴያቸውን አጠናክረው መቀጠላቸውም ተመልክቷል።

በትንሽ ቦታ በርካታ የግብርና ተግባራትን በማከናወን እና ጥምር ግብርናን እውን በማድረግ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እየሰሩ እንደሆነም ጭምር አብራርተዋል ሞዴል አርሶ አደሩ።

ታዲያ በትንሽዬ መኖርያ ቤት ገና አሃዱ በማለት ህይዎታቸዉን የጠነሰሱት ምሁሩ፣ ሥራ ወዳዱ፣ ጠንካራና ሞዴል አርሶ አደር ስምዖን ያዕቅም ሥራ ሳይንቁ ጠንክሮ በመሥራት የራሳቸውንና የቤተሰባቸውን ሕይወት ትርጉም ባለው መልኩ ቀይረዋል፣

ከራሳቸው አልፈው ለበርካታ አካባቢው ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል መፍጠር የቻሉ ትጉህ ሞዴል አርሶ አደር ናቸው።

በአሁን ጊዜ እጅግ ዘመናዊና ቅንጡ መኖሪያ ቤት ባለቤት ከመሆናቸውም ባሻገር መንግስት በከተማ የተጀመረው የዜጎችን ሕይወት በመልካም በመቀየር ይህንኑ መልካም እሳቤ ወደ ገጠሩ ማህበረሰብ በማስፋፋት የጀመረው የገጠር ኮርደር ልማት አስቀድመው አሳክተዋል።

አቶ ስምዖን ያዕቅም ለሌሎችም አርኣያ የሚሆኑ ጠንካራ ሞዴል አርሶ አደር መሆናቸውን በተግባር ያረጋገጡ የልማት አርበኛ መሆናቸውን እኛም በቤታቸውና በማሳቸው ተገኝተን ምልከታ በማድረጋችን የዓይን ምስክሮች ነንና እንደ ሞዴል አርሶ አደር ስምዖን ያሉ ጠንካራና ውጤታማ አርሶ አደሮች እንዲበዙ ምኞታችን ነው።

 #የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጉብኝትና የሀምበርቾ ዳግም 777 ፕሮጀክት መጠናቀቁን አስመልክተው የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ_አቶ_ አረጋ እሸቱ ያቀረቡት የምስጋና_መልዕክት!  የል...
09/10/2025

#የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጉብኝትና የሀምበርቾ ዳግም 777 ፕሮጀክት መጠናቀቁን አስመልክተው የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ_አቶ_ አረጋ እሸቱ ያቀረቡት የምስጋና_መልዕክት!

የልማት ፕሮጀክት በህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎና በላቀ የፕሮጀክት አፈፃፀም ብቃት መጠናቀቁን ተከትሉ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ለመላው ከምባታ ዞን ህዝብ ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።

በትውልድ ቅብብሎሽ እሴት ጨምሮ በማልማት በተፈጥሮ የታደለውን ቀድሞውኑ የሰባት ጎሳዎች መኖሪያ ጅማሮ፣ የሳባት ሰንሰለታማ ተራሮች ህብረት፣ በሰባት ምንጮች ተውቦ የመደመር እሳቤ ደምቆ የታየበት ሀምበርቾ ተራራን ተማራጭ የሀገር አቀፍና አለም አቀፍ የቱሪስት መዳረሻ እንዲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር) በሰጡት የቤት ሥራ ተጨማሪ ግንባታ መጀመሩ ይታወሳል።

የዛሬ ሶስት ወር ገደማ የኢፌዴሪ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነውን የገጠር ኮሪደር ልማት ባስጀመሩበት ወቅት ሀምበርቾን ጎብኝተው ሀምበርቾ ድንቅ አለም አቀፍ የቱሪዝም መዳረሻ የመሆን አቅም እንዳለው በመመስከር ተጨማሪ የደረጃ ግንባታዎች እንዲሠሩ የቤት ሥራ ሰጥተው ተመልሰዋል።

ይህንኑ የጠቅላይ ሚኒስትር ለዞኑ አመራርና ህዝብ የሰጡትን የቤት ሥራ ይዘን ወትሮም ታታሪነት እና ጠንካራ የሥራ ባህል ብሎም መተባበር መገለጫው ወደ ሆነው ህዝባችን ስንቀርብ ፈጣሪ ይመስገን ህዝቡን በባለቤትነት ስሜት ከልቅ እስከ ደቂቅ በገንዘቡ፣ በሀሳቡ፣ በጉልበቱ፣ በንብረቱ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የልብ አንድነት ፈጥረን ስንተባበር ተዓምር መሥራት እንደምንችል ማሳያ የሆነ ዘመን ተሻጋሪ ሥራ ሠርቷልና ለመላው የዞናችን ህዝብ ያለኝን አክብሮትና ልባዊ ምስጋናዬን መግለፅ እፈልጋለሁኝ።

በሀምበርቾ ተራራ ላይ የተሠራው ድንቅ ሥራ ከፕሮጀክት አፈፃፀም ባሻገር ህዝቡ የአንድነት፣ የመደማመጥና ጀምረን ባጠረ ጊዜ የመፈፀም አቅማችን ጎልቶ የታየበት ልዩ አጋጣሚ በመሆኑ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ያሉ የዞኑ ህዝቦችና ልማት ወዳዶች የአካባቢ ህብረተሰብ ተወካዮች፣ አመራሮች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ስኬታማ እንዲሆን ላበረከታችሁት ለላቀ አስተዋጽኦ ከልብ እናመሰግናለን።

እንዲሁም፣ በዞኑ ውስጥ ያሉ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ሀብቶችን በመጠቀም የህዝቡን አቅምና ተሳትፎን በማጉላት ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል በሀምበርቾ ዳግም 777 ተጨማሪ የልማት ፕሮጀክቱ ላይ ያደረጋችሁትን ንቁ አስተዋጽኦ፣ በቀጣይም በሁሉም አካባቢና ከተሞች፣ እንዲሁም በሁሉም የልማት ዘርፎች በመድገም የህዝባችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንድንችል የከበረ ጥሪዬን በዞኑ አስተዳደር ስም አቀርባለሁኝ።

የተከበሩ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር) በተደጋጋሚ ዞናችንን በመጎበኘት ለዚህ ታላቅ እና ታታሪ ህዝብ ላሳዩት ፍቅርና አክብሮት እንዲሁም ለሰጡን ከፍተኛ ድጋፍ በዞኑ ህዝብና አስተዳደር ስም ልባዊ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁና።

ቃላቸውን አክባሪ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትራችን እንደገና የሰጡንን የቤት ሥራ በተለመደው ልባዊ አንድነትና ትብብር ሠርተን እንደምናሳይና ለ4ኛ ጊዜ ወደ ዞናች እንዲመጡ እንደምናደርግ እምነቴ የፀና ነው።

!!
#አመሰግናለሁ።

#የተከበሩ አቶ አረጋ እሸቱ የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ

09/10/2025

የኢፌዲሪ መንግስት ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር አብይ አህመድ በሀምበርቾ ተራራ ጫፍ ቁጭ ብለው ያወሩት ሀሳብ

በዱራሜ ከተማ አስተዳደር የጉበት ቫይረስ በሽታ መከላከያ ክትባት (Hepatitis) ስልጠና ለከተማ ጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ፣ አዋላጅ ኔርሶች ፣ ለክትባት ፎካሎች እየተሰጠ መሆኑ ተገለፀ...
09/10/2025

በዱራሜ ከተማ አስተዳደር የጉበት ቫይረስ በሽታ መከላከያ ክትባት (Hepatitis) ስልጠና ለከተማ ጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ፣ አዋላጅ ኔርሶች ፣ ለክትባት ፎካሎች እየተሰጠ መሆኑ ተገለፀ።

ሥልጠናዉን ንግግር በማድረግ ያስጀመሩት የዱራሜ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሀብትነህ ቲቶስ እንደገለፁት የህፃናት የጉበት ቫይረስ መከላከያ ክትባት ስልጠናና የኩፍኝ ክትባትን ከ10 ዶዝ ወደ 5 ዶዝ መቀየርን አስመልክቶ ለጤና ኤክስቴንሽን እና ባለሙያዎች የሚሠጥ ስልጠና መሆኑን ገልፀዋል።

የጉበት ቫይረስ በሽታ መከላከያ ክትባት (Hepatitis -B) እና የኩፍኝ መከለካያ ክትበት ከ10 ዶዝ ወደ 5 ዶዝ መቀየርን አስመልክቶ ለሁሉም ህጻናት ለማስጀመር እንደሆነ ተናግረዋል።

የሚሰጠው ክትባት በሰው ህይወት ላይ የሚሰራ በመሆኑ የዘርፉ ሰልጣኞች ሥልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ለህብረተሰቡ ተገቢ አገልግሎት መስጠት እንደለበቸው አሳስበዋል።

ሥልጠናዉ ለሁሉም ከተማ ጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ፣ አዋላጅ ኔርሶች ፣ ለክትባት ፎካሎች ፣ ኤች ኤም አይ ስ(መረጃ አጠናክሪ ባለሙያዎች ) ለጽ/ቤቱ ባለሙያዎች እየተሰጠ ይገኛል።

የመደመር ዕሳቤ ሃልዮታዊ መሠረት የሥርዓት ንድፈ ሐሳብ ነው፡፡ የዚህ ንድፈ ሐሳብ ዋነኛ መርሕ የአንድ ሥርዓት ተዋንያን ለጋራ ዓላማ በትብብርና በቅንጅት መሥራት እመርታዊ ለውጥን እንደሚያስመ...
09/10/2025

የመደመር ዕሳቤ ሃልዮታዊ መሠረት የሥርዓት ንድፈ ሐሳብ ነው፡፡ የዚህ ንድፈ ሐሳብ ዋነኛ መርሕ የአንድ ሥርዓት ተዋንያን ለጋራ ዓላማ በትብብርና በቅንጅት መሥራት እመርታዊ ለውጥን እንደሚያስመዘግብ ያስረዳል፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ውስብስብ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ሥርዓታዊ ችግር ያለባቸው ሀገራት ማድረግ የሚችሉት አንድ ብልሐት ትንንሽ መናበቦችንና የጋራ ዓላማ ያላቸው የተባበሩ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ ሲሆን ይሄም ባልተጠበቀ ሁኔታ ትልልቅ ባሕርያዊና የአዝማሚያ መቀየሮችን ይፈጥርላቸዋል፤ እመርታዊ ለውጦችንም እንዲያስመዘግቡ ያደርጋቸዋል፡፡

የመደመር መንግሥት ገጽ 81፣ 2018 ዓ.ም

የተሟላ ብልፅግናን ለማምጣት የገጠሩን አኗኗር ዘዬ ማዘመን ግድ ይላል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)*******ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል...
08/10/2025

የተሟላ ብልፅግናን ለማምጣት የገጠሩን አኗኗር ዘዬ ማዘመን ግድ ይላል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በክረምት በጎ ፈቃድ መርሐ-ግብር የተገነቡ ሞዴል የገጠር መንደሮችን ለተጠቃሚዎች አስረክበዋል።

በወቅቱም የእኛ የብልፅግና ትርክት እያንዳንዱን ዜጋ፣ ቤተሰብ እና መንደር ካልነካ የተሟላ አይሆንም ሲሉ ተናግረዋል።

በከተሞች የተከናወነው የዘመናዊ መንደሮች ግንባታ ወደገጠር መስፋፋት አለበት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህን ለማሳካት በጎ ፈቃደኞች፣ ባለሃብቶች፣ የመንግሥት ተቋማት እና ኩባንያዎች ነብስን በሚያስደስተው የዘመናዊ መንደር ግንባታ ሊሳተፉ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ከነበረው የኑሮ ዘይቤ ከፍ ያለ የገጠር አኗኗርን የሚከተል፣ የተሻገረ ገጠርን መፍጠር አለብን የሚል ትልም ነበረን፤ ዘንድሮ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ አምስቱም ዞኖች ይህ ሥራ ታይቷል ብለዋል።

በዚህም ለገጠሩ ኅብረተሰብ ዘመናዊ የእንስሳት እርባታ እና እርሻ የሚያከናውንበትን ቦታ፣ የባዮ ጋዝ ፣ የፀሐይ ብርሃን ቴክኖሎጂ፣ ዘመናዊ የንፅሕና መጠበቂያዎች እና መሰል አገልግሎቶችን የሚያገኝበትን መንደር መገንባት ተችሏል ሲሉ አስረድተዋል።

በከተማም ሆነ በገጠር የተሻለ ኢኮኖሚ ያላቸውን እና እጅ አጠሩን የሚያቀራርብ አኗኗርን በመፍጠር የተሟላ ውጤት ማስመዝገብ ይቻላል ሲሉ አስረድተዋል።

አርሶ አደሩን የሚጠቅም የዘመናዊ መንደር ግንባታም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከመደመር መንግሥት መጽሐፍ ሽያጭ ለሀምበሪቾ ተራራ ሥር የማረፊያ ግንባታ ስጦታ አበረከቱጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመደመር መንግሥት መጽሐፍ ሽ...
08/10/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከመደመር መንግሥት መጽሐፍ ሽያጭ ለሀምበሪቾ ተራራ ሥር የማረፊያ ግንባታ ስጦታ አበረከቱ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመደመር መንግሥት መጽሐፍ ሽያጭ የተገኘ ገቢን በሀምበሪቾ ተራራ ሥር የማረፊያ ግንባታ እንዲገነባ በስጦታ አበርክተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሶስት ወራት በፊት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን ጎብኝተው በገጠር ኮሪደር ልማት ሥራ ሞዴል የገጠር መንደሮችን ጨምሮ ዓመታዊውን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር ማስጀመራቸው ይታወሳል፡፡

በጉብኝታቸው ወቅት የሀምበሪቾ ተራራ 777 ደረጃዎችን ወጥተው ለከምባታ ዞን አስተዳደር ደረጃዎቹን ጨምረው እንዲገነቡ የቤት ሥራ ሰጥተው ነበር የተመለሱት።

በሶስት ወራት ውስጥ የቤት ሥራውን አከናውነው የሀምበሪቾ ተራራ ዳግም 777 ክፍልን እውን በማድረግ በድምሩ ከ1 ሺህ 500 ደረጃዎች በላይ በማድረስ አስደናቂው የተራራ ላይ እይታ ድረስ ገንብተው አጠናቅቀዋል።

ለክልሉ ቁርጠኝነት እና ውጤት እውቅና ለመስጠትም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከመደመር መንግሥት መጽሐፍ ሽያጭ የተገኘ ገቢን በሀምበሪቾ ተራራ ሥር የማረፊያ ግንባታ ይገነባ ዘንድ ስጦታ አበርክተዋል።

ይህም አካባቢው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትዕይንታዊ የቱሪዝም መዳረሻነት መጎልበት የበለጠ የሚያገለግል ስለመሆኑ ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶር) መልዕክት ዛሬ በክረምት በጎፈቃድ መርሃግብር  ከምባታ እና ሀላባ  ዞኖች የተገነቡ ሞዴል የገጠር መንደሮችን አስረክበናል። እነኚህ መንደሮች የአርሶ አ...
08/10/2025

የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶር) መልዕክት

ዛሬ በክረምት በጎፈቃድ መርሃግብር ከምባታ እና ሀላባ ዞኖች የተገነቡ ሞዴል የገጠር መንደሮችን አስረክበናል። እነኚህ መንደሮች የአርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮችን ሕይወት ለማሻሻል የምናደርገው ጥረት ተስፋ ሰጪ ጅማሮ ናቸው። ቤቶቹ የፀሃይ ኃይል ማመንጫ የተገጠመላቸው፣ ለማብሰል ደግሞ ከእንስሳት እዳሪ ባዮጋዝ የሚጠቀሙ፣ የተለየ ሳሎን፣ መጸዳጃ እና ሰርቪስ ቤቶች የተሟላላቸው ናቸው። ንጽህናን በሚያረጋግጥ እና የአኗኗር ደረጃን ከፍ በሚያደርግ አኳኋን የተለየ የእንስሳት በረት ተሰርቶላቸዋል። እነዚህ የገጠር ኮሪደር ልማት መንደሮች የገጠሩን አኗኗር የማሳደግ ሕልማችን አካል በመሆን ተስፋፍተው የሚሰሩ ይሆናል።

ባለፉት ሰባት አመታት የክረምት በጎ ፈቃድ በከተሞች ለሚኖሩ ለችግር የተጋለጡ ወገኖች መኖሪያ ቤቶችን ስናቀርብ ቆይተናል። አሁን ደግሞ በገጠር ኮሪደር ልማት የሥራውን እመርታ ወደገጠር አስፋፍተናል። ግለሰቦች፣ ድርጅቶች እና የዲያስፖራው ማኅበረሰብ እነኚህን ሥራዎች እንዲደግፉ እና እንዲሳተፉ አበረታታለሁ።

ባለፈው ጉብኝቴ ወቅት ያቀረብኩላቸውን የቤትሥራ በመወጣት በአጭር ጊዜ ውስጥ በራስ አቅም የሀምበሪቾ ተራራ ደረጃንም በእጥፍ ሠርተው ላጠናቀቁት አመራሮች ያለኝን ምስጋና አቀርባለሁ። ወደፊትም የየአካባቢ አመራሮች ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሠሩትን ሞዴል መንደሮች በመጪው አመት በየዞኑ ወደ100 ቤቶች እንዲያሳድጉ አሳስባለሁ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ ወደ ከምባታ ዞን በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ በሀምዶ ጎፎሮ ቀበሌ የገጠር ኮርዴር ልማት መርቀው ከፍተዋል።እንኳን የሰላም ደሴት ወደ ሆነው ከምባታ ዞ...
08/10/2025

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ ወደ ከምባታ ዞን በአዲሎ ዙሪያ ወረዳ በሀምዶ ጎፎሮ ቀበሌ የገጠር ኮርዴር ልማት መርቀው ከፍተዋል።

እንኳን የሰላም ደሴት ወደ ሆነው ከምባታ ዞን በሠላም መጡ!

Xummiin Waalteen!
!
Nagaan Dhuftani!

Address

Durame

Telephone

+251948156400

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የዱራሜ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share