Hambericho Post

Hambericho Post Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hambericho Post, Media/News Company, Durame.

ራዕይና ተልዕኮን ወደ ተግባር የቀየረ ድንቅ መሪ!!!በአመራርና አስተዳደር ሳይንስ ራዕይ (Vision) ማለት «ወደፊት የት መድረስ እንፈልጋለን?» ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ፣ በግልፅ ታቅዶ...
24/08/2026

ራዕይና ተልዕኮን ወደ ተግባር የቀየረ ድንቅ መሪ!!!

በአመራርና አስተዳደር ሳይንስ ራዕይ (Vision) ማለት «ወደፊት የት መድረስ እንፈልጋለን?» ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ፣ በግልፅ ታቅዶ እውን የሚደረግ ተስፋ ሰጪ የመዳረሻ ፍኖተ ካርታ ነው። ተልዕኮ (Mission) ደግሞ «ለምን ወደ ሀላፊነት መጣን? አሁንስ ምን እየሰራን ነው?» የሚለውን መሠረታዊ ዓላማና የዕለት ተዕለት የትጋት መንገድን ይገልፃል።
ይህንን ሳይንሳዊ የአመራርነት ዋና ፅንሰ ሃሳብ ወደ መሬት ከማውረድና ወደ ትግበራ ከመቀየር አንፃር ስናይ፤ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ያሳዩት ቁርጠኛና ብቁ የአመራርነት ሚና ሁነኛ ማሳያ ነው።
በግልፅ የተደራጀ ራዕይ፦ ዶ/ር እንዳሻው ክልሉን መምራት ሲጀምሩ ግልፅና አቅጣጫ ጠቋሚ ራዕይ በመሰነቅ ጀምረዋል። ክልሉን ባለፉት ሶስት ዓመታት ውስጥ በሁሉም ዘርፎች የላቀ ውጤት የሚያስመዘግብና ለሌሎችም «የተሞክሮ ማዕከል» የሚሆን ሞዴል ክልል የማድረግ ራዕያቸው ይኸው በተጨባጭ የታየ እውነታ ሲሆን፤ ከዚህም ውስጥ ክልሉን ከዕዳ ወደ ምንዳ ማሸጋገር አንዱ ነው፡፡
🎯 ተልዕኮን በተግባር መተርጎም፦ የተሰጣቸውን ህዝባዊ ሀላፊነትና ተልዕኮ በብቃት በመምራት፣ የአመራር መዋቅሩን አስተባብረው የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ በመመለስ ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ የህዝብ አገልጋይነት ባህሪ መላበሳቸው አንዱ ማሳያ።
💎 የዶ/ር እንዳሻው ጣሰው የብቁ አመራርነት ልዩ ባህሪያት፦
* ተግባር ተኮር ስብዕና፦ ራዕይን በወረቀት ላይ ማስቀመጥ ብቻ ሳይሆን፤ ወደ መሬት በማውረድ መቆጠርና መለካት በሚችሉ ስኬቶች ማረጋገጥ።
* ጽናትና ቁርጠኝነት፦ አላስፈላጊ ሀሰተኛ ወሬዎችንና የፀረ-ልማት አጀንዳዎችን በልማት፤ በሰላምና የፀጥታ ስራዎች መመከት።
* አካታች መሪነት፦ ህዝብንና አመራሩን አስተባብሮ የጋራ ህልምን በጋራ ክንድ የመገንባት ጥበብ።

ራዕይና ተልዕኮን አጣምሮ የያዘ ብቁ መሪ ሲኖር; ሁልጊዜም ውጤቱ ዘላቂ ብልፅግናና እድገት ነው!

24/08/2026
24/08/2026
ገቢር-ነበብ የለውጥ አመራር፤ ለክልላዊ ሁለንተናዊ ብልፅግና!💪💪💪የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሰረተ ጀምሮ ባሉ ሦስት ዓመታት በየዘርፉ የታዩት አስደማሚ ስኬቶች በዘፈቀደ የተገኙ ሳይሆን፣ ...
16/08/2026

ገቢር-ነበብ የለውጥ አመራር፤ ለክልላዊ ሁለንተናዊ ብልፅግና!
💪💪💪
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሰረተ ጀምሮ ባሉ ሦስት ዓመታት በየዘርፉ የታዩት አስደማሚ ስኬቶች በዘፈቀደ የተገኙ ሳይሆን፣ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው አቅጣጫ ጠቋሚነትና መሪነት በተገነባው "የአስተሳሰብ እና የተግባር አንድነት" የመጡ ውጤቶች ናቸው።

ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩና የክልሉ የየደረጃው አመራር ከተለምዶው "Business as Usual" አሰራር በመውጣት፣ እውነታና ተግባር ተኮርና፤ ገቢር ነበብ (Pragmatic Approach) እና አሻጋሪ (Transformative Leadership) ስልቶችን በመከተል ክልሉን ወደ ላቀ ዕድገት መርቷል።

ለእነዚህ ስኬቶች መሰረት የሆኑት 3 ዋና ዋና የአመራርነት ስትራቴጂዎች፦

1. "ትንሽ ማውራት፤ ብዙ መስራት" — የተግባር ፖለቲካ መርህ
👉ከቃላት በላይ ተግባር፦ በክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ ተመንጭቶ በየደረጃው አመራር ባህል የሆነው ይህ መሪ ቃል፣ ብዙ ከማውራት ይልቅ በውጤትና በፈጠራ ላይ ያተኮረ አመራርን (Knowledge-based Leadership) አግዝፏል።

👉የጊዜ እና የሀብት ብክነትን ማስቀረት፦ ቀድሞ ከ1 እስከ 3 ቀናት ይወስዱ የነበሩ ክልላዊ መድረኮች በጥራትና በውጤታማነት በግማሽ ወይም በአንድ ቀን ብቻ እንዲጠናቀቁ በማድረግ ከፍተኛ ሀብትና ጊዜ ማዳን ተችሏል።

2. በዕውቀት እና መረጃ ላይ የተመሰረተ ስትራቴጂ
👉የሳይንሳዊ ጥናት ውጤት፦ ክልሉ በተመሰረተ ማግስት ከተለያዩ 6 ዩኒቨርሲቲዎች እና የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር የክልሉ ተፈጥሯዊና ሰዋዊ ሀብት ጥናት እንዲካሄድ ተደርጓል። ጥናቱ በቀጥታ በሴክተሮች ዕቅድ ውስጥ ገብቶ ለምርትና ምርታማነት እድገት መሰረት ሆኗል።

👉የክልላዊ አጠቃላይ ምርት (GDP) ጥናት፦ በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች የተመዘገበውን ዕድገት በሳይንሳዊ መንገድ ለመለካት የክልሉ አጠቃላይ ምርት (GDP) ጥናት በማጥናት በውጤቱም በዘርፎች መካከል መዋቅራዊ ሽግግር የተደረገባቸውና፤ ለክልሉ ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋፆ ያላቸው የርብርብ ማዕከል ተለይተው ተግባራዊ ተደርጓል፤

3. የተሳለጠ የድጋፍና ክትትል ስርዓት
👉የአካል ምልከታ እና ፈጣን ውሳኔ፦ ከክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ ጀምሮ ያሉ አስተባባሪዎች በመስክ በአካል በመገኘት የስራዎችን አፈጻጸም በቅርበት በመከታተል ለተከሰቱ ማነቆዎች በቦታው ፈጣን የመፍትሔ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

👉ቃሉን የሚጠብቅ አመራር፦ አመራሩ የማይፈፅመውን ለህዝብ ቃል ሳይገባ፣ ቃል የገባውን ደግሞ በታቀደለት ጊዜና ጥራት በማጠናቀቅ የህዝቡን አመኔታ አትርፏል።

የለውጥ አመራር ሁለንተናዊ ስኬቶች፤ በሀሰተኛ ትርክቶች እና በዲጂታል ዘመቻዎች ማጠልሸት አይቻልም!

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የለውጥ አመራር በጥቂቱ አውርቶ በብዙ በመተግበር ህዝባዊ ቅቡልነቱንና አገልጋይነቱን በተግባር ያስመሰከረ፣ የሚገባውን ክብርና ዕውቅና ሊቸረው የሚገባ የህዝቡ የልማት አለኝታ ነው!

🎉 እንኳን አደረሰን! እንኳን አደረሳችሁ! 🇪🇹🥳✨ ቃልን በተግባር የ3 ዓመት ጉዞ (ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል) ✨ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሰረተ 3ኛ ዓመቱን ይዞ እነሆ በልማት፣ በሰላም ...
16/08/2026

🎉 እንኳን አደረሰን! እንኳን አደረሳችሁ! 🇪🇹🥳

✨ ቃልን በተግባር የ3 ዓመት ጉዞ (ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል) ✨

ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሰረተ 3ኛ ዓመቱን ይዞ እነሆ በልማት፣ በሰላም እና በህዝብ ኑሮ መሻሻል ታላቅ ምዕራፍ ላይ ደርሷል! 👏💯

ለዚህ ድንቅ ስኬት የአንበሳውን ድርሻ ለተወጡት ለክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ከልብ እናመሰግናለን! 🤝👏👏

📊 በ3 ዓመታት ውስጥ የተከናወኑ ዋና ዋና ስራዎች፡

🛡️ ሰላም እና ጸጥታ፦ የህዝቦችን አብሮነት በማጠናከር እና የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ ህዝቡ ሙሉ ትኩረቱን ወደ ልማት እንዲያዞር ተደርጓል።

🌾 ግብርና እና ምግብ ዋስትና፦ በኩታ ገጠም እርሻ፣ በመስኖ ልማት (በዓመት ከሁለት እስከ ሶስት ጊዜ ማምረት) እና በሌማት ትሩፋት ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።

💻 ቴክኖሎጂ እና ዲጂታላይዜሽን፦ እንደ መሶብ ያሉ የዲጂታል አሰራሮች በመዘርጋታቸው አገልግሎቶች ፈጣንና ቀልጣፋ ሆነዋል።

🏫 ትምህርት እና ጤና፦ ትምህርት ቤቶችና የጤና ተቋማት ተስፋፍተዋል፤ የተማሪዎች የምግብ ፕሮግራም እና የእናቶችና ህጻናት ጤና ጥበቃ ተጠናክረዋል።

💰 ኢኮኖሚ እና ንግድ፦ የውስጥ ገቢ አቅም አድጓል፤ የሰንበት ገበያዎች በመከፈታቸው የኑሮ ውድነት ጫና እንዲቀነስ ተደርጓል።

🛣️ መሰረተ ልማት፦ የገጠር እና ከተማ መንገዶች፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና የኮሪደር ልማት ስራዎች ተስፋፍተዋል።

👩‍🦰 ወጣቶች እና ሴቶች፦ ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የብድር አቅርቦት እና በውሳኔ ሰጪነት ያላቸው ሚና ከፍ እንዲል ተደርጓል።

🏭 ኢንቨስትመንት፦ ክልሉ ለባለሀብቶች ሳቢ በመሆኑ በርካታ ኢንዱስትሪዎች ገብተው ለወጣቶች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።

⭐ ማጠቃለያ ክቡር ፕሬዝዳንታችን ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ያቀዱትን ራዕይ መሬት ላይ አውርደው፣ በቅርብ ክትትልና በስልታዊ አቀራረብ ስራዎችን በብቃት በመምራታቸው ትልቅ ምስጋና ይገባቸዋል! 🏆🇪🇹

መልካም የ3ኛ ዓመት በዓል ለአማካለዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝቦችና አመራሮች ይሁንልን! 🎉🎊👏

13/08/2026

📊 የ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ አፈጻጸም፡ ጠንካራ ዕድገት እና አበረታች ውጤቶች!
%%%%%%%
ባለፉት ሶስት በጀት ዓመታት (ከ2016 እስከ 2018) በተከናወኑ ሰፊ የልማት ሥራዎች የክልላችን ኢኮኖሚ እያደገ እና ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል። የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸማችንን እና የዋና ዋና የኢኮኖሚ ዘርፎችን የዕድገት ንጽጽር፦

🔍 ዋና ዋና የዕድገት ድምቀቶች፦
• የተፋጠነ አጠቃላይ ዕድገት: የክልላችን ጠቅላላ ዓመታዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ከ2016 ዓ.ም 7.0% የነበረ ሲሆን፣ በ2018 ዓ.ም ወደ 10.2% ከፍ በማለት በአማካይ 8.9% ጠንካራ አፈጻጸም ተመዝግቧል።
• የኢንዱስትሪ ዘርፍ አመርቂ ዝላይ: በኢንዱስትሪው ዘርፍ የታየው ሰፊ እድገት (ከ8.5% ወደ 21.8% ከፍ ማለቱ) የኢኮኖሚ ማሻሻያዎቻችን እና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ውጤታማ መሆናቸውን ያሳያል።
• ዘላቂ የግብርና እና አገልግሎት አስተዋጽኦ: የግብርናው ዘርፍ (አማካይ 7.5%) እና የአገልግሎቱ ዘርፍ (አማካይ 9.3%) በተቀናጀ መልኩ በማደግ ለክልላችን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገት የማዕዘን ድንጋይ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ለተመዘገቡት እነዚህ አበረታች ውጤቶች መሳካት የክቡር ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ጠንካራ አመራር ልባዊ ምስጋና እናቀርባለን!

#ልማት #የኢኮኖሚዕድገት #የ2018በጀትዓመት #አፈጻጸም #የክልልልማት

12/08/2026

ልማትና ትስስር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል! 🚀🛣️

የመንገድ ልማት ፕሮግራም አርሶ አደሩ ያመረተውን ምርት በቀላሉ ወደ ገበያ እንዲያወጣ፣ ገጠሩን ከከተማ በማስተሳሰር ፈጣንና ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እንዲመዘገብ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልም የህብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል፣ ቱሪዝምን ለማስፋፋት እና የገበያ ትስስርን ለማጠናከር በርካታ አበረታች ስራዎች እየተሰሩ ነው።

በክልሉ እየተመዘገቡ ያሉ ዋና ዋና ስኬቶች በጥቂቱ፦
📍 የጥናትና ዲዛይን ስራዎች: በገጠር ትስስርና ተደራሽነት ፕሮግራም የታቀዱ የ18 አዳዲስ መንገዶች፣ የ13 የተንጠልጣይ ድልድዮች እና የ18 ልዩ መዋቅሮች (Special Structures) የጥናትና ዲዛይን ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል።

🛣️ የተጠናቀቁ መንገዶች: የማሬ - አቡና - መሠና - ጃጁራ እና የወልቂጤ - ቃጥባሬ የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

🌉 የድልድይ ግንባታ: በማሬ-አቡና-መሠና-ጃጁራ መንገድ ላይ የሚገኙ አምስት ጥምር ድልድዮች፣ የዉንቅየ ወንዝ ድልድይ እና የገሙና ወንዝ ድልድይ ግንባታዎች ተጠናቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።
በተጨማሪም በአሊቾ ዊሪሮ፣ ሶዶ፣ እኖር፣ ዌራ እና ቃጫ ቢራ የተጀመሩት የተንጠልጣይ ድልድይ ፕሮጀክቶች በጥሩ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

🌱 አረንጓዴ ልማትና ዘመናዊ ትራንስፖርት: ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ትራንስፖርት ለመፍጠር በመንገድ ዳርና መናኸሪያዎች በርካታ ችግኞች ተተክለዋል።
በቡታጅራ፣ ሆሳዕና፣ ሀላባ ቁሊቶ እና ወልቂጤ ከተሞች የብስክሌት ትራንስፖርት ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን (ኢቪ) የማስመጣት ስራ ተከናውኗል።

💼 የስራ ዕድል ፈጠራ: በኢትዮጵያ መንግስትና በአለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በ8 ወረዳዎች በተጀመረው የፓይለት ፕሮጀክት ለብዙሃኑ የስራ ዕድል መፍጠር ተችሏል።

በአጠቃላይ እነዚህ ስራዎች ለዘመናት ሲነሱ የነበሩ የህብረተሰቡን የቀበሌ ተደራሽ መንገድና ድልድይ ጥያቄዎች እየመለሱ ይገኛሉ።

#የመንገድልማት #ማዕከላዊኢትዮጵያ #ልጆችማትናእድገት

Address

Durame
1234

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hambericho Post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share