ጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገጽ

  • Home
  • Ethiopia
  • Gofa
  • ጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገጽ

ጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገጽ Gofa Zone Prosperity party Official page

"ለፀጥታ ስራዎች ውጤታማነት የአመራሩ ቁርጠኝነት የመጀመሪያው ቁልፍ ጉዳይ ነው" ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት 3ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በ...
27/10/2025

"ለፀጥታ ስራዎች ውጤታማነት የአመራሩ ቁርጠኝነት የመጀመሪያው ቁልፍ ጉዳይ ነው" ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት 3ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል ።

በክቡር ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ሰብሳቢነት የተካሄደው የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት 3ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤ የክልሉን ሰላም በማፅናት የክልሉን አጠቃላይ የፀጥታ ሁኔታ አስተማማኝ ደረጃ ለማድረስ ያለሙ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ የክልሉ መንግስት በክልሉ ያሉ ፀጋዎችን ተጠቅሞ በኢኮኖሚ የበለፀገ፣ በፖለቲካ የጠነከረና የተረጋጋ እንዲሁም ሰላምና ፀጥታው የተረጋገጠ ምሳሌ መሆን የሚችል ክልል ለመገንባት በትኩረት በመስራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ለዚህም ባለፉ ጊዜያት ሰላምን ቀዳሚው አጀንዳ በማድረግ ዘርፈ ብዙ የሰላምና የፀጥታ ስራዎች ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ጉባኤው የተከናወኑ ስራዎችንና የተገኙ ውጤቶችን በማጠን ለቀጣይ ስራዎች አቅም የሚፈጥርና የክልሉን ሰላም ለማፅናት የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በባለፈው ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ተከትሎ በህብረተሰቡ ግንባር ቀደም ተሳትፎ በተከናወኑ በርካታ ስራዎችም ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ ክልሉ ደህንነቱ ተጠብቆ እንዲቆይና የታለሙ የልማት ስራዎችን ከዳር በማድረስ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የፀጥታ ተግባራትን አጠናክሮ መቀጠል እንዲመገባ አስገንዝበዋል፡፡

ሰላም ስለተመኘን ሳይሆን ስለሰራን የሚመጣ ጉዳይ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ ባለፉ ጊዜያት በፀጥታና እና ደህንነት ተቋማት ላይ ውጤታማ የሪፎርም ስራዎችን ጨምሮ የሰላም እሴቶችንና ማህበራዊ ተቋማት በመጠቀም መሰራቱ በክልሉ ማስመዝገብ ለተቻለው አንፃራዊ ሰላም ድርሻው የጎላ መሆኑንም አስረድተዋል።

በተከናወኑ ውጤታማ ስራዎችም ዛሬ ላይ ክልሉ የበርካታ ፀጋዎች ባለቤት ብቻ ሳይሆን፤ አንፃራዊ ሰላም የሰፈነበት በመሆኑ ተንቀሳቅሶ ለመስራት፣ ለኢንቨስትመንትና ቱሩዝም ምቹ ሁኔታ መፍጠር በመቻሉ የክልሉን የኢኮኖሚ እንቀስቃሴ ከማነቃቃት ባለፈ ተመራጭነቱን በእጅጉ ማሳደግ መቻሉንም አብራርተዋል።

ክልሉን የሰላም፤ የመቻቻልና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ ለሰነቅነው ራዕይ ስኬት፤ በክልሉ ያለን ብዝኃነትና የህዝቦች ዘመን የተሻገረ አብሮትና አንድነት ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተካናወኑ ባሉ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች እየተመዘገቡ ያሉ አመርቂ ውጤቶች አልጋ በአልጋ በሆነ አግባብ የተገኙ አለመሆኑንም ገልፀዋል፡፡

በዚህ ረገድ የክልሉ ህዝቦች አብሮ የማደግና የመልማት ትልም እና እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች የሚያማቸው ዕኩይ ዓላማ ያነገቡ አካላት፤ የክልሉን አንጻራዊ ሰላም ለማደፍረስ መጣራቸውን ጠቅሰው፤ በቀጣይም በህብረተሰቡ ተሳትፎ ሰላምን የማፅናትና የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ተግባራትን ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ለፀጥታ ስራዎች ውጤታማነት የአመራሩ ቁርጠኝነት የመጀመሪያው መሆኑንም ገልፀው፤ አመራሩ ከህብረተሰቡ ጋር በቅርበት በመስራት እና በየወቅቱ ጊዜ የማይሰጡ የፀጥታ ጉዳዮችን በመለየትና ለመፍትሄው በቁርጠኝነት በመስራት ሰላምን ማፅናት የሚገባው መሆኑን በአጽንኦት ገልፀዋል፡፡

አክለው ሰላምን ለማፅናት የፀጥታ መዋቅሩን ማጠናከር ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም ጠቅሰው፤ ለህገ መንግስቱ ታማኝ ፣ በስነ ልቦና እና ስነ-አካል የበላይነት የያዘ፤ ወትሮ ዝግጁ የሆነ የፀጥታ ኃይል የማደራጀት ተግባሩን ማጠናከር የሚገባ መሆኑን ተናግረዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ በማድፍረስ የዜጎችን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል በሚሞክሩ አካላት ላይም አስተማሪ ህጋዊ እርምጃዎችን ከመውሰድ ጀምሮ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከርና በመዋቅሮች መካከል ትብበርና ጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራርን በማጎልበት የክልሉን ሰላም ማፅናት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በጉባኤው የተገኙት በኢፌዲሪ የመከላከያ ሰራዊት የደቡብ ዕዝ አዛዥ መ/ጀነራል ሰለሞን ኢተፋ በበኩላቸው፤ በክልሉ የውስጥ ሰላምን ለማስጠበቅ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ገልፀው፤ ሰላምን ለማፅናት ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

የክልሉን ፀጥታ አስተማማኝ ደረጃ ለማድረስ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ ቁልፍ መሆኑንም ጠቅሰው፤ በዚህ ረገድ ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ በቀጣይም ከክልሉ መንግስት ጋር በቅርበት በመስራት አስፈላጊ ድጋፎችን የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም ምክር ቤቱ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ አስተማማኝ ለማድረግ የሚያስችሉ ቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ጉባኤውን አጠናቋል፡፡

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ 2.8 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል-   ወጣት ሚካኤል ዋዳጥቅምት 17/2018 ዓ.ምየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርን...
27/10/2025

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ 2.8 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል-
ወጣት ሚካኤል ዋዳ

ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት የ 2018 1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ሚካኤል ዋዳ ባለፉት 3 ወራት በክንፉ መሪነት ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል።

በሩብ ዓመቱ ከ1 ሚሊየን በላይ ወጣቶችን በልዩ ልዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች በማሳተፍ ከመንግሥት ካዝና ይወጣ የነበረ 1 ቢሊዮን 105 ሺ በላይ ብር ማዳን መቻሉንና በተግባሩም ከ 2.8 ሚሊየን በላይ የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ መደረጉን ገልፀዋል።

ወጣት ሚካኤል አክለውም በክረምት በጎ ፈቃድ ስራ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከክልል ክልል እና ከዞን ወደ ዞን በመንቀሳቀስ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን እንዲሁም ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውን ገልፀዋል።

በዲጂታል ኢትዮጵያ ፕሮግራም ፋይዳ መታወቂያ ምዝገባና ኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና ሁሉም የክልሉ ወጣቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ወጣት ሚካኤል ገልፀዋል።

በቀጣይ 90 ቀናት ዕቅድ የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ተግባራት እና በወጣቶች ስብዕና ግንባታ (mindset) ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት በልዩ ትኩረት እንደሚሠራም ጠቅሰዋል።

በቀጣይም በሶስተኛው ዙር የ 90 ቀናት ዕቅድ ጠንካራ አፈፃፀም ለማስመዝገብ መረባረብ፣ የፋይዳ ንቅናቄ እና ኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን ማጠናከር፣ የወጣቶችን የኢኮኖሚ አቅም የሚያጎለብቱ ተግባራት ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ከስምምነት በመድረስ መድረኩ ተጠናቋል።

በመድረኩ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ እንዲሁም የ 12ቱም ዞኖችና 3ቱ ሪጂዮ ፖሊሲ ከተሞች ወጣቶች ክንፍ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

 የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለገዜ ጎፋ ወረዳ አስተዳደር የተለያዩ ሹመቶችን መርምሮ አጽድቋል።  በዚህ መሠረት፦1ኛ. አቶ አድስ ዓለም ወዛ የገዜ ጎፋ ወረዳ የመንግስት ዋና ...
27/10/2025



የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለገዜ ጎፋ ወረዳ አስተዳደር የተለያዩ ሹመቶችን መርምሮ አጽድቋል።

በዚህ መሠረት፦

1ኛ. አቶ አድስ ዓለም ወዛ የገዜ ጎፋ ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪና ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ

2ኛ.አቶ ታደለ ታደሴ የገዜ ጎፋ ወረዳ ምክትል አስተዳደርና ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ

3ኛ.አቶ ወልደማርያም ወዛ የገዜ ጎፋ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ለዛላ ወረዳ አስተዳደር  የተለያዩ ሹመቶችን ሰጠ።  በዚህ መሠረት፦1ኛ. አቶ እስራኤል ሰገለ የዛላ ወ/የመንግስት ዋና ተጠሪና ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ 2...
27/10/2025

የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ለዛላ ወረዳ አስተዳደር የተለያዩ ሹመቶችን ሰጠ።

በዚህ መሠረት፦

1ኛ. አቶ እስራኤል ሰገለ የዛላ ወ/የመንግስት ዋና ተጠሪና ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ

2ኛ.አቶ አብድቀ አውቴ የዛላ ወረዳ ብ/ፓ/ቅ ጽ/ቤት ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ

3ኛ.አቶ ደመቀ ጸደቀ የዛላ ወረዳ ብ/ፓ/ቅ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ለዑባ ደብረፀሀይ ወረዳ አስተዳደር  የተለያዩ ሹመቶችን ሰጠ።  በዚህ መሠረት፦1ኛ. አቶ መልካሙ ሩንጎ ካርኬዝ የዑባ ደ/ፀ/ወ/የመንግስት ዋና ተጠሪና ብ...
27/10/2025

የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ለዑባ ደብረፀሀይ ወረዳ አስተዳደር የተለያዩ ሹመቶችን ሰጠ።

በዚህ መሠረት፦

1ኛ. አቶ መልካሙ ሩንጎ ካርኬዝ የዑባ ደ/ፀ/ወ/የመንግስት ዋና ተጠሪና ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ

2ኛ.አቶ ሙርቴ ሙርቃላ ዶኣ የዑባ ደ/ፀ/ወ/ም/አስ/ርና ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።

ውጤታማ የአስፈፃሚ ተቋማት መዋቅራዊ አደረጃጀት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ፣ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ እና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ዓይነተኛ ሚናን ይጫወታል፤ ክቡር አቶ ጋሻያለው ገ...
27/10/2025

ውጤታማ የአስፈፃሚ ተቋማት መዋቅራዊ አደረጃጀት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ፣ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ እና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ዓይነተኛ ሚናን ይጫወታል፤ ክቡር አቶ ጋሻያለው ገላ

ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም

በጎፋ ዞን የአስፈጻሚ ተቋማት አደረጃጀት፣የመንግስት ሰራተኛው ሀገራዊ የደመወዝ ስከል ጭማሪ ማስተካከያ መመሪያ እና የቀጣይ ዘጠና ቀናት ዕቅድ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።

የጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ጋሻያለው ገላ እንደገለፁት ውጤታማ የአስፈፃሚ ተቋማት መዋቅራዊ አደረጃጀት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ፣ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ እና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ዓይነተኛ ሚናን ይጫወታል ብለዋል።

የአስፈፃሚ ተቋማት አደረጃጀት ዋና ዓላማ የተልዕኮ ግልፅነት መፍጠር፣ውጤታማነትና ወጭ ቆጣቢነትን በማስፈን እና የሕዝብን አዳጊ ፍላጎቶችን የማስተናገድ አቅም መፍጠርን ያለመ እንደሆነም አብራርተዋል።

በመመሪያው ላይ የተቀመጡ ጉዳዮችን ተፈፃሚ የማድረግ ትልቁ የአመራሩ ሥራ መሆኑን ተናግረው በየመዋቅሩ ግንዛቤ መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።

አመራሩ ሕዝብን ማገልገልና ለሕዝብ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ተቀዳሚ ተግባሩ መሆኑን አውቆ የጠራ ዕቅድ በመያዝ መትጋት አለበት ብለዋል።

በየደረጃው የታቀዱ ዕቅዶች ተፈፃሚ እንዲሆኑ የአመራሩ ሚና ከፍተኛ ነው ያሉት ኃላፊው አመራሩ የመደገፍ፣ የመገምገምና ግብረ-መልስ የመስጠት ኃላፊነቱን መወጣት እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል።

አክለውም አዲሱን የአስፈፃሚ አካላት አደረጃጀት ስራ ላይ ማዋል የፓርቲው እና የአመራሩ ቁልፍ ስራ መሆኑን ተገንዝቦ በየደረጃው ከሚገኙ የሲቪል ሰርቪስና የፋይናንስ መምሪያ ህግን በተከተለ አግባብ ወደ ትግበራ መግባት ይጠበቃል ብለዋል።

የጎፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና ሥ/ፈ/ኢ/ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ምናሴ ኤልያስ እንደገለፁት የህዝብ ፍላጎትን፣ባለን የሀብት ዓቅም እና የመፈፀም አቅምን መሠረት ባደረገ መልክ ተደራጅቶ ለህዝባችን ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት እንዲሆን ተናግራል።

ምክትል አስተዳዳሪው አክለውም አደረጃጀቱን ወደ መረት ስናወርድ መመሪያን መሠረት በማድረግ የአመራሩን የመፈፀም አቅምን መነሻ ባደረገ መልኩ ተፈፃሚ ልሆን ይገባል።

በተለይ በ3ተኛው ዘጠና ቀናት የሚፈፀሙ ተግባራትን በተመለከተ ተቋማት እና መዋቅሮች እየገመገሙ ውጤታማነትን ለማምጣት መስራት ያስፈልጋል።

በመድረኩ የጎፋ ዞን ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ ኃላፊ አቶ አካሉ አምቦ ሀገራዊ የመንግስት ሠራተኛውን የደመወዝ ስከል ጭማሪ እና የውሎ አበል መመሪያን አቅርበዋል።

የመምሪያ ኃላፊው በበኩላቸው በየደረጃው ያሉ የሲቪል ሰርቪስ ተቋማት እና የየተቋማቱ ሰው ሀብቶች የሚከናወኑ ስራዎችን በቁርጠኝነት ተፈፃሚ እንድሆን መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

በአጠቃላይ ሀገራዊ የደመወዝ ስከል ጭማሪ ከመስከረም ወር ጀምሮ ተግባራዊ ተደርጎ ተፈፃሚ እንዲሆን የተወሰነው ተግባራዊ ይሆናል ብሏል።

በመድረኩ የዞኑ የፓርቲና መንግስት ያለፉት 90 ቀናት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የቀጣይ 90 ቀናት የትኩረት አቅጣጫዎች ቀርበዉ ዉይይት ተካሂዷል።

በመድረኩ የዞኑ ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ሀብታምነሽ ግራዝማች የዞኑ ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይሁን ደምሴ ፣የዞን ማዕከል አጠቃላይ አመራር፣የወረዳ/ከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እና የሲቪል ሰርቪስ እና የፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ተሳትፈዋል ።

የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት የ3ኛ ዓመት 2ኛ ዙር መደበኛ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል  ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት የደቡብ ኢትዮጵያ የክልል የፀጥታ ምክር ቤት የ3ኛ ዓመት 2ኛ...
27/10/2025

የክልሉ የፀጥታ ምክር ቤት የ3ኛ ዓመት 2ኛ ዙር መደበኛ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት የደቡብ ኢትዮጵያ የክልል የፀጥታ ምክር ቤት የ3ኛ ዓመት 2ኛ ዙር መደበኛ ጉባኤ በአርባምንጭ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመድረኩ በክልሉ የተሰሩ የፀጥታ ስራዎችን በመገምገም ጥንካሬና ጉድለቶችን ለይቶ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል እና ጉደለቶችን ለይቶ በማረም፣ በክል የክልሉን ሰላም ለማፅናት እና በባለፈው ምክር ቤት የተቀመጡ አቅጣጫዎች ትግበራን ለመገምገም ያለም መድረክ እንደሆነ ተገልጿል።

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

የጎፋ ዞን መንግስት ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች አደረጃጀት እና ሀገር አቀፍ የደመወዝ ስኬል ጭማሪ ትግበራ ላይ የኦሬንቴሽን መድረክ እያካሄደ ይገኛል።ጥቅምት 17/2018 ...
27/10/2025

የጎፋ ዞን መንግስት ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች አደረጃጀት እና ሀገር አቀፍ የደመወዝ ስኬል ጭማሪ ትግበራ ላይ የኦሬንቴሽን መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም

የጎፋ ዞን መንግስት ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች አደረጃጀት እና ሀገር አቀፍ የደመወዝ ስኬል ጭማሪ ትግበራ ላይ የኦሬንቴሽን መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

የጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ጋሻያለው ገላ የዞኑን አስፈፃሚ አካላት ተቋማት የበለጠ ቀልጣፋ ውጤታማ እንዲሆኑ የህዝብን ጥያቄ ምላሽ ሰጪ ለማድረግ የውስጥ መዋቅሮችን ስርዓቶችን እና ተግባራትን እንደገና የማሻሻል ሂደት ነው ብለዋል።

በየደረጃው ያሉ ተቋማት የተልዕኮ ግልጽነትን በመፍጠር፣ ተናባቢነት ተዋረዳዊ የጎንዮሽ ግንኙነት በማጠናከር፣ የአገልግሎት አሰጣጥ በማሻሻል ውጤታማነትና ወጪ ቆጣቢነት ለማስፈን ዓላማ ተደርጎ እንደተሰራ ተናግረዋል።

በመድረኩ የጎፋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት መምሪያ አቶ ምናሴ ኤልያስ፣የዞኑ ህዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ሀብታምነሽ ግራዝማች የዞኑ ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ይሁን ደምሴ ፣የዞን ማዕከል አጠቃላይ አመራር፣የወረዳ/ከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እና የሲቪል ሰርቪስ እና የፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባዉን እያካሄደ ነዉ17/02/2018 ዓ.ምየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባዉ...
27/10/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባዉን እያካሄደ ነዉ

17/02/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባዉን በወላይታ ሶዶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገ/መስቀል ጫላ በኢትዮጵያ መናገር፣ መፃፍና ፍትሃዊነት መሠረታዊ የዴሞክራሲ ጥያቄዎች ሆነው መቆየታቸውን ገልፀዋል።

እነኚህ ጥያቄዎች ለዘመናት ደም አፋሳሽ ጥያቄዎች ሆነዉ መቆየታቸውንም አቶ ገ/መስቀል አስታዉሰዋል።

በለዉጡ መንግስት በተለይም ከዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ጋር በተያያዘ በሀሳብ የበላይነት በማመን ማንኛውም ሀሳብ በነፃነት የሚራመድበት አዉድ ተፈጥሯል ብለዋል።

"የምንታገልለት ሕዝብ አንድ ነዉ፤ የምንታገልበት መንገድ ነዉ የሚለያየዉ። ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ሀሳባችንን ለሕዝብ ማቅረብ ከቻልን የሚፈርደው ሕዝብ ነዉ።" በማለት አስረድተዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ም/ሰብሳቢ ዶ/ር ፍሬዉ ሞገስ ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ የዘመናት ጥያቄ ሆኖ መቆየቱን ገልፀዋል።

የሚፈለገው የዴሞክራሲ ባህል ላይ ለመድረስ ተጋግዞ መስራት የግድ መሆኑን ዶ/ፍሬዉ ጠቅሰው መንግስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ተገቢውን ሚና እንዲጫወቱ ብሎም ተቋማዊ ቅርጽ ይዘው እንዲንቀሳቀሱ ለጋራ ምክር ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

ፓርቲዎች ሰላማዊ፣ በፉክክርና ትብብር መካከል ያለዉን ሚዛን በመጠበቅ የመንቀሳቀስ ኃላፊነት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።

የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ጎበዜ አበራ ዴሞክራሲ የአንድ ጀንበር ሳይሆን የዘመናት ትግል ዉጤት መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ በጋራ ጉዳዮች ላይ ተቀራርቦ የመስራትና የመነጋገር ባህል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዳበረ መምጣቱን ጠቁመዋል።

በመድረኩ የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ስራ አስፈፃሚ አባላት፣ ከ 12ቱ ዞኖችና 3ቱ ሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች የተወጣጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነገው ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነገው ዕለት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላ...
27/10/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነገው ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነገው ዕለት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉ።

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ይካሄዳል።

በመደበኛ ስብሰባው ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ለሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ም/ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከም/ቤቱ አባላት በሚቀርቡ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉ።

ምክር ቤቱም የመንግሥትን አቋም በማዳመጥ የድጋፍ ሞሽኑን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

‎በጎፋ ዞን  ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ (National ID) ምዝገባ ተጠናክሮ መካሄዱን ቀጥሏል።ጥቅምት 16/2018 ዓ/ም በጎፋ ዞን በወረዳዎች በተለያዩ ቀበሌያት ማዕከል እንዲሁም በከተማ ...
26/10/2025

‎በጎፋ ዞን ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ (National ID) ምዝገባ ተጠናክሮ መካሄዱን ቀጥሏል።

ጥቅምት 16/2018 ዓ/ም

በጎፋ ዞን በወረዳዎች በተለያዩ ቀበሌያት ማዕከል እንዲሁም በከተማ አስተዳደር በከተማ ማዕከል በተለያዩ ተቋማት በዛሬው ዕለት የምዝገባ ሂደቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

''ፋይዳ'' መታወቂያ የህዝብና የመንግስት አገልግሎቶችን የሚያሳልጥ፣ጊዜ ቆጣቢና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያግዝ በመሆኑ ማህበረሰቡ በፍጥነት በተዘጋጁ የምዝገባ ቦታዎች በመምጣት እንዲመዘገቡ መልዕክት እናስተላልፋለን።

ፋይዳ መታወቂያ እንደ ስሙ ፋይዳው ብዙ ነው። ፋይዳ መታወቂያ በማውጣት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን እናድርግ!!

የሰላም አማራጭን ለሚቀበሉ አካላት ከግማሽ ርቀት በላይ ተጉዘን እናስተናግዳለን - አቶ አደም ፋራህጥቅምት 15/2018 ዓ.ም የሰላም አማራጭን ከማስፋት ጎን ለጎን የሕግ የበላይነትን የማረጋገ...
25/10/2025

የሰላም አማራጭን ለሚቀበሉ አካላት ከግማሽ ርቀት በላይ ተጉዘን እናስተናግዳለን - አቶ አደም ፋራህ

ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም

የሰላም አማራጭን ከማስፋት ጎን ለጎን የሕግ የበላይነትን የማረጋገጡ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል አሉ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንትና የዋና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አደም ፋራህ፡፡

አቶ አደም ፋራህ በብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ የተሰጡ አቅጣጫዎችን አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በማብራሪያቸውም የሰላም አማራጭን ለሚቀበሉ አካላት ምንጊዜም ከግማሽ ርቀት በላይ ተጉዘን እናስተናግዳለን ብለዋል፡፡

ከሰላም አኳያ በሀገራችን ውስን አካባቢዎች የሰላም ችግር እንደነበር ጠቅሰው÷ አሁን ላይ አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል ሰላምና ጸጥታ የተረጋገጠበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የሰላምና የጸጥታ ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች ወደ ተረጋጋ ሁኔታ ለመቀየር ሰፊ ሥራ ሲከናወን መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡

በዚህም ውጤት መገኘቱን ጠቁመው ÷ በቀጣይ በቀሪ ቦታዎች ከሕዝብ ጋር በመሆን ሰላምና ጸጥታን እንዲሁም የሕግ የበላይነትን የማረጋገጥ ሥራ ይከናወናል ነው ያሉት፡፡

ማንኛውም የፖለቲካ ጥያቄ ያለው አካል ጥያቄውን የተፈጠረውን ምቹ ምሕዳር በመጠቀም በሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ ማቅረብ እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡

ለሰላም አማራጭ ሁሌም በራችን ክፍት ነው፤ የሰላም አማራጭን የሚቀበሉ አካላትን ምንጊዜም ከግማሽ ርቀት በላይ ተጉዘን የምናስተናግድ ይሆናል ሲሉም አረጋግጠዋል፡፡

የሰላም አማራጭን ከማስፋት ጎን ለጎን ከሕዝብ ጋር በመሆን የሕግ የበላይነትን የማረጋገጡ ሥራ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስገንዝበዋል፡፡ (ኤፍ ኤም ሲ)

Address

Gofa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገጽ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share