ጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገጽ

  • Home
  • Ethiopia
  • Gofa
  • ጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገጽ

ጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገጽ Gofa Zone Prosperity party Official page

የመደመር መንግሥት ነገን የተሻለ ለማድረግ የትናንት፣ የዛሬና የነገ ተደራራቢ ኃላፊነቶቻችንን በአስቸኳይ እንድንወጣ ያደርጋል፡፡ እንዲሁም ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም ሁኔታ ውስጥ፣ ጥንካሬያችንን...
29/09/2025

የመደመር መንግሥት ነገን የተሻለ ለማድረግ የትናንት፣ የዛሬና የነገ ተደራራቢ ኃላፊነቶቻችንን በአስቸኳይ እንድንወጣ ያደርጋል፡፡ እንዲሁም ተለዋዋጭ በሆነው የዓለም ሁኔታ ውስጥ፣ ጥንካሬያችንን ለማረጋገጥና ከግባችን ለመድረስ እንድንፈጥን ያስችላል፡፡ የመደመር መንግሥት ፍጥነትና ፈጠራን መሠረት ያደረገ ዕሳቤ ነው፡፡

ለትምህርት ዘመኑ የትምህርት ዘርፍ ስራዎች ውጤታማነትና ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደመስከረም 20/2018 ዓ.ም     ርዕሰ መስ...
29/09/2025

ለትምህርት ዘመኑ የትምህርት ዘርፍ ስራዎች ውጤታማነትና ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል የተቀናጀ ርብርብ ማድረግ ይገባል -ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

መስከረም 20/2018 ዓ.ም

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ወቅቱ በየደረጃው ባሉ የትምህርት ዕርከኖች የትምህርት ዘመኑ የመማር ማስተማር ስራ ጅማሮ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ለትምህርት ዘመኑ የትምህርት ስራዎች ውጤታማነት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ርብርብ በማድረግ የትምህርት ጥራትን የማሻሻል፤ ትውልድን በተሻለ መሠረት ላይ የማነፅ እና ለተሻለ ውጤት የማብቃት የተጀመሩ ተግባራትን በማጠናከር የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ሁለንተናዊ ብልጽግናን የማረጋገጥ ራዕይ ለሰነቀ ሀገር እና መንግስት የትምህርት ዘርፍ ውጤታማነትን ማረጋገጥ ለነገ የማይባል ተግባር ሊሆን ይገባል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የክልሉ መንግስት በማህበራዊ ልማት ዘርፍ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች ትምህርት ቀዳሚው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ ባለፉ ጊዜያት እንደ ሀገር ያጋጠመን የትምህርት ስብራት ለማከም በህብረተሰቡ ግንባር ቀደም ተሳትፎ በተከናወኑ የትምህርት ተደራሽነትን የማሳደግ እና የትምህርት ጥራትን የማሻሻል ዘርፈ ብዙ ስራዎች አበረታች ውጤት መገኘቱንም ገልጸዋል፡፡

ትምህርት በበቂ ዕውቀትና ክህሎት የተገነቡና በመልካም ስነምግባር የታነጹ የዛሬ ሀገር ገንቢዎችንና የነገ ሀገር ተረካቢዎችን በማፍራት ጠንካራ ሀገር ለትውልድ የማሻገር ታላቅ ተግባር ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ለዘርፉ ውጤታማነት የሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡

በክልሉ የህብረተሰቡ የትምህርት ልማት ተሳትፎ በተለይም ትምህርት ቤቶችን በመጽሐፍትና ሌሎች ግብዓቶች የማጠናከር፤ የማደስና አዳዲስ ትምህርት ቤቶችን የመገንባት ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣ መሆኑንም ጠቅሰው፤ በተያዘው የ2018 የትምህርት ዘመንም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ለተማሪዎች ውጤታማነት ማደግ እና የትምህርት ጥራት መረጋገጥ የግብዓት መሟላት ቁልፍ ጉዳይ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በዚህ ረገድ በክልላዊ የአንድ መጽሐፍ ለአንድ ተማሪ ኢንሼቲቪ እና በሀገራዊው የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተገኙ ስኬቶች ተሞክሮን ቀምሮ ማላቅ ይገባል ብለዋል፡፡

በትምህርት ዘመኑ የተማሪዎችን ውጤታማነት ለማሳደግ በቀዳሚነት የተማሪ ወላጆች፤ መምህራን እና በየደረጃው ያለው የትምህርት ዘርፍ አመራር የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ከወዲሁ ሊወጡ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

በተለይ የተሟላ ዕውቀትና ክህሎት ያለው፤ መልካም ስነምግባርና ስብዕናን የተላበሰ ዜጋ ማፍራት የሚቻለው የቀለም አባት የሆኑት መምህራን የተጣለባቸውን ከፍተኛ ኃላፊነት በአግባቡ ሲወጡ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ እንደተለመደው ከምንም በላይ ቅድሚያ ለትውልዱ በመስጠት በትጋት እንዲሰሩ ከአደራ ጭምር ጠይቀዋል፡፡

በክልሉ ለተማሪዎች ውጤታማነት ማደግና በተለያዩ ምክንያቶች ከትምህርት ገበታቸው እንዳይቀሩ ለማድረግ ከሚከናወኑ በርካታ ስራዎች መካከል ከ873 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተደራሽ ያደረገ የትምህርት ቤት የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር አንዱ መሆኑንም ጠቅሰው፤ በትምህርት ዘመኑ ለታለመው የማህበረሰብ አቀፍ የምገባ ፕሮግራም ስኬት በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡

በኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፈሴር ኢያሱ ኤሊያስ ለሸፊቴ 2ኛ ደረጃ እና መሰናዶ ት/ቤት የመጽሐፍት ድጋፍ አደረጉ።  መስከረም 17/2018 ዓ/ም ድጋፉ...
27/09/2025

በኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፈሴር ኢያሱ ኤሊያስ ለሸፊቴ 2ኛ ደረጃ እና መሰናዶ ት/ቤት የመጽሐፍት ድጋፍ አደረጉ።

መስከረም 17/2018 ዓ/ም

ድጋፉን በውክልና ለሸፊቴ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት የሰጡት በኢፌዲሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የኦይዳ ህዝብ ተወካይ የተከበሩ ወ/ሮ በየነች ደመቀ ሲሆኑ የተደረገው ድጋፍ ፕሮፈሴሩ በየትኛውም ጊዜ ለአከባቢው አለኝታ መሆኑን ማሳያ ነው በማለት ለተደረገው ድጋፍ በኦይዳ ህዝብ ስም አመስግነዋል።

የኦይዳ ወረዳ አስተዳደርም በተደረገው ድጋፍ ከልብ የመነጨ ምስጋና በማቅረብ ፕሮፈሴር ኢያሱ ኤሊያስ በሁሉም ዘርፍ እያደረጉ ያሉ ስራዎች ህዝብን መሠረት ያደረገ በመሆኑ ሁሉም ሰው ከእሳቸው ት/ት በመውሰድ ለህዝብ አለኝታነቸውን ማሳየት ይገባል ብለዋል።

በኢፌዲሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ዶ/ር ተስፋዬ በልጂጌ ለኦይዳ ወረዳ አስተዳደር ከ300,000 ብር በላይ የሚገመት የኮሚፕዩተር ድጋፍ አደረጉ። ሳውላ ፣ መ...
27/09/2025

በኢፌዲሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ዶ/ር ተስፋዬ በልጂጌ ለኦይዳ ወረዳ አስተዳደር ከ300,000 ብር በላይ የሚገመት የኮሚፕዩተር ድጋፍ አደረጉ።

ሳውላ ፣ መስከረም /2018 ዓ/ም

ዶ/ር ተሰፋዬ በልጂጌን በመወከል የኮሚፕዩተር ድጋፉን ያስረከቡት የጎፋ ዞን ብ/ፓ/ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ እና የመንግሥት ረዳት ተጠሪ አቶ ይሁን ደምሴ በዶ/ር ተስፋዬ በልጂጌ በኩል የተደረገው ድጋፍ ዶክተሩ ለአከባቢው ያለውን መቆርቆር የሚያሳይ መሆኑን በመግለጽ ዶ/ር ተስፋዬ በየጊዜው ለሚያደርገው ድጋፍ በዞኑ ስም አመስግነዋል።

የኦይዳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታዘቤ ጋትሦ በበኩላቸው ዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌ ከአከባቢው አልፎ በሀገር ደረጃ ትላልቅ ሥራዎችን የሠራ እና እየሠራ ያለ ብርቱ ሰው መሆናቸውን በመጥቀስ ከዚህ በፊትም ለወረዳው በተለያየ መልኩ ድጋፍ ስያደርጉ መቆየታቸውን በማስታወስ በተደረገው ድጋፍ ደስተኛ መሆናቸውን በመግለጽ ከልብ አመስግነዋል።

የጎፋ ዞን ዋና አስተዳደር ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ የመስቀል በዓልን በሣውላ ማረሚያ ተቋም ከሚገኙ ከህግ ታራሚዎች ጋር  በድምቀት አከበረ።ሳውላ፤ መስከረም 17 ቀን 2018 ዓ.ም የጎፋ ዞን ...
27/09/2025

የጎፋ ዞን ዋና አስተዳደር ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ የመስቀል በዓልን በሣውላ ማረሚያ ተቋም ከሚገኙ ከህግ ታራሚዎች ጋር በድምቀት አከበረ።

ሳውላ፤ መስከረም 17 ቀን 2018 ዓ.ም

የጎፋ ዞን ዋና አስተዳደር ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ የመስቀል በዓልን በሣውላ ማረሚያ ተቋም ከሚገኙ ከህግ ታራሚዎች ጋር የ2018 የመስቀል በዓልን በድምቀት አክብሯል፡፡

የጎፋ ዞን ዋና አስተዳደር ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ለተቋሙ አመራር፣ አባላት፣ ሰራተኞች፣ የሕግ ታራሚዎች፣ ለህግ ታራሚ ቤተሰቦች እና ለክርስትና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

አስተዳዳሪው በመልዕክታቸው ሃይማኖታዊም ይሁን ብሄራዊ በዓላት ሲመጡ የሕግ ታራሚዎች ከቤተሰቦቻቸው ጋር ያሳለፉ ያህል እንዲሰማቸው ለማድረግ በማረሚያ ተቋም የበዓሉን ስርዓት ጠብቆ አዝናኝ በሆነ መልኩ በዘር፣ በቀለም፣ በጾታ እና በብሔር ሳይለያዩ በደመቀ ሁኔታ አብሯቸው ለማክበር መምጣታቸውን ገልፀዋል።

አክለውም ወንጀል ማህበራዊ ክስተት በመሆኑ በዚህ አጋጣሚ ወደ ማረሚያ ተቋም የሚገቡ ታራሚዎች በተቋሙ የበርካታ ሙያዎች ባለቤት ሆነው በመልካም ሥነ-ምግባር ታንፀው ከወንጀል የፀዳ ሆነው ወደ ኅብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ አሳስበዋል።

በበዓሉ አከባባር ላይ የህግ ታራሚዎች አጠቃላይ ኮሚቴ የህግ ታራሚ አቡሽ አይናቴ በማረሚያ ቤት ለሚገኙ እና ለመላው የዕምነቱ ተከታዮች ሁሉ የእንኳን የአደረሳችሁ መልካም ምኞቱን አስተላልፏል፡፡

የኢቦ ባንድ ሙዚቃና ቴያትር ቡድንም ከበአሉ ጋር የሚገናኙ የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችን በማቅረብ ልዩ ለበአሉ ድምቀት ሰጥቷል፡፡

አርቲስት ምስክር ምንዳዬ(ባራንቼ) ለሁለተኛ ጊዜ በመምጣት ከታራሚዎች ጋር በዓሉን ክብሯል።

የተቋሙ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ብርቱካን መንግሥቱ የጎፋ ዋና አስተዳደር ክቡር ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ፣ የኢቦ ባንድ ሙዚቃና ቴያትር ቡድን፣ የተቋሙ ማኔጅመንት እና አጠቃላይ ሠራተኞች ከታራሚዎች ጋር በዓሉን ለማክበር በመምጣታቸው በታራሚዎችና በተቋሙ ስም አመስግነው ለህግ ታራሚዎች እና ለመላው ለእምነቱ ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በዓሉ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት፣ የተቋሙ ማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች በተገኙበት የሙዚቃና ትያትር ቡድን አባላት ታጅቦ በድምቀት ተከብሯል።

"ከራሷ አልፎ ሌሎች ሀገራትን እየመገቡ ካሉ የውኃ ተፋሰሶች ጋር ተዳምሮ፣ ቆላማ አካባቢዎችንም ጭምር ለማልማትና በአጠቃላይም ከዝናብ ጥገኝነት ለመላቀቅ የሚያስችል ደረት የሚያስነፋ ዕምቅ ዐቅ...
27/09/2025

"ከራሷ አልፎ ሌሎች ሀገራትን እየመገቡ ካሉ የውኃ ተፋሰሶች ጋር ተዳምሮ፣ ቆላማ አካባቢዎችንም ጭምር ለማልማትና በአጠቃላይም ከዝናብ ጥገኝነት ለመላቀቅ የሚያስችል ደረት የሚያስነፋ ዕምቅ ዐቅም ባለቤት ነን። ግን አልተጠቀምንበትም።"

(የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 50)

ሕዝባዊ እና ሃይማኖታዊ በዓላት የኢትዮጵያ ብዝኃነት ማሳያ ናቸው!የመስቀል ደመራ በዓል ኢትዮጵያ በዓለማቀፍ ደረጃ በማይዳሰስ ቅርስነት ካስመዘገበቻቸው መካከል አንዱ ነው፡፡ በዓሉ በመላው ኢት...
27/09/2025

ሕዝባዊ እና ሃይማኖታዊ በዓላት የኢትዮጵያ ብዝኃነት ማሳያ ናቸው!

የመስቀል ደመራ በዓል ኢትዮጵያ በዓለማቀፍ ደረጃ በማይዳሰስ ቅርስነት ካስመዘገበቻቸው መካከል አንዱ ነው፡፡ በዓሉ በመላው ኢትዮጵያ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተወራረሰ እና ተጠብቆ የቀጠለ ክዋኔን የሚያሳይ የኢትዮጵያ ብዝኃነት እና ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ማሳያ ነው፡፡

በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበዉም ይህንን ነባር የአከባበር ትውፊቱን ይዞ እንዲቀጥል፣ ከኢትዮጵያ አልፎ የሰው ልጆች ኹሉ የጋራ ቅርስነቱ እንዲጠበቅ ለማስቻል ነው፡፡

ኢትዮጵያውያንም የመስቀል ደመራ በዓልን በየዓመቱ ጥንታዊነቱንና ማኅበራዊ እሴቱን ጠብቀዉ ያከብሩታል፡፡ መንግሥት ልዩ ትኩረት ከሰጣቸዉ የኢኮኖሚ ዘርፎች አንዱ ለኾነው የቱሪዝም ዕድገትም የራሱን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡

የዘንድሮዉን የመስቀል ደመራ በዓል የምናከብረዉ ደግሞ ኢትዮጵያውያን በጋራ ያሳካነውን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ድልን እያከበርን ባለንበት ወቅት ነው፡፡ ይህም በዓሉን የበለጠ ደማቅ ያደርገዋል፡፡

እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል አደረሳችሁ!

የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህግና ፍትህ ክላስተር ማዕከል በሆነችው በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ  የመስቀል ደመራ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ ሣዉላ፣ መስከረም 16/2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በ...
26/09/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህግና ፍትህ ክላስተር ማዕከል በሆነችው በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ የመስቀል ደመራ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ

ሣዉላ፣ መስከረም 16/2017 ዓ.ም

የመስቀል ደመራ በዓል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህግና ፍትህ ክላስተር ማዕከል በሆነችው በጎፋ ዞን ሣውላ ከተማ የሀይማኖት አባቶች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን፣ የእምነቱ ተከታዮች እና የከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሯል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በአደባባይ ከምታከብራቸው ሃይማኖታዊ በዓላት መካከል አንዱ የሆነው የመስቀል ደመራ በዓል ዕለቱን በሚዘክሩ ዝማሬዎች፣ካህናትና ዲያቆናት፤ ያሬዳውያን ሊቃውንት፤ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ፣ምእመናንና ምእመናት በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተከብሯል።

በበዓሉ ላይ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የደምባ ጎፋ ወረዳ ቤተክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ቆሞስ አባ ወልደ ጊዮርጊስ የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ከተቀበረበት ቦታ በብዙ ፍለጋ የተገኘበት በመሆኑ በክርስቲያኖች ከፍተኛ ቦታ የሚሰጠውና አብሮነትን የሚያጎላ በዓል ነው ብለዋል።

የመስቀል በዓል የማህበረሰቡን አንድነት፣ መተሳሰብ እና አብሮነትን የሚያጠናክር ሃይማኖታዊ ይዘት ያለው መሆኑንም ገልጸዋል ።

በአከባበሩ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ባስተላለፉት መልዕክት በጎፋ ምድር ላይ መስቀል አበራ ሲሉ ካህናት ማዜማቸውን ጠቁመው ይህ ወቅት ለጎፋ ታላቅ ብረሃን የፈነጠቀበት ድንቅ ጊዜ መሆኑን ገልጸዋል ።

የመስቀል ደመራ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ለማዳን የተሰቀለበት ሲሆን በግፈኞች አይሁዳዊያን ተቀብሮ ለሦስት መቶ ዓመታት ቢቆይም በንግስት እሌኒ ብርቱ ፍለጋ የተገኘበት ታላቅ በዓል መሆኑን የሚዘከርበት ዕለት ነው ብለዋል ።

በበዓሉ ላይ ሰፊ የወንጌልና የዝማሬ አገልግሎት የተካሄደ ሲሆን የሃይማኖት አባቶችና መምህራን ዕለቱን አስመልክተው ሀይማኖታዊ ትምህርቶችን ሲሰጡ ቆይተዋል።

የመስቀል በዓል አከባበርን አስመልክቶ በመምህር እንደግ ገረመው የስብከተ ወንጌል አገልግሎት የተሰጠ ሲሆን ኢየሱስ ክርቶስ ለሰው ልጆች ሲል ተሰቅሎ ያዳነበት የድህነት ምልክት ጥንት ጠላታችን ዲያብሎስ የወደቀበት በእግዚአብሔር በሰዎች መካከል ያለው የፀብ ግርግዳ የፈረሰው በመስቀሉ ላይ በተከፈ ድንቅ ዋጋ መሆኑን አስረድተዋል።

በደመራ ሥነ-ስርዓቱ የሃይማኖት አባቶች ፣ የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ ፣ የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ጋሻያለው ጋላ ፣ የሣውላ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ንጉሴ መኮንን የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ከተማ ከበደን ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የእምነቱ ተከታይ ምእመናንና ምእመናት ተገኝተው በዓሉ በሠላም ተካሂዷል።

የመስቀል ደመራ በዓል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህግና የፍትህ ክላስተር ማዕከል በሆነችው በጎፋ ዞን በሣዉላ ከተማ የመስቀል ደመራ በዓል በተለያዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች እየተከበረ ይገኛል።መስከ...
26/09/2025

የመስቀል ደመራ በዓል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህግና የፍትህ ክላስተር ማዕከል በሆነችው በጎፋ ዞን በሣዉላ ከተማ የመስቀል ደመራ በዓል በተለያዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች እየተከበረ ይገኛል።

መስከረም 16/2018 ዓ.ም

የመስቀል ደመራ በዓል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህግና የፍትህ ክላስተር ማዕከል በሆነችው በጎፋ ዞን በሣዉላ ከተማ የመስቀል ደመራ በዓል በተለያዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች እየተከበረ ይገኛል።

‎በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ልዩ ክብርና ቦታ የሚሰጠው በዓለም ከማይዳሰሱ ቅርሶች ተርታ የተመዘገበው የመስቀል ደመራ በዓል በርካታ ምዕመናን በተገኙበት እየተከበረ ይገኛል።

‎በመርሃ ግብሩ ላይ የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዳግማዊ አየለ (ኢንጂነር) የጎፋ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ ክቡር ጋሻያለው ገላ ፣የዞኑ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣ከፍተኛ የመንግስትና የፓርቲ የሥራ ኃላፊዎች የሀይማኖት አባቶችና ምዕመናን ተገኝተዋል።

የጎፋ ቁጥር 1 ምርጫ ክልል የፌዴራል እና የክልል ተወካዮች በሣውላ ከተማ እየተገነባ ያለውን የዞኑን የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የህንፃ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ጎበኙትመስከረም  16/2018...
26/09/2025

የጎፋ ቁጥር 1 ምርጫ ክልል የፌዴራል እና የክልል ተወካዮች በሣውላ ከተማ እየተገነባ ያለውን የዞኑን የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የህንፃ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ጎበኙት

መስከረም 16/2018 ዓ.ም

የጎፋ ቁጥር 1 ምርጫ ክልል የፌዴራል እና የክልል ተወካዮች በሣውላ ከተማ እየተገነባ ያለውን የዞኑን የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የህንፃ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ጉብኝት አደረጉ

በጉብኝቱ በሚኒስትር ድኤታ ማዕረግ በፍትህ ሚኒስቴር የፍትህና ሕግ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የጎፋ ቁጥር 1 ምርጫ ክልል የፌዴራል ተወካይ አቶ ዘካሪያስ እርኮላ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የውሃ መስኖና ማዕድን ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር አክልሉ አዳኝ እና የጎፋ ቁጥር 1 የክልል ምክር ቤት ተወካይ ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ንግድና ገበያ ልማት ምክትል ቢሮ ኃላፊ እና የጎፋ ቁጥር 1 ምርጫ ክልል የክልል ተወካይ ዶክተር ጌትነት በጋሻው እና ለሎች የክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለደመራ እና መስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ    የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-   ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች፤...
26/09/2025

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለደመራ እና መስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች፤ እንኳን ለደመራ እና መስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

መስቀል መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች ድኅነት መስዋዕትነት የከፈለበት መንበር በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ክብር የሚሰጠው እና በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዐት የሚከበር ደማቅ በዓል ነው፡፡

በዓሉ ምእመኑ የቅዱስ መስቀሉን መገኘት በመዘከር፤ በኅብረት ደመራ በመደመርና ችቦ በማብራት በልበ ብርሃን ተሞልቶ ስለሀገር ሰላምና ስለህዝብ አንድነት ጽሎት በማድረስ ጭምር በልዩ ልዩ ኃይማኖታዊ ሥርዓቶች በአደባባይ የሚያከብረው፤ የኅብረትና የአንድነት እሴቶች ያሉት ታላቅ በዓል ነወ፡፡

ብርሃነ መስቀሉ ከጨለማ ወደ ብርሃን መሻገርን፣ ከፈተና ወደ ድል መጓዝን ማብሰሪያ ምልክት ሲሆን፤ ደመራው ፈታኙን ወቅት የመሻገራችን ብስራት፤ የመጪው የብሩህ ተስፋ ስንቅ ምልክት ነው፡፡

የዘንድሮውን የመስቀል በዓል የምናከብረው ታላቁ የህዳሴ ግድባችንን በህዝባችን የተደመረ አቅም በድል አጠናቀን፤ በስኬት ከተስፋ ወደ ሚጨበጥ ብርሃን በመሸጋገር መፃይ የኢትዮጵያን የንጋት ዘመን በተጨበጠ ብርሃን ተሞልተን ባበሰርንበት ታሪካዊ ወቅት ላይ መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡

እንደ ሀገር ተደማሪ አቅማችንን ይዘን መዳረሻችንን ሁለንተናዊ ብልጽግና በማድረግ በኅብረትና በአንድነት የለኮስነው የዘላቂ ሰላምና ልማት ችቦ ተቀጣጥሎ ብርሃኑን ማየት በጀመርንበት በዚህ ወቅት፤ በዓሉን ስናከብር ከመስቀሉ ታሪክ የተስፋ፤ የጥንካሬና የፅናት ተምሳሌትነት ትምህርት በመውሰድ ሊሆን ይገባል፡፡

የመስቀሉን ብርሃን በልቦናቸው አኑረው ተስፋ ሳይቆርጡ የጸኑ፤ የብርሃነ መስቀሉን መገኘት ለዓለም እንዳበሰሩ ሁሉ፤ ጊዜያዊና ወቅታዊ ችግሮችንና ተለዋዋጭ ፈተናዎች በጽናት በመሻገር በኅብረትና በትብበር ለድል መብቃት እንደምንችል በማሰብ በጋራ ለሰነቅነው የብልጽግና ትልም ስኬት በጽናት መነሳት ይኖርብናል፡፡

መስቀል በእምነቱ አስተምህሮ መሰረት የሰላምና የድኅነት አርማ በመሆኑ፤ በዓሉን አስተምህሮው በሚያዘው መሠረት ፍቅርን በማስቀደም፤ ዕርቅና ይቅርታን በማውረድ እና ሰላምን በማስፈን ማክበር ይገባል፡፡

ሰላም የሁሉ ነገር መሰረት ነውና በዓሉን ስናከብር ለጋራ ሰላም በጋራ በመቆምና የአካባቢያችንን ሰላም በማፅናት፤ ያሉንን ፀጋዎች ተጠቅመን ሙሉ አቅማችንንና ትኩረታችንን ልማት ላይ በማዋል የጀመርነውን የዕድገትና የብልፅግና ጉዞ ከዳር ለማድረስ በመነሳት መሆን ይኖርበታል፡፡

መስቀል ክርስቶስን የምንመለከትበት መስትዋት እንደመሆኑም ብርሃነ መስቀሉን ስናከበር ከትዕቢት ይልቅ ትህትናን ተላብሰን፤ ከመገፋፋት ይልቅ አብሮነትንና አንድነትን አጽንተን፤ ፍቅርንና በጎነትን አንብረን፤ ከራስ በላይ ሌሎች በማሰብ ሰው ተኮር በጎ ተግባራትን የሁልጊዜ ምግባራችን በማድረግ ሊሆን ይገባል፡፡

በዓሉን ስናከብር፤ በየተሰማራንበት መስክ ህዝብንና ሀገርን በታላቅ የአገልጋይነት ስሜት፤ በፍጹም ቅንነትና ታማኝነት ለማገልገል የመንፈስ ዝግጅት በማድረግ ጭምር መሆን ይኖርበታል፡፡

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እና የአንድነት እንዲሆን መልካም ምኞቴን ለመግለጽ እወዳለሁ!!

ፈጣሪ ሀገራችንና ሕዝቦቿን ይባርክ!

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን ! የመስቀል በዓል በታላቅ ኃይማኖታዊ ስርዓት ከሚከበሩ የአደባባይ በዓላት መካከል አንዱና በ...
26/09/2025

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን !

የመስቀል በዓል በታላቅ ኃይማኖታዊ ስርዓት ከሚከበሩ የአደባባይ በዓላት መካከል አንዱና በዓለም አቀፉ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም /UNESCO/ በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበ ልዩ በዓል ነው።

መስቀል በመደመር ዉስጥ ያለዉ ኃይልና ጉልበት የታየበት፣ በተለያዩ ባህሎችና ማህበረሰቦች ዉስጥ በድምቀት የሚከበር፤ ከኃይማኖታዊ ስርዓቱ በላይ የህብረ ብሄራዊ አንድነታችን መገለጫ የሆነ በዓል ነዉ።

በዓሉ ፍቅር የሚገለፅበትና አንድነት የሚያብብበት በዓል በመሆኑ በዓሉን ስናከብር እርስ በእርሳችን በመተሳሰብ፣ በመጠያየቅ፣ ከምንም በላይ ሰላማችንን አብዝተን በመጠበቅ እንዲሆን አደራ ለማለት እወዳለሁ።

በድጋሜ መልካም የመስቀል በዓል እንዲሆን እመኛለሁ።

አቶ ገ/መስቀል ጫላ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ
መስከረም 16/2018 ዓ.ም

Address

Gofa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጎፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገጽ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share