Mereja Daily24

Mereja Daily24 This is official Page of Mereja Daily
Ethiopia's Information & Entertainment
Website.

 🇪🇹 💪⚡ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ዓመታዊ የኃይል ምርት አቅሙ 15,760 ጊጋ ዋት ነው።🟢 የታላቁ የህዳሴ ግድብ በዓመት እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ያስገኛል ተብሎ ይታመናል። የታላቁ የህዳሴ...
02/09/2025

🇪🇹
💪

⚡ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ዓመታዊ የኃይል ምርት አቅሙ 15,760 ጊጋ ዋት ነው።

🟢 የታላቁ የህዳሴ ግድብ በዓመት እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ያስገኛል ተብሎ ይታመናል።

የታላቁ የህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ ከተቀመጠለት መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም. በአምስት ዓመታት ግንባታውን ለማጠናቀቅ ቢታቀድም ግንባታውን ለማጠናቀቅ 14 ዓመታትን ፈጅቷል።

ግድቡ ሲጠናቀቅ ቀድሞ በ16 ተርባይኖች 6,450 ሜጋ ዋት ኃይል ያመነጫል ተብሎ የነበረ ቢሆንም አሁን ላይ ኃይል የማመንጨት አቅሙ በ13 ተርባይኖች 5,150 ሜጋ ዋት ነው። ከተባለው 1,300 ሜጋ ዋት እና የ3 ተርባይኖች ቅናሽ ያሳያል።

ለመሆኑ ለምን ይመነጫል በተባለው የኃይል መጠን ላይ ቅናሽ ታየ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብን በጉባ ተገኝቶ በጎበኘበት ወቅት የፕሮጀክቱ ከፍተኛ አመራሮች ለጥያቄው ምላሽ ሲሰጡ የተከታተለ ሲሆን የተለያዩ ባለሞያዎችንም አነጋግሯል።

በዚህም የታላቁ የህዳሴ ህዳሴ ግድብ ኃይል የሚያመነጨው በዋነኛነት በሰበሰበው የውኃ መጠን ሲሆን ይህም ማለት ኃይል የማመንጨት አቅሙ የውኃ ፍሰቱ ላይ መሰረት ያደረገ ነው።

ባለሞያቹ እንደገለጹት የአባይ ወንዝ አማካኝ ዓመታዊ የፍሰት መጠኑ 50 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር (BCM) ነው። ይህም በዓመት ማመንጨት ይችላል ተብሎ የሚጠበቀው ከ15 ሺ እስከ 16 ሺ ጊጋ ዋት በዓመት ነው።

ይህ ማለት አሁን ባሉት 13 ተርባይኖች ማመንጨት የምንችለው ዓመታዊ የኃይል ምርት በተመሳሳይ በ16 ተርባይኖች ከምናመርተው ዓመታዊ የኃይል ምርት ጋር ተመሳሳይ እንደሆነ ያስረዳሉ።

የታላቁ የህዳሴ ግድብ ዓመታዊ የኃይል ምርት አቅሙ 15,760 ጊጋ ዋት በዓመት ሲሆን ከዚህ የተቀነሰ ነገር እንደሌለ ኃላፊዎቹ ገልጸዋል።

ይሄንን በምሳሌ ሲገልጹም

አንድ ገበሬ በአንድ አንድ ሄክታር መሬት አርሶ 50 ኩንታል እህል እንደሚያገኝ ቢነገረው እና በአንዱ ደግሞ ሁለት ሄክታር አርሶ ተመሳሳይ 50 ኩንታል እህል እንደሚያገኝ ቢነገረው ገበሬው ያለ ጥርጥር የሚመርጠው አንድ ሄክታሩን ማረስ ነው።

ለዚህም በተመሳሳይ የተርባይኑ ቁጥር ከ16 ወደ 13 እንደዚሁም የማመንጨት አቅም ከ6450 ወደ 5150 መቀነሱ በአመታዊ የኢነርጂ ምርት ላይ ለውጥ እንደማያመጣ ነው ባለሞያዎች ያስረዱት።

ከ16 ተርባይን ወደ 13 ተርባይን መቀነሱስ ምን ጥቅም ያስገኛል ?

ይህ ውሳኔ በመወሰኑ ከፍተኛ ወጪን መቀነስ ተችሏል። ከላይ እንደተገለጸው ለሦስት ተርባይኖች ሊወጣ የሚችል በመቶ ሚሊዮን ዶላሮችን ማዳን ተችሏል ተብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ ወጪ በመቀነስ ከግድቡ ሊገኝ የሚችለውን ትርፍ የሚጠበቅበትን ጊዜ ማሳጠር ተችሏል።

ህዳሴ ግድብ የወጣበትን ወጪ ከ5 እስከ 7 ዓመት ውስጥ ውስጥ ይሸፍናል ተብሎ ሲጠበቅ፤ ይህም ከግድቡ በዓመት እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ያስገኛል የሚል ግምት ተቀምጧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 🇪🇹

       #ባለዉለታወቻችን መቸም አንረሳችሁም🤟
02/09/2025



#ባለዉለታወቻችን መቸም አንረሳችሁም🤟

02/09/2025


  News 😔የ 1ሺህ ሰው ህይወት አለፈ‼️በሱዳን በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ1 ሺህ ሰዎች ህበሱዳን ዳርፉር ግዛት በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ ቢያንስ የ1 ሺህ ሰዎች ህይወት አ...
02/09/2025

News 😔

የ 1ሺህ ሰው ህይወት አለፈ‼️
በሱዳን በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ1 ሺህ ሰዎች ህበሱዳን ዳርፉር ግዛት በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ ቢያንስ የ1 ሺህ ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡

አደጋው የደረሰው በሀገሪቱ ያለውን ግጭት በመሸሽ በርካታ ተፈናቃዮች በተጠለሉበት ታራሲን መንደር መሆኑ ተገልጿል፡፡

ባሳለፍነው እሁድ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት የመኖሪያ መንደሩ መውደሙን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

አደጋው ከመከሰቱ አስቀድሞ በተከታታይ ቀናት ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን፥ በአካባቢው ለሚገኙ ወገኖች የሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል፡፡
===================

የኢንጂነር ስመኘው ልጆች* 1ኛ ትልቁ :- በእምነት ስመኘው * 2ኛው : - አሜን ስመኘው * 3ኛው ሴቷ :- በፅናት ስመኚው 😳* ይሀው የአባታችሁን ህልም* እናንተ ትቶ ነበር ለሀገሩ ብሎ በ...
02/09/2025

የኢንጂነር ስመኘው ልጆች

* 1ኛ ትልቁ :- በእምነት ስመኘው
* 2ኛው : - አሜን ስመኘው
* 3ኛው ሴቷ :- በፅናት ስመኚው 😳

* ይሀው የአባታችሁን ህልም
* እናንተ ትቶ ነበር ለሀገሩ ብሎ በረሀ ለበረሀ ሲንከራተት የነበረው

እንኳን የአባታችሁን ህልም አያችሁ ብሎ

ግድቡ ሲመረቅ በአንደኝነት በእንግድነት መጋበዝ ያላባቸው ልጆች ናቸው ብለን እናስባለን::

እናንተስ በዚህ ሀሳብ ትስማማላችሁ ?
ከተሰማማችሁ ለሚመለከተው አካል ሼር በማድረግ ተባበሩ::

🙏🙏🙏

" የተፈጠረውን የፖለቲካ ልዩነት በማጥበብ የትግራይን ህዝብ ቀጣይ እጣ ፈንታ ማቃናት ይገባል " - ጄነራል ታደሰ ወረደ ➡️ " ጊዜያዊ አስተዳደሩ ነፃነቱን ጠብቆ ስራውን አንዲሰራ የበኩሌን ...
11/04/2025

" የተፈጠረውን የፖለቲካ ልዩነት በማጥበብ የትግራይን ህዝብ ቀጣይ እጣ ፈንታ ማቃናት ይገባል " - ጄነራል ታደሰ ወረደ

➡️ " ጊዜያዊ አስተዳደሩ ነፃነቱን ጠብቆ ስራውን አንዲሰራ የበኩሌን አስተዋፅኦ እወጣለሁ " - ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመሩት ህወሓት

በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ፤ " የጊዜያዊ አስተዳደሩ ተቋማዊ ነፃነቱን ጠብቆ ስራውን አንዲሰራ የበኩሌን አስተዋፅኦ እወጣለሁ " አለ።

የአዲሱ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ በይፋ ስራቸውን የጀመሩ ሲሆን ከነባሩ ካቢኔና ከደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት ጋር ተገናኝተዋል።

ካቤኔያቸው መልሰው እንደሚያደራጁ የገለፁት ፕሬዜዳንቱ ጎን ለጎን የሦስት ወር እቅድ እንዲዘጋጅ አዘዋል።

የስራቸው ዋና ማጠንጠኛ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ ለሙሉ መተግበር መሆኑ ገልጸዋል።

- የህዝብ ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝነት መጠበቅ
- የክልሉ ኢኮኖሚ ማነቃቃት
- የአስተዳደር መዋቅሩን ማስተካከል የትኩረት አቅጣዎች መሆናቸው ተናግረዋል።

የተፈጠረውን የፓለቲካ ልዩነት በማጥበብ የትግራይ ህዝብ ቀጣይ እጣ ፈንታ ማቃናት እንደሚገባ ያሳሰቡት ጄነራል ታደሰ " አሸናፊና ተሸናፊ ከሚል መገፋፋት በመውጣት በአብሮነት በመደጋገፍ በጋራ መስራት አለብን " ብለዋል።

" ህወሓትና ጊዚያዊ አስተዳደር " የሚል ልዩነት የሚያሰፋ አጀንዳ እንዲፈታና እንዲዘጋ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

በቅርብ ጊዜ የህዝብ ኮንፈረንስ በማካሄድ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንዳቀዱና እቅዳቸው እውን እንዲሆን የሁሉም ፓለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ እንደሚሹ ጠይቀዋል።

በተያያዘ ፕሬዜዳንቱ ትላንት ማምሻውን ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመሩት ህወሓት በፅህፈት ቤቱ ይፋዊ አቀባበል አድርጎላቸዋል።

የፓርቲው ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በአቀባበል ስነ-ስርዓቱ ለፕሬዜዳንቱ ያላቸው መልካም ምኞት በማስቀደም ፤ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ተልእኮዎቹ ለመፈፀም በሚያደርገው ጥረትና እንቅስቃሴ የህወሓት ድጋፍ አይለየውም ብለዋል።

" የክልሉና የህዝቡ ችግሮች መፍታት የጋራ አጀንዳ ነው " ያሉት ጄነራል ታደሰ የፓርቲው አመራሮች ላደረጉላቸው አቀባበልና ለገለፁላቸው መልካም ምኞች አመስግነዋል።

" የትግራይና ህዝቡን መልካም ገፅታ ለመመለስ በጋራ ከመስራት ውጪ ሌላ አማራጭ የለም " ሲሉም ተናግረዋል።

መረጃው ከክልሉ ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት እና ከህወሓት የማህበራዊ የትስስር ገፅ የተወሰደ ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

ፎቶ፦ TPLF

አቶ ጌታቸው ረዳ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አቶ ጌታቸው ረዳ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አ...
11/04/2025

አቶ ጌታቸው ረዳ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አቶ ጌታቸው ረዳ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ አቶ ጌታቸው ረዳን የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትራቸው አድርገው ሾመዋል።

ሶፍት የሚያጎርሱ ፓስተሮች‼️በቤተክርስቲያን ዉስጥ ለምዕመናን ላብ የተጠረገበት ሶፍት በሚያበሉ አካላት ላይ እርምጃ ተወስዷል ተባለ‼️የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል በ...
02/04/2025

ሶፍት የሚያጎርሱ ፓስተሮች‼️

በቤተክርስቲያን ዉስጥ ለምዕመናን ላብ የተጠረገበት ሶፍት በሚያበሉ አካላት ላይ እርምጃ ተወስዷል ተባለ‼️
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል በስሩ አባል ለሆኑ በሙሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ዉጪ የሆኑ አጃሄዶች እና ልምምዶችን በሚመለከት ከድርጊቶቹ እንዲቆጠቡ መክሯል።

ዳጉ ጆርናል ከተመለከተዉ እና የርኆቦት አብያተክርስቲያናት ህብረት ለካዉንስሉ የላከው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ፤ አባላት በቤተክርስቲያን ዉስጥ ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ ከሆኑ ተግባራት እንዲቆጠቡ የሚያሳስብ ነዉ።

ለአብነትም ዘይት ፣ ዉሃ ፣ ጨርቃጨርቅ የሚሸጡ እንዲሁም ላባቸዉን የጠረጉበትን ሶፍት ለምዕመናን የሚሰጡ መኖራቸዉን አመላክቷል። ካዉንስሉ አባላት ቤተክርስቲያኖች ከመሰል ድርጊቶች እንዲቆጠቡ በጥብቅ አስጠንቅቋል መባሉንም ዳጉ ጆርናል ሰምቷል።

የርኆቦት አብያተክርስቲያናት ህብረት ካዉንስሉ ያወጣዉን መመሪያ እንደምትተገብር አሳዉቃ መሰል ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ ልምምዶችን እንደምትጸየፍ ገልጻለች።

ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል ከነብይ እዩ ጩፋ ጋር ዉጥረት ዉስጥ መግባታቸዉ የሚታወስ ሲሆን ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ ልምምዶችን በሚተግብሩ አካላት ላይም እርምጃ እየወሰደ ነዉ።

ነብይ እዩ ጩፋ በጸጥታ አካላት ሀዋሳ ከተማ ላይ እጀባ የተደረገላቸዉ መሆኑ ፤ ካዉንስሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ዉጪ ነዉ ብሎ የነበረ ቢሆንም ነብይ እዩ ጩፋ ግን የካዉንስሉን መግለጫ አጣጥለዉ ነበር። በዚህም የተነሳ በነብዩ የሚመራዉ የክራይስት አርሚ ቸርች በካዉንስሉ እገዳ ተጥሎበታል።
አዩዘሀበሻ

7 አመት ደፈኑ‼️ ሀሳብ ስጡበት ‼️ክቡር ጠ/ር ዐብይ አህመድ መጋቢት 24 ,2010 ከዛሬ 7 አመታት በፊት ነበር ወደ ስልጣን የመጡት። ያለፉት ሰባት አመታት ለናንተ እንዴት ነበር⁉️
02/04/2025

7 አመት ደፈኑ‼️

ሀሳብ ስጡበት ‼️

ክቡር ጠ/ር ዐብይ አህመድ መጋቢት 24 ,2010 ከዛሬ 7 አመታት በፊት ነበር ወደ ስልጣን የመጡት።

ያለፉት ሰባት አመታት ለናንተ እንዴት ነበር⁉️

ኢትዮጵያ 15 ሚሊዮን ዶላር ለሱዳን ሰብዓዊ ድጋፍ ለገሰች‼️ኢትዮጵያ በጦርነት ለምትታመሰው ሱዳን የ15 ሚሊዮን ዶላር (1.8 ቢሊዮን ብር) ለሰብዓዊ ድጋፍ መለገሷን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ...
14/02/2025

ኢትዮጵያ 15 ሚሊዮን ዶላር ለሱዳን ሰብዓዊ ድጋፍ ለገሰች‼️
ኢትዮጵያ በጦርነት ለምትታመሰው ሱዳን የ15 ሚሊዮን ዶላር (1.8 ቢሊዮን ብር) ለሰብዓዊ ድጋፍ መለገሷን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ ለጎረበት አገር ሱዳን እርዳታ እንምታደርግ ይፋ ተደረገው በሱዳን የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት ላይ የሚመክር የመሪዎች ጉባኤ ላይ ነው፡፡ ጉባኤው በኢትዮጵያ፣ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ በአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ አዘጋጅነት በአዲስ አበባ እየተካሄ ይገኛል፡፡

በጉዳባኤው ላይ ተገኝተው ንግግር ያድጉት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ኢትዮጵያ ለሱዳን የሰብዓዊ ድጋፍ 15 ሚሊየን ዶላር ለግሳለች ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለሱዳን ህዝብ ሰላምና መረጋጋት ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

በሱዳኑ ጦርነት እጇ አለበት የምትባለው የኢትዮጵያ መንግሥት አጋር የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በበኩሏ 200 ሚሊዮን ዶላር ለግሳለች፡፡ የኢትዮጵያ እና ዱባይ የገሱት ድጋፍ በሱዳን ጦርነት ለተገዱ ሰዎች የሰብዓዊ አቅርቦት የሚውል ነው ተብሏል፡፡

💥 vacation time 🇪🇹 💥💘💘💘
14/02/2025

💥 vacation time 🇪🇹 💥
💘💘💘




  ❤
14/02/2025

❤

Address

Gondar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mereja Daily24 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Mereja Daily24:

Share