Al meded Islamic media-አል መደድ ኢስላሚክ ሚድያ

  • Home
  • Al meded Islamic media-አል መደድ ኢስላሚክ ሚድያ

Al meded Islamic media-አል መደድ ኢስላሚክ ሚድያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Al meded Islamic media-አል መደድ ኢስላሚክ ሚድያ, Media/News Company, .

06/09/2025

ቡሌ ሆራ አንዋር መስጂድ

1500 መውሊድ በማስመልከት #ርችት ቶክሰናል አልሃምዱሊላህ።

Temam AL Hadra
👆👆Follow

31/08/2025
11/08/2025

ሰበር ዜና‎በመጅሊሱ ጉዳይ የሀገር አቀፍ ቅሬታ አቅራቢ ግብረሀይል የመንግስት ተወካዮች ባሉበት በመጅሊስ ግቢ ድርድር አካሂደናል ‎  ‎እንደሚታወቀዉ አሁን ያለዉ መጅሊስ የመጅሊስን መንበረ ስ...
02/05/2025

ሰበር ዜና

‎በመጅሊሱ ጉዳይ የሀገር አቀፍ ቅሬታ አቅራቢ ግብረሀይል የመንግስት ተወካዮች ባሉበት በመጅሊስ ግቢ ድርድር አካሂደናል

‎እንደሚታወቀዉ አሁን ያለዉ መጅሊስ የመጅሊስን መንበረ ስልጣን ከተቆናጠጠ ጀምሮ በህዝበ ሙስሊሙ ላይ የሚደርሱ በደሎች ጭቆናዎች ፣ ማሣደድ የመጅሊሱ መዋቅር አካታች አለመሆን አስመልክቶ ለሰላም ሚኒሰተር ጨምሮ ለተለያዩ ለሚመለከታቸዉ የመንግስት ተቋማት ማስገባታቸዉ ይታወቃል

‎ሀገር አቀፍ ግብረሀይሉ ይህንን የአህለ ሱና ወል ጀምዓ (የሱፍያ) ህዝበ ሙስሊም ጥያቄ በተመለከተ ለመጀመሪያ ግዜ በመንግስት አመቻችነት ከሰላም ሚኒስተር ጋር ዉይይት ማካሄዱ በቀጣይነት ቀጠሮ መያዙ መግለፃችንም ይታወሳል

‎በዚህ መሠረት ትላንት ሐሙስ ሚያዝያ 23/8/17 በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፅ/ቤት በመንግስት አዘጋጅነት ከሀገር አቀፍ ግብረሀይሉ ከተለያየ ክልል የተወጣጡ ዑለሞች ፣የሀሪማ ባለቤቶች ፣ወጣቶች እና ምሁራን በመገኘት የሰላም ሚኒስተር ተወካዮች ባሉበት የድርድሩ የዉይይት ሀሳቦች ቀርበዉ ዉይይት ተካሂዶባቸዋል

‎የሀገር አቀፉ ታስክ ፎርስ ግብረ ሀይል(ኮሚቴ) መጅሊሱ አካታች ባለመሆኑ ሁሉን አካታች እንዲሆን ፣ ቀድመዉ የተሰሩ የዑለማእ መግባቢያ ሰነዶች ፣የመጅሊሱ መተዳደሪያ ደንብ ፣እንዲሁም የመጅሊስ የምርጫ ደንብ ‎በድጋሚ ታይተዉ ተፈትሸዉ ሁሉን ባማከለ መልኩ ተስተካክለዉ እንዲከለሱ ፣ በየመስጂዱ ፣በየ መድረሳዉ ፣በኢማሞች ፣ በሙአዚኖች በሰራተኞች ላይ ሆን ተብሎ የተፈፀሙ በደሎች ጭቆናዎች የመጅሊሱ አሳሳሪነት ራሱንም አስፈቺ እንደሆነ ባጠቃላይ መጅሊሱ ከመጣ ወዲህ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተፈፀሙ ወንጀሎች በዝርዝር ቀርቧል

‎ተወካዮቻችን ከመጅሊስ ከተወከሉ አካላት ጋር ዉይይቶች የመንግስት ተወካይ አካላት በተገኙበት ዉይይት ከተካሄደ በሗላ ቀጣይ ቀጠሮዎች ይዘዉ ተለያይተዋል

‎ኢንሻአላህ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የሚገኘዉ መላዉ አህለ ሱና ወል ጀምዓ(ሱፍያ) ህዝባችን በመረጋጋት በንቃት ‎ጥያቄያችን እስኪመለስ ከዳር እስክናደርሰዉ ከጎኑ በመሆን እንድትከታተሉና እንድትደግፉ አደራ እንላለን

‎ይህ በእንዲህ እንዳለ የሀገር አቀፍ ታስክ ፎርሱ (ግብረ ሀይል) በቅርቡ ሂደቱን አስመልክቶ በዝርዝር መግለጫ የሚሠጥ ይሆናልና ህዝበ ሙስሊሙ በመላው ሀገሪቷ ነቅቶ ሊዘጋጅ ሊደራጅ ይገባል

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር

‎ሰበር ዜና ! በመጅሊሱ ጉዳይ የሀገር አቀፍ ቅሬታ አቅራቢ ግብረሀይል ከጁመዓ ጀምሮ ታላቅ ሀገር አቀፍ የያሲንና የዱአ ፕሮግራም በኡለሞች እንዲመራ ዝግጅት መደረጉ ገለፀ‎  ‎የኢትዮጵያ እስ...
15/04/2025

‎ሰበር ዜና ! በመጅሊሱ ጉዳይ የሀገር አቀፍ ቅሬታ አቅራቢ ግብረሀይል ከጁመዓ ጀምሮ ታላቅ ሀገር አቀፍ የያሲንና የዱአ ፕሮግራም በኡለሞች እንዲመራ ዝግጅት መደረጉ ገለፀ

‎የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች በሀይል የተቆጣጠረዉ ህገወጥ መጅሊስ ከመጣ ወዲህ በህለሱናወልጀማአ(ሱፍያ) ሙስሊም ማህበረሰብ በርካታ በደሎችና እንግልቶች ደርሰዉበታል አስተናግዷል እያስተናገደም ይገኛል ብሏል ግብረሀይሉ ።

‎በዚህ ምክንያት በመጅሊሱ ጉዳይ የሀገር አቀፍ ቅሬታ አቅራቢ ግብረሀይል ከጂመአ ጀምሮ ታላቅ ሀገር አቀፍ የያሲንና የዱአ ፕሮግራም ኡለሞች እንዲመሩ መርሃግብር መዘጋጀቱን አስታዉቋል ።

‎በዚህ ፕሮግራም በአህለሱናዉ ላይ በመጅሊሱ የሚደርሰዉ ጫፍ የደረሰ በደል አላህ መፍትሄ እኔዲያበጅ እና አላህ ነስሩን እንዲያመጣዉ የተጀመረዉ ትግል ዉጤታማ እንዲያደርገዉ ሲሆን ከምንም በላይ ለሀገራችን ሰላም አንድነት ልማት ዱአ ምናረግበት ጭምር ነዉ በማለት የግብረሀይሉ የህዝብግንኙነት አቶ ሰይፉ አሊ ከሚዛን ጋር በነበራቸዉ አጭር ቆይታ ገልጸዋል ።

‎የየያሲንና የዱአ ፕሮግራሙ ለይለተል ጁመአ ዱአ እያደረጉ መሻኢኾቹ ያድራሉ እንዲሁም አርብ ከአምስት ሰአት ጀምሮ በሀሪማዎች ፣በሀድራ ቦታዎች ፣በግል መኖሪያ ቤቶች ፣በዛዉያዎች እንደሚጀመርም አስታዉቀዋል ።

ሚዛን ሚዲያ Mizan Media

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Al meded Islamic media-አል መደድ ኢስላሚክ ሚድያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share