26/08/2026
ሀገራዊ ምክክራችን ለሀገረ መንግስት ግንባታችን የራሱን አስተዋህጾ በማበርከት ተጠናቋል!!!
የሀገራችን ዜጎችን በአንድ ቦታ በማሰባሰበድ እዲተዋወቁና እዲመካከሩ እድል ሰጥቶል፤ከአራቱም የሀገራችን መዕዘናት እንዲሁም በዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን ጭምሮ 4ሺ የሚሆኑ ምናልባትም በአይነ-ቁራኛ የሚተያዩ ሰዎችን በማሰባሰብ በሀገራቸዉ ጉዳይ እዲወያዩና ምክረ-ሃሳብ እንዲሰጡ ማድረጉ በራሱ አዲስ የባሀል-ለዉጥ/ግንባታ ሲሆን ሁሉን ነገር በሀገራችን በግልም ይሁን በቡድን አብዛኛዉን ግዜ እንደለመድነዉ በጉልበት፤በነፍጥና ሌላዉን በማበርከክ የመፍታት አባዜያችን ተላቀን በዉይይትና በምክክር የመፍታትን ባህል በአዲስ መልክ ማለማመድ ማስጀመሩ ትልቅ እምርታ ነዉ፡፡
ለዉይይትና ለምክክር ከቀረቡት 8ቱ አጀንዳዎችና በሌሎች የተሰጡት ምክረ-ሃሳቦች ለሀገራችን ፖሊሲ አዉጭዎች፤ፖሊቲከኞች፤ህግ አዉጭዎች፤የሚዲያ ባለሙያዎች፤ለምሁራኖችና ተመራማሪዎች ከፍተኛ ግብአት በመሆን የሚያገለግል ሲሆን ይህም ፖሊሲና ህጎችን ለማዉጣትና ተጨማሪ ጥናትና ምርምር ለሚፈልጉ ጉዳዮችን ለማከናወን ጥሩ የመነሻ ሃብት ሁኖ የሚያገለግል ጉዳይ ነዉ ብሎ መዉሰድ ይቻላል፡፡
ምንም እንኳን በሁሉም አጀንዳዎች ላይ መስማማት ላይ ባይደረሰም መድረኩ ላይ የተገኙ ሰዎች የተለያዩ የኢትዮጵያዊያን ያለቸዉን አመለካከት፤ህመምና ፈላጎት ብዙ መሆኑን እዲገነዘቡና የኛ ሀገር ጉዳይ ከርቀት ወሬና በማህበራዊ ሚዲያዉ አንደሚናፈሱ ሳይሆን ከፍተኛ የሆነ ማስተዋልን፤እዉቀትን፤ጥበብና በስለት የሚፈልግ መሆኑን ሁሉም ተሳታፊዎች የተማሩበት መድረክ ነበረ ማለት ይቻላል፡፡
ስለሆነም ሁላችንም ኢትዮጵያዊያን መደረኩን እንደ የሁሉም ነገር መነሻ በማድረግ የጋራ ሀገራችንን ለመገምባት መደማመጥን፤ሆደ ሰፊነትን፤መከባበርንና መተባበርን ከመቼዉም በላይ ልናስብበት የሚገባን ጉዳይ ነዉ፡፡