Mohammed Redwan Mume

Mohammed Redwan Mume Agriculture is a key for development, thus late joint together & promote the success, achivement & efforts made in agricultural sectors as a whole.

21/09/2025
10/09/2025
24/08/2025
03/07/2025
02/07/2025

በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የአገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ-ኢንስቲትዩቱ

አዲስ አበባ፤ሰኔ 25/2017(ኢዜአ):-በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የአገሪቱ አካባቢዎች ብዙ ቦታዎች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት አስር ቀናት ለክረምት ዝናብ መፈጠር ምቹ ሁኔታን የሚፈጥሩ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ይበልጥ እየተስፋፉና እየተጠናከሩ ይቀጥላሉ።

በደቡብ ምዕራብ፣ምዕራብ፣ሰሜን ምዕራብ፣ሰሜን፣ መካከለኛው እና ሰሜን ምስራቅ የአገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የዝናብ መጠንና ሥርጭት እንደሚኖር አሃዛዊ የትንበያ መርጃዎች እንደሚያሳዩ ተጠቁሟል።

በተለይ በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ሰሜን ምዕራብና መካከለኛ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ ብለዋል።

አልፎ አልፎ በውሃ አካላትና አካባቢ በምዕራብ፣ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን ምስራቅ እና መካከለኛው የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ በ24 ሰዓት ውስጥ ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ሊኖራቸው እንደሚችል ገልጸዋል።

በተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ነጎድጓዳማና በረዶ አዘል ዝናብ እና የዝናቡ ጥንካሬም ለረጅም ሰዓታት ያለማቋረጥ ዝናብ ሊኖር እንደሚችል በመግለጫው ተመላክቷል።

በክረምቱ ወቅት የሚዘንበው ዝናብ በአመዘኙ አዎንታዊ ሚና የሚኖረው መሆኑ ተገልጿል።

ይህም አስቀድሞ ለተዘሩ ሰብሎች፣ ለመኽር ሰብሎች፣ ለቋሚ ተክሎችና የጓሮ አትክልት የውሃ ፍላጎት ለማሟላት በኩል መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።

አብዛኛው የአገሪቱ ተፋሰሶች ላይ ከመጠነኛ እስከ ከፍተኛ የገጸ ምድር የውሃ ፍሰት ይኖራቸዋል፤ነገር ግን አልፎ አልፎ የሚኖረው ከባድ ዝናብ ጎርፍ ሊያስከትል ስለሚችል ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ ተመላክቷል።

በሌላ በኩል በመጪው አስር ቀናት የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር፣ በምስራቅ አማራ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ምዕራብ እና ደቡብ ምስራቅ የአገሪቱ ሥፍራዎች ላይ ከ26 እስከ 41 ዲግሪ ሴልሺዬስ በላይ ሙቀት እንደሚኖራቸው ትንበያው ያሳያል።

#ኢትዮጵያ
#ኢዜአ

በሀረሪ ክልል በድሬ ጠያራ በወረዳ 150 ሄክታር መሬት በቃሪያ ክስተር እየለማ መሆኑ ተገለፀ። *****************************በወረዳው የሚገኙ አርሶ አደሮች አነስተኛ ማሳቸውን...
02/07/2025

በሀረሪ ክልል በድሬ ጠያራ በወረዳ 150 ሄክታር መሬት በቃሪያ ክስተር እየለማ መሆኑ ተገለፀ።
*****************************

በወረዳው የሚገኙ አርሶ አደሮች አነስተኛ ማሳቸውን ተጠቅመው ምርትና ምርታማነታቸውን በማሳደግ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ መሆኑን የድሬ ጠያራ ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት አስታወቀ።

የድሬ ጠያራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት አስተባባሪ አቶ ናዊ ዳውድ ከሀረሪ ብዙሃን መገናኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ አነስተኛ ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ባላቸው መሬት ላይ የተለያዩ አይነት ዘሮችን በማምረት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በወረዳው በአሁኑ ወቅት 150 ሄክታር መሬት በቃሪያ ክላስተር እየለማ መሆኑን ገልጸው በዚህም ከ650 አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡

ለቃሪያ ምርቱም የገበያ ትስስር በመፍጠር በአካባቢ ለሚገኙ ከተሞች የማቅረብ ስራ እየተሰራ ነው ሲሉም አስተባባሪው ገልጸዋል፡፡

የቃሪያ ክላስተር ተጠቃሚ የሆኑ አርሶ አደሮች በበኩላቸው ከዚህ ቀደም በማሳቸው አንድ አይነት ምርት ብቻ ሲያመርቱ እንደነበሩ ገልጸው አሁን ግን ባገኙት ተሞክሮ የተለያዩ ምርቶችን እያመረትን ተጠቃሚ ሆነናል ብለዋል።

የወረዳ ግብርና ጽ/ቤትም የተለያዩ ምርጥ ዘሮችና ግብአቶችን እያቀረበላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አርሶ አደሮች በአነስተኛ ማሳቸው የተለያዩ ምርቶችን በማምረት ተጠቃሚ እንዲሆኑም አቶ ናዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ዘጋቢ፦ ሙህየዲን ሙክታር
25/11/17

ለተጨማሪ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከታተሉን።

ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/

ዩቲዩብ : https://www.youtube.com/

ቴሌግራም: https://t.me/hararimassmediaagency

Address

Harar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mohammed Redwan Mume posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share