15/08/2026
በሀረሪ ክልል ቅርስን የማልማትና ከመጠበቅ ባሻገር ባህልና ቋንቋን ለማሳደግ ይሰራሉ- ባህል ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ
በሀረሪ ክልል በያዝነው በጀት አመት ቅርስን የማልማትና ከመጠበቅ ባሻገር ባህልና ቋንቋን ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ የክልሉ ባህል ቅርስና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ናስር አህመድ በበጀት ዓመቱ በሚከናወኑ አበይት ተግባራት ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።
ምክትል ኃላፊው በመግለጫቸው በክልሉ በተለይም ከቅርብ አመታት ወዲህ ቅርስን በመንከባከብና በማልማት ረገድ የተከናወኑ ስኬታማ ስራዎችን የበለጠ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በክልሉ የሚገኙ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ቅርሶችን ምዝገባ፣ ጥገና፣ እድሳት በማድረግ ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ የማስችል ስራዎች በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።
በክልሉ የሚገኙ ቱባ ባህሎች የመጠበቅና የማልማት ስራ የበጀት አመቱ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ገልጸዋል።
የሀረሪ ቋንቋን ለማሳደግም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት እንደሚሰራ ገልፀው የዘርፉ ባለሙያዎችን አቅም የማሳደግ ስራም ሌላው ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ነው የተናገሩት።
የህብረተሰቡን የዘርፉ ተጠቃሚነት ለማሳደግም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ይሰራል ብለዋል።