Today is my Day

Today is my Day Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Today is my Day, Digital creator, Hawassa.

24/05/2024

የወሊድ መቆጣጠሪያ መውሰድ ይቻላል?

መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ወሊድ መቆጣጠሪያ ምን ይላል?

ከሰዎች ወቅታዊ ችግር አንጻር እንዴት ይታያል?

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ላላወቁ አሳውቁ

ተወዳጆች ሆይ በዚህ ርእስ እንደ ቤተ ክርስቲያናችን መጻሕፍት ሥርዐት እና ከሰዎች ወቅታዊ ችግር አንጻር በሰፊው እንመለከታለን፡፡

የወሊድ መቆጣጠርያ መውሰድ ይቻላል ወይስ አይቻልም ብለን ስናስብ በመጀመሪያ ከእግዚአብሔር መለኮታዊ እቅድ እና ሐሳብ ብሎም የሰውን ልጅ ዘር ከማስቀጠል ጋር ነው የምንጋጨው፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር መውለድን ተቆጣጠሩ ሳይሆን በመውለድ ተባዝታችሁ ኑሩ ነው ያለን፡፡ እኛ ገና ያልተፈጠሩት ልጆች በወሊድ መቆጣጠሪያ ወደዚህች ምድር እንዳይመጡና ከእኛ አብራክ እንዳይወለዱ እንከላከላለን፡፡ ግን ልዑል እግዚአብሔር ገና ሳንፈጠር አካላችን በእናታችን ማሕፀን ሳይሠራ፣ ነፍሳችን በሥጋችን ሳትዘራ ያውቀናል፡፡ ለዚህም ነው ‹‹ያልተሠራ አካሌን ዓይኖችህ አዩኝ፤ የተፈጠሩ አካሌን ቀኖቼ ሁሉ አንድስ እንኳ ሳይኖር በመጽሐፍ ተጻፉ›› ያለው፡፡

ወዳጆቼ እግዚአብሔር በማሕፀን ሳንሠራ አካላችንን ያውቃል ያያል፡፡ /መዝ 139፣16/ እንዲሁም እግዚአብሔር እኛ ገና ለገና ሳይፈጠሩ የወሊድ መቆጣጠሪያ ወስደን እንዳይወለዱ የምንከላከላቸውን ልጆች አስቀድሞ ሳይፈጠሩ እንደሚያውቃቸው በመጽሐፈ ኤርሚያስ ላይ ‹‹በሆድህ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ›› በማለት ተናግሯል፡፡ ስለዚህ እኛ መውለድ እየቻልን ግን በወሊድ መቆጣጠሪያ ይምከኑ አይምከኑ የማናውቃቸው ልጆች በእግዚአብሔር ዘንድ የታወቁ ናቸው፡፡ እግዚአብሔር ‹‹ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት›› ብሎ በቡራኬ አዞናል፡፡ ግን እጅጉን በሚያሳዝን ሁኔታ ዛሬ ልጆች እንደ ሸክም ተቆጥረዋል፡፡ እኛ አንወልድም እያልን በወሊድ መቆጣጠሪያ የምንከላከላቸው ልጆች መካኖች መውለድ የሚመኟቸው ልጆች ናቸው፡፡ እኛ ለምለም ማሕፀን ይዘን ልጅ መውለድ አልፈልግም የምንለው መካኖች ዐሥር በወለድኩበት የሚሉበት ማሕፀን ነው፡፡

እግዚአብሔር በመጀመሪያ ደረጃ የወሊድ መቆጣጠሪያን በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተቃወመው በይሁዳ ልጅ በአውናን ነው፡፡ ትዕማርን ያገባው ዔር ክፉ ስለነበር አካሄዱም ከእግዚአብሔር መንገድ የወጣ ስለሆነ እግዚአብሔር ቀሠፈው ሞተ፡፡ ምስኪኗ ትዕማርም ያለ ባል ቀረች፡፡ ከዚያም ለሟቹ ለዔር ወንድም ለአውናን በጋብቻ ተሰጠች፡፡ አውናንም እንደ ወንድሙ ክፉ ነበርና ያለውን ርስት ገና ለገና በሟች ወንድሙ ፈንታ ለሚወልዳቸው ልጆች ላለማካፈል ብሎ በወቅቱ በነበረው የእርግዝና መከላከያ ዘዴ እና በነበረው ልምምድ ከትዕማር ጋር ሩካቤ ሥጋ ሲፈጽም ዘሩን ከማሕፀንዋ ውጭ እያፈሰሰ እርግዝናን ይከላከል ነበር፡፡ ይህንን ተግባሩን መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ይህም ሥራው በእግዚአብሔር ዘንድ ክፉ ሆነበት፣ እርሱንም ደግሞ ቀሠፈው›› ይለናል፡፡ /ዘፍ 38፣10/ ወዳጆቼ አውናን በወቅቱ በነበረው ልምድ ባደረገው እርግዝና መከላከያ ዘዴ እርሱም ዘርን ከማሕፀን ውጪ በማፍሰስ ቢጠቀምም ከእግዚአብሔር ዘንድ ግን ቅሥፈትን አስተናግዷል፡፡

አንዳንድ ሰዎች አውናን የተቀሠፈው ዘሩን ከማሕፀን ውጭ በማፍሰሱ ሳይሆን ራስ ወዳድነት በተሞላው ክፉ ተግባሩ ነው የሚሉ አሉ፡፡ ይህ ግን ትልቅ ስሕተት ነው፡፡ አውናን ዘሩን ከማሕፀን ውጭ በማፍሰሱ እርግዝና እንዳይፈጠር በፈጣሪ ሥራ ስለገባ እና ዘሩን ያለ ቦታው ስላፈሰሰ ነው የተቀሠፈው፡፡ ወዳጆቼ አንድ ወንድ ከሚስቱ ጋር በሩካቤ ሥጋ ጊዜ ዘሩን ከማሕፀን ውጭ ቢያፈስ እና ሌላ ሰው ደግሞ ሚስቱን የእርግዝና መድኃኒት ውሰጂ ብሎ ወይም ሚስቱ የእርግዝና መከላከያ ወስዳ በሩካቤ ሥጋ ጊዜ ግን ዘሩን በማሕፀንዋ ውስጥ ቢያፈስ ዘሩን ከማሕፀን ውጪ ካፈሰሰው ሰው ጋር ልዩነቱ ምንድን ነው? መቼም ዘሩን ከማሕፀን ውጪ ያፈሰሰውን ኮንነን እንዲሁም ዘሩን የወሊድ መቆጣጠሪ በወሰደች ሴት ማሕፀን ውስጥ ያፈሰሰውን ልክ ነው ልንል አንችልም፡፡ ዘሩን በማሕፀን ያፈሰሰውን ሰው ምናልባት ዘሩን በተገቢው ቦታ ማፍሰሱን ነው የምናየው እንጂ ቀድሞ ዘሩ ልጅ እንዳይሆን የተጠቀሙትን የወሊድ መቆጣጠሪያ አናስብም፡፡ አውናን በራሱ የልምድ መንገድ እርግዝናን ስለተከላከለ ተቀሠፈ፡፡ እኛ ደግሞ በሰው ሠራሽ ዘዴ እርግዝናን ብንከላከል ጥፋት አይደለምን?

ወዳጆቼ የትኛውንም የወሊድ መቆጣጠሪያ ስንጠቀም መድኃኒቱ የወንድና የሴቷን ዘር እንዳይዋሐድ፣ በማሕፀን ግድግዳ ላይ ጸንቶ እንዳይቀመጥ እና እንዲመክን/እንዲፈርስ ያደርገዋል፤ ይህ ድርጊት ከአውናን በምን ይለያል? ይህን መሰል ድርጊት ፍትሐ ነገሥ ‹‹መጀመሪያው ግን ስለ ጋብቻ የሆነው መጀመሪያው ፈቃድ አስቀድመን እንዳስረዳን ዘርን ለመተካት ካልሆነ በቀር አይጸናምና፡፡ ዘርንና የሚመስለውን ከማራቅ ጋራ እንግዲህ ሚስት ማግባት እርሱን የሚፈልጉት የማይገኝበት ትሆናለች፡፡ እንዲህ ከሆነ ለሚያገባ ሰው ሚስት ማግባትን መተው ይገባዋል›› ይለናል፡፡ /ፍት.ነገ አንቀ 24÷927/ ይህ ማለት ዘሩን ከማሕፀን ውጪ እያፈሰሰ እና በሰው ሠራሽ መንገድ ልጅ እንዳይወለድ የሚያደርግ ከሆነ ባያገባ ይሻላል ማለቱ ነው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እኛ የሰው ልጆች ወደ ፊት እርግዝና መከላከያ እንደምንጠቀም አውቆ በማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜ ላይ ‹‹ለተፈጥሯቸው ልጅ እንዳይገኝ እነሆ ይጥራሉ፡፡ ይሄስ ካሉት መታጣት ይከፋል፡፡ ይህም ክፋት ያሉት ይታጡ ዘንድ ነው፡፡ ይህም ዘርን አውጥቶ በማይሆን ቦታ ስለማፍሰስ ይሆናል፡፡ ፅንስንም ስለ መከልከል ሥራይ በማድረግ ነው›› ብሎናል፡፡ ወዳጆቼ እዚህ ላይ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ‹‹ፅንስን ስለ መከላከል ሥራይ በማድረግ›› ብሎ የገለጠው አሁን ፅንስን ለመከላከል መድኃኒት ለምንውጥ እና መርፌ ለምንወጋ ሰዎች ቀድሞ በመንፈስ ቅዱስ መገለጥ የጻፈልን ነው፡፡ ‹‹ሥራይ›› የሚለውን ቃል የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ‹‹መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ›› ‹‹የሚዋጥ መድኃኒት፣ የሚላመጥ፣ የሚጠጣ፣ የሚቀባ›› በማለት ይተረጉመዋል፡፡ ስለዚህ ፅንስን ለመከላከል ሥራይ ወይም መድኃኒት መውሰድ/መዋጥ የሚገባ እንዳልሆነ ነው፡፡

ተወዳጆች ሆይ እዚህ ላይ ልብ ልትሉት እና በአግባቡ ልትጠቀሙበት የሚገባው፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሠራችልን አጽዋማት እና በዓላት ካወቅንባቸው በራሳቸው የወሊድ መከላከያም ናቸው፡፡ ምክንያቱም በአጽዋማት እና በበዓላት ወራት እና ቀናት ከሩካቤ ሥጋ የምንታቀብባቸው ስለሆኑ በትክክል ከተጠቀምንባቸው ልጆችን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ባሰብነው መልኩ እንወልዳለን፡፡ ችግሩ ግን አጽዋማትንና በዓላትን እየሻርን ሩካቤ ሥጋ ስለምንፈጽም ልጅን በአናት በአናቱ ልንወልድ እንችላለን፡፡ አስኪ አስቡት የእርግዝና ወራት፣ ሰባቱ አጽዋማት፣ የአራስነት ወራት፣ ዓርብ ረቡዕ፣ እሑድ ቅዳሜ፣ የሴቶች የወር አበባ ቀናት፤ እነዚህ ከታቀብንባቸው እና በፈቃድ ቀናት ሩካቤ ሥጋ ብንፈጽም ‹‹ያለ ዕቅድ እና ድንገተኛ እርግዝና›› እያልን ከምንሳቀቀው ሰቆቃ ነፃ እንሆናለን፡፡

ይቀጥላል

በ አቤኔዘር ዘተዋሕዶ 🙏

ታማኝ እንሁን!!
24/05/2024

ታማኝ እንሁን!!

09/04/2024

በረሮ ጭንቅላት ተቆርጦ ሳይሞት ለ 1 ሳምንት ይቆያል።

05/04/2024
21/03/2024

የወንድ የዘር ፍሬ እና የሴት እንቁላል ልገሳ ጥሪ

👉 ወንድ የዘር ፍሬ ለጋሾች የሚሰጡት የዘር ፈሳሽ ከ1.5 ሚሊ ሊትር በላይ መሆን አለበት።
👉 ለእንቁላል ልገሳ ብቁ የሚሆኑት ሴቶች ዕድሜያቸው ከ20 እስከ 30 ባለው ውስጥ የሚገኙት ናቸው።
👉 የዘር ፍሬው በሚወሰድበት ዕለትም “በማስተርቤሽን መንገድ የዘር ፈሳሽ ይሰጣሉ” ሲሉ ሂደቱን ያስረዳሉ።
👉 ዘር ፍሬ የሚለግሱ ወንዶች አስር ሺህ ብር “የማበረታቻ ገንዘብ” እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።
👉 እስካሁን ድረስ ግን እንቁላልም ይሁን የዘር ፍሬ የሚለግሱ ፈቃደኞችን ማግኘት አለመቻሉን የማዕከሉ ባለቤት ተናግረዋል።

አዶ የእናቶች እና ህጻናት እንዲሁም የመካንነት ህክምና ማዕከል፤ ይህንን ህክምና ለመስጠት ዝግጅት የጀመረው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከመጀመሩ አስቀድሞ እንደነበር ዶ/ር ሳምሶን ይናገራሉ። በጦርነቱ ምክንያት ህክምናውን ለማስጀመር የተደረገው ጥረት ተቋርጦ የቆየ ሲሆን፣ ጦርነቱ ከቆመ በኋላ ሂደቱ እንደገና ቀጥሎ ህክምና መስጠት ላይ ተደርሷል።

ማዕከሉ በአሁኑ ሰዓት እየተጠባበቀ ያለው የወንድ ዘር ፍሬ እና የሴት እንቁላል ለመለገስ ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎችን ነው።

እንደ ዶ/ር ሳምሶን ገለጻ፤ ሁሉም ሰው የዘር ፍሬ ወይም እንቁላል መለገስ አይችልም። በሁለቱም ፆታዎች ያሉ ለጋሾች ከፈቃደኝነት ባሻገር ብቁ የሚያደርጋቸው መስፈርት አለ።

ወንድ የዘር ፍሬ ለጋሾች የሚሰጡት የዘር ፈሳሽ ከ1.5 ሚሊ ሊትር በላይ መሆን አለበት። በአንድ ሚሊ ሊትር የዘር ፈሳሽ ውስጥም ከ15 ሚሊዮን በላይ የዘር ፍሬ ህዋሶች ሊኖሩ ይገባል። በተጨማሪም ለጋሾቹ በሚደረግላቸው ምርመራ ከኤችአይቪ፣ ከጉበት ቫይረስ እና ከሌሎች ተላላፊ በሽታዎች ነጻ መሆናቸው መረጋገጥ አለበት።

እንቁላል የሚለግሱ ሴቶች ላይ ደግሞ የዕድሜ ገደብም እንዳለ ዶ/ር ሳምሶን ያስረዳሉ። ለእንቁላል ልገሳ ብቁ የሚሆኑት ሴቶች ዕድሜያቸው ከ20 እስከ 30 ባለው ውስጥ የሚገኙት ናቸው። ከዚህም ባሻገር ሴት ለጋሾች ከዚህ ቀደም የወለዱ መሆን አለባቸው።

ዶ/ር ሳምሶን ይህ መስፈርት የተቀመጠበትን ምክንያት ሲያስረዱ፤ “[የወለዱ ሴቶች] እንቁላላቸው የተፈተነ ነው። ምክንያቱም ወልደዋል፤ እንቁላላቸው ኖርማል እንደሆነ ማረጋገጫ አለ። ዕድሜያቸው አነስ ሲል ደግሞ እንቁላሉ ጥራት ይኖረዋል። ጥራት ያለው እንቁላል ሲሆን ጽንስ የመፈጠር ዕድሉ ሰፊ ነው፤ ወደ 80፣ 85 በመቶ ይደርሳል። ይህም በዓለም ላይ የሚሠራበት ልምድ ነው” ይላሉ።

እነዚህን መስፈርቶች የሚያሟሉ ለጋሾች ከተቋሙ ጋር የሚገቡት ስምምነትም እንዳለ የማዕከሉ ባለቤት ገልጸዋል። የማህጸን እና የጽንስ ስፔሻሊስቱ እንደሚያስረዱት፤ በስምምነቱ ላይ ከተቀመጡ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የተለገሰው የዘር ፍሬ ወይም እንቁላል ለማን እንደሚሰጥ የማይገለጽ መሆኑ ነው።

“ደም ሲለገስ ለማን እንደሚሰጥ አይታወቅም። የሰው ሕይወትን ማዳን ነው የሚታሰበው። እዚህም ላይ ሰውን መርዳት ነው የሚታሰበው” ሲሉ አካሄዱ ከደም መለገስ ጋር ተመሳሳይ መርኅን እንደሚከተል ይጠቅሳሉ።

ይሁንና የተለገሰው የዘር ፍሬ ለማን እንደተሰጠ ሊታወቅ የሚችልባቸው አጋጣሚዎች አሉ። ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ተቀባዮች ልገሳ የሚያደርጉላቸውን ሰዎች ራሳቸው ይዘው ሲመጡ ነው።

በልገሳ ወቅት የሚፈረመው ስምምነት ለዚህም መፍትሔ ማስቀመጡን ዶ/ር ሳምሶን ጠቅሰዋል። ለጋሾች በሚሰጡት እንቁላል ወይም የዘር ፍሬ አማካኝነት ጽንስ ከተፈጠረ በኋላ የሚወለደው ልጅ ላይ የወላጅነት ጥያቄ ማንሳት እንደማይችሉ የማህጸን እና ጽንስ ስፔሻሊስቱ ይገልጻሉ።

“ውሉ ላይ የሚፈረመው ‘እኔ በፍቃደኝነት እየለገስኩ ነው። የሚፈጠረው ጽንስ፣ ልጅ ባለቤትነቱ የተቀባዮቹ ነው’ ተብሎ ነው። ስለዚህ ብዙ ጭቅጭቅ ውስጥ የሚያስገባ ነገር አይደለም” ሲሉ ከስምምነቱ ዋነኛ ጉዳዮች ውስጥ አንዱን አንስተዋል።

በዚህ ውል ተስማምተው የሚፈርሙ ወንድ እና ሴት ለጋሾች በተለያዩ ሂደቶች ውስጥ ያልፋሉ። ወንድ ለጋሾች በምርመራ ነጻ መሆናቸው ከተረጋገጠ በኋላ የዘር ፍሬ እስከሚሰጡበት ቀን ድረስ ከማንኛውም ዓይነት ወሲባዊ ግንኙነት ተቆጥበው መቆየት እንዳለባቸው ዶ/ር ሳምሶን ይናገራሉ።

የዘር ፍሬው በሚወሰድበት ዕለትም “በማስተርቤሽን መንገድ የዘር ፈሳሽ ይሰጣሉ” ሲሉ ሂደቱን ያስረዳሉ። ዘር ፍሬ የሚለግሱ ወንዶች አስር ሺህ ብር “የማበረታቻ ገንዘብ” እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።

እንቁላል የሚለግሱ ሴቶች የሚከተሉት ሂደት በአንጻሩ ወንድ ለጋሾች ከሚያልፉበት የበለጠ ቀናትን ይወስዳል። በዚህ ሂደት የሚያልፉ ሴቶች ከመለገሳቸው በፊት “እንቁላል እንዲያድግ የሚያደርግ መርፌ” እንደሚወስዱ ዶ/ር ሳምሶን ይገልጻሉ።

“[ለጋሽ ሴቶች] ወደ 10 ቀን አካባቢ መርፌ ይወስዳሉ። እንቁላሉ አድጓል ብለን ስናስብ [እንቁላል] የምንሰበስበው በማህጸን የሚገባ አልትራሳውንድ አለ በዚያ አማካይነት ነው” ሲሉ ሂደቱን አብራርተዋል።

ሴት ለጋሾች እንቁላል ለመስጠት የሚያልፉበት ሂደት እንደ ወንዶች “ቀላል” ባለመሆኑ እና ለቀናት ወደ ማዕከሉ ስለሚመላለሱ የሚያገኙት የ“ማበረታቻ ገንዘብ” ከወንድ ለጋሾች ይበልጣል። ማዕከሉ ለለጋሽ ሴቶች የሚሰጠው ገንዘብም 30 ሺህ እንደሆነ ዶ/ር ሳምሶን ገልጸዋል።

እስካሁን ድረስ ግን እንቁላልም ይሁን የዘር ፍሬ የሚለግሱ ፈቃደኞችን ማግኘት አለመቻሉን የማዕከሉ ባለቤት ተናግረዋል። ለዚህም የግንዛቤ እጥረት መሆኑን በመጥቀስ “…በሌላ ዓለም እንደሚሠራ፣ ለተቸገረ ሰው መርዳት እንደሆነ ለማስረዳት ጥረት ላይ ነን። ትንሽ ጊዜ የሚፈጅ ይመስለኛል” ብለዋል።

ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው።
***

በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja

20/03/2024

Today is the day of Happiness

18/03/2024
15/03/2024
14/03/2024
💎ከታላላቅ ሰዎች አንደበት ባዶ በርሜል ባዶ በርሜል ስታንከባልለው ይጮሀል። በዛው ልክ በውሀ የተሞላን በርሜል ስታንከባልለው ድምፅ የለውም። ሲንከባለልም በእርጋታ ነው። የሰው ልጅም እንደዛ ...
14/03/2024

💎ከታላላቅ ሰዎች አንደበት

ባዶ በርሜል

ባዶ በርሜል ስታንከባልለው ይጮሀል። በዛው ልክ በውሀ የተሞላን በርሜል ስታንከባልለው ድምፅ የለውም። ሲንከባለልም በእርጋታ ነው። የሰው ልጅም እንደዛ ነው። ጭንቅላቱ ባዶ የሆነ ሰው ከመጮህ እና ከመቸኮል የዘለለ ማድረግ የሚችለው ነገር የለም። በእውቀት የተሞላ ሰው ግን ዝምተኛ እና የተረጋጋ ነው። በጮህን እና በቸኮልን ልክ ጭንቅላታችን ይገመታል።

🗣ከዶ/ር ምህረት ደበበ

join and follow our page

Address

Hawassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Today is my Day posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share