29/11/2025
የህገ-መንግስት ጥሰት!
ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ደ/ር)
የህገ መንግስት ጥሰት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ተፈፀመ!
እንደሚታወቀው የብልጽግና መንግስት በዚህች ሀገር ላይ ለውጡን መምራት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች ለዐይን የሚታዩና የሚዳሰሱ አስገራሚ ለውጦችን አስመዝግቧል። አብዛኛው ሥራዎቹም ሰው ተኮር እንደነበርም የሚዘነጋ አይደለም።
በተለይም ባለፉት(ከለውጡ መንግስት) በፊት በነበሩ ጊዜያቶች በሕዝባችን ጫንቃ ላይ የተጫነውን የሰላም ፣ የፍትህ ፣ የዴሞክራሲ ፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ትልቅ ለውጥ አስመዝግቧል።
ይሁን እንጂ በዚህ ሁሉ ሂደት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች የህግ የበላይነት እየጣሰ መብቶች እየተገፈፉ ዜጎች ለከፍተኛ እንግልትና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ተዳርገዋል።
በክልሉ ውስጥ ከሚገኙ ዞኖች መካከል አንዱ የሀዲያ ዞን ሲሆን የዞኑ ዋና ከተማ የሆነችው ሆሳዕና የክልሉ መንግስትም ዋና መቀመጫ ናት። በዚህ ዞን ውስጥ በተደጋጋሚ የሰው ልጅ ያለ ጥፋቱ በግለሰብ ፈቃድ የሚታሰሩበትና በግለሰብ ፈቃድ የሚፈቱበት የግለሰብ ክልል ከሆነ ሰንብቷል።
በቅርቡም ከሁለት ወር ወዲህ ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም በሚል የዳቦ ስም ምንም ያላጠፉ ልጆችን አፍሶ በማሰር አካባቢውንና ሕዝብን ለማንገላታት ሆን ተብሎ እየተሰራ ይገኛል።
ይባስ ብሎ ሰሞኑን የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ለሎምባሜ ሀቢብ ለተባለች ግለሰብ የፈቀደውን የዋትና መብት ትዕዛዝ በመተላለፍ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የአቶ እንዳሻው ጣሰውን ቀጭን ትዕዛዝ በመቀበል ህገ መንግስት በግልጽ እንዲናድ በማድረግ ህዝቡን ፣ ፍ/ቤቱን እንዲሁም ወጣቱን አስቆጥቷል። የግለሰቧንም አካላዊ ነጻነት አፍኖ አቆይቷል።
ፍትሕ ለሎምባሜ ሀቢብ