20/05/2025
ዉድ ኢትዮጵያውያን እነዛ ለኢትዮጵያና ስለምን ወይም አንድነትና የሚፈልጉ የራሳቸውን ከራስ ለማለት የምሮጠው አድን ተመልከት በUSA America Virginia ተሰበሰቡ የመጡት መግለጫ ነው ስለዝህ እነዚህን ስዎች ምን ትላለች
ኮሚቴ ሰጡት 👇👇
ትኩስ መረጃ
ከወደ አሜሪካ የተገኘ መረጀ በዛሬዉ እለት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት ስመላለስ ዉሏል። የዚህ መረጃ ይዘትመ በ Virginia በነ ታማኝ በየነ ነዓምን ዘለቀ እና ኤፍሬም ማዴቦ አስተባባሪነት ስለተካሄደ ስብሰባ እና ለፋኖ ሀይሎች የተላለፈ ጥሪን ይመለከታል።
ሙሉ መረጃዉ እንደወረደ
====
"ለአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል
ከታማኝ በየነ፣ ነዓምን ዘለቀ እና ኤፍሬም ማዴቦ እና ሌሎች የትግሉ አጋሮች
ከ Virginia , USA
የአማራ ትግል ወደ ማይቀለበስበት ምዕራፍ መድረሱ አጠራጣሪ አይደለም። ቀደም ሲል ተከፋፍሎ በአዉራጃ ሲደራጅ የነበረዉን የፋኖ ሀይል ወደ አንድ ማዕከል ለማምጣት ከፍተኛ ትግል እና ኪሳራ ጭምር አምጥቶ ተሳክቷል። ከዚህ ወዲያ ወደ ኋላ እንዳይመለስ መደረግ የሚገባቸዉን ነገሮች ማወቅ ይበጃል። ይህን በቅጡ በመረዳት ሁሉም የድርሻዉን መወጣት አለበት ብለን እናምናለን በመሆኑም ለቀጣይ የትግል አቅጣጫ ይሆን ዘንድ ይህን አጭር የሁኔታ ዳሰሳ እና Systematic እርምጃ አቅርበናል።
የመጀመሪያ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ከማንጋር መስራት እንዳለበት በተጠና መልኩ መታወቅ አለበት። በተለይ እንደ አጋር የምናያቸዉ ቡድኖች #ከነድክመታቸዉ መሆኑ መረሳት የለበትም።
❗ከወያኔ ሰዎች ጋር ያለን ትብብር እስከ ምን ድረስ እንደሆነ ግልፅነዉ ለታሪካዊ ርስቶቻችን መቋጫ የምንሰጠዉ አንዱ መንገድ እራሷን ወያኔን በመጠቀም መሆን አለበት።
እንዴት እና በምን ሁኔታ የሚለዉን እራሱን የቻለ የትግል ስልት በቀጣይ ሰፋ ባለ መለኩ እናደርሳችዋለን
❗ከኤርትራ ጋር ያለዉ ወዳጅነት ከሌሎች በአንፃሩ ጥሩ የሚባል ነገር ግን አመኔታ የሚጣልበት አይደለም። ሀገሪቱ ካለባት ዘርፈ ብዙ ችግሮች አንፃር አብይ አህመድ በቀላሉ ነገሮችን ሊቀይርባቸዉ ሚችልበት ሚዛን ያመዝናል። እንዲሁም ወያኔ ከ ኢሳያስ ጋር እየፈጠረች ያለችሁ ቅርርብ በበጎ የምናየዉ መሆን የለበትም።
❗ ከኦሮሞ ተቃዋሚዎች ጋር በተለይ ከ #ጀዋር መሃመድ ጋር ያለን ግንኙነት ከዚህ በታች እንዳለዉ ተዳሷል። በቅርቡ የጀመረዉ የህክምና ባለሙያዎች እንቅስቃሴ መደገፍ ግድ ይለናል ቢሆንም ይጠቅመናል። ጃዋር መሃመድ ያለዉ ተሰሚነት እና ተቀባይነት እንደ ቀድሞዉ ባይሆነም አሁንም የእሱን ኮቴ የሚከተሉ ጥቂት አይደሉም ይህን እንደ ጥሩ እድል መጠቀም የትግላችንን አስተላለፍ ለማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋዕፆ ይኖረዋል የሚል እምነት አለን።ስለዚህ በሚያደርጋቸዉ እንቅስቃሴዎች ሁሉ ድጋፍ በማድረግ ተፅዕኖ መፍጠር ወደሚችልበት ሁኔታ መመለስ ትርፉ ብዙ ይሆናል
ይህን ለማድረግ ፦
1 ጀዋር መሃመድ በብልፅግና ስርዓት ላይ የጀመረውን የሃኪሞችን ተቃውሞ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግና መርዳት፣
2. በቀጣይ ደግሞ እኛም ዲያስፖራውን አነሳስተን ይህ ተቃውሞ ወደ ሌሎች የሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች እንዲዛመትና አገራዊ ለውጥን ሊያስከትል በሚችል መልኩ እንዲቀጣጠል ማድረግ
3. ጀዋር አሁን ባለው ደረጃ በአማራ ምሁራን ዘንድ ብዙ ቅቡልነት ባያገኝም በተወሰነ ደረጃ የሚደግፉት ስላሉ እያቀነቀነ ያለው ሃሳብ በሚገባ ከእሱ ጋር ውይይት ማድረግና መደገፍ
4. ጀዋር በኦሮሞ ማህበረሰብ ዘንድ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቅቡልነቱ እየቀነሰ የመጣ ቢሆንም ከተወሰኑ መንግስትን ከሚቃወሙ ዲያስፖራ ምሁራኖች ጋር በመነጋገር ግንኙነቱ ተጠናክሮ እንዲሄድ ማድረግ ፣
5. ከወያኔ ጋር የሚኖረውን ግንኙነት ግን ጥንቃቄ ማድረግ፣
6. ጀዋር አሁን ያለው በአውሮፖ ጀርመን አገር ስለሆነ በቅርብ ወደ አሜሪካ መጥቶ ውይይቱን በሚገባ ማካሄድ ይገባል የሚል እምነት አለን
ግንቦት 9 /2017 ዓ ም"