Jemal Wanoro

Jemal Wanoro Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Jemal Wanoro, Digital creator, Central, Hosanna.

13/10/2024

መደመር ማለት ምን ማለት ነው ......❓

መደመር ኢትዮጵያን በሁሉም መስኮች የተገኙ ስኬቶችንም ሆነ ችግሮች ሀገራዊ አውድን መሠረት አድርገን ችግሮቻችንን እንዴት ልንፈታ እንችላለን የሚለውን ጥያቄ መልስ ለማመላከት ያለመ ሀገራዊ ዕሳቤ ነው። ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታንና የሰውን ልጅ ተፈጥሮን ያገናዘበ ለሀገር በቀል ችግር ሀገር በቀል መፍትሄ አስፈላጊ በመሆኑ ያጋጠሙንን ችግሮች ለማረም የተነደፈ ሀገራዊ የመፍተሔ ሃሳብ ነው፡፡ በመሆኑም መደመር የሰው “ልጆችን” ፍላጎትና አቅም በማለት በሁለት ይከፍላቸዋል፡፡ የሰው ልጅ ፍላጎቶች ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ በማለት በሁለት ይከፍላቸዋል፡፡ ቀጥተኛ ፍላጎቶች ራስን ከጥፋት መከላከልና ማቆየት ሲሆኑ ተዘዋዋሪ ፍላጎቶች ደግሞ ስጋዊ፤ መልካም ስም እና ነጻነት ናቸው ብሎ ያምናል፡፡ መደመር የሰው ልጆች አቅም ነጻ ፍቃድ አላቸውም የላቸውምም ብሎ ያምናል፡፡

መደመር የሰው ልጆችን የብቸኝነት ጉድለት የሚለካው በፉክክርና በትብብር መሀል ሚዛን መዛባት እንዲሁም ካለንበት አካባቢ ጋር ግንኙነት መቋረጥ ወደ ቁልቁል እድገትና የህልውና አደጋ ውስጥ ያደርሳል ብሎ ያምናል፡፡ ይህን የብቸኝነት ጉድለት ለመሙላት መፍትሄው መደመር ነው፡፡ መደመር የምልዑነት ጉዞ ነው፣ መንገዱም ሁሉንም ተደማሪዎች አቅምና ፍላጎት በመሰብሰብ በማከማቸት እና በማካበት ሁለንተናዊ ብልጽግና ማምጣት ነው፡፡ የመደመር እሳቤ ዋነኛ አላማው በሀገራችን የተሰሩ መልካም የፓለቲካና የኢኮኖሚ ድሎችን ጠብቆ ማቆየት የተሰሩ ስህተቶችን ማረም እና የመጪውን ትውልድ ጥቅምና ፍላጎት በማሳካት ሀገራዊ ብልጽግና ማረጋገጥ ነው፡፡ መደመር ምልዑ መሆን የሚችለው የመደመር አምዶች የምንላቸው ነገሮችን በሙሉ እይታ በመረዳት፤ ለአንድ አላማ በጋራ መቆም፤ የጋራ ሀገር መገንባትና ተባብሮ ለመኖር የሚመች ስርአት መዘርጋት ናቸው፡፡

የመደመር መሰረታዊያን የተደማሪዎች ተነሳሽነት፤ ነገሮችን ሚዛን መጠበቅና የጋራ ግብ ይዞ መስራት ሲሆን የመደመር ግብ የዜጎችን ክብር በማረጋገጥ ሀገራዊ እንድነትን በማስጠበቅ የኢትዮጲያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ማረጋገጥ ነው፡፡ በነገሮች ላይ እኔ ብቻ ነኝ ልክ የሚል አስተሳሰብ፤ የተበጣጠሰ እይታ መኖር፣ በትላንት ወይም በዛሬ ላይ መታከክና የለውጥ ሀሳቦችን አለመቀበል የእንቢተኝነት አስተሳሰብ ሲሆን በሌላ በኩል ሁሉን ነገር ሳያላምጡ የሚውጡ አድርባዮች መኖር እንዱሁም ሙያን መናቅ የመደመር የአስተሳሰብ እንቅፋቶች ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ ሌብነት እና ልግመኝነት ወይም አዲስ እውቀት ለማወቅ ተነሳሽነት አለመኖር የመደመር የተግባር እንቅፋቶች ሲሆኑ የእሳቤውን በተግባር ለመተርጎም በእንቅፋትነት የተለዩ ጉዳዮችን ማረም የሀገርን ሁለንተናዊ ብለፅግናን የማረጋገጥ ጉዞ የሀይል አሰላለፍ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡

12/10/2024

እኛ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ፋይዳ በሌላቸውና ማንም ተነሥቶ የግሉን እና የቡድን ፍላጎቱን ለማሳካት የሚያቀብለን አጀንዳ ላይ ጉልበታችንን ከመጨረስ ወጥተን፣ በዋናው ጎዳናችን ላይ እናተኩር። ክብርንና ፍቅርን ይዘን ድህነትና ችግር አውልቀን እንጣል። ወደ ብልጽግና መልካ እንገሥግሥ።
የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ

08/10/2024

"የህልም ጉልበት ለእመርታዊ እድገት ! "

  !ከእለታት በአንድ ቀን አንድ ዝሆንና አንድ ዉሻ በተመሳሳይ ቀን አረገዙ፡፡ከሶስት ወር በኋላ ዉሻዋ 6 ቡችሎችን ወለደች፡፡ ከስድስት ወር በኋላም በድጋሜ አረገዘች እናም በዘጠነኛዉ ወር ሌ...
03/10/2024

!
ከእለታት በአንድ ቀን አንድ ዝሆንና አንድ ዉሻ በተመሳሳይ ቀን አረገዙ፡፡

ከሶስት ወር በኋላ ዉሻዋ 6 ቡችሎችን ወለደች፡፡ ከስድስት ወር በኋላም በድጋሜ አረገዘች እናም በዘጠነኛዉ ወር ሌሎች ብዙ ቡችሎችን ወለደች ፡፡ ዉሻዋ እንዲህ እንዲህ እያለች ብዙ ቡችሎችን ወለደች፡፡

በ18ኛዉ ወር ግን ግራ የገባት ዉሻ ወደቀድሞ ዝሆን ጓደኛዋ ሂዳ እንዲህ ስትል ጠየቀቻት

"ማርገዝሽን ግን እርግጠኛ ነሽ? "

ካስታወሽ የ ዛሬ 18 ወር እኩል ነበር ያረገዝነዉ። ይሁን እንጂ ባለፋት ወራት እኔ ብዙ ቡችሎችን ወልጄ አሁን ትላልቅ ሆነዋል፡፡

አንቺ ግን እስካሁን ምንም አልወለድሽም። የምር ግን እርጉዝ ነሽ? ምን እየሆነ ነዉ?” ስትል ጠየቀቻት፡፡

ይህን የሰማችዉ ብልህ ዝሆን በእርጋታ እንዲህ ስትል መለሰች።

“ዉድ ጓደኛዬ፥ እንድታዉቂዉ የምፈልገዉ አንድ ነገር አለ፡፡ ያረገዝኩት እኮ ቡችላ ሳይሆን ዝሆን ነዉ፡፡ በሁለት አመት አንድ ዝሆን ብቻ ነዉ እኔ ልወልድ የምችለዉ፡፡ ነገር ግን ልጄን በወለድኩ ጊዜና ልጄ መሬት ሲረግጥ መሬት ራሱ ትናወጣለች ፡፡ ልጄ መንገድ ሲያቋርጥ የሰዉ ልጆች ሁሉ ቆመዉ በአድናቆት ይመለከቱታል፡፡

እኔ ያዘልኩት ፅንስ ትኩረትን የሚስብ ነዉ፡፡ የያዝኩት ትንሽ ነገር ሳይሆን ሀያል የሆነ ዝሆን ነዉ። “ ብላ መለሰች፡፡
--------------------------
👉ከዚህ ምን እንማራለን?

➡️ሌሎች የራሳቸዉን ግብ በፍጥነት ሲመቱ የኔ አይሳካም ብለን ተስፋ አንቁረጥ፣ በሌሎችም አንቅና ምክንያቱም:-

⓵. የኛ ስኬት የሚወሰነዉ በራሳችን ትጋት (ፅንስ) እንጂ በሌሎች ላይ ስላልሆነ

⓶. ጥሩ ነገር ሁሌ ጊዜ ይወስዳል (ትልቅ ነገር ለመስራት ብቻ ሳይሆን ለማሰብም ጊዜ ይወስዳል። ዉጤቱ ግን ታላቅ ነዉ!)

➡️አንድ ሰው ትዳር ሳይመሰርት ከእሱ ጋር አብሮ የተማረ አብሮ አደግ ጓደኛው የሆነ ሰው ግን የብዙ ልጆች አባት ሆኖ ይሆናል።

➡️ ኦባማ በ 55 አመቱ ከፕሬዚዳንትነት ጡረታ ሲወጣ፤ ትራምፕ በ 70 አመቱ ፕሬዝዳንት ሆኗል።

➡️በዚህ ዓለም ውስጥ ያለ ማንኛውም ሰው የራሱ የጊዜ ክልል አለው።

➡️በዙሪያህ ካሉ ሰዎች አንዳንዶቹ ከፊት የቀደሙህ፤ አንዳንዶቹ ደግሞ ከኋላህ የቀሩ ሊመስልህ ይችላል። ነገር ግን ሁሉም የየራሱን ሩጫ፣ በራሱ ጊዜ እየሮጠ ነው።

✔️የቀደሙህ በመሰሉህ ሰዎች አትቅናባቸው!
✔️የቀደምካቸው በመሰለህ ላይ ደግሞ እራስህን አትኮፍስ!
✔️እነሱ በራሳቸው የጊዜ ክልል ውስጥ ናቸው፣ አንተም እንዲሁ በራስህ የጊዜ ክልል ውስጥ ነህ!
ከማንም ወደኋላ አልቀረህም፤ አልቀደምክምም!

↔️ተስፋ ይኑርህ ዘና በል!

✅ተስፋ አስፈላጊ ነው ። ህይወትን በተስፋ መነፅር ብቻ መመልከት ግን በእድሜ መጫወት ነው ።
ተስፋ ከዛሬ እውነትና ከትናንት እምነት ጋር ካልተናበበና ካልተዋዋጠ እድሜን አስይዞ የመጫወት አደገኛ ቁማር ነው ።

✌️ከሕልምም ከፊደልም ገበታ የራቁ ልጆቻችንን ይዘን ተስፋ ልንመግባቸው አንችልም ። ተስፋ ላይ ተለጥፈን የማናልፋቸው እንቅልፍ የሚነሱ ጉዳዮች አሉብን ‼️

🖐ተፈጥሯዊ እና ህጋዊ መርህ ወስጥ ሆነህ ሚዛንህን ጠብቀህ መጓዝ ነዉ።

ካሸነፍናቸዉ ሀገራት ስር ጥገኛ ለመሆን ባህር መግባት፤....ሞራል አልባ፣ ቆሻሻ በሆነ እኩይ ሴራና ድርጊት መሰማራት ከኩሩዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ባህሪይ ጋር አብሮ አይሄድም !!
02/10/2024

ካሸነፍናቸዉ ሀገራት ስር ጥገኛ ለመሆን ባህር መግባት፤....ሞራል አልባ፣ ቆሻሻ በሆነ እኩይ ሴራና ድርጊት መሰማራት ከኩሩዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ባህሪይ ጋር አብሮ አይሄድም !!

በሃሳብም በአካልም ሃገር ትቶ መሰደድ፤ለፖለቲካውም ለኢኮኖሚውም የፈረንጅን ዳረጎት መሻት፤ ካሸነፍናቸው ሃገራት ስር ጥገኛ ለመሆን ባህር መግባት፤ ከኩሩው የኢትዮጲያ ህዝብ ባህሪይ ጋር አይሄድምና ላይመለስ መፋቅ አለበት። መጪው ትውልድ በራሱና በኢትዮጲያ አቅም የሚያምንና ህልሙን በሀገሩ ላይ ያደረገ፤ለሌሎች የተፈቀደ ለእኛ ያልተፈቀደ ምንም ነገር የለምና፤ ኢትዮጲያ እንደ ተራራዎቿ ከፍ ትላለች ብሎ ያመነ መሆን ይኖርበታል። ይኸን ለማድረግ ግን ኩሩነትንና በራስ መተማመንን የሚገነቡ ነገሮችን ሳንዘነጋና ችላ ሳንል መፈጸም ይኖርብናል።

የመደመር_ትዉልድ

 ።በጣም አሪፍ  ሀሳብ  ነዉ!!
24/09/2024



በጣም አሪፍ ሀሳብ ነዉ!!

ብልጽግና ፓርቲ በጽንፎች መሐል ሚዛን ጠብቆ የሚጓዝ ፓርቲ ነው!

ብሔራዊነት ከዋልታ ረገጥነት የወጣ ነው ፤ ብሔራዊነት ፍፁማዊ አንድነት እና ፍፁማዊ ልዩነት አይደለም፡፡ ብሔራዊነት ሀገራዊ አንድነት ሳይከፋፍል፤ ብዝኃ ማንነትንም ሳይደፈጥጥ ሁሉንም በልኩ እውቅና የሚሰጥ አሰባሳቢ እሳቤ ነው፡፡

የብሔራዊነት መንገዱ መደመር ነው፡፡ መዳረሻው ሁለንተናዊ ብልጽግና ነው፡፡ ብሔራዊነት አካታችነት መለያው ነው፡፡ ዋልታ ረገጥነት የብሔራዊነት ተቃራኒ ነው፡፡ ብልጽግና ፓርቲ በጽንፎች መሐል ሚዛን ጠብቆ የሚጓዝ ፓርቲ ነው፡፡ የመሐል ፖለቲካ፤ ፈተናዎች እንደሚበዙበት እሙን ነው፡፡

ከምሥረታው ጀምሮ በፈተናዎች እየጠነከረ የመጣው ፓርቲያችን ዕሳቤውን በብቃት ዳር ማድረስ እንጂ ለፈተናዎች እጅ መስጠት መለያው አይደለም፡፡ የመሐል ፓለቲካውን በማስጠበቅ የኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በመደመር መንገድ ይጓዛል፡፡

በወንድማማችነት/እህትማማችነት/ ገመድ የተራራቁ ጽንፎችን ያቀራርባል፡፡ ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር ለማንነቶች ተገቢውን ዕውቅና ይሰጣል፡፡

የፍጽማዊ አንድነት እና የፍፁማዊ ልዩነት ጽንፎችን በማዳከም ብሔራዊነትን በገዥ ትርክትነት ማጽናት ወቅቱ የሚጠይቀው ቁልፍ የፖለቲካ ሥራችን ይሆናል፡፡

Address

Central
Hosanna

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jemal Wanoro posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share