Hossana Online ሆሳዕና ኦንላይን

Hossana Online ሆሳዕና ኦንላይን

😭የናኒ ወይም የታሪኩ ጳውሎስ ውላጅ አባት የሆኑት አንጋፋው መምህር ጳውሎስ ሎብዱኖ ከዚህ ዓለም ድካም በሞት ተለይተዋል። የትውልድ አባት መልካም ዕረፍት!! 😭😥ለመላው ቤተሰብና ወዳጅ ዘመድ ...
02/07/2025

😭የናኒ ወይም የታሪኩ ጳውሎስ ውላጅ አባት የሆኑት አንጋፋው መምህር ጳውሎስ ሎብዱኖ ከዚህ ዓለም ድካም በሞት ተለይተዋል። የትውልድ አባት መልካም ዕረፍት!! 😭😥
ለመላው ቤተሰብና ወዳጅ ዘመድ በሙሉ መፅናናትን ተመኘን

Rip ጋሼ 😭😭😭

🏆 ሆሳዕና ከተማ ሻንፒዮን ሆነ 🏆የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእግርኳስ ክለቦች ሻንፒዮና ውድድር ሆሳዕና ከተማ ወራቤን 1-0 በማሸነፍ ሻንፒዮን መሆን ችሏል።ሆሳዕና አብዬ ኤርሳሞ ስቴድየም በ...
26/06/2025

🏆 ሆሳዕና ከተማ ሻንፒዮን ሆነ 🏆
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእግርኳስ ክለቦች ሻንፒዮና ውድድር ሆሳዕና ከተማ ወራቤን 1-0 በማሸነፍ ሻንፒዮን መሆን ችሏል።

ሆሳዕና አብዬ ኤርሳሞ ስቴድየም በደስታ ጩህት ተሞልታለች💪
✍️ናኒ

ለሆሳዕና ከተማ የኮሪደር ልማት  ።🔆የሆሳዕና ከተማ የኮሪደር ልማት በህዝብ ተሳትፎና በመንግሥት አስተዋጽኦ እየተሰራ ሲሆን እስከ መስከረም 30 ለማጠናቀቅ እየተሰራ ሲሆን የመጀመሪያ ዙር እስ...
20/06/2025

ለሆሳዕና ከተማ የኮሪደር ልማት ።

🔆የሆሳዕና ከተማ የኮሪደር ልማት በህዝብ ተሳትፎና በመንግሥት አስተዋጽኦ እየተሰራ ሲሆን እስከ መስከረም 30 ለማጠናቀቅ እየተሰራ ሲሆን የመጀመሪያ ዙር እስካሁን ያለው አፈፃፀም 70% መድረሱ ነው የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ዳዊት ጡምደዶ ገልፀዋል።
✍️ናኒ

🤔🤔🤔
05/06/2025

🤔🤔🤔

  ❤Colonel Bezabih Petros Square Area📷📷 Biruk Butisha 👊
29/05/2025



Colonel Bezabih Petros Square Area

📷📷 Biruk Butisha 👊

* 2ቱ ተይዘዋል* 3ቱ የ75 ሺህ ብር ይዘው ጠፍተዋልበሆሳዕና ከተማ ጀሎ ናረሞ አካባቢ* 5 ሰዎች * 4ቱ የመከላከያ ልብስ የለበሱ * 1ዱን የሲቪል የለበስ ከቤተክርስቲያን የሚመለሱ 4ሰዎች...
28/04/2025

* 2ቱ ተይዘዋል
* 3ቱ የ75 ሺህ ብር ይዘው ጠፍተዋል

በሆሳዕና ከተማ ጀሎ ናረሞ አካባቢ

* 5 ሰዎች
* 4ቱ የመከላከያ ልብስ የለበሱ
* 1ዱን የሲቪል የለበስ

ከቤተክርስቲያን የሚመለሱ 4ሰዎችን
2 ሴት እና 2 ወንድ መንገድ ላይ አንበርክከው

ስልካቸውን ተቀብለው ለማምለጥ ቢሞክሩም ሴቶቹ ባሰሙት ጩኸት እና እንዲሁም አንድ ደፋር ጀግና ሞተረኛ ተከታትሎ

* 2 የመከላከያ ልብስ የለበሱት ሲያዙ
* 3ቱ የ75 ሺህ ብር የሚገመት ስልክ ይዘው አምልጠዋል

ለጊዜው ህብረተሰቡ በስሱ
የማይባል ኮርኩም አድርገዋቸዋል::

Via ጉርሻ Page

በሆሳዕና ከተማ በፌዴራል መንገዶች ባለስልጣን የሚገነባውን የ5.2 ኪ.ሜ  የአስፋልት መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነው በመብራት ሀይል ወላይታ መውጫ ያለው የ3.1 ኪሎ ሜትር አስፋልት የማንጠፍ...
12/04/2025

በሆሳዕና ከተማ በፌዴራል መንገዶች ባለስልጣን የሚገነባውን የ5.2 ኪ.ሜ የአስፋልት መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነው በመብራት ሀይል ወላይታ መውጫ ያለው የ3.1 ኪሎ ሜትር አስፋልት የማንጠፍ ሥራ እየተከናወነ ነው።

የሆሳዕና ከተማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን

አሳዛኝ ዜና 😭😭😭ከ ደቡብ አፍሪካ እጅግ ልብ ሰባሪ ከባድ ለማመን የሚቸግር ዜና ከወደ ደቡብ አፍሪካ ተሰማ።  የደቡብ አፍሪካ ሀዲያ አባት 😭 የብዙዎቻችን ኩራት የነበሩ እጅግ የምንወዳቸው አ...
06/04/2025

አሳዛኝ ዜና 😭😭😭

ከ ደቡብ አፍሪካ

እጅግ ልብ ሰባሪ ከባድ ለማመን የሚቸግር ዜና ከወደ ደቡብ አፍሪካ ተሰማ። የደቡብ አፍሪካ ሀዲያ አባት 😭 የብዙዎቻችን ኩራት የነበሩ እጅግ የምንወዳቸው አባታችን ዳኛ ግርማ ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች በተተኮሰ ጥይት ተመተው ህይወታቸው አልፏል 😭😭😭

ነፍስ ይማር!! ለቤተሰቦቻቸው ለመላው የደቡብ አፍሪካ የሀዲያ ማህበረሰብ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መፅናናትን እንመኛለን 😭

25/03/2025

ፍትህ እንዲያገኝ ለዚህ ልጅ ድምፅ እንሁንለት ሰዎች ጋር እንዲደርስ አድርጉ

  ❤Political Capital City of Central Ethiopia Regional State
18/03/2025



Political Capital City of Central Ethiopia Regional State

 #አባትነት 😘💪ብርቱ ሰው❤❤ከመለመን የቻለውን ያህል ለመስራት ስራ እየጠየቀን ነው!
15/03/2025

#አባትነት 😘💪

ብርቱ ሰው❤❤

ከመለመን የቻለውን ያህል ለመስራት ስራ እየጠየቀን ነው!

ከነገ 01/07/2017 ዓ.ም ጀምሮ በሆሳዕና ከተማ ለሚኖሩ ለበጃጆችና ለሞተር  መንገድ ይኖራቸዋል። ይህም ልሆን የቻለው በዋና ዋና መንገዶች ከተማን የሚመጥን የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት...
10/03/2025

ከነገ 01/07/2017 ዓ.ም ጀምሮ በሆሳዕና ከተማ ለሚኖሩ ለበጃጆችና ለሞተር መንገድ ይኖራቸዋል። ይህም ልሆን የቻለው በዋና ዋና መንገዶች ከተማን የሚመጥን የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በመጀመሩ ነው ።
የሆሳዕና ከተማ አስተደደር ትራንስፖርት ጽ/ቤት በከተማው የትራፊክ ፍሰትን ለመቀነስና አገልግሎትን ለማዘመን በተለዋጭ መስመሮች ለማሰማራት እየሠራ መሆኑን ገለፀ ።

ታክሲዎችን፣ ዳማሶችን፣ ባጃጆንና የንግድ ባለሁለት ጎማ ሞተር ሳይክሎችን ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ መሆኑንም ተጠቁሟል ።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ተሾመ ኤርቆጮ እንደገለጹት በከተማው ከ30 በላይ በሆኑ የስምሪት መስመሮች ወደ ትግበራዉ ከመገባቱ በፊት በዝግጅት ምዕራፍ ዙሪያ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ከትራንስፖርትና ከባለንብረት ማህበራት ጋር በቂ ውይይት የተደረገበት እንደሆነ ተናግረዋል ።

የሆሳዕና ከተማ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የፖላቲካ መቀመጫ መሆኑን ተከትሎ የተለያዩ እንግዶችንና ሁነቶችን የሚያስተናግድባት ከተማ ስለሆነች የተሽካሪዎች ፍሰትና ቁጥጥሩ ዘመናዊ መሆን ስለሚገባው ነው ብለዋል።

በከተማው ወቅቱንና የከተማው አቅም የሚመጥን የትራንስፖርት አገልግሎት መኖር እንዳለበት የጠቆሙት አቶ ተሾመ፣ ከዚህ ቀደም ሁሉም አይነት ተሽከርካሪዎች ያለ ክልከላ በሁሉም መንገዶች ሲንቀሳቀሱ እንደነበረ ጠቅሰው ይህም ሁኔታ አሁን ካለንበት አጠቃላይ የከተማው ስፋ ጋር የማይጣጣም መሆኑም ጨምረው አብራርተዋል ።

ስምሪቱም ተግባራዊነቱ ከሰኞ መጋቢት 01/2017 ዓ/ም ጀምሮ ለሁሉም ተሽከርካሪዎች ክፍት የሚሆን ሲሆን በየምድቡ ህጋዊና የተፈቀዱ ማሰማሪያ መስመሮች የተመቻችቷል ብለዋል ።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ተሾመ ኤርቆጮ በተጨማሪ እንደ ገለፁት
ከዚህ ቀደም ፣

=ከነባር መናኻሪያ በኢየሩሳሌም አድርጎ ወደ ሺላንሻ የሚያስኬድ መንገድ፣

=ከነባር መናኻሪያ በማሪያም አደርጎ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሚኬድበት መንገድ፣

=ከነባር መናኻሪያ በ18 አድርጎ ወደ ሮማ ሎጅ ይኬድባቸው የነበሩ መንገዶች (መስመሮች )

ከመጋቢት 01/2017 ጀምሮ በሚኒባስ፣ በዳማስና በታክሲ እንደሚሸፈኑ ገልፀዉ፤ ለነዚህ ዋና ዋና የአስፋልት መንገዶች ከ60 በላይ ተሽከርካሪዎች መዘጋጀታቸዉን አስታውቀዋል ።

እንዲሁም በአዲስ መልክ ለባጃጆች፣ ለኮድ 02 የግል ሞተር ሳይኪሎችና ለአህያ ጋሪ አሽከርካሪዎች የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ክፍት እንደሚሆኑ በመግለጽ፣

ከዋና ዋናዎቹ መንገዶች (3ቱ ትልልቅ መስመሮች ) ለሚወጡ ባጃጆች የተጠኑ አዳዲስ መስመሮች ፦

ለአብነትም ፦ወደ አዲሱ መናኻሪያ የሚሰማሩት ከጎምቦራ ታክሲ ማዞሪያ በብርሃን ባንክ፣ በኦሜጋ መካከለኛ ክልኒክ፣ በስፓርት ሆቴል አቋርጦ በማሪያም፣በአቢዮ ኤርሳሞ መታሰቢያ ስታዲዬም፥ሲሆን ለመመለሻም ያንኑ መስመር ተከትሎ ይሆናል።

# ከገብረፃዲቅ ሉሲድ እና ከሀዲያ መድሃኒት ቤት ሆስፒታል እንደነበረ ይቀጥላል።

#ከጎምቦራ ታክሲ ማዞሪያ ወደ ንግስት እሌኒ መታሰቢያ ሆስፒታል መሄጃ፦

# ከዋንዛ፣ አድነዉ ሙጎሮ ወፍጮ ቤት፣ በእናት ቃለ ሕይወት ቤተክርቲያን ይሆናል።

=በሌላ በኩል ደግሞ ከነባር መናኻሪያ ከሆስፒታል ወደ ቁጥር 1 ት/ቤት፣ ከዋንዛ ጆን ፋርም ፣ ከሺላንሻ ባቴና የጠጠር መንገድ፣ ከሲኖዶስ - ኬላ-ሄጦ ኔትወርክ፣ ከስፖርት ሆቴል በኢየሩሳሌም ንግስት እሌኒ መታሰቢያ ሆስፒታል፣ ከአዲላ ሆቴል በTTC ቦቢቾ፣ ከሲኖዶስ ኬላ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ፣ ከኢየሩሳሌም አደባባይ ዋቸሞ 2ኛ ደረጀ ት/ቤት መሆኑን የሆሳዕና ከተማ ትራንስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተሾመ በመግለጫቸዉ የገለጾዋል

Address

Hossaena
Hossana

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hossana Online ሆሳዕና ኦንላይን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category