Hadiya zone Government Communication

Hadiya zone Government Communication የሀድያ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ተደራሽ የሆነ የመንግሥት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት በመገንባት መንግስትና ሕዝብን ማገናኘት

This is the offical facebook home page of Hadiya Zone Communication

‹ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ተደራሽ የሆነ የመንግሥት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ሥርዓት በመገንባት መንግሥትንና ሕዝብን ተጠቃሚ በማድረግ አንድ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ማኀበረሰብን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረግ ነው።

ሴቶች በልማት ሕብረት ተደራጅተው ሁለተናዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው ሊሠሩ ይገባል ሆሳዕና፣ ሐምሌ 27/2018  (ሀድያ ዞን ኮሙኒኬሽ...
03/08/2026

ሴቶች በልማት ሕብረት ተደራጅተው ሁለተናዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው ሊሠሩ ይገባል
ሆሳዕና፣ ሐምሌ 27/2018 (ሀድያ ዞን ኮሙኒኬሽን)

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ሕፃናት ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት የሴቶች ልማት ሕብረት ስቲሪንግ ኮሚቴ፣ ፆታዊ ጥቃትና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች አስወጋጅ ግብረ-ኃይል የ2018 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ፣ እንዲሁም የንቅናቄ ተግባራት ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

"የሴቶች አቅምና ንቁ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የ2018 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

በውይይት መድረኩ ላይ የአመራር አካላት፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የስቲሪንግ ኮሚቴ አባላት፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች አስወጋጅ ግብረ-ኃይል አባላት፣ የሴቶችና የወጣት አደረጃጀቶች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ እና ረዳት የመንግሥት ተጠሪ ወ/ሮ በረከት ታደሰ ባደረጉት ንግግር፤ መድረኩ አረንጓዴ አሻራን ለማሳካት እንደ ሀገር ከ800 ሚሊዮን በላይ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ በተካሄደበት በዛሬው ዕለት መካሄዱ ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል። አያይዘውም ሴቶች በልማት ሕብረት ተደራጅተው ሁለተናዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ሕፃናት ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ስንታየሁ ምህርቱ በበኩላቸው፤ በከተማው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከባለድርሻ አካላት በመቀናጀት የሴቶችን ሁለተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት የተገኘውን አበረታች ውጤት ለማስቀጠል ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ ተናግረዋል።

የሀዲያ ዞን ሴቶችና ሕፃናት ጉዳዮች መምሪያ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ሊረሴ ለማ በበኩላቸው፤ ባለድርሻ አካላት በከተማው የሴቶችን ሁለተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚከናወኑ ተግባራት የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆን እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።

#የሆሳዕና ከተማ ኮሙኒኬሽን

በሴቶች ክንፍ አስተባባሪነትና በደመቀ አደረጃጀት የተከናወነው የሀዲያ ዞን የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላሆሳዕና፣ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም (ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን)"ተስፋን እን...
03/08/2026

በሴቶች ክንፍ አስተባባሪነትና በደመቀ አደረጃጀት የተከናወነው የሀዲያ ዞን የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ
ሆሳዕና፣ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም (ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን)

"ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ በሀዲያ ዞን ጊቤ ወረዳ ሙማ ቀበሌ በተካሄደው ዞናዊና ወረዳዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የሴቶች ክንፍ አስተባባሪነትና የሴቶች አደረጃጀቶች ላቀና ደማቅ ተሳትፎ አሳይተዋል።

የርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) መልዕክት ፣"የተከበራችሁ መላዉ የማዕከላዊ  ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች፣ሀገራችን ኢትዮጵያ፣ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ያቀረበች...
03/08/2026

የርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) መልዕክት ፣

"የተከበራችሁ መላዉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሕዝቦች፣

ሀገራችን ኢትዮጵያ፣ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ያቀረበችዉን ጥሪ ተቀብላችሁ፣በክልላችን በአንድ ጀምበር ለማሳካት ያቀድነዉ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ከዕቅዱ በላይ እንዲፈፀም ላበረከታችሁት ታላቅ ገድል ኢትዮጵያ ታመሰግናችኋለች፤ በጥረታችሁ ባስመዘገባችሁት ሰኬት እንኳን ደስ አላችሁ!

በቀጣይ የተተከሉ ችግኞችን ተንከባክቦ በማፅደቁ ሂደት እና በሌሎችም የሠላም፣ የልማት እና የመልካም አስተዳደር መስኮች ተሳትፏችሁ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በራሴ እና በክልሉ መንግስት ስም እጠይቃለሁ!"

ቃሏን አክባሪዋ ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር ከ805 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል አዲስ ደማቅ ክብረወሰን አስመዘገበችበአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ታላቅ ሀገራዊ ...
03/08/2026

ቃሏን አክባሪዋ ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር ከ805 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል አዲስ ደማቅ ክብረወሰን አስመዘገበች

በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ታላቅ ሀገራዊ ዕቅድ በታላቅ ድምቀትና በስኬት ተጠናቋል።

ይህ ታሪካዊ ድል የዛሬው ዕለት ስኬት ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ ለተከታታይ ስምንት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ያቀደችውን ግብ ያለምንም መጓደል በተግባር እያሳካች መሆኗን በድጋሚ ያረጋገጠ ነው።

መላው ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ አንድነትና ሀገራዊ ተሳትፎ ዘንድሮም ያቀዱትን ከዳር በማድረስ አዲስ ደማቅ ክብረወሰን በዓለም አደባባይ ማስመዝገብ ችለዋል።

በሀዲያ ዞን ጊቤ ወረዳ ሙማ ቀበሌ የተከናወነው ዞናዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር - በፎቶግራፍሆሳዕና፣ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም (ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን)በሀዲያ...
03/08/2026

በሀዲያ ዞን ጊቤ ወረዳ ሙማ ቀበሌ የተከናወነው ዞናዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር - በፎቶግራፍ
ሆሳዕና፣ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም (ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን)

በሀዲያ ዞን ጊቤ ወረዳ ሙማ ቀበሌ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል በግንባር ቀደምት የሥራ ኃላፊዎች እና በሰፊው ማኅበረሰብ ተሳትፎ የተካሄደው ዞናዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በፎቶግራፍ የተደገፈ ከፊል ማሳያ።

03/08/2026
እንኳን ደስ አለን! - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ቃሏን አክባሪዋ ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ደማቅ ክብረ ወሰን አስመዘገበች።ኢትዮጵያ ዛ...
03/08/2026

እንኳን ደስ አለን! - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ቃሏን አክባሪዋ ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ደማቅ ክብረ ወሰን አስመዘገበች።

ኢትዮጵያ ዛሬ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅዳ 805.3 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ታላቁን ሀገራዊ ዕቅድ በላቀ ስኬትና በታላቅ ድምቀት ማሳካቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ አደረጉ።

ይህ ታሪካዊ ድል የዛሬው ዕለት ስኬት ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ ለተከታታይ ስምንት ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ያቀደችውን ግብ ያለምንም መጓደል በተግባር እያሳካች መሆኗን በድጋሚ ያረጋገጠ ነው።

03/08/2026

በሀዲያ ዞን ጊቤ ወረዳ ሙማ ቀበሌ የተከናወነው ዞናዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር - እንቅስቃሴ

።።ሆሳዕና፣ ሐምሌ 27/2018 (ሀዲያ ዞን ኮሙኒኬሽን)።።

በሀዲያ ዞን ጊቤ ወረዳ ሙማ ቀበሌ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል በግንባር ቀደምት የሥራ ኃላፊዎች እና በሰፊው ማኅበረሰብ ተሳትፎ የተካሄደው ዞናዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከፊል ማሳያ።

በዘንድሮ ዓመት እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ***************************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ...
03/08/2026

በዘንድሮ ዓመት እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
***************************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት በመላው ኢትዮጵያ የተካሄደውን የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በስኬት መጠናቀቅ አስመልክተው የማጠቃለያ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም ኢትዮጵያ በተያዘላት ዕቅድ መሠረት በአንድ ቀን ብቻ 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ወደር የማይገኝለት ታሪካዊ ስኬት ማስመዝገቧን አረጋግጠዋል።

ከ26 ሚሊዮን በላይ የሚሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ ምንም ዓይነት ክፍያ ሳይጠይቅ፣ አብዛኛው በዝናብ ውስጥ ሙሉ ቀን ችግኝ እየተከለ መዋሉ በዋዛ ፈዛዛ ሊተገበር የሚችል ቀላል ተግባር አለመሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአጽንኦት ተናግረዋል።

ይህን ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በከፍተኛ ጽናትና ቁርጠኝነት የተወጣውን መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከልብ ያመሰገኑት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ በዚሁ ልክ ተደምረን እና በአንድነት ቆመን ለነገው ትውልድ ተስፋን መትከላችን ከፍተኛ ሞራልና መነሳሳት የፈጠረ መሆኑን አስረድተዋል።

በዘንድሮ ዓመት እስካሁን 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መተከላቸውን ገልጸው፣ ቀሪው 1.5 ቢሊዮን ችግኞች በቀሪ ወራት የሚፈጸም ይሆናል ብለዋል።
EBC

03/08/2026

Address

Centeral Ethiopia Region
Hossana

Telephone

+251465551908

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiya zone Government Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share