Melaku Abraham

Melaku Abraham bio ለጊዜ ባዶ ይሁን

እንዲታሰር ስትማፀኑ የነበራችሁ ይሄው ታሰረ ምን ይሆን ትርፋችሁ!!!ወንድሜ ብሩክ ካሜራ ፊት ሲቀርብ እንደሚያወራው አይደለም። ካሜራ ፊት ሲናገር ድምፁን ከፍ አድርጎ በስሜት ሲናገር በትክክለ...
18/09/2025

እንዲታሰር ስትማፀኑ የነበራችሁ
ይሄው ታሰረ ምን ይሆን ትርፋችሁ!!!

ወንድሜ ብሩክ ካሜራ ፊት ሲቀርብ እንደሚያወራው አይደለም። ካሜራ ፊት ሲናገር ድምፁን ከፍ አድርጎ በስሜት ሲናገር በትክክለኛ ሕይወቱም የተረጋጋ አይመስለንም። እኔም እንደዛ ነው የሚመስለኝ የነበረው። ነገር ግን አንዴ ሐረር ለስራ አብረን ሄደን ያየሁት ግን ከማስበው የተለየ ነው። የተረጋጋ አብዝቶ የሚጸልይ ልታይ ልታይ የማይል ሰው ነው። ምናልባትም ይህ ወንድም እንዲታሰር ግፊት ያደረጋችሁት የልጅቷን እናት ሄዶ በመቅረፁ ሳይሆን ልክ ቀድሞ እኔ እንደምረዳው አይነት ሰው ስለመሰላችሁ በምክንያት እርካታን ለማግኘት ይሆናል።

ለማንኛውም ወንድማችን ሌሎች ወንድሞች ታስረው እንደተፈቱት እርሱም ይፈታል። በእራሳችሁ ልጅ ውድቀት እርካታ የሚሰማችሁ ግን ህሊና ይውቀሳችሁ።
#አሉ

17/09/2025
ከጉሊት ለህዳሴ ግድብ ቦንድ የገዙ ብዙ እናቶች አሉ። በወቅቱ ኢቲቪ እያቀረበ አናግሯቸዋል። ከአርካይቩ ፈልጎ በግድቡ ምርቃ ቀን ልዩ እንግዳ ሆነው እንዲጋበዙ አሳስባለሁ‼
09/09/2025

ከጉሊት ለህዳሴ ግድብ ቦንድ የገዙ ብዙ እናቶች አሉ። በወቅቱ ኢቲቪ እያቀረበ አናግሯቸዋል። ከአርካይቩ ፈልጎ በግድቡ ምርቃ ቀን ልዩ እንግዳ ሆነው እንዲጋበዙ አሳስባለሁ‼

07/09/2025

🌘🌙🌙🌙🌙
እኛጋ በደመና ተጋርዳለች!
ምን ይታያችኋል??

ፓስፖርት ለመወጣት ፈልገዋል?አሊያም በፓስፖርት ዙሪያ መረጃ ወይም እገዛ ፈልገዋል? ያማክሩን! በታማኝነት በፍጥነት እና በቅናሽ እንሰራለን።ያስታውሱ፦ እኛ አገልግሎት የምንሰጠው በኦንላይን ነ...
01/09/2025

ፓስፖርት ለመወጣት ፈልገዋል?
አሊያም በፓስፖርት ዙሪያ መረጃ ወይም እገዛ ፈልገዋል? ያማክሩን! በታማኝነት በፍጥነት እና በቅናሽ እንሰራለን።
ያስታውሱ፦ እኛ አገልግሎት የምንሰጠው በኦንላይን ነው።
ሲዶና ዲጂታሎች ነን!!

30/08/2025

ቴክኖሎጂን ለመልካም ነገር እንጠቀም።

30/08/2025

በሕይወታችሁ ውስጥ 'በእውነት እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ነበር' ብላችሁ በልባችሁ የመሰከራችሁበትን አንድ አጋጣሚ እስኪ ንገሩን?

27/08/2025

አሜን! ይነበብ 👇👇👇

?
እሄው ወራት ተቆጠረ
​በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
​ልጄ ሆይ፣ "አሜን" ብለህ በመቀበልህ ልቤ ደስ አለው። እግዚአብሔር እንዲህ በየዕለቱ ልባችንን ሲያይ ይመረምራል። አሁን የጠየቅከው ጥያቄ የብዙዎች ጥያቄ ነው፤ የነፍስን መታመም አንዱ ምልክት ነው። ስለዚህ ይህንን ጥያቄ ለመጠየቅ ድፍረት በማግኘትህ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። ብቻህን አይደለህም።
​እስኪ አንድ ምሳሌ ልንገርህ። አንድ ሰው በጠና ቢታመም፣ የምግብ ፍላጎቱ ይጠፋል። የሚወደውን ምግብ እንኳን ሲያይ ያስታውከዋል። ችግሩ የምግቡ መጥፎ መሆን ሳይሆን፣ የሰውየው አካል መታመሙ ነው። ልክ እንደዚሁ፣ ነፍስ በኃጢአት፣ በጭንቀት ወይም በዝለት ስትደክም፣ መንፈሳዊ ምግቧ የሆነውን ቤተ ክርስቲያንን መመገብ ትጠላለች። የጸሎት ፍላጎቷ ይጠፋል፣ ቃለ እግዚአብሔር መስማት ይከብዳታል። ስለዚህ ችግሩ ያለው ከእናት ቤተ ክርስቲያን ሳይሆን ከደከመችው ነፍስህ ነው።
​ለምን ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ እንጠላለን? ጥቂት ምክንያቶችን እንይ፦
​የድካመ መንፈስ (Spiritual Sloth/Acedia)፦ ሰይጣን በልባችን ውስጥ "ምን ይጠበስ?"፣ "ምንም አዲስ ነገር የለም"፣ "ዛሬ ብቀር ምን ይሆናል?"፣ "ደክሞኛል ልተኛበት" የሚሉ ሀሳቦችን እየዘራ መንፈሳዊ ዝለትንና መሰልቸትን ይፈጥርብናል። ይህ የነፍስ ስንፍና ነው።
​ስውር ኃጢአትና ያልተናዘዙት በደል፦ በልባችን የደበቅነው ኃጢአት ሲኖር፣ ሕሊናችን ይወቅሰናል። ወደ እግዚአብሔር ቤት ለመቅረብ ያሳፍረናል፣ "እኔ ምን ያህል ርኩስ ሆኜ ነው ይህንን የተቀደሰ ቦታ የምረግጠው?" የሚል የሐሰት ትህትናና የተስፋ መቁረጥ ስሜት በውስጣችን ይፈጥራል። ኃጢአት ከእግዚአብሔር መገኘት ያርቃል።
​በሰዎች ላይ ማተኮር፦ ወደ ቤተ ክርስቲያን ስንሄድ ዓይናችን ከእግዚአብሔር ይልቅ በሰዎች ላይ ሲሆን ችግር ይፈጠራል። "እገሌ እንዲህ አደረገ"፣ "የሰባኪው ስብከት አልተመቸኝም"፣ "ዘማሪው ተሳሳተ"፣ "ቀሲሱ ፊታቸውን አላሳዩኝም" እያልን በሰዎች ድካም ላይ ስናተኩር፣ ልባችን ይታወካል፣ ለመሄድም እንሰንፋለን።
​የዓለም አሳብ መብዛት፦ ልክ በእሾህ መካከል እንደተዘራ ዘር፣ የዓለም ሀሳብ፣ የሥራ ጭንቀት፣ የገንዘብ ፍቅርና የደስታ ፍለጋ ልባችንን ሲይዘው፣ ለመንፈሳዊ ነገር ቦታ እናጣለን። (ማቴ. 13፡22)
​መፍትሔው ምንድን ነው?
​ልጄ ሆይ፣ በሽታው ታወቀ ማለት የመዳኛው መንገድ ተጀመረ ማለት ነው። አሁንም ተስፋ አትቁረጥ።
​እግርህን አስገድደው፦ ስሜትህ እስኪመጣ አትጠብቅ። ስሜት የተግባር ውጤት ነው እንጂ የተግባር መሪ አይደለም። "ልቤ ባይፈልግም፣ ነፍሴ ብትሰንፍም፣ እግሬ ግን ወደ እግዚአብሔር ቤት ይሄዳል" ብለህ ወስን። ልክ የምትጠላውን መድኃኒት ለመዳን ስትል እንደምትውጠው፣ እንዲሁ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሂድ። አንዴ ከገባህ በኋላ እግዚአብሔር ልብህን መለወጥ ይጀምራል።
​እንደ በሽተኛ እንጂ እንደ ዳኛ አትግባ፦ ወደ ቤተ ክርስቲያን ስትገባ፣ የሰዎችን ሥራ ለመገምገም ሳይሆን፣ "አምላኬ ሆይ፣ እኔ የታመምኩት በሽተኛ ነኝና ፈውሰኝ" ብለህ ገብተህ ከኋላ ተቀመጥ። የነፍስህ ሐኪም ክርስቶስን ብቻ እያሰብክ ጸልይ።
​የንስሐ አባትህን አግኝ፦ ይሄንን ስሜትህን ለንስሐ አባትህ ንገራቸው። "አባቴ፣ ወደ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ጠልቻለሁ፣ ወራት አለፉኝ" በላቸው። እነርሱ ሚስጢሩን ገብቷቸው ትክክለኛውን የንስሐ መድኃኒት ይሰጡሃል። ምናልባት በጸሎትህ ውስጥ የረሳኸው፣ ነገር ግን ነፍስህን ያቆሰላት ኃጢአት ይኖራል። ንስሐ የነፍስን ሸክም ያራግፋል።
​በትንሽ ጀምር፦ ሙሉውን ቅዳሴ መቆም ከከበደህ፣ ለ30 ደቂቃ ብቻ ለመቆም ወስነህ ግባ። ወይም ደግሞ ማንም በሌለበት ሰዓት ገብተህ ሻማ አብርተህ፣ ለብቻህ አስር ደቂቃ ጸልየህ ውጣ። ዋናው ቁምነገር ከእናትህ ቤት ጋር ያለህን ግንኙነት እንደገና ማደስህ ነው።
​ልጄ ሆይ፣ እናት ልጇ ቢታመምባትና ከእቅፏ ቢርቅባት ምን ያህል እንደምታዝን አስብ። እናት ቤተ ክርስቲያንም አንተ ስትቀርባት ታዝናለች፤ እጆቿን ዘርግታ ትጠብቅሃለች። ሰይጣን ከእናትህ ሊነጥልህ ይፈልጋልና ፍላጎቱን አትፈጽምለት። በርታና ነገ ወይም ከነገ ወዲያ የመጀመሪያውን እርምጃ ውሰድ።
​የልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ" (መዝ. 122፡1) ያለው ደስታ ለአንተም እንዲሆንልህ እጸልያለሁ።
​ወስብሐት ለእግዚአብሔር።

26/08/2025

የግዕዝ አጀንዳ ተጀምሯል😂😂

ሙስሊም ባንዳዎች እረፉ

አረብኛ መናገር መብታችሁ ነው ግዕዝ ማንቋሸሽና በኦርቶዶክስ ላይ ጣት መቀሰር ግን....💀💀💀

24/08/2025

የክህደትን ክብደት ለማወቅ
ውሃ ያሳደገው አሳ
ተቀቅሎ የተበላው በውሃ እንደሆነ
መረዳት በቂ ነው dawit mitiku

Address

Hossana
0000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Melaku Abraham posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share