AGEW TV Fans

AGEW TV Fans Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from AGEW TV Fans, TV Channel, injibara, Injibara.

የዜና እና የወቅታዊ መረጃ ገጽ ነው።
አዳዲስ መረጃ ለማግኘት Like Page የሚለውን
በመጫን Follow ያድርጉ!
መረጃ ሲኖራችሁ፣ የሚዲያ ሽፋን ስትፈልጉ በውስጥ መስመር inbox ያድርጉልን ወይም በቴሌግራም
ገጻችን በኩል ላኩልን።
👉Voice of Voiceless ✅

🌐 https://linktr.ee/agewtv

06/06/2026

ምስጋናና ዕውቅና መግለጫ‼

ሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት በ7ኛው አጠቃላይ ሀገራዊ ምርጫ በተበደሉ፣ በተጨቆኑ፣ ከልማት ተገልለው በቀሩ፣ ሰላምን ለሚሹ፣ ፍትህና እኩልነትን ለሚናፍቁ፣ እንዲሁም ማንነታቸውና ሉዓላዊነታቸው በተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ ለሚገኝ ህዝባችን ድምፅ የሚሆኑ ብቁ፣ ስነ-ምግባራቸው የተመሰገነ፣ በዕውቀት የበለጸጉ፣ በህዝባዊ ፍቅር የተነሱ እና ለህዝባቸው መብት ለመታገል ቁርጠኛ የሆኑ ዕጩዎችን ማቅረቡ የማይካድ እውነታ ነው።

እነዚህ እውነተኛ የህዝብ ልጆች በተወዳደሩባቸው የምርጫ ክልሎች ሁሉ በግልም፣ በቡድንም፣ በጥምረትም ሳይደክሙና ሳይሰለቹ፣ ፀሐይና ዝናብ፣ አቧራና ጭቃ ሳይገድባቸው በትጋት የምርጫ ቅስቀሳቸውን አካሂደዋል።

በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት በተለያዩ አካባቢዎች የደረሱብን የመንቀሳቀስ ገደቦችና የመብት ጥሰቶች በአንድ ጽሑፍ የሚገለጹ አይደሉም። እነዚህ ክስተቶች ለትውልድ ትምህርት እንዲሆኑ በተገቢው መልኩ ተሰንደው ወደፊት ይቀርባሉ።

በዚህ አጋጣሚ ለተለያዩ አካላት ያለንን ክብርና ምስጋና መግለጽ እንወዳለን።

1. ለመላው ህዝባችን
በምርጫ ቅስቀሳ ጉዞዎቻችን ወቅት ላሳያችሁን ፍቅር፣ ክብር፣ አቀባበልና ለደህንነታችን ላደረጋችሁት ጥበቃ በጥምረታችንና በራሴ ስም ከልብ የመነጨ ምስጋና እናቀርባለን።

2. በሀገር ውስጥና በውጭ የምትኖሩ ማህበረሰብ አንቂዎች
ለህዝባችን ግንዛቤ ለመፍጠር፣ በዕጩዎቻችን ላይ የተፈጸሙ ጫናዎችንና በደሎችን በማጋለጥ እና በመቃወም ላደረጋችሁት ቀንና ሌሊት ያልተቋረጠ ህዝባዊ ተጋድሎ ከፍተኛ ምስጋናችንን እንገልጻለን።

3. ለወጣቱ ትውልድ
ከገጠር እስከ ከተማ ድረስ በጽናት ከጎናችን በመቆም፣ የደረሰባችሁን ጫናና ወከባ በመቋቋም ላሳያችሁት ቆራጥነትና ህዝባዊ ተሳትፎ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባችኋል።

4. ለሞተርና ባጃጅ ሹፌሮች
በተለያዩ ጫናዎች፣ ማስፈራሪያዎችና ዛቻዎች መካከል ሆናችሁ ለጥምረቱ ያበረከታችሁት አገልግሎትና የሞራል ድጋፍ በታላቅ ክብር የሚታሰብ ነው። ለዚህም ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

5. ለአገው ምሁራን
በሃሳብ ማመንጨት፣ በምክር፣ በትግል አቅጣጫ ማሳየት እና ገንቢ አስተያየቶችን በመስጠት ላደረጋችሁት ውድ አስተዋጽኦ ከፍተኛ አድናቆታችንንና ምስጋናችንን እንገልጻለን።

እንዲሁም በዚህ መግለጫ በስም ሊጠቀሱ ያልቻሉ ሁሉም ወገኖች በመጀመሪያው ነጥብ ስር የተገለጸው ከፍተኛ ምስጋና እንደሚመለከታቸው በአክብሮት እናሳውቃለን።

በመጨረሻም፣ ሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት በ2018 ዓ.ም. ሀገራዊ ምርጫ አቅሙ የፈቀደውን ሁሉ በትጋት ለመፈጸም መሞከሩን እየገለጽን፣ እንደሠራናቸው ጠንካራ ሥራዎች ሁሉ ሊሻሻሉ የሚገባቸው ድክመቶችም እንዳሉብን በግልጽነት ለህዝባችን ማስገንዘብ እንፈልጋለን።

ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ በህጋዊ ሂደት እየተንቀሳቀስን በመሆናችን፣ የደረስንበትን ውሳኔ በተገቢው ጊዜ ለህዝባችን በይፋ እንደምናሳውቅ በአክብሮት እንገልጻለን።

ሠላም፣ ፍትህ፣ እኩልነትና ዴሞክራሲ ለህዝባችን!

አዲሱ መኮንን (ዶ/ር)
የሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ምክትል ፕሬዝዳንት
እንጅባራ፣ ኢትዮጵያ
ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም.

02/06/2026

ምርጫ 2018 ወይስ ቅርጫ 2018😁😂
AGEW TV 🔴 AGEW TV Fans

   የአምበላ ቀበሌ 9 ምርጫ ጣቢያዎች በፀጥታ ምክንያት መምረጥ ስለማይቻል ካርዳችሁን መልሱ በሚል በጎበዝ አለቃ ተሰብስበቦ ለማ ቀበሌ ላይ ኮረጆውን መሙላታቸው ተረጋግጧል።AGEW TV Fan...
31/05/2026

የአምበላ ቀበሌ 9 ምርጫ ጣቢያዎች በፀጥታ ምክንያት መምረጥ ስለማይቻል ካርዳችሁን መልሱ በሚል በጎበዝ አለቃ ተሰብስበቦ ለማ ቀበሌ ላይ ኮረጆውን መሙላታቸው ተረጋግጧል።
AGEW TV Fans 🔴 AGEW TV

«አላማ የለሹ ሰላማዊ ሰልፍ» በአዊ ብሔረሰብ ዞን እየተደረገ ያለው የህዝብ እና የመንግስት አለመጣጣም በጣም የከረረ ሁኗል ፤  ሐሳብ በፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ ጫናዎች ከእለት ወደለት እየሰፋ ነ...
26/05/2026

«አላማ የለሹ ሰላማዊ ሰልፍ»

በአዊ ብሔረሰብ ዞን እየተደረገ ያለው የህዝብ እና የመንግስት አለመጣጣም በጣም የከረረ ሁኗል ፤ ሐሳብ በፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ ጫናዎች ከእለት ወደለት እየሰፋ ነው።

አንድን ሰልፍ «ዓላማ የለሽ» ብሎ መፈረጅ፣ ሰልፉ ግልጽ የሆነ የፖለቲካ ጥያቄ፣ መፈክር ወይም ወደ አንድ የተወሰነ የውሳኔ ለውጥ የሚያመራ ስትራቴጂ የሌለው መሆኑን በግልፅ አስመስክሯል።


ብልፅግና ለፍቶ አዳሪውን የድሃ ድሃ ማህበረሰብ አስገድዶ ሰልፍ ማውጣቱ ትልቅ ፖለቲካዊ ኪሳራ እንጂ ትርፍ የለበትም። ከተማ የሚገባውን ነዋሪ እንዳይገባ አግዷል፣አሽከርካሪው ተከልክሏል የመከራ መከራ ሰልፍ በእንጅባራ ከተማ!!

የብልፅግና ስርዓት አልበኝነት መዋቅር ሙሉ በሙሉ ትርጉም ባጣበት ወቅት፣ ሰዎች ያለምንም ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳ ወይም ጥቅማጥቅም፣ ዝም ብለው አደባባይ በመውጣት መገኘታቸው ብቻ ራሱን የቻለ የተቃውሞ መግለጫ ይሆናል። «እኛ እዚህ አለን፣ እየኖርን ነው፣ ነገር ግን ነገሮች ሁሉ ትርጉም አጥተውብናል» የሚል ድምፅ አልባ መልዕክት እያስተላልፉ ይገኛሉ።

የአገው ህዝብ በብልፅግናው መንግስት በርካታ ውጥንቅጦች የታዩበት የዜጎች ህይወት እንደ ቄጤማ የረገፈበት፣ዜጎች ከቅያቸው የተፈናቀሉበት፣የህዝብ ጥያቄዎች መስሚያ ያጡበት፣የኑሮ ውድነት ቅጥምጡን ያጣበት፣ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ያልቻሉበት፣ የስቃይ ስቃይ መከራን ተሸክመው ያሉበት በብልፅግና መሆኑን እንኳን ኢትዮጵያዊያን ዓለም ሁሉ የምያውቅበት ሀቅ ነው።

ከታች በፎቶ የምትመለከቱት እንጅባራ ከተማ ነው፣ሰልፍ እያለ ለምን በሚል ጋሪዎችን ከልክለው የጋሪ አሽከርካሪዎችን ሚኒሻው በቁጥጥር ስር አውለው በቅሎዎችን ለቀው በማባረር አምባገነናዊ ስርዓትን በግልፅ እያሳዩ ይገኛሉ።

ሌላው ከዚህ ከእንጅባራ ዩንቨርሲቲ አጥር ዳር ቁጭ ያሉት እናቶች፣አባቶች ፣አቅመ ደካሞች ከአገው ግምጃቤይ ወደ እንጅባራ ለመግባት ፈልገው በፀጥታ አካላት ተከልክለው የተቀመጡ ናቸው። አንዳንድ ነዋሪዎችን እንዳነጋገርነው መሰረት ማንነው የምትመርጡት ብለን መጠይቅ ስናቀርብላቸው ልባችን ማንን እንደሚመርጥ ያውቃል። የእኛን ስቃይ የምናውቅ እኛ ነን የሚል ምላሽ ሰጠዋል።

ቡና በህዝባችን ልብ ውስጥ መግባቷል!!
ቡና ምርጫችን ነው!!
AGEW TV Fans 🔴 AGEW TV

26/05/2026

ፍርዱን ለአገው ህዝብ፣
።።።።።።።።።።።፡።።።።
መቼም ይህንን ቪድዮ ያላዳመጠ አገው ይኖራል ብለን አናምንም። ለሌሎች አገዎች ያልታየው ለዚህ ሰውዬ ብቻ የታየው ነገር ምን ይሆን? ለአገው ህዝብ አቶ አረጋ ምን ሰራ? ምን አደረገለት? የአገው ፖለቲከኞች ብሎ ከመጥራት ከራሱ ጋር ብቻ ቁጭ ብሎ ያወራውን ከእኔ ጋር ቁጭ ብሎ አወራ ነው ማለት ያለበት።

በእርግጥ አቶ አላምረው ብቻውን እንደግለሰብም እንደ ፓርቲም ከአቶ አረጋ ጋር በአዲስ አበባ እንደተወያየ እናውቃለን። ቃል የተገባለት ካለ ራሱ ያውቃል፣ ለአገው ህዝብ ግን ጠብ ያለ ነገር የለም። ሌላኛው የአገው ፖለቲካ ፓርቲ በእውነቱ አልተነጋገረም። ለምን ብትሉን? ለውጥ እንደሌለው ስለምናምን ነው። ለማንኛውም ህዝባችን አዳምጦ ፍርድ ይስጥ።
AGEW TV 🔴 AGEW TV Fans

በታሪካዊቷ አገው ግምጃቤት ከተማ ዛሬ ግንቦት 12 አዲሱ ትውልድ ከ ሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ጋር ለውጥን እንፈልጋለን በሚል ከወጣት እስከ አዛውንቶች፣ከሴቶች ፣ አካል ጉዳተኞች ፣የሀይማኖት ...
20/05/2026

በታሪካዊቷ አገው ግምጃቤት ከተማ ዛሬ ግንቦት 12 አዲሱ ትውልድ ከ ሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ጋር ለውጥን እንፈልጋለን በሚል ከወጣት እስከ አዛውንቶች፣ከሴቶች ፣ አካል ጉዳተኞች ፣የሀይማኖት አባቶች ድረስ አብሮነታቸውን እየገለፁ ነው። ግንቦት 24ትን በጉጉት እየጠበቁ ነው!!
👇👇👇👇👇
12ኛ ቀን መልእክት ለመላው ሠላም ጥምረት ዳጋፊዎች!!
መልዕክት ለአገው ህዝብና ደጋፊዎች በሙሉ

በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ነጩን ነጭ ጥቁሩን ጥቁር ብለህ አውቀህ
>መብትህን የሚያስከብርልህን ምረጥ
>ጥየቄህን የሚያዳምጥልህን ምረጥ
>ሴረኛን ሳይሆን ትጉ የህዝብ ምረጥ
>የሚገልህንና የሚያሳድድህን ሳይሆን የሚያዳምጥህን ምረጥ
>አሽከርንና ሉሌን ሳይሆን የህዝብን ልጅ ምረጥ
>ልማት የሚያፍን ሳይሆን ልማት አነፍንፎ የሚያመጣልህን ምረጥ
>በጨለማ ውስጥ አስቀምጦ የሚቀልድ ሳይሆን ብርሃን የሚያመጣልህን ምረጥ
>በዉሃ ጥም የሚገልህን ሳይሆን የሚያጠጣህን ምረጥ
>አደር ባይ አጋስስን ሳይሆን ራሱን ለህዝብ የሰጠ ንፁሕ ህሊና ያለውን ምረጥ
>የሚገልህን ሳይሆን ለህዝቤ ብሎ የሚሞትልህን ምረጥ
>ቋንቋህን ባህልህንና ወግህን የሚያከብር የሚያስከብር እንጅ የመያጠፋ የማያከብር የማያስከብር አትምረጥ
>ህዝብህን የሚወድ የሚያከብር እንጅ የወከለውን ህዝብ የሚጠላ የሚያንቋሽሽ አትምረጥ
>በራሱ ማንነት የሚኮራ እንጅ የሌላን ማንነትና ባህል ለመልበስ የሚዳዳ አትምረጥ
>የህዝብ ኑሮ የሚየስጨንቀውን እንጅ በህዝብ ኑሮ የሚቀልድ አትምረጥ
>ባንዳንና ተላላኪን ሳይሆን ቁርጠኛ ጀግና የህዝብ ልጅ ምረጥ
>ተወካይ እንዲኖርህ አምርረህ ታገል መሪህን ፍጠር አትሽኮርመም አትፍራ አትሸወድ መብትህ ነው !!

ቡናችን የወደፊት ራዕያችን
💪💪💪💪💪
Getaneh Anejet
12/09/2018

ቻ-ጝኒ(ቻግኒ) ምርጫ ክልል  ሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ይፋዊ ይምረጡኝ ቅስቀሳ ጀምረዋል። ቅስቀሳውንም የጥምረቱ ም/ፕሬዚዳንት እና የአገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አዲሱ መኮንን...
19/05/2026

ቻ-ጝኒ(ቻግኒ) ምርጫ ክልል ሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ይፋዊ ይምረጡኝ ቅስቀሳ ጀምረዋል።

ቅስቀሳውንም የጥምረቱ ም/ፕሬዚዳንት እና የአገው ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አዲሱ መኮንን በተገኙበት ይፋዊ ቅስቀሳቸውን ቀጥለዋል።
ዝርዝሩን እንመለስበታለን!!

የልማት ንፅፅር፦፨፨፨፨፨፨፨፨ይህ ከታች የምታዩት አስፓልት መንገድ የቡሬ አጋምሳ መንገድ ነው። መንገዱ በዚህ ልክ መሠራቱ መልካም ነው ሲሉ የሰላም ሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ም/ፕሬዝዳንት እና...
18/05/2026

የልማት ንፅፅር፦
፨፨፨፨፨፨፨፨
ይህ ከታች የምታዩት አስፓልት መንገድ የቡሬ አጋምሳ መንገድ ነው። መንገዱ በዚህ ልክ መሠራቱ መልካም ነው ሲሉ የሰላም ሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ም/ፕሬዝዳንት እና የአገው ለፍትህ ፕሬዝዳንት Addisu Mekonnen ( PHD) ገለፁ ።

ሌላኛው የገበሬ እርሻ መሬት የሚመስለው ደግሞ ከ400 ዓመት በላይ የዕድሜ ባለፀጋ የሆነችው አገው ግምጃ ቤት ከተማ ናት። ማሰብ፣ ማንሰላሰልና ቁጭት ለሚሰማቸው አካላት ልዩነቱ ግልፅ ነው።

አገው ሆነው በሆድ ራሳቸውን ለሸጡና ሞራል አልባዎች ደግሞ አገው ግምጃ ቤት ከተማ በዚህ ልክ መሆኗ ትክክለኛ ሲሆን ቡሬ አጋምሳ መንገድ እንዲህ አስፓልት መሆኑ ያስደስታችዋል። ከዚህ በላይ ብሔራዊ ውርደትና መገፋት ምን አለ አገዎች?

እኛ የአዊ ብልፅግናን ስንቃወም በምክንያት መሆናችንን ህሊና ያለው ሁሉ እውነቱን እንዲፈርድ ይህንን የልማት ልዩነት እንጠይቃለን ብለዋል።

ዶ/ር አዲሱ አደገለፁት የአገው ህዝብ ለመንግስት ግብር አይከፍልም ይሆን? የአገው ህዝብ ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚ የማይሆንበት ምክንያት ምን ይሆን? መልሱ ትክክለኛ የሚከራከርና የሚሟገት ተወካይ ባለኖሩ ነው።

ለማንኛውም ህዝባችን በቀጣይ ተገቢና ፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆን ህዝባችን ሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረትን መምረጥ አማራጭ የሌለው መፍትሔ መሆኑን መረዳት ይኖርበታል።

ቡናን እየጠጣን!! ፤ የቡና ተክልን እንምረጥ!!። ድል ለህዝባችን!!!

ይህ የቅንጦት ፎቶ እንዳይመስላችሁ ለመስእዋትነት የተከፈለ ነው‼የአገው ህዝብ ለበርካታ ችግሮችና ተጋልጦ  ታሪክ፣ ቋንቋ ፣ ማንነትና መብት ለማስከበር እንዲሁም ባለፉት ዘመናት የደረሱ ታሪካዊ...
18/05/2026

ይህ የቅንጦት ፎቶ እንዳይመስላችሁ ለመስእዋትነት የተከፈለ ነው‼

የአገው ህዝብ ለበርካታ ችግሮችና ተጋልጦ ታሪክ፣ ቋንቋ ፣ ማንነትና መብት ለማስከበር እንዲሁም ባለፉት ዘመናት የደረሱ ታሪካዊና መዋቅራዊ በደሎችን ለመቀልበስ በየደረጃው በርካታ የፖለቲካ፣ የማህበራዊና የባህል እንቅስቃሴዎችና መስዋዕትነቶች እየተከፈሉ ይገኛሉ። ይህ ትግል ማንነትን ለማዳን እና ለማረጋገጥ ጀምሮ ራስን በራስ የማስተዳደር መብታችንን እስከ ማስከበር እየተደረገ የሚገኝ ተጋድሎ ነው።

የአሁኗ እያንዳንዷ የእንቅስቃሴችን እርምጃ ለነገዋ ስኬት አዲሱ ትውልድ በቀይ ቀለም ፅፎ የሚያሸጋግርበት ድልድይ ይሆናል።

​ የትግላችን ግብ ራስን በራስ ማስተዳደር ትግል ​የአደረጃጀትና የፖለቲካ ትግል፣ የማንነት ጥያቄዎችን በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ለማስመለስ እየተደረገ ያለው ተጋድሎ እጅግ ውጤታማና ስኬታማ እየሆነ እንዳለ ከአዲሱ ትውልድ አረጋግጠናል።

ድርጅታችን ብሎም ጥምረታችን ፖለቲካዊ ​የመዋቅር ጥያቄዎች ህገ-መንግስታዊ መብቶችን መሰረት በማድረግ፣ ህዝቡ በራሱ ቋንቋና ባህል የመዳኘት፣ የመማርና እራሱን የማስተዳደር መብቱ እንዲከበር በርካታ የህግና የፖለቲካ ጥረቶች ተደርገዋል፣ እየተደረጉም ይገኛሉ።

ምርጫ የአንድ ሀገር የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ትልቅ ዋጋ ያለው ቢሆንም እንደህዝባችን ግን​የቋንቋ መሞትን መከላከል፦ ቋንቋችን እንዳይጠፉና እንዲያድጉ በትምህርት ስርዓት ውስጥ እንዲካተቱ ማድረግ፣ የሬዲዮና የጋዜጣ ስርጭቶችን የመጀመር ምዕራፍ ነው።

የአገው ህዝብ ቁጥሩ እየቀነሰ የመጣበትን እና የማንነት መዋጥ የደረሰበትን ታሪካዊ ሂደት ለመቀልበስ፣ ማህበረሰቡ አካባቢውን፣ ባህሉንና ሰላሙን ለመጠበቅ ከፍተኛ የህይወትና የንብረት መስዋዕትነትን ከፍሏል አሁንም እየከፈለ ይገኛል።

ትግላችን ቅንጦታዊ ሳይሆን እየሆነብን እየደረሰብን ባለው በደላዊ ትግል ነው! የአገው ህዝብ ታሪካዊ በደሎችን ለመቀልበስ የሚያደርገው ጥረት የበቀል ሳይሆን የህልውና፣ የእኩልነት፣ የፍትህ እና የማንነት መከበር የሚደረግ ፍልሚያ ነው። ይህንን ለማሳካት የሚደረገው መስዋዕትነት ህዝቡ ከሌሎች ወንድም ኢትዮጵያውያን ጋር በሰላምና በእኩልነት የሚኖርባትን የስርዓት ግንባታ ለመፍጠር ያለመ ነው።
ስለሆነም ሁላችንም ይህን ትግል በጋራ ለመቀልበስ ምርጫችሁን የቡና ተክል አድርጉ!!
AGEW TV Fans

Address

Injibara
Injibara

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AGEW TV Fans posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share