AGEW TV

AGEW TV Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from AGEW TV, TV Channel, injibara, Injibara.

የዜና እና የወቅታዊ መረጃ ገጽ ነው።
አዳዲስ መረጃ ለማግኘት Like Page የሚለውን
በመጫን Follow ያድርጉ!
መረጃ ሲኖራችሁ፣ የሚዲያ ሽፋን ስትፈልጉ በውስጥ መስመር inbox ያድርጉልን ወይም በቴሌግራም
ገጻችን በኩል ላኩልን።
👉Voice of Voiceless ✅

🌐 https://linktr.ee/agewtv

የጨነቀ ለት አለ ዳኜ ዋለ😂የአማራ ፋኖ አላማ የሌለው በመርህ የማይመራ ፀረ ሰላም፣ አውዳሚ፣ዘራፊ፣አሳዳጅ ስብስብ ነው በማለት ሚድያችን በተከታታይ ስንዘግብ መቆያታችን ይታወቃል።ይህ ከታች የ...
31/08/2026

የጨነቀ ለት አለ ዳኜ ዋለ😂

የአማራ ፋኖ አላማ የሌለው በመርህ የማይመራ ፀረ ሰላም፣ አውዳሚ፣ዘራፊ፣አሳዳጅ ስብስብ ነው በማለት ሚድያችን በተከታታይ ስንዘግብ መቆያታችን ይታወቃል።

ይህ ከታች የምትመለከቱት ሰው ፅንፈኛው ማርሸት ይባላል 4ኪሎ መግባት ከፈለግን በ24 ሰሀት ውስጥ መግባት እንችላለን እያለ ቅርሻቱን ሲተፋ የቆየ የአውዳሚው የኮሙኒኬሽን ዋና ሀላፊ ነበር።

አርሸት(ማርሸት) ፋኖ ራሱ አስሮት ቆንጆ አድርጎ "በአስረሽ ምቺው" ከቀጣው በኋላ እንሆ መርህ የለሹ ስብስብ እጅ ሰጦ በቁጥጥር ስር ውሏል።

የማርሸት ጥሩ አርያ ከዘመነ ካሴ፣ከምሬ ወዳጆ እና ከመሳሰሉት በረከቱ ይድረሳቸው።
ህዝባችንም በሰላም ወቶ እንዲገባ ሁሉም የታጠቀ ቡድን እጅ እንዲሰጥ ጥሪችንን እናስተላልፋለን።
AGEW TV

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በወገራ  ቀጠና ቀማኛ ሌ*ባ ተሽከርካሪ እያስቆመ ሲቀማ በቁጥጥር ስር ዋለ።ከኪፋዝ  ወገራ  መስመር  መኪና  አስቁሞ  ሲዘርፍ  የነበረ  ቀማኛ ሌባ በምታዩት መልኩ እ...
31/08/2026

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በወገራ ቀጠና ቀማኛ ሌ*ባ ተሽከርካሪ እያስቆመ ሲቀማ በቁጥጥር ስር ዋለ።

ከኪፋዝ ወገራ መስመር መኪና አስቁሞ ሲዘርፍ የነበረ ቀማኛ ሌባ በምታዩት መልኩ እጅ ከፍንጅ ተይዟል።

ይሄን ስራ የሰራችሁ የፀጥታ አካላት እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብ ባላችሁበት ምስጋናችን ይድረሳችሁ።
AGEW TV

🚨  የፓኪስታን ፓይለቶች 5 የእስራኤል የጦር ጀቶችን መደብደባቸው ተዘገበ!!🇵🇰🇮🇱 የህንድ የመከላከያ ጉዳይ ድረ-ገጽ The Eurasian Times እንደዘገበው፣ የፓኪስታን ፓይለቶች በተለያ...
30/08/2026

🚨 የፓኪስታን ፓይለቶች 5 የእስራኤል የጦር ጀቶችን መደብደባቸው ተዘገበ!!

🇵🇰🇮🇱 የህንድ የመከላከያ ጉዳይ ድረ-ገጽ The Eurasian Times እንደዘገበው፣ የፓኪስታን ፓይለቶች በተለያዩ ሁለት ክስተቶች ላይ እስራኤላዊ የጦር አውሮፕላኖችን በመደብደብ 5 የእስራኤል የጦር ጀቶችን አውድመዋል የሚል দাবি ቀርቧል።
ሪፖርቱ በተለይ ትኩረት የሳበው፣ የዜናው ምንጭ ህንድ መሆኑ ነው። ህንድና ፓኪስታን የረጅም ጊዜ የፖለቲካና የወታደራዊ ተቀናቃኞች ሲሆኑ፣ ሁለቱም የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አገራት ናቸው።
✈️ የፓኪስታን ወታደራዊ አቅም
ጽሑፉ ፓኪስታንን እስራኤል ላይ 5 የጦር አውሮፕላኖችን መደብደቧ የተገለጸላት ብቸኛዋ ሙስሊም-አብዛኛዋ አገር እንደሆነች ይገልጻል። በተጨማሪም የፓኪስታን ወታደሮች የሥልጠና ደረጃና የውጊያ አቅም ከፍተኛ መሆኑን ያወድሳል።
🇵🇰🇹🇷🇸🇦 ከቱርክና ሳዑዲ ጋር ያለው ትብብር
ዘገባው ፓኪስታን፣ ቱርክ እና ሳዑዲ ዓረቢያ በመከላከያ መስክ እየጠናከሩ ያሉትን ትብብርም ይመለከታል። ይህ የሶስቱ አገራት የጦር ትብብር እየጠናከረ መሄዱ በእስራኤል ዘንድ ስጋትን ሊያሳድር እንደሚችል ጽሑፉ ይጠቁማል።
🕊️ በአረብ–እስራኤል ጦርነቶች የፓኪስታን ሚና
ሪፖርቱ በተጨማሪ ፓኪስታን በ1967 እና 1973 የአረብ–እስራኤል ጦርነቶች ወቅት ለአረብ አገራት ድጋፍ ለመስጠት ፓይለቶችን፣ ወታደራዊ አሰልጣኞችን እና ሌሎች ወታደራዊ ሰራተኞችን በሚስጥር መላኳን ይገልጻል።
AGEW TV

በአገው አዊ ብሔረሰብ ዞን ግን የመንገድ ትራንስፖርት አግልግሎት ይኖር ይሆን❓ህዝባችን በተደጋጋሚ ለሚመለከተው ሁሉ ቅሬታ ቢያቀርቡም ማንም የሚሰማቸው ስለጠፋ ነዋሪዎች ለከፋ አደጋ እየተጋለጡ...
30/08/2026

በአገው አዊ ብሔረሰብ ዞን ግን የመንገድ ትራንስፖርት አግልግሎት ይኖር ይሆን❓

ህዝባችን በተደጋጋሚ ለሚመለከተው ሁሉ ቅሬታ ቢያቀርቡም ማንም የሚሰማቸው ስለጠፋ ነዋሪዎች ለከፋ አደጋ እየተጋለጡ እንደሆነ ይታወቃል።

የአገው ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር ህገመንግስታዊ መብቱ ካልተከበረ ገና የስቃይ ስቃይ እየቀጠለ ይሄዳል!!
ህዝቤ ሆን ጥያቄህን በህብረት ድምፅህን አሰማ!!?
AGEW TV

የቅጥር ማስታወቂያ‼የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2019 በጀት ዓመት የተቋሙን የሰው ኃይል ለማጠናከር በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰብና ሕዝቦች፣ የጾታ ...
30/08/2026

የቅጥር ማስታወቂያ‼

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2019 በጀት ዓመት የተቋሙን የሰው ኃይል ለማጠናከር በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰብና ሕዝቦች፣ የጾታ ተዋፅዖን ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ ተመልምለው በተቋሙ ባሉት ልዩ ልዩ የሥራ ዘርፎች ተመድበው ማገልገል የሚፈልጉ ዕጩ ፖሊሶችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል።

ዕጩ ተመልማዮቹ ምልመላው ተጠናቆ ወደ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሥልጠና ማዕከል ገብተው ሥልጠና ከመጀመራቸው በፊት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 720/2004 እና ደንብ ቁጥር 268/2005 በሚያዘው መሠረት የ7 ዓመት የሥራ ውል ግዴታ በመግባት በማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ አማካይነት የሚሰጣቸውን ሥልጠና በሚገባ በመከታተል ማጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል፡፡

በሥልጠና ቆይታ ጊዜያቶችም በማሠልጠኛ ትምህርት ቤቱ በኩል የምግብ፣ የመኝታ፣ የሕክምና እና ለሥልጠናው የሚያስፈልጉ የአልባሳት፣ የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችና የኪስ ገንዘብ ይሰጣል።

ሥልጠናው ሲጠናቀቅም እያንዳንዱ ተመራቂ በተቋሙ የደመወዝ ስኬል መሰረት ወርሃዊ ደመወዝና የቀለብ ሂሳብ የሚከፈለው ሆኖ በተቋሙ ልዩ ልዩ የስራ አልባሳት፣ ነፃ የሕክምና አገልግሎት፣ በካምፕ የጋራ መኖሪያ ቤት እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎት ያገኛሉ።

ተመርቀው ፖሊሳዊ የሙያ አገልግሎት በሚያበረክቱባቸው ጊዜያትም በተቋሙ ውስጥ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ማቋቋሚያ አዋጅ፣ ደንብ እና የስልጠና መመሪያዎች መሠረት በሚወጡ መመዘኛዎች አማካኝነት በልዩ ልዩ የትምህርትና ሥልጠና ፕሮግራሞች በመወዳደር ተጠቃሚ የመሆን ሠፊ ዕድል የሚጠብቃቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በደስታ ይገለፃል።

የምልመላ መስፈርት (መመዘኛ)

1. ዜግነት ኢትዮጵያዊ የሆነ/የሆነች፣

2. ለሕገ-መንግስንቱና ለሀገሪቱ ሕጎች ተገዥና ታማኝ የሆነ/የሆነች፣

3. ከማናቸውም ደባል ሱሶች የፀዳ/የፀዳች እና መልካም ስነ-ምግባር ያለው/ያላት፣

4. በሚመለመልበት አካባቢ ነዋሪ ስለመሆኑ የቀበሌ መታወቂያ ወይም የፋይዳ መታወቂያ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣

5. ከሚኖርበት ቀበሌ አስተዳደር፣ ከአካባቢው ፖሊስ እና ከተማረበት ትምህርት ቤት የተዘጋጁ ቅፆችን በማስሞላት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፤

6. በብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም በሃይማኖት እኩልነት የሚያምን/የምታምን፣

7. ለፖሊስነት የሚያበቃ ሙሉ ጤናማ መሆኑን/መሆኗን በህክምና የተረጋገጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣

8. ዕድሜው/ዋ ከ18 እስከ 25 ዓመት ያላነሰና ያልበለጠ/ያልበለጠች፣

9. የማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆነ/ያልሆነች፣

10. የትምህርት ደረጃ 10ኛ ክፍል እና በላይ የሆነ/የሆነች እንዲሁም ትምህርት ያጠናቀቀበት ካርድ ዋናውንና የማይመለስ አንድ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣

11. ብዝሃነትንና አካታችነትን ለማረጋገጥ ሲባል ያልተካተቱና አነስተኛ ቁጥር ባለባቸው ብሔሮች አካባቢ ለሚመለመሉ ወጣቶች ቢያንስ 6ኛ ክፍል እና በላይ የሆነ/የሆነች፣

12. ቁመት ለወንድ 1.65 ሜትር በላይ የሆነ፣ ለሴት 1.60 ሜትር በላይ የሆነች፣

13. የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 720/2004 እና ደንብ ቁጥር 268/2005 በተደነገገው መሠረት የ7 ዓመት የሥራ ውል ግዴታ በመግባት ሥልጠናው ሲጠናቀቅ በየትኛውም የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ተቋም የሥራ አከባቢ ተመድቦ/ተመድባ ለመሥራት ፈቃደኛ የሆነ/የሆነች፣

14. ከአሁን በፊት በወንጀል ተከሶ ያልተቀጣ/ያልተቀጣች ወይም የወንጀል ሪከርድ የሌለበት/የሌለባት የአሻራ ምርመራ ለማድረግ ፍቃደኛ የሆነ/የሆነች፣

15. ከአሁን በፊት በማንኛውም የፖሊስ እና የመከላከያ ሰራዊት ተቋም ሥልጠና ያልተሳተፈ/ያልተሳተፈች ወይም በአባልነት ተቀጥሮ ያልሰራ/ያልሰራች፤

16. ያላገባ እና ያልወለደ ወይም ያላገባች እና ያልወለደች፣

ማሳሰቢያ፡- ማንኛውም ዕጩ ተመልማይ በምዝገባ ወቅት ከላይ የተገለፁት መመዘኛዎች እንደተጠበቁ ሆኖ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ይዞ በመቅረብ መመዝገብ ይኖርበታል፡፡

1) የትምህርት ማስረጃ ዋናውንና የማይመለስ 1 ፎቶ ኮፒ፣

2) ከ2 ዓመት በላይ ነዋሪነትን የሚያመለክት የቀበሌ ነዋሪነት መታወቂያ ወይም የፋይዳ መታወቂያ ይዞ መቅረብና መመዝገብ ይጠበቅበታል፣

3) የተመልማዩን ማንነት አጠቃላይ ሁኔታ ለመገንዘብ እንዲያስችል ታስቦ በሥልጠና ማዕከሉ አማካይነት የተዘጋጀውን ፎርም ከምዝገባ ጣቢያው በመቀበል የመጨረሻ አመት ካጠናቀቀበት ወይም ካጠናቀቀችበት ትምህርት ቤት፣ ከመኖሪያ ቀበሌና ከአከባቢው የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ጽ/ቤት ቀርቦ ወይም ቀርባ የማስሞላትና በተጠቀሰው የቀን ገደብ መሰረት ለምልመላ ጣቢያው አስቀድሞ ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

4) ሴት ተወዳዳሪዎች ይበረታታሉ።
ማንኛውም ምልምል ከ500 ብር በላይ፣ ወርቅ፣ የተለያዩ ስለታማ ነገሮችን፣ ምግብ ነክ ነገሮች እና ከሁለት ቅያሪ ልብስ በላይ ይዞ ወደ ማሰልጠኛው ማዕከል መግባት የተከለከለ ነው፡፡

የምዝገባ ጊዜው ከጳጉሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 18 ቀን 2019 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ የሥራ ቀናት የሚካሄድ ሲሆን፣ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በየክልሉ በሚገኙ ዞኖች፣ ወረዳዎች እና በምልመላ ጣቢያዎች በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። መረጃው የኢትዮጵያ ፌድራል ፖሊስ ነው
AGEW TV

29/08/2026

ታምብስ አፍሌን አዋዋስ!!
AGEW TV

አባቴ ምላስ እና ተግባር የተለያዩ ናቸው። "ሴዶ" ድሪል የማይበሳው ሰውነትህ እንዴት "በጆኒ" እንዲህ የራስዳሽን ተራራ አከለሳ😂😭ቻለው አባቴ😭AGEW TV
29/08/2026

አባቴ ምላስ እና ተግባር የተለያዩ ናቸው።
"ሴዶ" ድሪል የማይበሳው ሰውነትህ እንዴት "በጆኒ" እንዲህ የራስዳሽን ተራራ አከለሳ😂😭
ቻለው አባቴ😭
AGEW TV

29/08/2026

የአፍሪካ ታሪክ ሲነሳ የኩሽ ህዝቦች ስልጣኔ አብሮ ይነሳል። በጣምም ነው የሚገርመው። በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና በአጠቃላይ ከ1-15 በታታሪ በኩሽ ልጆች ኢትዮጵያ አሸንፋለች🙏

 #አሱሪቴ፡ ከበዓል ባሻገር‼️ 🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁የአገው ህዝብ ቀደምት የአደባባይ በዓላት ከሆኑት አንዱ አሱሪቴ ነው። አሮጌው የዘመን ሲጠናቀቅ፣ የክረምቱ ጥቁር ደመና ገፎ የብርሃን ጮራ ሲፈነ...
28/08/2026

#አሱሪቴ፡ ከበዓል ባሻገር‼️
🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁
የአገው ህዝብ ቀደምት የአደባባይ በዓላት ከሆኑት አንዱ አሱሪቴ ነው። አሮጌው የዘመን ሲጠናቀቅ፣ የክረምቱ ጥቁር ደመና ገፎ የብርሃን ጮራ ሲፈነጥቅ፣ የአገው ህዝብ ከትውልድ ትውልድ ያወረሰውን የታላቅነት ምዕራፍ #አሱሪቴን በድምቀት ይቀበለዋል። ከጳጉሜ 1 እስከ 5 ባሉት ልዩ ቀናት ውስጥ የሚከበረው ይህ አደባባይ በዓል፣ ከቀን መቁጠሪያ መለወጫነት እና ከከአደባባይ በዓልነት ባለፈ የህይወት መታደሻ ትልቅ ምዕራፍ ነው።

ወንዞች አቧራቸውን አራግፈው ይጸዳሉ፣ ወፎች በአዲሱ ዜማቸው ተስፋን ይሰብካሉ፣ አዝመራው በምድር ውበት ጎምርቶ ፈገግ ይላል። ይህ የውጭ መታደስ ከሰው ልጅ ውስጣዊ መንፈስ ጋር ተቀናጅቶ ይመጣል።

እናቶች አዲሱን ዘመን በጽዱ ቤትና በደማቅ ዝግጅት ለመቀበል ሽርጉድ ሲሉ፣ ወጣቶች ትኩስ ተስፋን በልባቸው ይሰንቃሉ። አሱሪቴ የጨለማው የክረምት ካባ ተገፍፎ የብርሃን አየር የሚተነፈስበት የንፃት ወቅት ነው።

የአሱሪቴ እጅግ ውብና ታላቁ ምዕራፍ ግን ከበዓሉ አስቀድሞ የሚከናወነው የማህበራዊ ዕርቅ ስርዓት ነው። በባህሉ መሰረት፤ በዓሉ ከመከበሩ በፊት የተጣላ መታረቅ አለበት! የሚለው የዕድሜ ጠገብ ህግ የሰላም አንዱ ማዕዘን ነው።በዚህ ጊዜ አባቶች በሸንጎ ተቀምጠው የቆዩ ቂሞችና ኩርሾዎች እንዲፈቱ ያደርጋሉ። የተጣሉት ታርቀው፣ በደል ይቅር ተባብለው ልባቸውን ያነጻሉ። በዚህ የሽምግልና ማዕቀፍ ውስጥ አልታረቅም ማለትና ቂም ይዞ በዓልን ማክበር በፍጹም አይታሰብም። በዓሉ የፍቅርና የአንድነት ማጠናከሪያ የሚሆነውም በዚህ ምክንያት ነው።

በአጠቃላይ አሱሪቴ የዘመን መለወጫ ብቻ ሳይሆን፣ ማህበራዊ ስብራቶች የሚጠገኑበት፣ የሰላም ማህተም የሚቀመጥበት የህዝብ መዋጀት ነው። ህብረተሰቡን በአንድ መንፈስ አስተሳስሮ የሚያቆመው ይህ የሰላም መሳሪያ፣ ትናንት የነበረውን ቁርሾ ቀብሮ ለነገ አብሮ የመቆም ምለው ቃል የሚፈጸምበት የተቀደሰ አደባባይ ነው።

አሱሪቴ- ለሰላም የቆመ የህዝብ ትንፋሽ፣ ለአንድነት የሰመረ የዘመን ቃና!

✍️በተግባር አንዱዓለም
AGEW TV

በሻደይ እለት ክቡር ፕሮፌሰር አለማየሁ እርቂሁን ያቀረቡት ጥናታዊ ፁሁፍበመካከላችሁ ተገኝቼ የዚህን የታላቅ ህዝብ በዓል አብሬ ማክበር በመቻሌ የተሰማኝ ደስታ በጣም ትልቅ ነው። እኔ የማቀርበ...
27/08/2026

በሻደይ እለት ክቡር ፕሮፌሰር አለማየሁ እርቂሁን ያቀረቡት ጥናታዊ ፁሁፍ

በመካከላችሁ ተገኝቼ የዚህን የታላቅ ህዝብ በዓል አብሬ ማክበር በመቻሌ የተሰማኝ ደስታ በጣም ትልቅ ነው። እኔ የማቀርበው ጽሑፍ «የአገው ህዝብ አበርክቶ እና የሻደይ ባህላዊ ፋይዳ» ይሰኛል። አዎ፣ ለኢትዮጵያ ብዙ አበርክቶ ያለው፣ በርካታ የቅርስ አሻራ ያለው ማህበረሰብ ነው። አገው በቅርብ የተሰራ ማንነት ያለው ህዝብ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያ ስትፈጠር ጀምሮ አብሮ የኖረ፣ በኢትዮጵያ ቀደምት ከሚባሉ ማህበረሰቦች ውስጥ አንዱ ማህበረሰብ ነው። ከኩሽ ህዝቦች የሚመደብ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ቀንድ ነባር ጥንታዊ ማህበረሰብ ነው።

አሁን በተበጣተነ መልክዓ ምድርና የወሰን አስተዳደር የነበረ ማህበረሰብ ሳይሆን፣ ከቀይ ባህር ጀምሮ እስከ አባይ ተፋሰስ ባለው ሰፊ ግዛት ውስጥ በሰፊው ሰፍሮ የነበረ፣ በኢትዮጵያ ቀደምት ከሚባሉ ማህበረሰቦች ውስጥ የሚመደብ ጥበበኛ ማህበረሰብ ነው። ዘመናዊ የኢንጂነሪንግ መስክ በዓለም ላይ ባልነበረበት ወቅት፣ የኪነጥበብና የኪነ-ህንጻ ጥበብን ለዓለም እና ለአፍሪካ ያበረከተ ታላቅ ህዝብ ነው። ፈረስን ከበሬ ጋር በማቀናጀት የእርሻ ስራን ለኢትዮጵያ ያስተማረ፣ በዘመናዊ የዘረመል ጥበብ ሳይንስ አህያን ከፈረስ ጋር በማዳቀል በቅሎን ያስገኘ፣ እጅግ በጣም ጥበበኛ የሆነ ህዝብ ነው።

በዲፕሎማሲ ታሪክና በውጭ ፖሊሲ ታላቅ የሆነ አሻራን ያሳረፈ ህዝብ ነው። የዛግዌ ስርወ-መንግስት በነበረበት ጊዜ ዓለም በሁለት ጎራ ተከፍሎ፣ የኦቶማን ቱርክ እና የምዕራብ አውሮፓ የክርስቲያን ሀገራት ህብረት ተብለው ዓለም የመስቀል ጦርነትን ይዋጋ ነበር። ይሄ ዘመን በኢትዮጵያና በአፍሪካ ቀንድ የዛግዌ መንግስት የነበረበት ጊዜ ነው። ነገር ግን የዛግዌ መንግስታት የሚከተሉት የውጭ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ያስከበረ ስለነበር፣ ዓለም በሁለት ጎራ ተከፍሎ ሲዋጋ የዛግዌ ነገስታት ገለልተኛ ነበሩ። በእየሩሳሌም የሚገኘውን፣ በዓለም እጅግ በጣም ውድ እና ብርቅዬ የሆነውን የዴር ሱልጣን ገዳምን ያገኘው የዛግዌ መንግስት ነው። «ዴር ሱልጣን» ማለት በአረብኛ የንጉሱ ስጦታ ማለት ነው። ኢትዮጵያ ይህንን ዓለም ላይ ከሚገኙ እጅግ በጣም ውድ እና ብርቅዬ የሆነ ቦታ ያገኘችው አገው በኢትዮጵያ በነገሰበት ጊዜ ነው።

እኔ እድለኛ ሆኜ ይህንን አካባቢ አይቼዋለሁ። በዓለም እጅግ በጣም ውድ እና ብርቅዬ በሆነው አካባቢ ያደጉ ሀገራት በረጅሙ የዓለም ታሪክ ውስጥ እየተፈራረቁ ይዋጉበት የነበረበት ጊዜ ነው። በኢትዮጵያ የዛግዌ ስርወ-መንግስት እጅግ በጣም የሰላም ዘመን በመባል ይታወቃል። ኢትዮጵያ በዓለም ላይ የምንታወቀው በጦርነት እንደሆነ ብዙዎቻችን እናውቃለን፤ ነገር ግን የዛግዌ ዘመን በኢትዮጵያ ፍጹም የሆነ ሰላም የነገሰበት፣ ኢትዮጵያ በዓለም ላይ የምትታወቅበት የሰላም ጊዜ እንደሆነ ብዙዎቻችን አናውቀውም።

ከዛ ስርወ-መንግስት በኋላ አገው ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳር ከመሀል ወደ ዳር የወጣበት ዘመን ነው። የግዛት አስተዳደሩም በእጅጉ ቀንሷል። ቋንቋና ባህላዊ ማንነቱ በሌሎች ተጽዕኖ ስር መውደቁ አልቀረም። ይሁን እንጂ ግን በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሳትፎ ሙሉ በሙሉ የተገለለ አይደለም፣ እጅግ በጣም ንቁ ተሳትፎ ያደርግ ነበር። ለዚህም ማሳያ የሚሆነው ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ ካረፉ በኋላ ወደ ስልጣን የመጡት፣ ታላቁ የዋግ ሹሞች ልጅ ዋግሹም ጎበዜ ገብረመድህን ናቸው። በስልጣን ስማቸው አፄ ተክለጊዮርጊስ ተብለው ይታወቃሉ። እንግዲህ ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ ካረፉ በኋላ በኢትዮጵያ ሶስቱ ታላላቅ ነገስታት ከፍተኛ የሆነ የስልጣን ትንቅንቅ ያደርጉ ነበር። እርሳቸው በጊዜው ከነበሩት ኃያል ስለነበሩ፣ እንዳለመታደል ሆኖ ብዙ ጊዜ ባይቆዩም በዛች በአጭር ጊዜም ቢሆን አፄ ተክለጊዮርጊስ ኢትዮጵያን ያስተዳደሩ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ደማቅ የሆነ አሻራ ያሳረፉ ናቸው።

አገው በኢትዮጵያ የውጭ ወረራ እና የእርስ በእርስ ጦርነት ሲከሰት አብሮ የቆሰለ፣ አብሮ የደማ፣ ለኢትዮጵያ ትልቅ ዋጋ የከፈለ ማህበረሰብ ነው። እንደሚታወቀው ታላቁ የአድዋ ጦርነት ከሁሉም አካባቢ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ እየተሳተፈበት የተካሄደ ነው። በዚህ ታላቁ ጦርነት ተጋድሎ ላይ ከጣልያን የምስራቅ አፍሪካ አራቱ ጀነራሎች ውስጥ አንዱ የሆኑትን ጀነራል አልቤርቶኒን የማረኩት የዋግ ሹሞች ልጅ ዋግሹም ጓንጉል ናቸው ። በፈረስ ስማቸው «አባ መርከብ» ተብለው የሚታወቁት፣ የዋግና የላስታን ከ10 ሺህ በላይ ጦር ይዘው የተሰለፉት፣ በማርያም ሸዊቶ ተዋግተው ሀገርን ሊወር የመጣውን ከጣልያን አራቱ ጀነራሎች ውስጥ አንዱን የማረኩት ዋግሹም ጓንጉል ናቸው።

ከአድዋ ጦርነት በኋላ ጣልያን 40 ዓመት የፈጀ ዝግጅት አድርጎ ሲመጣ፣ የአገው ልጆች ለኢትዮጵያ ትልቅ ዋጋ ከፍለዋል። ከእነዚህ ውስጥ ጀነራል ኃይሉ ከበደ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያውን የሌተናል ጀነራል ማዕረግ የተቀበሉ የዋግ ተወላጅ ናቸው።
እንግዲህ አገው በኢትዮጵያ በርካታ በዓላት አሉት፤ ከእነዚህ ባህላዊ ቅርሶች ውስጥ የሻደይ (የልጃገረዶች) በዓል አንዱ ነው። ቀደም ሲል እንደገለጽኩት አገው ከቀይ ባህር እስከ አባይ ሸለቆ ግዛት የሰፈረ ማህበረሰብ በመሆኑ፣ የሻደይ (የልጃገረዶች) ባህላዊ ክዋኔ በተለያየ ስያሜ በተለያየ አካባቢ ይዘቱን ሳይለቅ እስካሁን ድረስ እንደቀጠለ ይታወቃል። በብዙ አካባቢዎች የሚታየው ይህ የሻደይ ክዋኔ ተመሳሳይ ይዘት ቢኖረውም በተለያየ ስያሜ የሚጠራበት ዋናው ምክንያት፣ በጊዜ ሂደት ውስጥ ማህበረሰቡ የአማርኛ ተናጋሪ እና የትግረኛ ተናጋሪ እየሆነ ሲመጣ ባህላዊ ይዘቱ እና ስያሜውም በዛው መጠን እየቀነሰ በመምጣቱ ነው።

ሻደይ የአገው ህዝቦች የማንነት መገለጫ ነው። ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቱን አጣምሮ የያዘ ጥንታዊ የሆነ ባህላዊ ቅርስ ነው። ለብዙ ሺህ ዓመታት የቆየ የሴቶች የነጻነት ምልክት ነው። ቤተሰብን ከወዳጅ ዘመድ ጋር የሚያገናኝ፣ የራሱ የሆነ ውዝዋዜ እና ዜማ ያለው ባህላዊ ቅርስ ነው። ስለ ሻደይ ታሪካዊ አመጣጥ እና ባህላዊ ክዋኔ ይዘት ትልቅ ድርሳን መጻፍ ይቻላል።

ዋናው ማሰብ ያለብን ቁምነገር ግን ሻደይን ከህዝብ ዘላቂ ሰላምና ከህዝብ ጥቅም ጋር ማሳሰር፣ በማንነቱ የሚኮራ ትውልድ በማፍራት ላይ ነው። የአንድ ህዝብ ባህላዊ ማንነት ፋይዳ በገንዘብ አይተመንም። ባህል የአንድ ማህበረሰብ የማንነትና የአንድነት መገለጫ ብቻ አይደለም፤ በህዝቦች መካከል የአንድነት ማስተሳሰሪያ፣ ማጠናከሪያ ገመድ ነው።

የችግሮች ሁሉ የጋራ መፍቻ መንገድም ነው። ባህል ትውልድ በማንነቱ እንዲኮራ ያደርጋል፤ በማንነቱ የማይኮራ ትውልድ የሃሳብና የእውቀት ድርቃት ያጋጥመዋል።
እንግዲህ ሻደይን ስናከብር እነዚህን ሁሉ እያሰብን መሆን አለበት። በዓሉን ስናከብር ባህላዊ ማንነቱን በማስጠበቅ መሆን መቻል አለበት። ሻደይ በተለያየ አካባቢ ያለውን የአገውን—የጎጃም አገው፣ የጎንደር፣ የሰቆጣ፣ የላስታ አገውን በጋራ የሚያሳስብ ሀብት መሆን አለበት። ይህ ሲሆን አንድነት ይኖራል፣ የጋራን ችግር በጋራ ለመፍታት ይጠቅማል፣ በልማት እንዲተባበሩም ያደርጋል።ከብርሃኑ ሽቱነህ ገጽ የተወሰደ
AGEW TV

Address

Injibara
Injibara

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AGEW TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category