SRTV አማርኛ

SRTV አማርኛ የሶማሊ ክልል መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ
Reliable Media Service, With Your Language Preference! SRS Mass Media Agency

15/10/2025

የምሽት 12 ሰዓት የአማርኛ ዜና ጥቅምት 05/2018 ዓ.ም

15/10/2025

የሶማሊ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ቢሮ ከአማራ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር የልምድ ልዉዉጥ መድረክ ዛሬ በጅግጅጋ ከተማ አካሄደ

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ ጋር ተወያዩጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥቅምት 05/2018 አ.ም)የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ እና...
15/10/2025

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ ጋር ተወያዩ

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥቅምት 05/2018 አ.ም)የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ ከዓለም ባንክ እና የዓለም ገንዘብ ድርጅት ዓመታዊ ጉባኤ ጎን ለጎን ከዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ ጋር በዋሽንግተን ተወያይተዋል።

ውይይቱ ፍሬያማ እንደነበር የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

በውይይቱ ላይ በአቶ አሕመድ ሽዴ የተመራው እና የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፍተኛ አማካሪ ተክለወልድ አጥናፉ እና ሌሎች ከፍተኛ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን አባላት ተገኝተዋል።

15/10/2025

የሶማሊ ክልል የስራ ሀላፊዎች በቀብሪዳሀር ከተማ እየተካሄዱ ያሉ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን እና የአገልግሎት አሰጣጥን ጎበኙ

15/10/2025

የሶማሊ ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አብዱረህማን አህመድ ከጀረር ዞን ወረዳዎችና ከደጋህቡር ከተማ አመራሮች ጋር ተወያዩ.

የሶማሊ ክልል ተፈናቃይ ወገኖች መልሶ ማቋቋም ስራዎች ጠቃሚ ልምድ የሚቀሰምበት ነው ፦ዲያቆን ተስፋው ባታብል ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥቅምት 05/2018 አ.ም)የሶማሊ ክልል ተፈናቃይ ወገኖች...
15/10/2025

የሶማሊ ክልል ተፈናቃይ ወገኖች መልሶ ማቋቋም ስራዎች ጠቃሚ ልምድ የሚቀሰምበት ነው ፦ዲያቆን ተስፋው ባታብል

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥቅምት 05/2018 አ.ም)የሶማሊ ክልል ተፈናቃይ ወገኖች መልሶ ማቋቋም ስራዎች ጠቃሚ ልምድ የሚቀሰምበት መሆኑን የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዲያቆን ተስፋው ባታብል ገለፁ ።

የሶማሊ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ቢሮ ከአማራ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ከመጡ አመራሮች ጋር የልምድ ልዉዉጥ መድረክ ዛሬ በጅግጅጋ ከተማ አካሂዷል።

የልምድ ልዉዉጥ መድረኩ የክልሉ የአደጋ ስጋት አመራር ቢሮ አመራሮችን ጨምሮ የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አመራሮች እንዲሁም የአጋር ድርጅት ተወካዮች በተገኙበትም ተካሂዷል።

የልምድ ልውውጡ በሶማሊ እና በአማራ ክልሎች በሰዉ ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ የተፈናቀሉ ወገኖችን በዘላቂነት መልሶ ማቋቋም እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃነታቸዉን ለማሳደግ በሚከናወኑ ስራዎች ላይ ያተኮረ መሆኑንም ተገልጿል።

ከዚህ ቀደም የክልሉ መንግስት እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር በሶማሊ ክልል በተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎች የሚኖሩ ወገኖችን ወደ መኖሪያ ቄያቸዉ በመመለስና መልሶ በማቋቋም ህይወታቸውን በዘላቂነት ለማሻሻል የሚያስችሉ ስራዎች መከናወኑን ተጠቁሟል።

የሶማሊ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ቢሮ ም/ሀላፊ አቶ አብዲፈታህ መሀመድ የልምድ ልውውጥ መደረኩ በሰው ሰራሽ እና በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው የሚገኙ ወገኖችን በዘላቂነት መልሶ ማቋቋም እየተከናወኑ በሚገኙ ስራዎች ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በክልሉ ከለውጡ ወዲህ ከተለያዩ አከባቢዎች የተፈናቀሉ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም ሰፊ ስራዎች መከናወኑን የገለፁት ምክትል የቢሮ ሀላፊው ለኑሮ አመቺ በሆኑ አከባቢዎች ኑሮ መምራት የጀመሩ ነዋሪዎች በሌማት ትሩፋት ፣ በምርትና ምርታማነት እና በሌሎች የልማት ስራዎች ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙም ተናግረዋል፡፡

የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዲያቆን ተስፋው ባታብል በበኩላቸው በሶማሊ ክልል ተፈናቃይ ወገኖችን በዘላቂነት መልሶ ማቋቋም ዙሪያ ጠቃሚ ልምድ ማቅሰማቸውን ጠቁመው ያገኙትን ልምድና ተሞክሮ በስራ ላይ ለማዋል ይሰራል ብለዋል ፡፡

ኮሚሽነሩ በአማራ ክልል የሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖችን ፍላጎት መረጃ የማሰባሰብ እና የግንዛቤ ማስጨበጫዎችን የመስጠት ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው፤ በቀጣይም ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያስችሉ ስራዎች እንደሚከናወን ገልፀዋል፡፡

በሌይላ መሀመድ

15/10/2025

የኢንዱካንስ ፋዉንዴሽን ለቴክኒክና ሞያ ስልጠና ኮሌጅ ባለሞያዎች በልብስ ምርትና ፋሽን ዲዛይን ስራዎች የአረንጓዴ ክህሎት የአሰልጣኞች ስልጠና በጅግጅጋ ከተማ መስጠት ጀመረ

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የኢትዮጵያን የሪፎርም አጀንዳ መደገፉን እንደሚቀጥል ገለጸ ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥቅምት 03/2018 አ.ም)  የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) ለ...
14/10/2025

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የኢትዮጵያን የሪፎርም አጀንዳ መደገፉን እንደሚቀጥል ገለጸ

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥቅምት 03/2018 አ.ም) የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) ለኢትዮጵያን የሪፎርም አጀንዳ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።

በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የኢትዮጵያ ልዑክ በዋሽንግተን ዲሲ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(IMF) አመታዊ ስብሰባ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

በሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራው ልዑክ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ከፍተኛ አማካሪ ተክለወልድ አጥናፉና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ያካተተ ነው።

የኢትዮጵያ ልዑክ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) ምክትል ማኔጂንግ ዳይሬክተር ናይጀል ክላርክ እና ከተቋሙ የአፍሪካ የስራ ክፍል ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ ከኢትዮጵያ ሀገር በቀል ማክሮ ኢኮኖሚ አጀንዳ ጋር የተሳሰረው የአይኤምኤፍ ድጋፍ ፕሮግራም ላይ ያተኮረ ነው።

የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ለኢትዮጵያ የሪፎርም አጀንዳ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አድንቀዋል።

ሪፎርሙ የኢትዮጵያን ሙሉ የኢኮኖሚ አቅም ለመጠቀም፣ የስራ ዕድል ለመፍጠርና የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የኑሮ ደረጃ ማሻሻልን ያለመ ነው ብለዋል።

ሚኒስትሩ የሪፎርሙን ሂደት እና እስከ አሁን የተገኙ ውጤቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የዋጋ ንረት በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን፣ ወርቅን ጨምሮ የወጪ ንግድ ገቢ ከፍተኛ እድገት ማሳየቱን፣ የፊሲካል ምህዳሩን ያሰፋው የግብር ማሰባሰብ አቅም ማደግ እና የኢትዮጵያ የቢዝነስ ከባቢ ሁሉን አቀፍ መሻሻልን ለአብነት ጠቅሰዋል።

አይኤምኤፍ ሪፎርሙ ካለው ግዝፈት አኳያ የሚያደርገውን የፋይናንስ ድጋፍ እንዲያሳድግም ጠይቀዋል።

በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) ለአይኤምኤፍ ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ መንግስት ቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ የዕዳ ሽግሽግ(G20 Common Framework debt treatment) ስር ከኢትዮጵያ ኦፊሴላዊ አበዳሪዎች ኮሚቴ እያደረገ ያለውን ድርድር ላይ የታዩ አዎንታዊ ለውጦችን አስመልክቶ ገለጻ አድርገዋል።

የዕዳ ሽግሽጉ የኢትዮጵያ አጠቃላይ የሪፎርም ፕሮግራም ወሳኝ ምሰሶ መሆኑን አመልክተው በፋይናንስ ዘርፉ ላይ እየተደረጉ ባሉ ሪፎርሞች የተገኙ ውጤቶችን አስመልክቶም ገለጻ አድርገዋል።

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) በኢትዮጵያ እየታየ ያለውን ጠንካራ የኢኮኖሚ እድገት፣ እየተሻሻለ የመጣው የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትና ኢኮኖሚውን ለውጭ ዘርፍ ክፍት የማድረግ ጥረቶችን ጨምሮ የታዩ ለውጦችን አድንቋል።

የአይኤምኤፍ ምክትል ማኔጂንግ ዳይሬክተር ናይጀል ክላርክ የኢትዮጵያ ጠንካራ እና ድፍረት የተሞላበት የሪፎርም አጀንዳ ለሌሎች ሀገራት ምሳሌ እንደሆነ ገልጸው ተቋሙ የኢትዮጵያን የሪፎርም አጀንዳ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ የሪፎርም ትግበራ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ መሆኑን በውል እንደሚረዱ ገልጸው ለዚህም ዓለም ባንክን ጨምሮ ከሌሎች የልማት ፕሮግራሞች ጋር በመተባበር ተጨማሪ ሀብት ማሰባሰብ እንደሚገባ አመልክተዋል።

ክላርክ እ.አ.አ ዲሴምበር 2025 ላይ በኢትዮጵያ ጉብኝት ለማድረግ ማቀዳቸውም ተመላክቷል።

ሁለቱ ወገኖች አይኤምኤፍ በአዲስ አበባ በቀጣይ የኢትዮጵያን ብድር ፕሮግራም አስመልክቶ በሚያካሂደው አራተኛ ግምገማ ላይ በቅርበት ለመስራትም ተስማማተዋል።

14/10/2025

የምሽት 12 ሰዓት የአማርኛ ዜና ጥቅምት 04/2018 ዓ.ም

14/10/2025

የክልል ፣ የዞን እና የወረዳ የስራ ሀላፊዎች በሶማሊ ክልል ኤረር ዞን ፊቅ ወረዳ የአገልግሎት አሰጣጥ የስራ ሂደትን ጎበኙ

የሶማሊ ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ከጀረር ዞን ወረዳዎችና ከደጋህቡር  ከተማ አመራሮች ጋር ተወያዩጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥቅምት 04/2018 አ.ም)የሶማሊ ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲ...
14/10/2025

የሶማሊ ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ከጀረር ዞን ወረዳዎችና ከደጋህቡር ከተማ አመራሮች ጋር ተወያዩ

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥቅምት 04/2018 አ.ም)የሶማሊ ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አብዱረህማን አህመድ ከጀረር ዞን ወረዳዎችና ከደጋህቡር ከተማ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።

በብልፅግና ፓርቲ የሶማሊ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አብዱረህማን አህመድ በፓርቲ የተቀመጡ አቅጣጫዎችና በመንግስት እቅዶች ዙሪያ ከጀረር ዞን ወረዳዎች እና ደጋህቡር ከተማ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በጀረር ዞን ወረዳዎች እና በደጋህቡር ከተማ አስተዳደር በ2018 የበጀት አመት 1ኛው ሩብ አመት የተከናወኑ ስራዎችና በ2ኛው ሩብ አመት ለህብረተሰቡ የሚሰጡ አገልግሎቶችን እና የልማት ስራዎችን ማጠናከርና ማፋጠን ላይ ያተኮረ መሆኑን በብልፅግና ፓርቲ የሶማሊ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አብዱረህማን አህመድ ገልፀዋል።

የጀረር ዞን አመራሮች በበኩላቸው የፓርቲ ስራዎችን እና የመንግስት እቅዶችን እስከ ታች የመንግስት መዋቅር እና ህዝቡ ድረስ በማውረድ ለተግባራዊነታቸው በትኩረት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

አቶ ሳንዶካን ደበበ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥቅምት 04/2018 አ.ም) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቶ ሳንዶካን ደበበ...
14/10/2025

አቶ ሳንዶካን ደበበ የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥቅምት 04/2018 አ.ም) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቶ ሳንዶካን ደበበን የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አድርገው ሾመዋል።

አቶ ሳንዶካን ደበበ ከዛሬ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ መሾማቸውን ነው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ያስታወቀው፡፡

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 49ኛ መደበኛ ስብሰባ በኮሚሽኑ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ በመወያየት ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡

Address

Somali Region, Jigjiga City, Harar Kella.
Jijiga
SRTVAMHARICOFFICIAL

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when SRTV አማርኛ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to SRTV አማርኛ:

Share