SRTV አማርኛ

SRTV አማርኛ የሶማሊ ክልል መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ
Reliable Media Service, With Your Language Preference! SRS Mass Media Agency

የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ እየተከናወነ ነውጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  25/2017 አ.ም)  የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ በግልፅ፣ አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ መንገ...
02/02/2025

የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 25/2017 አ.ም) የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ በግልፅ፣ አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን የፓርቲው የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ።

ብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤውን ከጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በማካሄድ ላይ ነው::

የጉባኤውን ሶስተኛ ቀን ውሎ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ የሰጡት የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ከማለዳው ጀምሮ የአመራር ምርጫ ሲካሄድ መዋሉን ገልጸዋል።

በዚህም በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን በከፍተኛ የድምፅ ብልጫ ለፓርቲው ፕሬዝዳንት መምረጡን ተናግረዋል።

አቶ አደም ፋራህና አቶ ተመስገን ጥሩነህ ደግሞ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶች ሆነው በከፍተኛ ድምፅ መመረጣቸውን አንስተዋል።

ፕሬዝዳንቱና ምክትል ፕሬዝዳንቶቹ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ቃለ መሃላ መፈጸማቸውንም ነው ያነሱት።

ጉባኤው በከሰዓት ክፍለ ጊዜው የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ በማካሄድ ላይ ነው ብለዋል።

በአዲሱ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ቀድሞ የማዕከላዊ ኮሚቴ የሚለው አወቃቀር አሁን የብልጽግና ምክር ቤት በሚል መተካቱን ተናግረዋል።

በአዲሱ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ቀርቶ የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።

በምርጫው በርካታ ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የተወከሉ ተሳታፊዎች ነጻ፣ ገለልተኛና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እጩዎችን ጠቁመው ድምጻቸውን እየሰጡ እንደሚገኙም አንስተዋል።

ከጥቂት ሰዓታት በኋላ የምክር ቤት አባላት መርጫው ውጤት ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን አንስተው፥ በመቀጠል የፓርቲው ኢንስፔክሽንና የስነምግባር ኮሚሽን እንዲሁም የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫ እንደሚከናወን አንስተዋል።

የድምፅ አሰጣጡ ለመጀመሪያ ጊዜ በቀጥታ በቴክኖሎጂ በተደገፈ መንገድ ድምጽን ለመስጠት በሚያስችል መልኩ እየተካሄደ ነው ብለዋል።

ጉባኤው የብልጽግና የሀሳብ ልዕልና የተገለጸበት እና የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲ እየጎለበተ መምጣቱ የታየበት ነው ብለዋል።

እስከሚቀጥለው ጉባኤ የሚተገበሩ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ይፋ እንደሚደረጉም ገልጸዋል።

02/02/2025

የምሽት 12 ሰዓት የአማርኛ ዜና ጥር 25/2017 ዓ.ም

02/02/2025

በሶማሊ ክልል በጥር ወር መጨረሻ የእናትነት ወር በተለያዩ መርሐ-ግብሮች እንደሚከበር የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ መሀሙድ መሀመድ ገለፁ

የተጣለብን አመኔታ እና ኃላፊነት በአዲስ ቁርጠኝነት ለሥራ እንድንነሳሳ የሚያበረታታን ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  25/2017 አ.ም) የተጣለብ...
02/02/2025

የተጣለብን አመኔታ እና ኃላፊነት በአዲስ ቁርጠኝነት ለሥራ እንድንነሳሳ የሚያበረታታን ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 25/2017 አ.ም) የተጣለብን አመኔታ እና ኃላፊነት በአዲስ ቁርጠኝነት ለሥራ እንድንነሳሳ የሚያበረታታን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የብልፅግና ፓርቲን ምርጫ አካሂደናል ብለዋል።

ይኽም ወደ ዲጂታል ሽግግር የምናደርገው የሀገራዊ ጉዞ አካል ነው ሲሉም ነው የገለጹት።

በምርጫው ውጤት በእኔና በምክትል ፕሬዝዳንቶች የተጣለብን አመኔታ እና ኃላፊነት በአዲስ ቁርጠኝነት ለሥራ እንድንነሳሳ የሚያበረታታን ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።

ሰበር ዜናክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ።ሦስተኛ ቀኑን የያዘው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ክቡር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) እጅግ ከፍተኛ ...
02/02/2025

ሰበር ዜና
ክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ።

ሦስተኛ ቀኑን የያዘው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ክቡር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) እጅግ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ መርጧቸዋል።

ተመራጩ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል።

በተያያዘ ዜና ጉባኤው ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና ክቡር አቶ አደም ፋራህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚደንቶች አድርጎ እጅግ ከፍተኛ በሆነ ድምጽ መርጧል።

ሁለቱ ምክትል ፕሬዚደንቶች በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በጉባኤተኛው ፊት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል።

የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በሦስተኛ ቀን ውሎው የፓርቲውን ፕሬዚደንትና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ምርጫ በማካሄድ ላይ ይገኛል።
02/02/2025

የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በሦስተኛ ቀን ውሎው የፓርቲውን ፕሬዚደንትና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ምርጫ በማካሄድ ላይ ይገኛል።

የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አሳለፈጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  24/2017 አ.ም)  የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ በዛሬ ውሎ...
01/02/2025

የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባዔ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አሳለፈ

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 24/2017 አ.ም) የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ በዛሬ ውሎው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የፓርቲው የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ።

የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ 2 ሺህ 100 ተሳታፊዎች በታደሙበት በደማቅ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት በትናንትናው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።

በጉባዔው 1 ሺህ 700 የድምፅ ተሳታፊዎች እንዲሁም የ15 ሀገራት ፓርቲዎች አመራርና ተወካዮችን ጨምሮ 400 የሀገር ውስጥና የውጭ እንግዶች በተጋባዥነት ተገኝተዋል፡፡

ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ጉባዔውን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፥ጉባዔው ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ተወካዮችን ባሳተፈና በዴሞክራሲያዊነት እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

በዛሬው ዕለትም ጉባዔው መድረኩን የሚመሩ የፕሬዚዲየም አባላትን በመሰየም በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ በስፋት መወያየቱንና አጀንዳዎችን መርምሮ ማጽደቁንም ተናግረዋል።

በዚህም የጉባዔው አዘጋጅ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት እና የስብሰባ ሥነ-ሥርዓት ደንብ ላይ በስፋት በመወያየት በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ብለዋል።

በመቀጠልም የማዕከላዊ ኮሚቴ እንዲሁም የኢንስፔክሽንና ሥነምግባር ኮሚቴ ሪፖርቶች ለጉባዔው ቀርበው ሰፊ ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ መጽደቃቸውን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ ጉባዔው በፓርቲው የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል ነው ያሉት።

ከአንደኛ ጉባዔ ማግስት በፓርቲው በተከናወኑ ተግባራት የተገኙ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ፈተናዎች እና ፈተናዎችን ለማለፍ የተኬደበትን ርቀት በስፋት መገምገሙንም አንስተዋል።

በዚህም የብልፅግና እሳቤ እስከ ታችኛው ህብረተሰብ ክፍል መድረሱ እና እሳቤው ባህል እየሆነ መምጣቱ የተረጋገጠበት ጉባኤ መሆኑን ገልጸዋል።

ጉባዔው በነገው ዕለትም ቀጥሎ የሚካሄድ ሲሆን÷ የፓርቲ ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንቶችን ጨምሮ የአመራር ምርጫ ይደረጋል ብለዋል።

ለዚህም በዛሬው ዕለት አስመራጭ ኮሚቴ በመሰየም የዕለቱ ስብሰባ አሳታፊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እንደተጠናቀቀ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ጉባዔው ለመጪዎቹ ዓመታት የሚያገለግሉ ውሳኔዎች የሚተላለፉበት እንደሆነም ጠቁመዋል።

በሶማሊ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ የተመራ የቢሮው የስራ ሀላፊዎች ቡድን የሽንሌ ሆስፒታልን ጎበኙጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  24/2017 አ.ም) በሶማሊ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አ...
01/02/2025

በሶማሊ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ የተመራ የቢሮው የስራ ሀላፊዎች ቡድን የሽንሌ ሆስፒታልን ጎበኙ

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 24/2017 አ.ም) በሶማሊ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ መሀመድ አያንሌ የተመራ የቢሮው የስራ ሀላፊዎች ቡድን በሲቲ ዞን የሽንሌ ከተማ ሆስፒታልን ጎብኝተዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ መሀመድ አያንሌ ከቢሮው የተለያዩ የስራ ሀላፊዎች ጋር በመሆን በሶማሊ ክልል ሲቲ ዞን የሽንሌ ከተማ ሆስፒታል የስራ ሂደትን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ጉብኝቱ የሽንሌ ሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጥ የስራ ሂደትን ፣ የሆስፒታሉ ፍላጎቶችን ለመመልከትና ለማዳመጥ ማዳመጥእና ሆስፒታሉን ለማልማት የታቀዱ እቅዶችን ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ተገልጿል።

በዚህ ወቅት የሶማሊ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ መሀመድ አያንሌ የክልሉ መንግስት በክልሉ ሆስፒታሎች የሚሰጡ የህክምና አገልግሎቶችን ጥራት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

የወዳጅ ሀገራት እህት ፓርቲ ተወካዮች የመዲናዋን የመስህብ ስፍራዎች ጎበኙ ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  24/2017 አ.ም) ለብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ የመጡ የወዳጅ ሀገራት የእ...
01/02/2025

የወዳጅ ሀገራት እህት ፓርቲ ተወካዮች የመዲናዋን የመስህብ ስፍራዎች ጎበኙ

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 24/2017 አ.ም) ለብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ የመጡ የወዳጅ ሀገራት የእህት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ብሔራዊ ቤተ-መንግስትን ጨምሮ የተለያዩ የመስህብ ስፍራዎችን ጎብኝተዋል።

የሀገራት እህት ፓርቲዎች አመራሮች በብሔራዊ ቤተ-መንግስት፣ በእንጦጦ ፓርክ፣ በአንድነት ፓርክና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

በብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ የመክፈቻ ሥነ-ስርዓት ላይ የፓርቲው አመራር አባላት፣ የአፍሪካና የብሪክስ አባል ሀገራት የእህት ፓርቲዎች የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የዓለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሳቢያ እየተካሄደ ባለው ጉባኤ በዛሬው የሁለተኛ ቀን ውሎ በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ውይይት በማካሄድ ላይ ይገኛል።

በሶማሊ ክልል ሲቲ ዞን ሀዲጋላ ወረዳ የተገነባ የህዝብ ቤተ መጻሕፍት ተመረቀጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  24/2017 አ.ም) በሶማሊ ክልል ሲቲ ዞን ሀዲጋላ ወረዳ የተገነባ የህዝብ ቤተ መጻ...
01/02/2025

በሶማሊ ክልል ሲቲ ዞን ሀዲጋላ ወረዳ የተገነባ የህዝብ ቤተ መጻሕፍት ተመረቀ

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 24/2017 አ.ም) በሶማሊ ክልል ሲቲ ዞን ሀዲጋላ ወረዳ የተገነባ የህዝብ ቤተ መጻሕፍት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።

በሲቲ ዞን ሀዲጋላ ወረዳ የተገነባው የህዝብ ቤተ መጻሕፍት የሶማሊ ልማት ማህበር ፣የሲቲ ዞን እና የሀዲጋላ ወረዳ አመራሮች እንዲሁም የወረዳው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ተመርቋል።

ቤተ መጻሕፍቱ የተለያዩ አስፈላጊ መፅሀፍት የተሟሉለት በመሆኑ ለወረዳው ተማሪዎች ፣ወጣቶች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የማንበብ ባህልን በማሳደግ ትልቅ እድል እንደሚፈጥርላቸው ተገልጿል።

የሶማሊ ልማት ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ መሀመድ ሁሴን በሀዲጋላ ወረዳ ተመርቆ ለአገልግሎት የበቃው ቤተ መጻሕፍት የህብረተሰቡን አጠቃላይ እውቀትን እና የማንበብ ባህልን በማሳደግ በኩል የጎላ ጠቀሜታ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።

01/02/2025

የምሽት 12 ሰዓት የአማርኛ ዜና ጥር 24/2017 ዓ.ም

የብልፅግና ፓርቲ 2ተኛ መደበኛ ጉበኤ ዛሬም ቀጥሏልጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  24/2017 አ.ም) ትናንት"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባ...
01/02/2025

የብልፅግና ፓርቲ 2ተኛ መደበኛ ጉበኤ ዛሬም ቀጥሏል

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 24/2017 አ.ም) ትናንት"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬም ቀጥሎ ይውላል።

በጉባኤው የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህን የእንኳን መጣችሁ መልዕክት ተከትሎ የመክፈቻ ንግግሩን የፓርቲው ፕሬዝዳንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርገዋል።

የፓርቲው ፕሬዝዳንት በንግግራቸው የፓርቲውን የአምስት ዓመታት ስኬታማ ጉዞዎች የዳሰሱ ሲሆን፤ በቀጣይም ፓርቲው ሊያካናውናቸው ያሰባቸውን ጉዳዮች አመላክተዋል።

በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ የተጋበዙት የተለያዩ ሀገራት የእህት ፓርቲዎች ተወካዮችም በጉባኤው መክፈቻ ላይ መልዕክታቸውን እንዳስተላለፉም ከፓርቲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው 2ኛ መደበኛ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ካነሱት ዋና ዋና ነጥብ … ማወቅ፣ ማላቅ ወይም ማሻሻል፣ መፍጠር፣ መፍጠን እና ...
31/01/2025

የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርቲው 2ኛ መደበኛ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ካነሱት ዋና ዋና ነጥብ …

ማወቅ፣ ማላቅ ወይም ማሻሻል፣ መፍጠር፣ መፍጠን እና ማስተሳሰር ብልጽግና ባህል መሆን አለባቸው ከሚላቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል ናቸው።

➡️ ማወቅ

ሀገርን በቅጡ ማወቅ ህዝቡን፣ ባህሉን፣ ቋንቋውን፣ ስነ ምግባሩን፣ በትክክል ማወቅ ይገባል

ኢትዮጵያን በቅጡ ስናውቅ ተዝቆ የማያልቅ ሀብት ያላት፣ የምታጓጓ መሆኗን መገንዘብ እንችላለን

➡️ማላቅ ወይም ማሻሻል

ያለንን የተሰጠንን ጸጋ ማወቅ ብቻ ሳይሆን ማላቅ ይገባል

የነበሩ ቅርሶችን እና ሀብቶችን ይበልጥ ልቀው እና ተሻሽለው እንዲታዩ ማድረግ ያስፈልጋል

➡️ መፍጠር

ከተለመደው ባሻገር መመልከት እና ማየትም አንዱ ባህል መሆን የሚገባው ጉዳይ ነው

በተለመደው መንገድ ከተጓዝን “መፍጠር” አንዳጋች ይሆናል

➡️መፍጠን

ጊዜ የለንም ብለን የምንሮጥ፣ ጠንክረን የምንሰራ በውጤት የምናምን፣ ጀምረን የምጨርስ፣ ተናግረን የምንፈጽም መሆን ይኖርብናል

➡️ማስተሳሰር

ህዝብን፣ ሀሳብን እና ውጤትን ማስተሳሰር ባህል መሆን አለበት።

"ብልፅግና አልቆ መገንባትን አስቀድሞ የሚያስብ ፓርቲ ነው"- የብልጽግና ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)   ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  23/2017 አ.ም) ብልፅግና ፓ...
31/01/2025

"ብልፅግና አልቆ መገንባትን አስቀድሞ የሚያስብ ፓርቲ ነው"- የብልጽግና ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 23/2017 አ.ም) ብልፅግና ፓርቲ ሊያፈርስ የሚፈልገውን ብቻ ማፍረስ ሳይሆን አልቆ መገንባትንም አስቀድሞ የሚያስብ ፓርቲ ነው ሲሉ የብልጽግና ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡

የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛው ጠቅላላ ጉባኤ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ይገኛል።

የፓርቲው ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ብልፅግና ሊያፈርስ የሚፈልገው በርካታ ኋላቀር አሰራሮች እና ልምምዶች ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳሉ ቢያውቅም አልቆ መገንባትን አስቀድሞ የሚያስብ ፓርቲ ነው ብለዋል፡፡

ለዚህም ነው "ፒያሳን ማፍረስ ሳይሆን አልቆ መገንባት የብልፅግና መለያው የሆነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ የፓርቲ ፖለቲካ ታሪክ 60 ዓመታትን ያልተሻገረ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በእነዚህ ዓመታት የነበረን የፓርቲ ፖለቲካ ልምምድ የምንፈልገውን ለውጥ ማመላከት ላይ ውስንነት የነበረበት ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

"ኢትዮጵያ ውስጥ የፓርቲ ፖለቲካ ስንጀመር ብልፅግናን እስከፈጠርንበት ድረስ ያሉ ድካሞች ውድቀቶች ልንሻገራቸው ያልቻልናቸው አንድ ፓርቲ ለውጥ ፈጣሪ ብቻ ሳይሆን ለውጥ መሪ መሆኑን አለመገንዘባችን ነው" ብለዋል፡፡

ለውጥ መፍጠር ብቻውን ለውጥ ለመመራት የሚያስችል ብቃት እስካልፈጠረ ድረስ የተሟላ የፓርቲ ህልውና አይኖረውም ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ለውጥ መፍጠር ማለት ስላለው ችግር ድካም ውድቀት አብዝቶ መናገር ሳይሆን መፍትሄም ማፍለቅ ይጠይቃል ነው ያሉት፡፡

"ኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት ሃምሳ እና ስልሳ አመታት የነበረን የፓርቲ ፖለቲካ ልምምድ የምንጠላውን አብዝተን መውቀስ፤ ልናፈርስ ልንንድ የፈለግነውን በብዙ ማስረጃ መክሰስ እንጂ ልንገነባ የምናስበውን ልናመጣ የምንመኘውን ለውጥ ማመላከት ላይ ውስንነት ነበረብን" ብለዋል፡፡

31/01/2025

የምሽት 12 ሰዓት የአማርኛ ዜና ጥር 23/2017 ዓ.ም

ብልፅግና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የነበሩ ተቃርኖዎችን የሚያስታርቅ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል፦ አደም ፋራህጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  23/2017 አ.ም) ብልፅግና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የ...
31/01/2025

ብልፅግና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የነበሩ ተቃርኖዎችን የሚያስታርቅ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል፦ አደም ፋራህ

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 23/2017 አ.ም) ብልፅግና በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የነበሩ ተቃርኖዎችን የሚያስታርቅ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ተናግረዋል፡፡

ምክትል ፕሬዚዳንቱ ብልፅግና ሚዛናዊነትን፣ አስተሳሳሪ ትርክትን እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልፅግናን መሰረት አድርጎ የተቋቋመ ፓርቲ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ብልፅግና እውን ለማድረግም ፤ ሁሉንም ኢትዮጵያውያን ያለ ልዩነት በማቀፍ እየሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል፡፡

እውነተኛ የኅብረ ብሔራዊ ፓርቲ ሥርዓትን በመተግበርም የዜጎችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በፍትሃዊነት እና በዘላቂነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ ጉባዔ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ከተለያዩ ሀገራት የመጡ እህት ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄድ ነው።

የብልፅግና ፓርቲ ጉባዔ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት መካሄድ ጀምሯል  ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  23/2017 አ.ም) የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛውን ጉባዔ የፓርቲው ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳን...
31/01/2025

የብልፅግና ፓርቲ ጉባዔ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት መካሄድ ጀምሯል

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 23/2017 አ.ም) የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛውን ጉባዔ የፓርቲው ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንቶች በተገኙበት በአዲስ አበባ የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱን ማካሄድ ጀምሯል።

የፓርቲው ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዲሁም ምክትል ፕሬዝዳንቶች በተማሪዎች የቀረበ የስዕል አውደ ርዕይንም ጎብኝተዋል።

የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር  23/2017 አ.ም) የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት ይካሄዳል፡፡ ‘ከቃ...
31/01/2025

የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል

ጅግጅጋ ፤ ( የሶመብኤ ጥር 23/2017 አ.ም) የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት ይካሄዳል፡፡

‘ከቃል እስከ ባህል’ በሚል መሪ ሐሳብ በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ በርካታ ውሳኔዎች እና ወሳኝ አቅጣጫዎች እንደሚተላለፉ ይጠበቃል፡፡

በጉባኤው ላይ ከፓርቲው አባላት እና አመራሮች በተጨማሪ የጎረቤት እና የብሪክስ አባል ሀገራት እህት ፓርቲዎች እንደሚሳተፉም ተገልጿል፡፡

Address

Somali Region, Jigjiga City, Harar Kella.
Jijiga
SRTVAMHARICOFFICIAL

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when SRTV አማርኛ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to SRTV አማርኛ:

Share