Kaba MultiMedia - ካባ መልቲ ሚዲያ

Kaba MultiMedia - ካባ መልቲ ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Kaba MultiMedia - ካባ መልቲ ሚዲያ, Media/News Company, Jijiga.

ሊቨርፑል አይዛክን ከኒዉካስትል ማስፈረማቸዉን ይፋ አድርገዋል።
01/09/2025

ሊቨርፑል አይዛክን ከኒዉካስትል ማስፈረማቸዉን ይፋ አድርገዋል።

ድምጻዊት ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ "ሰላም ለኪ ጎንደር" በተሰኘው አዲሱ የሙዚቃ ስራዋ ላይ "ሰላም ለኪ" የሚለውን የግዕዝ ቃል መጠቀሟን ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተነሳውን ውዝግብ አስመልክ...
01/09/2025

ድምጻዊት ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ "ሰላም ለኪ ጎንደር" በተሰኘው አዲሱ የሙዚቃ ስራዋ ላይ "ሰላም ለኪ" የሚለውን የግዕዝ ቃል መጠቀሟን ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተነሳውን ውዝግብ አስመልክቶ፣ ታዋቂው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሊቅ እና ሰባኪ መምህር ዘበነ ለማ ምላሽ ሰጥተዋል።

ውዝግቡ የተቀሰቀሰው፣ "ሰላም ለኪ" የሚለው አገላለጽ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስርአት ውስጥ በተለይ ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የሚቀርብ የጸሎት መጀመሪያ ("ሰላም ለኪ ኦ ማርያም...") በመሆኑ፣ ድምጻዊቷ ለጎንደር ከተማ መጠቀሟ ተገቢ አይደለም በሚሉ አንዳንድ ወገኖች ትችት መነሳቱን ተከትሎ ነው። ይህ ድርጊት የሀይማኖታዊ ቃላትን ክብር ያጎድፋል የሚሉ አስተያየቶች በማህበራዊ ሚዲያ በስፋት ሲዘዋወሩ ነበር።

መምህር ዘበነ ለማ በሰጡት ምላሽ፣ ይህንን አስተሳሰብ በማጣጣል የቃሉን ትክክለኛ ምንነት እና አጠቃቀም አብራርተዋል።

" 'ሰላም ለኪ' ማለት የግዕዝ ቃል ነው፤ ትርጉሙም 'ሰላም ለአንቺ ይሁን' ማለት ነው" ያሉት መምህር ዘበነ፣ ቃሉ ለሴት ጾታ የሚውል ሰላምታ እንጂ፣ ለቤተክርስቲያን ብቻ ተወስኖ የተቀመጠ እንዳልሆነ አስረድተዋል።

"እኔም ራሱ 'ሰላም ለከ' (ሰላም ለአንተ ይሁን) ነው የምባለው" በማለት ለወንድ ጾታ በሚውለው አቻ ቃል ምሳሌ የሰጡት መምህሩ፣ ቃሉ በዕለት ተዕለት የሰላምታ ልውውጥ ውስጥ ጥቅም ላይ ሊውል እንደሚችል ገልጸዋል።

በመሆኑም፣ ድምጻዊት ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ ለምትወዳት እና በሴት ጾታ ለምትጠራት የጎንደር ከተማ "ሰላም ለኪ ጎንደር" በማለት ቃሉን መጠቀሟ ምንም አይነት ስህተት እንደሌለበት እና ፍጹም ተገቢ መሆኑን መምህር ዘበነ አረጋግጠዋል።

የመምህር ዘበነ ለማ ምላሽ፣ በዘመናዊ የኪነ-ጥበብ ስራዎች እና በባህላዊና ሀይማኖታዊ እሴቶች መካከል በሚፈጠሩ አለመግባባቶች ላይ ሊቃውንት የሚኖራቸውን ሚና በጉልህ ያሳየ ክስተት ሆኗል። የድምጻዊቷ አጠቃቀም፣ ለከተማዋ ያላትን ጥልቅ ፍቅር እና ክብር ለመግለጽ የተጠቀመችበት የጥበብ አገላለጽ መሆኑን የተረዱ ወገኖች፣ የመምህሩን ምላሽ በደስታ የተቀበሉት ሲሆን፣ ይህም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲካሄድ የነበረውን ውዝግብ ያረገበ ይመስላል።

ከቀናት በፊት በትራምፕ ዕጅ ላይ የታየው የህመም ምልክት ለህይወት ቆይታ የሚሰጠው ፋታ ከ 6 ወር ያልበለጠ እንደሆነ ተነግሯል!ባለሙያዎቹ እንዳሉት ይሄ በሽታ በዋነኝነት የሰውነት ሚዛንን የሚ...
01/09/2025

ከቀናት በፊት በትራምፕ ዕጅ ላይ የታየው የህመም ምልክት ለህይወት ቆይታ የሚሰጠው ፋታ ከ 6 ወር ያልበለጠ እንደሆነ ተነግሯል!

ባለሙያዎቹ እንዳሉት ይሄ በሽታ በዋነኝነት የሰውነት ሚዛንን የሚያጠፋ እና ደም ስሮችን ከጥቅም ውጪ የሚያረግ ነው ያሉ ሲሆን በህይወት የማቆያ ጊዜ ቢበዛ 6 ወር ነው

አብዛኛዎቹ የዚህ ህመም ተጠቂዎች ከ 2ቀን እሰከ 1 ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ነው ህይወታቸውን ያጡት

ታዲያ ይሄ ምልክት በትራምፕ ዕጅ ላይ በታየ በሳምንቱ የትራምፕ ደብዛ ጠፍቷል ያለፉትን ሶስት ቀናት መገኘት በነበረበት ፕሮግራሞች ላይ አልተገኘም

ሊደረጉ ተሰናድተው የነበሩ ፕሮግራሞችም ተሰርዘዋል ይህንን ተከትሎ ነው በርካታ የመገናኛ ብዙሃኖች ትራምፕ ሙቷል አልያም ህመሙ ዕረፍት አሳጥቶት ስቃይ ውስጥ ነው ሲሉ የዘገቡት

በነገራችን ላይ የኢንግሊዟ ንግስት ኤልሳቤት የዚህ በሽታ ምልክት በተመሳሳይ በዕጇ ላይ በታየ በማግስቱ ነበር ህይወቷ ያለፈው።

ሀገሪቱ እሰከአሁን በጉዳዩ ዙሪያ ዝምታን መርጠዋል🤐

ተወዳጅ ኮሜዲያን አዝመራው መሉሰውአዲስ አመት  በአዲስ ስራ መጥቷል**********አውዳመት*********
01/09/2025

ተወዳጅ ኮሜዲያን አዝመራው መሉሰው
አዲስ አመት በአዲስ ስራ መጥቷል
**********አውዳመት*********

የታላቋ ጋዜጠኛና ደራሲዋ የምወድሽ በቀለ የቀብር ሥነሥርዓት  ተፈፀመ    | የፖሊስና እርምጃው ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆና ረጅም አመታት ያገለገለችው የምወድሽ በቀለ ሥርዓተ ቀብሯ ዛሬ ነሐሴ 2...
31/08/2025

የታላቋ ጋዜጠኛና ደራሲዋ የምወድሽ በቀለ የቀብር ሥነሥርዓት ተፈፀመ

| የፖሊስና እርምጃው ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆና ረጅም አመታት ያገለገለችው የምወድሽ በቀለ ሥርዓተ ቀብሯ ዛሬ ነሐሴ 25 2017 አየር ጤና በሚገኘው ኪዳነምህረት ቤተ ክርስቲያን ተፈፅሟል።

የፌዴራል ፓሊስ አባላት በሰልፍ ታጅበው የክብር አሸኛኘት ያደረጉ ሲሆን የቅርብ ቤተሰቦች፣ ባልደረቦችና ሌሎችም በቀብሩ ላይ ተገኝተዋል።

የምወድሽ፣በድርሰትና በስነ ግጥም ስራዎቿም በርካታ አበርክቶዎች የነበሯት ነበረች። በ1979 ዓ.ም አብዮታዊ ግጥሞች ከሚለው ስራዋ ጀምሮ ወደ 16 መፃሕፍትን አሳትማለች።

የኢትዮጵያ ሴት ደራሲያት ማሕበርን በፕሬዘደንትነት ዘለግ ላሉ ዓመታት መርታለች።

የኢትዮጵያ ሴቶች ማሕበራት የቦርድ ሰብሳሰቢም ሆና አገልግላለች።

ሴቶች ይችላሉ Women can do it የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ነበረች።

እጅግ በርካታ የበጎ ስራ ማሕበራት ውስጥ መስራችና አመራር ሆና ስታገለግል ኖራለች።

በሴቶች፣ በሕፃናት እና ማሕበረሰብ አቀፍ የበጎ ስራዎች ላይ ከፊት ተሰልፋ ሙሉ ጊዜዋን ስትሰራ ቆይታለች።

በአሐዱ ሬዲዮ ላይ ከምወድሽ ገፆች የተሰኘ በሴቶች ላይ ያተኮረ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ ነበረች።

በአሻም ቴሌቪዥን የሚተላለፍም የምወድሽ ገፃች አዘጋጅ ናት።

በሕይወት ዘመኗ በርካታ ሽልማቶችንም ባበረከተቻቸው አስተዋፅኦዎች አግኝታለች። የ2016 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማትን ጨምሮ ሌሎችንም አግኝታለች።

ነሐሴ 19 ቀን 1952 ዓ.ም አዲስ አበባ የተወለደችው የምወድሽ በቀለ የአራት ልጆች እናትና የ5 የልጅ ልጆች አያት ነበረች።

የብዙ አቅመ ደካሞች ጧሪ እና ደጋፊ የነበረችው ደራሲዋ ጋዜጠኛዋ የምወድሽ በቀለ ለአጭር ጊዜ ባጋጠማት ሕመም በሕክምና ስትረዳ ቆይታ ነሐሴ 23 ቀን ሌሊት አርፋለች።

" እናንተ ያገሬ ልጆች" ልደት 🧁🍰🎂49 ዛሬ የተወዳጁ እውቁ ጋዜጠኛ የጌጡ ተመስገን 49 ዓመት ልደቱ ነው በዛ በሚያምር ድምፅ በETV ብዙ አሰደሳች ፕሮግራሞች ያቀርብልን የነበረው ጌጡ ተመ...
30/08/2025

" እናንተ ያገሬ ልጆች"

ልደት 🧁🍰🎂

49

ዛሬ የተወዳጁ እውቁ ጋዜጠኛ
የጌጡ ተመስገን 49 ዓመት ልደቱ ነው

በዛ በሚያምር ድምፅ በETV ብዙ አሰደሳች ፕሮግራሞች ያቀርብልን የነበረው ጌጡ ተመሰግን እንኳን ተወለድክ መልካም ልደት

እረጅም እድሜ ከጤና ጋር ይስጥልን

🧁🍰 🎂

🌴🌴🌴

 #ተወልዶ ያደገው ፈረንሳይ ለጋሲዮን ነው። ዲያቆን ነው። ዶክተር ነው፤ የዓይን ሐኪም። ጎንደር ዩኒቨርስቲ እያከመ ያስተምር ነበር፦ ለሁለት ዓመት። ...ከዚያ ወደ አዲስ አበባ መጣ፤ በአውሮ...
30/08/2025

#ተወልዶ ያደገው ፈረንሳይ ለጋሲዮን ነው። ዲያቆን ነው። ዶክተር ነው፤ የዓይን ሐኪም። ጎንደር ዩኒቨርስቲ እያከመ ያስተምር ነበር፦ ለሁለት ዓመት። ...ከዚያ ወደ አዲስ አበባ መጣ፤ በአውሮፕላን አብራሪነት ተመረቀ። አሁን ረዳት ፓይለት ነው።

#ይህ ወጣት ናትናኤል ስንታየሁ ይባላል። ዲያቆን፣ ዶክተር፣ ፓይለት ናትናኤል ስለ ልጅነቱ እንዲህ ይናገራል ።

"ከትንሽነቴ ጀምሮ ሶስቱንም መሆን እመኝ ነበር፤ ዲያቆን፣ ዶክተር እና ፓይለት። ከትምህርት ጊዜዬ ውጪ ውሎዬ እዛው ስለሆነ፣ የፈረንሳይ ለጋሲዮን ገነተ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ዲያቆን ሆንኩ። እናቴ ጤና ጣቢያ ነው የምትሰራው፤ እዚያ ሥራ ቦታዋ ይዛኝ ትሄድ ነበር። ሐኪሞቹን እያየሁ እነሱን መሆን ተመኘሁ። አባቴ ደግሞ ሁሌም የአየር መንገድን ሠላምታ መፅሔት ይዞ ይመጣል። እሱን እያየሁ፤ እያነበብኩ፣ ፓይለት መሆን ተመኘሁ። ፓይለት ሆንኩ፦ አሁን ረዳት አብራሪ ነኝ።...."

ለዲያቆን ዶክተር ፓይለት ናትናኤል መልካም እድል ተመኙለት

    አንጋፋዋ ጋዜጠኛና ደራሲ የምወድሽ በቀለ ከእዚህ ዓለም በሞት ተለየች:: የብዙ አቅመ ደካሞች ጧሪ እና ደጋፊ የነበረችው ደራሲና ጋዜጠኛ የምወድሽ በቀለ ለአጭር ጊዜ ባጋጠማት ሕመም በሕ...
30/08/2025



አንጋፋዋ ጋዜጠኛና ደራሲ የምወድሽ በቀለ ከእዚህ ዓለም በሞት ተለየች:: የብዙ አቅመ ደካሞች ጧሪ እና ደጋፊ የነበረችው ደራሲና ጋዜጠኛ የምወድሽ በቀለ ለአጭር ጊዜ ባጋጠማት ሕመም በሕክምና ስትረዳ ቆይታ ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ሌሊት አርፋለች።

የምወድሽ በቀለ የፖሊስና እርምጃው ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆና ረጅም ዓመታት አገልግላለች።

በድርሰትና በስነ ግጥም ስራዎቿም በርካታ አበርክቶዎች የነበሯት ነበረች። በ1979 ዓ.ም አብዮታዊ ግጥሞች ከሚለው ስራዋ ጀምሮ ወደ 16 መፃሕፍትን አሳትማለች።

የኢትዮጵያ ሴት ደራሲያት ማሕበርን በፕሬዘደንትነት ዘለግ ላሉ አመታት የመራች ሲሆን የኢትዮጵያ ሴቶች ማሕበራት የቦርድ ሰብሳሰቢ ሆና አገልግላለች።

ሴቶች ይችላሉ Women can do it የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ነበረች።

እጅግ በርካታ የበጎ ስራ ማሕበራት ውስጥ መስራችና አመራር ሆና ስታገለግል ኖራለች።

በሴቶች፣ በሕፃናት እና ማሕበረሰብ አቀፍ የበጎ ስራዎች ላይ ከፊት ተሰልፋ ሙሉ ጊዜዋን ስትሰራ ቆይታለች።

በአሐዱ ሬዲዮ ላይ ከምወድሽ ገፆች የተሰኘ በሴቶች ላይ ያተኮረ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ ነበረች።

በአሻም ቴሌቪዥን የሚተላለፍም የምወድሽ ገፃች አዘጋጅ የነበረችው የምወድሽ በሕይወት ዘመኗ በርካታ ሽልማቶችንም ባበረከተቻቸው አስተዋፅኦዎች አግኝታለች። የ2016 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማትን ጨምሮ ሌሎችንም አግኝታለች።

ነሐሴ 19 ቀን 1951 ዓ.ም አዲስ አበባ የተወለደችው የምወድሽ በቀለ የአራት ልጆች እናትና የ5 የልጅ ልጆች አያት ነበረች።

ምንጭ:- ጋዜጠኛ እዝራ እጅጉ
ዳጉ_ጆርናል

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

ብሩክ ኒውስ የዎርልድ ሊንክ ኮሌጅ ብራንድ አምባሳደር በመሆን ስምምነት ፈጽሟል። ለዚህም 3 ሚሊዮን ብር ተከፍሎታል።
29/08/2025

ብሩክ ኒውስ የዎርልድ ሊንክ ኮሌጅ ብራንድ አምባሳደር በመሆን ስምምነት ፈጽሟል። ለዚህም 3 ሚሊዮን ብር ተከፍሎታል።

ሰበር ዜና !  የአዲስ አበባ ስታዲየም በሚቀጥለው አመት የፕሪሚየር ሊግ እግር ኳስ ውድድር በደጋፊ ታጅቦ እንዲያስተናግድ ዛሬ በአዲስ አበባ ከንቲባ ቢሮ ተወስኗል ። ዛሬ ክብርት ወ/ሮ አዳነ...
29/08/2025

ሰበር ዜና !

የአዲስ አበባ ስታዲየም በሚቀጥለው አመት የፕሪሚየር ሊግ እግር ኳስ ውድድር በደጋፊ ታጅቦ እንዲያስተናግድ ዛሬ በአዲስ አበባ ከንቲባ ቢሮ ተወስኗል ።

ዛሬ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አበቤ በተገኙበት ፣የክለብ አመራሮች ፣የስፖርት ኮሚሽን ሰዎች ፣የፀጥታ ሀይል አዛዦች በተገኙበት ሰፊ ውይይት ተደርጎ ውሳኔው መወሰኑን አውቄአለው።

ታሪካዊው የአዲስ አበባ ስታዲየም እንደቀድሞ ደምቆ በደጋፊ ታጅቦ ውድድር በሚቀጥለው አመት ይደረግበታል።

ለስፖርት አፍቃሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ!
Zelalem (ባላገሩ ቲቪ)

በቁጥጥር ሥር ውለዋል::የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ፣ ኢሰብዓዊ ድርጊት ፈጽመዋል የተባሉ ሁለት የፖሊስ አባላትን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።የልደታ ክፍለ...
29/08/2025

በቁጥጥር ሥር ውለዋል::

የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ፣ ኢሰብዓዊ ድርጊት ፈጽመዋል የተባሉ ሁለት የፖሊስ አባላትን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።

የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ አባላት የሆኑት ምክትል ሳጅን አሸብር ግምጃው እና ረዳት ሳጅን ናትናኤል በላይ በቁጥጥር ስር የዋሉት፣ የሙያ ኃላፊነታቸውን ጥሰው ኢሰብዓዊ ድርጊት ፈጽመዋል በሚል ነው።

ክስተቱ እንዴት ተፈጠረ?

ነሐሴ 21 ቀን 2017 ዓ/ም፣ በባልቻ ትምህርት ቤት አካባቢ ጫት ሲቅሙ እና አደንዛዥ ዕፅ ሲጠቀሙ የነበሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የሞከሩት እነዚህ ፖሊሶች፣ ከአንድ ተጠርጣሪ ጋር በተፈጠረው ግጭት ችግር ፈጥረዋል። ተጠርጣሪው አብስራ ሳሙኤል ሲሮጥ በያዙት ጊዜ፣ ከመሬት እየጎተቱ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሊወስዱት መሞከራቸው ነው የተገለጸው።

ይህ ድርጊት ከሙያዊ ኃላፊነት ያፈነገጠ እና የሰብአዊ መብት ጥበቃ መርሆችን ያልተከተለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አረጋግጧል።

ሁለቱ ፖሊሶች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው ሲሆን፣ ፖሊስ የሕዝብን መብት በሚያከብር መልኩ ሥራውን እንዲያከናውን ትእዛዝ ሰጥቷል።

በተጨማሪም፣ በሥነ-ምግባር ጉድለት ላይ
የሚወሰደው እርምጃ እንደሚቀጥልም አስታውቋል።

Via AAP

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

ድምፀ መረዋ ድምፃዊት ትዕግስት በቀለ በጣሊያን ከ20 ዓመት በኋላ ወደ ሀገሯ ገብታለች ቲጂን እንኳን ደህና መጣሽ በሏት 🙏
29/08/2025

ድምፀ መረዋ ድምፃዊት ትዕግስት በቀለ በጣሊያን ከ20 ዓመት በኋላ ወደ ሀገሯ ገብታለች

ቲጂን እንኳን ደህና መጣሽ በሏት 🙏

Address

Jijiga
1234

Telephone

+251909042930

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kaba MultiMedia - ካባ መልቲ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share