26/09/2025
የቅዱሳን ስዕላትን በመቅደድ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ስታሰራጭ የነበረችውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
***
ቤተልሄም ሚሊዮን ሳህሉ ሠሞኑን የቅዱሳን ስዕላት በመቅደድ በማህበራዊ ሚዲያ ማሰራጨቷ ይታወቃል፡፡ ኃይማኖትን ማንቋሸሽ እና ማዋረድ ተገቢነት የሌለው እና በህግ የሚያስጠይቅ ህገ-ወጥ ተግባር በመሆኑ ፖሊስ ግለሰቧን በፈፀመችው ድርጊት መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡