Belachew Belay-በላቸው በላይ

Belachew Belay-በላቸው በላይ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Belachew Belay-በላቸው በላይ, Bonga, Bonga.
(1)

Journalist
----------------
መረጃ/ መዝናኛ / ዜና እና ማስታወቂያ
----------------------------------------------------
👉❤️


👉 This is the official Belachew Belay (Be Be) page

ከ56  ሺህ ቶን በላይ የቅመማ ቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል - ክልሉ   በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በዘንድሮው ዓመት  ከ56  ሺህ ቶን በላይ የቅመማ ቅመም ምርት ለማዕ...
18/08/2025

ከ56 ሺህ ቶን በላይ የቅመማ ቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል - ክልሉ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በዘንድሮው ዓመት ከ56 ሺህ ቶን በላይ የቅመማ ቅመም ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በዚሁ ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

በክልሉ የቅመማ ቅመም ሰብሎች በስፋት ከሚመረትባቸው አካባቢዎች አንዱ የሸካ ዞን ነው።

በዞኑ የኪ ወረዳ ህብረት ፍሬ ቀበሌ ከ400 ሄክታር በላይ በሆነ ማሳ ላይ እርድ እየተመረተ ይገኛል።

በቀበሌው "ይቢ" ተብሎ በሚጠራው መንደር የሚገኙ 63 አርሶአደሮች ምርቱን በኩታ ገጠም የእርሻ ዘዴ በማልማት ተጠቃሚ በመሆን ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

አርሶ አደሮቹ ለማሳቸው የሚያደርጉት እንክብካቤ እና የሚጠቀሙት ተፈጥሯዊ ማዳበሪያ ለምርታማነቱ አይነተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

በየዓመቱ እየጨመረ የመጣውን የቅመማ ቅመም ምርት እሴት ጨምረው ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ወጪ እና ጊዜ ቆጣቢ ማሽኖች እንደሚያስፈልጉ አስረድተዋል።

የሸካ ዞን ግብርና ፣ አካባቢ ጥበቃ እና ህብረት ሥራ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አዕምሮ ደሣለኝ ከአርሶ አደሮቹ የቀረበው ጥያቄ ተገቢ መሆኑን በመግለጽ ምላሽ ለመስጠት ከሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በክልሉ ከ56 ሺህ ቶን በላይ የተለያዩ የቅመማ ቅመም ምርቶች ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን ለኢቢሲ ተናግረዋል።

የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማጎልበት ለዘርፉ ሥራ ትኩረት ተሰጥቶ እየተከናወነ እንደሚገኝም ተመልክቷል።

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለአማራ ብሄራዊ ክልል ግብርና ቢሮ በተመጣጣኝ ዋጋ ከ4000 በላይ የቡና ችግኞችን አበረከተ።  ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በቅጥር ጊቢው የለሙ የተለያየ ዝርያ ያላቸውን የቡና ችግኞች ...
18/08/2025

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ለአማራ ብሄራዊ ክልል ግብርና ቢሮ በተመጣጣኝ ዋጋ ከ4000 በላይ የቡና ችግኞችን አበረከተ።

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በቅጥር ጊቢው የለሙ የተለያየ ዝርያ ያላቸውን የቡና ችግኞች በማፍላት የዘንድሮውን አረንጓዴ አሻራ እያሳካ መሆኑ ይታወቃል።

የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮም የሀገር- ዓቀፉን አረንጓዴ አሻራ መርሀ -ግብር የበለጠ ለማሳካት ከ4000 በላይ የቡና ችግኞችን ተረክቧል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቡና በክልሉ እየለማ ሲሆን ይህንኑ ተግባር ማስፋት አላማው ያደረገ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የተሻሻሉ የቡና ዝርያ ችግኞችን ተረክቧል።

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ሌሎችም የቡና ችግኝ መግዛት የሚፈልጉ አካላት የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሲጋብዝ ሀገራችን በተለይ አረንጓዴ ወርቃችንን የበለጠ በሁሉም አካባቢ ተደራሽ የማድረግ ዓላማን በማንገብ ነው።

ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ    ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡ የፌደ...
18/08/2025

ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ

ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ፤ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው ብሏል፡፡

በዚህም ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት መወሰኑን አስታውቋል፡፡

በማሻሻያው ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4 ሺህ 760 ወደ ብር 6 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ነው ያለው።

ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21 ሺህ 492 ወደ ብር 39 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ብሏል።

የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6 ሺህ 940 ወደ ብር 11 ሺህ 500 የሚሻሻል መሆኑን ገልጿል።

ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ እንደሚደረግበት አስታውቋል ሲል ፋና ሚዲያ ዘግቧል።

ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል ያለው ኮሚሽኑ፤ ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል ብሏል።

አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ   አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡አርቲስት ደበበ እሸቱ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ...
17/08/2025

አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

አርቲስት ደበበ እሸቱ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ ነብዩ ባዬ (ረ/ፕ) ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

አርቲስት ደበበ እሸቱ በኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ዘርፍ የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን÷ በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በፊልም እና በጋዜጠኝነት ሙያ በርካታ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አቅርቧል፡፡

ተዋናይ፣ ኮሜዲያን እና አዘጋጅ ሆኖ ለረጅም ዓመታት ያገለገለው አርቲስቱ ÷ በቴአትር መድረኮች በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የሆኑ ሥራዎችን በማቅረብ ይታወቃል፡፡

አርቲስት ደበበ በሀገር ፍቅርና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ (በአሁኑ ብሔራዊ ቴአትር) መድረክ ላይ ለረዥም ዓመታት በተዋናይነትና በአዘጋጅነት አገልግሏል።

አርቲስት ደበበ መጀመሪያ በቴአትር መድረክ የታዩት በመንግስቱ ለማ ያላቻ ጋብቻ ሲሆን÷ በመቀጠልም በሬዲዮ እና ቴሌቪዥን የተለያዩ ሥራዎችን አቅርበዋል፡፡

አርቲስቱ ከተሳተፈባቸው ሥራዎች መካከል ያላቻ ጋብቻ፣ ሮሚዮና ዡልየት፣ ጠልፎ በኪሴ፣ዳንዴው ጨቡዴ ፣ዘ ጌም ኦፍ ቼዝ፣ ኦቴሎ፣ አንድ ዓመት ከአንድ ቀን፣ እናት ዓለም ጠኑ፣ በቀይካባ ስውር ደባ፣ የአዛውንቶች ክበብ፣ የወፍ ጎጆ ፣ የቬኒሱ ነጋዴ ፣ ማዕበል እና ሌሎች ይገኙበታል፡፡

በተለያዩ ታሪካዊና አዝናኝ ፊልሞች እንዲሁም የቴአትር ሥራዎች አድናቆት የተቸረው አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ÷ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም የክብር ዶክትሬት ተሰጥቶታል፡፡

አርቲስቱ ሀገር ችግር ውስጥ በምትሆንበት ጊዜ ከፊት በመቆም በርካታ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን÷በበጎ ፈቃድ ሥራዎችም ግንባር ቀደም ነበር፡፡

ይገምቱ ይሸለሙ  ማንቼስተር ዩናይትድ ከአርሰናል ...የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዲሱ የውድድር ዘመን ገና በመጀመሪያው ሳምንት ሁለቱን የምንጊዜም ተቀናቃኞች ማንቼስተር ዩናይትድ እና አርሰናል...
17/08/2025

ይገምቱ ይሸለሙ

ማንቼስተር ዩናይትድ ከአርሰናል ...

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዲሱ የውድድር ዘመን ገና በመጀመሪያው ሳምንት ሁለቱን የምንጊዜም ተቀናቃኞች ማንቼስተር ዩናይትድ እና አርሰናል አገናኝቷል፡፡

ዛሬ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 የሚደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በበርካታ የስፖርት ቤተሰቦች ዘንድ ተጠባቂ ሆኗል።

የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ የጨዋታ ግምታቸው ለተሳካ የመጀመሪያዎቹን ሶስት ገማቾችን የሞባይል ካርድ ይሸልማል።

ገፃችንን Follow, Like, Share በማድረግ ወዳጅ ይሁኑ

17/08/2025

ዳኞችን ያስለቀሰው የመድረክ ስራ /ሙዚቃ /live
🥰🥰🥰😭😭😭😭😭😭😭🥰🥰

ምክር ቤቱ የተለያዩ ሹመቶችን  አፀደቀ  አዲዮ ወረዳ ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት 28ኛ መደበኛ ጉባኤ በወረዳው ምክትል ዋና አስተዳዳሪ በአቶ ገሬመው ገብሬ አቅራቢነት በተለያዩ...
17/08/2025

ምክር ቤቱ የተለያዩ ሹመቶችን አፀደቀ

አዲዮ ወረዳ ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት 28ኛ መደበኛ ጉባኤ በወረዳው ምክትል ዋና አስተዳዳሪ በአቶ ገሬመው ገብሬ አቅራቢነት በተለያዩ ቦታዎች የአመራር ሹመት ተቀብሎ በማፅደቅ ተጠናቅቋል።

በዚህ መሰረት
1. ወ/ሮ ባንቻየሁ አጎናፍር - የወረዳው ሴቶች ህፃናት ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ፣

2. አቶ አሸብር ገባቦ- የወረዳው ባህል ቱርዝም ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ፣

3.አቶ ዓለሙ አሰፋ - የወረዳው ኢንዱስትሪና ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ፣

4.ወ/ሮ እታለም ግርማ -የአዲዮ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ

5.ወጣት ተካልኝ ቦጋለ የወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ፣

6.አቶ በረከት ባህሩ -የአዲዮ ወረዳ ሴቶች ህፃናት ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ፣

6.አቶ አስራት ታደሰ የአዲዮ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ በመሆን በምክር ቤት ቀርበው ቃለ-መሃላ መፈፀማቸዉን የዘገበው የወረዳው የመንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

በሞጆ-ባቱ መንገድ ላይ ሁለት ዲያቆናት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን አጡ   || ዛሬ ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም ጠዋት፣ ከአዳማ ወደ ባቱ ሲጓዝ በነበረ የመኪና አደጋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋ...
16/08/2025

በሞጆ-ባቱ መንገድ ላይ ሁለት ዲያቆናት በትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን አጡ

|| ዛሬ ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም ጠዋት፣ ከአዳማ ወደ ባቱ ሲጓዝ በነበረ የመኪና አደጋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የአዳማ ደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሁለት አገልጋዮች ህይወታቸውን ማጣታቸው ተዘግቧል።

አደጋው የደረሰበት ኮድ2 23313 አ/አ ፒክአፕ መኪና፣ ሁለት የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ጭኖ ከሚጓዝበት ሞጆ-ባቱ ፍጥነት መንገድ ላይ ነው። አደጋው የደረሰው ባቱ ከተማ ለመድረስ 2 ኪሎ ሜትር ሲቀረው መሆኑ ተነግሯል::

በዚህ አደጋ ዲያቆን ሰዩም ተ/ዮሐንስ (የካቴድራሉ የሂሳብ ሹም) እና ዲያቆን ቴድሮስ በጋሻው (የጠቅላላ አገልግሎት ክፍል ኃላፊ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ለ2018 የካፈቾ ዘመን መለወጫ (ማሽቃሮ) በዓል ዝግጅት  በካፋ ዞን የ2018 ዓ.ም. የካፈቾ ዘመን መለወጫ (ማሽቃሮ) በዓል በባህላዊ አልባሳት ደምቆ እንዲከበር የተለያዩ የልብስ ስፌት ማህ...
16/08/2025

ለ2018 የካፈቾ ዘመን መለወጫ (ማሽቃሮ) በዓል ዝግጅት

በካፋ ዞን የ2018 ዓ.ም. የካፈቾ ዘመን መለወጫ (ማሽቃሮ) በዓል በባህላዊ አልባሳት ደምቆ እንዲከበር የተለያዩ የልብስ ስፌት ማህበራት ሰፊ ዝግጅት እያደረጉ ነው።

በዞኑ የሚገኙ እንደ ድንጉዛ፣ነና ቱነባ፣ወገን እና ቢናቢና ያሉ የባህል ልብስ ስፌት ማህበራት፣ በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ የአዋቂና የህፃናት አልባሳትን በተመጣጣኝ ዋጋና ጥራት እያዘጋጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተለይ ከአስራ ሁለት ዓመታት በላይ ያስቆጠረው አንጋፋው ድንጉዛ የባህል ልብስ ስፌት ማህበር፣ ከአዋቂ እስከ ህፃናት ያሉ አልባሳትን ከማቅረብ ባለፈ የሽመና ስራዎችን እንደሚሰሩና ወደፊትም የስልጠና ማዕከል ለመክፈት ማቀዳቸውን የማህበሩ ሰብሳቢ ተናግረዋል።

ማህበራቱ የሁሉንም የመግዛት አቅም ባገናዘበ መልኩ አልባሳትን በማቅረብ ሁሉም ሰው በባህል ልብስ እንዲያከብር እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል። ለስራቸው መስፋፋትም ከሚመለከታቸው አካላት የመስሪያ ቦታ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል።

የካፋ ዞን ኢንዱስትሪ እና ኢኖቨሽን መምሪያ በበኩሉ፣ በዓሉ በድምቀት እንዲከበር ለማህበራቱ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጿል።

በመጨረሻም ማህበራቱ ለመላው የካፈቾ ብሄር ተወላጆችና ወዳጆች "እንኳን አደረሳችሁ" መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። መረጃዉ የዞኑ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ።

ለቤተሰቡና ለ6 ወጣቶች የስራ እድል የፈጠረዉ ረዳት ኢንስፔክተር ደረጀ መንገሻ  ረዳት ኢንስፔክተር ደረጀ መንገሻ ይባላል በካፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ በአመራርነት ስራ ላይ ተመድቦ ፖሊሳዊ ስራዎ...
16/08/2025

ለቤተሰቡና ለ6 ወጣቶች የስራ እድል የፈጠረዉ ረዳት ኢንስፔክተር ደረጀ መንገሻ

ረዳት ኢንስፔክተር ደረጀ መንገሻ ይባላል በካፋ ዞን ፖሊስ መምሪያ በአመራርነት ስራ ላይ ተመድቦ ፖሊሳዊ ስራዎቹን ያከናውናል፡፡

ከመደበኛ ወንጀል መከላከል ስራው በተጨማሪ ደረጀ መንገሻ ለቤተሰቡ እና ለ6 ወጣቶች የስራ እድል ፈጥሯል፡፡

የፖሊስ አባሉ በቦንጋ ከተማ የወተት እጥረት መኖሩን ይገነዘብና ባለቤቱ በመኖሪያ ቤቱ ስራ እየሰራች በገቢ እንድታግዘው በከተማ የከብት እርባታ ለመጀመር ያማክራታል እሷም በሀሳቡ ተስማምታ ስራውን ይጀምራሉ፡፡

ባለቸው ውስን ቦታ ከብት በመግዛት ስራውን ጀምረው ለባለቤቱ ስራን የፈጠረው ረዳት ኢንስፔክተር ደረጀ ከአመት በኃላ አጋዥ በማስፈለጉ 6 ወጣቶች የስራ እድል እንዲኖራቸው አድርገዋል፡፡

ቦንጋ ኮሌጅ ቀጠና ርብቃ ንፁህ የላም ወተት ለአከባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ከማበርከትም አልፎ ለወጣቶች ስራ ዕድል በመፍጠር ተሞክሮ ሊሆን የሚችለውን የፖሊስ ባልደረባ ነው፡፡

ለልጆጃቸዉ ወተት የሚገዙ ግለሰቦችን አነጋግረን ደረጀና ቤተሰቡ የሚያቀርቡት ወተት ንፁህ መሆኑን ተናግረዋል።

ይሁንና ይበልጥ ለመስራት እሱና ቤተሰቡ እቅድ ቢኖራቸውም ለከብቶቹ መኖ ሳር መትከያ ቦታ አለሞር፤የቦታ ጥበት ፈተና መሆኑን ነው የገለፀው ደረጀ የሚመለከተው አካል ድጋፍ ያድርግልኝ ብሏል፡፡(ደ አ )

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የካቢኔ አባላትን ሹመት አፀደቀ  በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ  አቶ አስማማው አደመ አቅራቢነት የካቢኔ አባላቱን ሹመት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ አፅድቋ...
16/08/2025

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የካቢኔ አባላትን ሹመት አፀደቀ

በቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አስማማው አደመ አቅራቢነት የካቢኔ አባላቱን ሹመት ምክር ቤቱ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል::

በዚህም መሠረት:-

1. አቶ አለማየሁ አባተ - የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካ እና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ፣

2. ወ/ሮ ቅድስት ፍቃዱ- ባህል ቱሪዝም እና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል፡፡

የቀይ ሽንኩርት ገበያ በካፋ ዞን ዴቻ ወረዳ ቦባ ገጫ ታዳጊ ማዘጋጃ ከተማ ምንጭ :- ዴቻ  ወረዳ የመንግሥት ኮ/ጉዳዮች
16/08/2025

የቀይ ሽንኩርት ገበያ በካፋ ዞን ዴቻ ወረዳ ቦባ ገጫ ታዳጊ ማዘጋጃ ከተማ

ምንጭ :- ዴቻ ወረዳ የመንግሥት ኮ/ጉዳዮች

Address

Bonga
Bonga

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Belachew Belay-በላቸው በላይ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Belachew Belay-በላቸው በላይ:

Share