ኢትዮጵያ Ethiopia

  • Home
  • ኢትዮጵያ Ethiopia

ኢትዮጵያ Ethiopia ትኩስ ዜናዎችን አስተማሪና አዝናኝ መረጃዎችን እናደርሳለን ! (Ethiopia )

‎‎‎በጣም ተዋደው እና ተፋቅረው የሚኖሩ ባልና ሚስት አንድ  ቀን ምሸት ላይ አለመግባባት ተፈጠረ ና ሚስቱን በጣም ደበደባት እና እያለቀሰች ጥሏት ከልጆች መኝታ ቤት ሂዶ ከልጆችጋ ተኛ  እሷ...
30/06/2025



‎በጣም ተዋደው እና ተፋቅረው የሚኖሩ ባልና ሚስት አንድ ቀን ምሸት ላይ አለመግባባት ተፈጠረ ና ሚስቱን በጣም ደበደባት እና እያለቀሰች ጥሏት ከልጆች መኝታ ቤት ሂዶ ከልጆችጋ ተኛ እሷም ማልቀሱን ተወችና ቆም.ብላ ማሰብ ጀመረች

‎ሀሳቧም ፦ልጆች በህፃንነት ህሊናቸው ጥሩና ተገቢ ያልሆነ ስነ ምግባር ማየትና መስማት እደሌለባቸውና ኩርፌዋን ብትቀጥል መጨረሻው እደሚከፋባቸው እና ፍቅራቸውም እደሚቀንስ ነበር።
‎ከዛም እምባዋን ጠራርጋ ባሏና ልጆቿ ከተኙበት በመሄድ ቀስ ብላ ባሏን ጥምጥም አድርጋ አቅፋው ተኛች እሱም ከእንቅልፉ ሲነቃ ጭራሽ ያላሰበው ና ያልጠበቀውን ነገር በተመለከተ ጊዜ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ እሷም ከእንቅልፏ ነቃች ና ለምን ታለቅሳለህ ብላ ጠየቀችው ምንም መልስ አልሰጣትም እሷም ፈገግ በማለት እሰይ እዳስለቀስከኝ አስለቀስኩህ እያለች ሳም አደረገችው እሱም በሁኔታዋ በመደሰት እቅፍ አድርጎ ሳማትና በሳቅ ወደቁ ልጆችም በሳቁ ድምቀት ነቁና ሳቁ

‎እሳት በውሀ እደሚጠፋ ሁሉ ጥላቻንም ፍቅር ያጠፋዋል ።
‎ "ፍቅር ያሸንፋል"

‎ብልህ እና አስተዋይ ሚስት ይስጣችሁ።
‎ባሎችም ትዕግስት ና ፀባይ ይኑራችሁ።

‎ምንጭ ከወሬ ፏፏቴ!!
‎መልካም ግዜ

ሴትን ልጅ በድለሀት እንድታለቅስብህ አታድርግ።የማንባቷ መንስኤ በፍፁም አትሁን።የሴት ልጅ እምባ ሲያዩት ቅጠል ላይ እንደሚንኳለል ውሀ ውበት ቢኖረውም አንድ ቀን ጠራርጎ የሚወስድህ ማእበል ሊ...
29/06/2025

ሴትን ልጅ በድለሀት እንድታለቅስብህ አታድርግ።

የማንባቷ መንስኤ በፍፁም አትሁን።
የሴት ልጅ እምባ ሲያዩት ቅጠል ላይ እንደሚንኳለል ውሀ ውበት ቢኖረውም አንድ ቀን ጠራርጎ የሚወስድህ ማእበል ሊሆን ይችላል።

ሴት ልጅ የአለም ጣእም ናት ስልህ ከመሬት ተነስቼ አይደለም እንደ አንበሳ ክንድ በጠነከረ ምክንያት ላይ ቆሜ እንጂ።

የትም ቦታ ሳቅ የትም ቦታ ደስታ የትም ቦታ ምቾትን መፍጠር ታውቅበታለች።

ፈሪን ታጀግናለች ቆራጥ ጀግኒት ሆና ቤተሰብህን እና ሀገር ትጠብቃለች።

ሴት ማለት በመስዋእትና በፍቅር የተሞላች ፍጥረት ነች።

ሴትን ልጅ በፍቅር ከተመለከትካት ንፁ ፍቅርን ከሰጠሀት በ10 እጥፍ አድርጋ ትመልስልሀለች።

ሴት ልጅ አንተ ትንሽ ነገር ሰጥተሀት እሷ ግን ልጅን የሚያክል በረከት ትሰጥሀለች።

ሴት ልጅ እናት ፡ እህት ፡ ሚስትህ ናትና ውደዳት አክብራት ተንከባከባት።

ክብር ፡ ፍቅር እና እውቅና ለሴቶች።

ሼርርርር

ገላዋ ልስልስ ያለ ነው:: ከሴቶች ይበልጥ ሴትነት የሰፈረበት፤ የግብረ ስጋ መቅደስ ያቀፍኩ መሰለኝ:: ትንፋሿ አንገቴ ላይ የፍትወት ነበልባል ያቀጣጥላል፡፡ ሁለታችንም ወጣት ነን፣ ሁለታችንም...
29/06/2025

ገላዋ ልስልስ ያለ ነው:: ከሴቶች ይበልጥ ሴትነት የሰፈረበት፤ የግብረ ስጋ መቅደስ ያቀፍኩ መሰለኝ:: ትንፋሿ አንገቴ ላይ የፍትወት ነበልባል ያቀጣጥላል፡፡ ሁለታችንም ወጣት ነን፣ ሁለታችንም ሰክረናል፣ ሁለታችንም ምስጢራዊ ጭለማ ውስጥ ተደብቀናል፣ ሁለታችንም የምኞት ማእበል የሚያናውፀው ሙቀት ውስጥ ተጠቅልለናል፣ የሁለታችንም ደም ፈልቷል። እጄን ከትከሻዋ ወረድ ባደርግና የማባብላት አስመስዬ ወገቧን ጥብቅ አድርጌ ባቅፈው... እንደዚህ! — ደስ ማለቱ!, . . ቀስ አድርጌ በቸልታ እጄን ወደታች ሰደድ ባደርገውና ዳሌዋ ላይ ባሰፍረውስ?. . እንደዚህ! ከፑንቲዋ ጠርዝ ከእጄ ስር ታወቀኝ፡ ከገላዋ ሙቀት የባሰ የሙታንቲዋ ጠርዝ በምኞት ወጠረኝ፡፡ እኔ ሳላውቀው እጄ ሙታንቲዋ ውስጥ እየገባ አፌ አፏን ጎረሰው:: የት እንደሆንኩና ማን እንደሆንኩ ረሳሁ:: በመርሳቴ ደመና ላይ የባህራም ፈገግታ ብልጭ አለ።

እጄን ከሙታንታዋ እያወጣሁና አፌን ከአፏ እያላቀቅኩ፤ በሹክሹክታ

«ደግ አይደለም» አልኳት

«አዎን ደግ አይደለም» አለችኝ እሷም በሹክሹክታ

«ግን በጣም በጣም እፈልግሻለሁ፡፡ አንቺም ፈልገሽኛል፣

አይደለም?»

«አዎን›

«ምን ይሻላል?>>

«እኔ 'ንጃ»

«እኔ በበኩሌ ልተውሽ አልችልም»

ዝም

«ደሞ ልተውሽ አልፈልግም:: አንቺን መተው ራስን መኮነን ነው

ዝም

«ምን ይሻል ይመስልሻል?»

«እኔ 'ንጃ»

«ባስገድድሽስ?»

«ማስገደድ አያስፈልግህም»

«እስከ ዛሬ ድረስ ያንቺን ያህል ያማረችኝ ሴት አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ ደሞ እስከ ዛሬ ድረስ ሴት አግኝቼ ለሌላ ሰው ስል ትቼያት አላውቅም፡፡ ዛሬ ግን እንዴት ልበልሽ»

«አሁን ሁለታችንም የማናምንበት ነገር ብናደርግ በኋላ ይቆጨናል፡፡ ግን እንድትለዪኝ አልፈልግም:: ምን ይሻላል?»

«እኔ 'ንጃ:: መብራቱን አብርተን የተረፈንን ካልቫዶ እየጠጣን ብናወራስ?»

በመብራቱ ስንጠጣ ስናወራ ምን ያህል እንደቆየን አላስታውስም፡፡ እንዲያውም ከዚያ በኋላ ምን እንዳደረግን ወይም ምን እንደተባባልን የማስታውስ አይመስለኝም፡፡ ብቻ፤ ከአንድ አመት በፊት እንዳየሁት ህልም ሆኖ ትዝ የሚለኝ አንድ ነገር አለ:: ጠርሙሱ ውስጥ የቀረውን መጠጥ ከጨለጥነው በኋላ፤ ራሴን ደረቷ ላይ እያንተራስኩ

«ይሄ ጡት መያዣሽ ይቆረቁረኛል» አልኳት

«ቆይ ላውልቅልህ» ብላ አውልቃው እንደገና ራሴን ደረቷ ላይ አንተራሰችልኝ፡፡ «ጡትሽ እንደ ሞቃት ሰማይ ነው፤ ሰማዩ ላይ በፅጌረዳ ብርሀን የተከበበች ወይን ጠጅ ጨረቃ አለች» አልኳት

«ውሸታም! መቼ አየኸው?» አለችኝ

«ማየት የለብኝም»

«አሁን ዝም ብለህ ተኛ» አለችኝ

ከዚያ ወዲያ ምንም አላስታውስም በነጋታው፣ ከሰአት በኋላ ወደ ስምንት ሰአት ላይ ስነቃ፣ ኒኮል ደረቴን ተንተርሳ ተኝታለች፡፡ አፌ ውስጥ የፋንድያ ጣእም ተሰማኝ፡፡ ኒኮልን ቀሰቀስኳት

«ደህና ነሽ?» አልኳት

«ደህና»

አፈርኩ

«ሳናውቅ የማንፈልገውን ነገር ስራን 'ንዴ?» አልኳት

«የለም»

«ጎሽ»

ከስብሀት ገብረእግዚአብሔር የወሰድኩት

የአስመሳይ ጓደኞችህ ባህሪዎች‼️ ==============================1). ማታ አንተ ላይ ያሤራሉ፣ ጥዋት ደግሞ ከአንተ ጋር ይስቃሉ። በፊትህ ፈገግ ብሎ ጥሩ መስሎ ይታዩሀል ነገ...
29/06/2025

የአስመሳይ ጓደኞችህ ባህሪዎች‼️
==============================
1). ማታ አንተ ላይ ያሤራሉ፣ ጥዋት ደግሞ ከአንተ ጋር ይስቃሉ። በፊትህ ፈገግ ብሎ ጥሩ መስሎ ይታዩሀል ነገር ግን ከጀርባ ያሙሀል።

2). አንተ ስታስፈልጋቸው ይኖራሉ ፣ እነሱ በጣም ሲያስፈልጉህ ግን አታገኛቸውም፣ ራስ ወዳድ እና ጥቅመኛ ናቸው።
3). ስኬትህ ያሰጋቸዋል፣ መልካም ነገር ሲሆንልህ ይናደዳሉ።
4). በንግግራቸው ያቆስሉሃል፣ ያታልሉሃል፣ ይጎዱሃል፣ ያሳምሙሃል።
5). ሁሌ ይፎካከራ፤ እነሱ ከአንተ የተሻሉ አድርገህ እንድታስብ ያደርጉሃል ።
6). ሁሌ በደካማነት ይነቅፉሃል፣ስለህይወትህ ደካማ ጎን ብቻ አንስቶ ያወራሉ፣ ስላንተ ጠንካራ ጎን አያወሩም።

7). ስምህን ያጠፋሉ፣የምታደርጋቸውን ሁሉ ነገሮች አጠራጣሪ እንዲሆኑ ያደርጋሉ፣ ዝቅ ያደርጉሃል፣ስላንተ የውሽት ወሬ ያሰራጫሉ።
8). ወጥ የሆነ ባህሪ የላቸውም፣ እምነት አይጣልባቸውም።
9). ሲጎዱህ አይጸጸቱም፣ሁሌ ራሳቸውን ሀቀኛ አድርጎ ይፈርዱብሃል እንጂ ይቅርታ አይጠይቁም።

10). መጥፎ ነገር ሲያጋጥምህ ይደሰታሉ፣ህመምህ ያስደስታቸዋል።
11). ለስኬታቸው ምክንያት ብትሆን እንኳ ጀግና አያደርጉህም፣ ምክንያቱም ቅናት አለባቸው።

12). ምስጥርህን ስታካፍላቸው ይደሰታሉ ምክንያቱም ሊጎዱህ፣ሊከዱህ ወይም ሊያታልሉ ይጠቀሙታል።

_________________________________
ምንጭ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ የተወሰደ

ልጁ ወደ ፋርማሲ ኮንዶም ሊገዛ ይሄዳል....ልጅ፦ ኮንዶም ስጠኝ?ፋርማሲስት፦ ስንት?ልጅ፦አንድ ስጠኝ ዛሬ ፍቅረኛዬ ራት ጋብዛኛለች። ይልናገዝቶእንደወጣ...ተመልሶ ይመጣና ሌላ አንድ ስጠኝ እ...
28/06/2025

ልጁ ወደ ፋርማሲ ኮንዶም ሊገዛ ይሄዳል....
ልጅ፦ ኮንዶም ስጠኝ?
ፋርማሲስት፦ ስንት?
ልጅ፦አንድ ስጠኝ ዛሬ ፍቅረኛዬ ራት ጋብዛኛለች። ይልና
ገዝቶ
እንደወጣ...
ተመልሶ ይመጣና ሌላ አንድ ስጠኝ እህትየዋ በጣም
ፍዝዝ ብላ ስታየኝ ነበር ብሎ ገዝቶ ይወጣል:: አሁንም
አንድ ደቂቃ
ሳይቆይ ተመልሶ ይመጣና አንድ ድገመኝ ይለዋል...
ፋርማሲስቱ በመገረም ያየውና ይሄኛው ደሞ ለምንህ
ነው?
ልጁም፦ የ እናትየው አስተያየት አላማረኝም ለሊት
ካስቸገረችኝ ብዬ
ነው ብሎ ገዝቶ ይሄዳል.....
ማታ እራት የተጋበዘበት ሰአት ይደርስና ሄዶ የእራት
ጠረንጴዛው ላይ
ቀርበው አባት እስከሚመጣ እየተጠበቀ ነው የሳሎኑ በር
እንደተከፈተ
አባወራው መጣ ወዲያውም ልጁ አንገቱን ይደፋና ፀሎት
ይጀምራል
ፍቅረኛውም በፀሎቱ መርዘም ትገረምና እንደዚህ
ሀይማኖተኛ
መሆንህን ነግረከኝ አታቅም ነበር ስትለው

ልጁም እንዳቀረቀረ አንቺም አባትሽ ፋርማሲስት
መሆናቸውን ነግረሺኝ
አታቂም ነበር። መልካም ምሽት 😋

ነገሩ እንዲህ ነው ይለናል ታሪኩ ? ይነበብ አንዲት ታዳጊ ልጅ አያቷን፣"አባባ፣ በሕይወቴ ሊጠቅመኝ የሚችል ምን ነገር ልታስተምረኝ ትችላለህ?" ብላ ጠየቀችው።አያት ለረጅም ጊዜ ካሰበ በኋላ ...
26/06/2025

ነገሩ እንዲህ ነው ይለናል ታሪኩ ?
ይነበብ
አንዲት ታዳጊ ልጅ አያቷን፣
"አባባ፣ በሕይወቴ ሊጠቅመኝ የሚችል ምን ነገር ልታስተምረኝ ትችላለህ?" ብላ ጠየቀችው።
አያት ለረጅም ጊዜ ካሰበ በኋላ እንዲህ አለ፣
"ላስተምርሽ የምችለው አንድ ታላቅ የሕይወት ትምህርት ያለኝ ይመስለኛል። ነገር ግን ከዚያ በፊት፣ የሁሉንም ሰው ትኩረት የሚስብ አንድ ትልቅ ነገር ማድረግ አለብሽ።"
ልጅቷ በደስታ ስሜት፣
"ምን ዓይነት ነገር ማለት ነው አባባ?" አለችው።
አያት ለአፍታ ዝም ካለ በኋላ በፉጨት፣
"ወደ ሰፈሩ ሁሉ በመዞር፣ የእኔ ሰጎን ስድስት የወርቅ እንቁላሎችን እንደጣለች ለሁሉም ሰው ንገሪ። ይህን ሲሰሙ ሁሉም ይደነግጣሉ። ከዚያም እያንዳንዱ እንቁላል በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እንደሚያወጣና እኔም እነሱን በመሸጥ ባለብዙ ሚሊዮን እንደምሆን ንገሪያቸው። በቅርቡ ሕይወቴ ሙሉ በሙሉ እንደሚለወጥና በማኅበረሰቡ ውስጥ ካሉ እጅግ ባለጸጋዎች አንዱ እንደምሆን ለሁሉም ሰው አውሪ።"
ታዳጊዋ ልጅ የነገሩን ፍሬ ነገር ሳትረዳ እንዳላት አደረገች። ከተመለሰች በኋላ፣ እሷና አያቷ ቀኑን ሙሉ እስከ ምሽት ድረስ ቢጠብቁም፣ ነገር ግን አንድም ጎረቤት እንኳን ደስ አለህ ሊለውና ደስታውን ሊካፈለው ወደ ቤታቸው አልመጣም።
በማግስቱ ጠዋት አያት ለልጅቱ እንዲህ አላት፣
"አሁን ደግሞ ወደ ሰፈሩ ተመልሰሽ በመሄድ፣ ባለፈው ምሽት ሌባ መጥቶ ቤቴን እንዳፈረሰው፣ ሰጎኔን እንደገደለብኝና የወርቅ እንቁላሎቹንም በሙሉ እንደሰረቀብኝ ለሁሉም ሰው ንገሪ። ሁሉንም ነገር እንዳጣሁ አውሪላቸው!"
ልጅቷ ወጥታ ለጎረቤቶቿ ነገረቻቸው። በአጭር ጊዜ ውስጥ ግን እጅግ አስደንጋጭ ቁጥር ያለው ሕዝብ በቤታቸው ተሰበሰበ። ታዳጊዋ ልጅ በሁኔታው ተገርማ አያቷን ጠየቀች፣
"አባባ፣ ትናንት አንድም ሰው ሳይመጣ ዛሬ ግን ይህን ያህል ብዙ ሕዝብ እንዴት ሊመጣ ቻለ?"
አያት ፈገግ አለና እንዲህ አላት፣
"ሰዎች ስለ አንቺ ጥሩ ዜና ሲሰሙ ዝምታን ይመርጣሉ፣ ቸል ይሉታል፤ ምንም እንዳልተፈጠረም ያስመስላሉ። ስለ አንቺ መጥፎ ዜና ሲሰሙ ግን እንደ ሰደድ እሳት ያዛምቱታል፤ እውነት መሆኑን ለማረጋገጥም ይጣደፋሉ። ሰዎች ስኬትሽን ለማክበር ይከብዳቸዋል፤ ነገር ግን ውድቀትሽን ለመመልከት ይቻኮላሉ..."
በዚያች ቅጽበት አያት አንዱን እጁን በልጅቱ ትከሻ ላይ አሳርፎ፣ በድጋሚ ፈገግ አለና ቀጠለ፣
"እንግዲህ ላስተምርሽ የፈለግኩት ታላቅ የሕይወት ትምህረት ይሄ ነው... በዙሪያችን ያሉ ሰዎች የሚነግሩን ትልቁ ውሸት፣ እኛ ስናድግና ስኬታማ ስንሆን ደስ እንደሚላቸው ነው። እውነታው ግን አብዛኞቹ ሰዎች፣ የቅርብ ጓደኞችና ጎረቤቶች እንኳ ስኬታማ ስትሆኚ ማየት አይፈልጉም። አንድ ሰው አንቺ ከእሱ የበለጠ ስኬታማ እየሆንሽ እንደሆነ ሲገነዘብ፣ ይህ ነገር ለእሱ ስጋት ይሆንበታል።
አብዛኞቹ ሰዎች ከእነሱ የተሻለ ነገር የሚያደርጉ ሰዎችን ከልባቸው አይወዱም። ይቀናሉ፤ በውስጣቸውም ያንን ሕይወት ከመመኘት ውጪ ሌላ ምንም ነገር አይፈልጉም።
ነገር ግን፣ ሌሎች ሰዎች እንዴት እንደሚያስቡ ወይም አንቺን እንዴት እንደሚመለከቱ መቆጣጠር እንደማትችዪ ማስታወስ በጣም አስፈላጊ ነው። ይልቁንስ አንቺ የምትችዪውን ምርጡን የራስሽን ማንነት በመሆን ላይ አተኩሪ። እነሱን ለመለወጥ መሞከርሽን አቁሚ፤ እነሱ ስለሚያደርጉት ነገር መጨነቅሽን ተዪ። ዓላማዎችሽን አስቀምጪ፣ ሕልሞችሽን ተከተይ፣ የልብሽን ስሚ፤ ማንም ሰው ወይም ምንም ነገር ሕልሞችሽን ከማሳካት እንዲያስቆምሽ አትፍቀጂ።"
እወዳችኋለሁ

‎“ህይወት ብስክሌት እንደመንዳት ናት ሚዛንህን ለመጠበቅ መንቀሳቀስህን መቀጠል አለብህ። የስኬት ሰው ብቻ ለመሆን አትሞክር ይልቅ ዋጋ ያለው ሰው ለመሆን ሞክር። ምክንያቱም ስኬት የሚለካው በ...
25/06/2025

‎“ህይወት ብስክሌት እንደመንዳት ናት ሚዛንህን ለመጠበቅ መንቀሳቀስህን መቀጠል አለብህ። የስኬት ሰው ብቻ ለመሆን አትሞክር ይልቅ ዋጋ ያለው ሰው ለመሆን ሞክር። ምክንያቱም ስኬት የሚለካው በምትወስደው ነገር ሲሆን ዋጋ የሚለካው ደግሞ በምትሰጠው ነገር ነው።

‎ሞኝ ማለት አንድ አይነት ነገርን ደጋግሞ ሰርቶ የተለየ ውጤት የሚጠብቅ ነው። የተለየውን መንገድ ተከተል አዲስ ነገር ታገኛለህ። አትቀመጥ ምክንያቱም ምድራችን አደገኛ የሆነችው በክፉ ሰዎች ስራ ሳይሆን ምንም በማይሰሩ ሰዎች ውጤት ነው።

‎ትምህርት እውነትን አያስተምርም ይልቅ የአእምሮ አስተሳሰብን ማበልጸጊያ ልምምድ ነው። የሌሎች ጫጫታ የአንተን የውስጥ ድምፅ እንዲውጠው ማድረግ የለብህም። ማንም ሰው ባንተ ላይ ገደቦች እንዲጥል አትፍቀድ፤ ገደብህ በራስህ ያወጣኸው የህይወት መመርያ መሆን አለበት!።

እሣት እና ውኃ ተባብረው አንድ በሬ ገዙ። እንደገዙም በሬው በሌባ ተሠረቀ።በዚህ ግዜ እሣት "ጓደኛዬ ውኃ እንደምታውቀው ካንተ በቀር ሁሉን አሸንፋለሁ ስለዚህ አሁን ባፋጣኝ ተነስቼ ቤቱንም ፣...
24/06/2025

እሣት እና ውኃ ተባብረው አንድ በሬ ገዙ።

እንደገዙም በሬው በሌባ ተሠረቀ።

በዚህ ግዜ እሣት "ጓደኛዬ ውኃ እንደምታውቀው ካንተ በቀር ሁሉን አሸንፋለሁ ስለዚህ አሁን ባፋጣኝ ተነስቼ ቤቱንም ፣ደኑንም፣ሣሩንም አቃጥዬ የበሬያችንን ሌባ ፈልጌ ላግኘው" አለው።

ውኃም "ጓዴ ሌባውንም ሌባ ያልሆነውንም አንድ ላይ ማቃጠል አይገባም።ሌባውን ለመያዝ ከሆነ እንደዛ ማድረግ አይጠበቅብንም አሁን እናገኘዋለን" አለው።

እሣትም እንዴት ሲል ጠየቀ።

ውኃም "እጠብስ ያለ ካንተ ፤ አጥብ ያለ ከኔ መምጣቱ አይቀርም"በዛ ግዜም እንይዘዋለን አለው።

ይህ ታሪክ ሁሌም ቢሆን እርምጃዎቻችንን በጥንቃቄ እና በብስለት እንዲሁም በማገናዘብ እንድናደርግ ያስተምረናል።

በንዴት እና በእልህ ውስጥ ሆኖ ውሳኔ ማሳለፍ ትርፉ ፀፀት ነው።

‎አንድ አጭር የፍቅር ታሪክ ልጋብዛቹ ‎በአንድ ወቅት ሁለት እጅግ የሚዋደዱ ፍቅረኛማቾች ነበሩ፡፡ በፍቅራቸው ሙሉ አካባቢው ይቀናባቸዋል፡፡ ከእለታት አንድ ቀን ግን በአንድ ሆቴል ልጆቷ በድን...
24/06/2025

‎አንድ አጭር የፍቅር ታሪክ ልጋብዛቹ
‎በአንድ ወቅት ሁለት እጅግ የሚዋደዱ ፍቅረኛማቾች ነበሩ፡፡ በፍቅራቸው ሙሉ አካባቢው ይቀናባቸዋል፡፡ ከእለታት አንድ ቀን ግን በአንድ ሆቴል ልጆቷ በድንገት ከሌላ ወንድ ጋር ትታያለች፡፡
‎በዚህ ሰአት የሆነ ሰው ደውሎ "ና የፍቅረኛህን ቅሌት ተመልከት" ብሎ ይነግረዋል፡፡
‎ልጁም ካለበት በፍጥነት ሲመጣ ክፍል ይዘው
‎ገብተዋል፡፡ ገቡ ወደ ተባለበት ክፍል ቀርቦ ሲያዳምጥ ከውስጥ ይሳሳቃሉ።
‎እስከመጨረሻው የመታገስ አቅም አልነበረውም፡፡ በኔ ላይ ሌላ ወንድ ? ሲል ይናደዳል ፡፡ በዚህ ግዜ የሷ ጉዋደኛ የሆነች ልታፅናናው ትቀርበዋለች፡፡
‎እሱም አጋጣሚውን በመጠቀም እንደውም ላስቀናት በሚል እሷ በምታየው ቦታ ጓደኛዋን እየወሰደ ያዝናናታል እንደፍቅረኛ አድርጎ ለሰው ያወራል፡፡ ከ ወር ቡሀላ ፍቅረኛው ሞተች፡፡ በዚህ ግዜ በእናቷ በኩል አንድ ደብዳቤ አስቀምጣለት ነበር፡፡ እሱ የኔ ግፍ ነው ብሎ በቀብር ስርአቱ ላይ እንኳን አልተገኘም፡፡
‎እናትየዋ ባለበት ሄዳ የልጇ አደራ የሆነውን ደብዳቤውን ሰጠችው፡፡ ደብዳቤው ይህን ይላል፡፡ "ውዴ የኔ ፍቅር አንተ አዝነክብኛል እኔ ግን ተደስቻለው፡፡ ያን ቀን ሆቴል ደውዬ እንድትመጣ ያደረኩት እኔ ነኝ፡፡
‎በዛ ክፍል ውስጥ ምንም አልተፈጠረም፡፡ አንተ በኔ ተናደክ ወደሌላ ሴት እንድትሄድ የሰራውት ድራማ ነበር፡፡ በሀዘንህ ሰአት ያፅናናችክ ጉዋደኛዬ እኔ ነኝ የላኳት፡፡ እሷ በጣም ትወድካለች ፡፡
‎እንዳትተዋት፡፡ አንተ እኔን ለማስቀናት ፍቅር ስትሰጣት ሳይ እኔ እደሰት ነበር ያንን ፍቅር ከልብህ አድርገው፡፡ ደስታህን አይቼ በመሞቴ እድለኛ ነኝ፡፡ ቢያንስ ብቻክን አልተውኩህም፡፡ ይሄንን ያደረኩት ዶክተሩ ባለብኝ ካንሰር ምክንያት ለመሞት ቢበዛ 30 ቀን ብቻ
‎እንደቀረኝ ስለነገረኝ ነው፡፡"
‎"ፍቅር ማለት አብረው ላሉት ብቻ ሳይሆን ትተውት ለሚሄዱትም ደስታ መጨነቅ ነው፡:

‎ለወጣቶች የማቀርበው ምክር‎‎1. የወሲብ ስሜታችሁን መቆጣጠራችሁ የስኬታችሁ ወይም የውድቀታችሁ ምክንያት ይሆናል።‎‎2. ፖርኖግራፊና ግለ ወሲብ የስኬት ትልቁ ጠላቶች ናቸው። አእምሯችሁን ያ...
23/06/2025

‎ለወጣቶች የማቀርበው ምክር

‎1. የወሲብ ስሜታችሁን መቆጣጠራችሁ የስኬታችሁ ወይም የውድቀታችሁ ምክንያት ይሆናል።

‎2. ፖርኖግራፊና ግለ ወሲብ የስኬት ትልቁ ጠላቶች ናቸው። አእምሯችሁን ያኮስሳሉ፣ ያጠፋሉ።

‎3. ልክ ግመል ውሃ እንደሚጠጣው አልኮል ከመጠጣት ተቆጠቡ። ህሊናችሁን ስታችሁ ሞኞች ከመሆን የከፋ ነገር የለም።

‎4. ደረጃችሁን ከፍ አድርጉ፤ ዝም ብሎ ስለተገኘ ብቻ ዝቅ ባለ ነገር አትርኩ።

‎5. ከእናንተ የበለጠ ብልህ ሰው ካገኛችሁ፣ ከእነሱ ጋር ስሩ እንጂ አትወዳደሩ።

‎6. ችግሮቻችሁን ሊፈታላችሁ የሚመጣ ማንም የለም። የህይወታችሁ 100% የራሳችሁ ኃላፊነት ነው።

‎7. በህይወት መድረስ ከምትፈልጉበት ደረጃ ካልደረሱ ሰዎች ምክር መቀበል የለባችሁም።

‎8. ገንዘብ የምታገኙበት አዳዲስ መንገዶችን ፈልጉ። ገንዘብ ስሩ፤ በሚያሾፉባችሁና በሚቀልዱባችሁ ፌዘኞች ጊዜ አታጥፉ/ችላ በሏቸው።

‎9. 100 ራስን መርጃ መጻሕፍት አያስፈልጓችሁም፤ የሚያስፈልጋችሁ ተግባርና ራስን መገዛት ብቻ ነው። ራሳችሁን ግዙ!

‎10. አደንዛዥ እጾችን አስወግዱ። በተለይ እንደ ጫትና ሀሺሽ (ካናቢስ) ያሉትን እርሟቸው።

‎11. በኔትፍሊክስ የማይረባ ይዘት እየተመለከታችሁ ጊዜያችሁን ከምታጠፉ፣ ከዩቲዩብ ክህሎቶችን ተማሩ።

‎12.ማንም ስለእናንተ ግድ የለውም። ስለዚህ ዓይን አፋር መሆናችሁን አቁሙና ወጥታችሁ እድሎቻችሁን ፍጠሩ።

‎13. ምቾት ከሁሉ የከፋ ሱስና ወደ ድብርት/ጭንቀት የሚወስድ ርካሽ ትኬት ነው።

‎14. ለቤተሰባችሁ ቅድሚያ ስጡ። መጥፎ ቢሆኑም ወይም ሞኞች ቢሆኑም እንኳ ተከላከሉላቸው፤ ነውራቸውን ሸፍኑ።

‎15. አዳዲስ እድሎችን ፈልጉ፤ ከእናንተ የቀደሙ ሰዎችን ተሞክሮ ተማሩ።

‎16. ማንንም አትመኑ። አንድም ሰው ቢሆን፣ ምንም ያህል ብትፈተኑ እንኳ። በራሳችሁ እመኑ።

‎17. ተአምራትን አትጠብቁ፤ እንዲፈጠሩ አድርጉ። አዎ፣ ሁልጊዜ ብቻችሁን ላታደርጉት ትችላላችሁ፤ ነገር ግን የሰዎችን አስተያየት አትስሙ።

‎18. ጠንክሮ መሥራትና ጽናት ማንኛውንም ነገር እንድታሳኩ ያስችሏችኋል። ራስን ዝቅ ማድረግ ከፍ ያደርጋችኋል።

‎19. ራሳችሁን እስክታገኙ/እስክታውቁ ድረስ መጠበቅ አቁሙ። ይልቁንስ ራሳችሁን ፍጠሩ።

‎20. ዓለም ለእናንተ ስትል ፍጥነቷን አትቀንስም/አትዘገይም።

‎21. ማንም ለእናንተ ምንም ዕዳ የለበትም።

‎22. ህይወት የአንድ ተጫዋች ጨዋታ ናት። ብቻችሁን ትወለዳላችሁ፤ ብቻችሁን ትሞታላችሁ። ሁሉም ትርጓሜዎቻችሁ የራሳችሁ ብቻ ናቸው። በሶስት ትውልድ ውስጥ ትረሳላችሁ ማንምም ለእናንተ ግድ አይሰጠውም። ከመምጣታችሁ በፊትም ማንም ግድ አልሰጠውም ነበር። ሁሉም ነገር የአንድ ተጫዋች ነው።

‎23. የህይወታችሁ መንገድ ሁልጊዜ ጥገኛ፣ የተጨነቃችሁና ደካማ እንድትሆኑ በሚያደርግ መልኩ የተነደፈ ሊመስል ይችላል። ነገር ግን መውጫው አንድ ብቻ ነው፤ እሱም ለመውጣት መወሰን። ከራሳችሁ በቀር ማንም እናንተንም ሆነ የምትወዷቸውን ሰዎች አያድንም።

‎24. ሁሉም ሰው እንደናንተ አይነት ልብ የለውም። ሁሉም ሰው እናንተ ለነሱ ቅን እንደሆናችሁት ለእናንተ ቅን አይሆንም። ለጥቅማቸው የሚጠቀሙባችሁና ያ የህይወታቸው ምዕራፍ ሲያልፍና ፍላጎታቸው ሲሟላ የሚጥሏችሁ ሰዎች ያጋጥሟችኋል። ንቁ ሁኑ!

‎25. በ25 ዓመታችሁ፣ የሚከተሉትን ለማድረግ ብልሆች መሆን አለባችሁ፦
‎→ የሌሎችን ስኬት አክብሩ
‎→ ቅናትንና ምቀኝነትን አስወግዱ
‎→ ክፍት አእምሮ ይኑራችሁ
‎→ ግምቶችን አስወግዱ
‎→ በዓላማ ተንቀሳቀሱ
‎→ ምስጋናን ተለማመዱ
‎→ በታማኝነት ተናገሩ
‎→ በየ

"ሰላም ጓደኞቸ ይችን ነገር ለዛሬ ይዢላችሁ መጥቻለሁ አንብቧት መልሱልኝ!!_______________________________________‎1-አሳማ በተፈጥሮ ወደ ሰማይ ማየት አያስችለውም::‎...
22/06/2025

"ሰላም ጓደኞቸ ይችን ነገር ለዛሬ ይዢላችሁ መጥቻለሁ አንብቧት መልሱልኝ!!
_______________________________________
‎1-አሳማ በተፈጥሮ ወደ ሰማይ ማየት አያስችለውም::

‎2 -አይጥ ከተራበች የራሷን ጅራት ትበላለች።

‎3 -ሰማያዊ አሳነባሪ በመጠን እስካሁን በአለማችን ከነበሩ እና ካሉ እንሰሳዎች ትልቁ ነው::

‎4- የለሌት ወፍ ብቸኛዋ ከአጥቢዎች መብረር የምትችል ሲሆን የእግር አጥንቶቾ ከመቅጠናቸው የተነሳ መብረር እንጂ መራመድ አትችልም::

‎5 -የለሌት ወፍ ምንግዚም ከዋሻ ሲወጡ ወደ ግራ ይበራሉ::

‎6 -እባብ አይኖቹ ቢከደኑም በአይኖቹ ቆብ ማየት ይችላል::

‎7 -ወንድ የወባ ትንኝ አይናደፍም ሴቷ ብቻ ናት መናደፍ
‎የምትችለው::

‎8- የዱር አይጥ በፍጥነት መራባት የሚችሉ ሲሆን በ18 ወራት ብቻ 2 አይጦች 1 ሚሊዮን ዘመዶችን ማፍራት ይችላሉ::

‎9 -አንድ ንብ አንድ የሾርባ ማንኪያ ማር ለማዘጋጀት ከ 4000 በላይ አበቦችን መጎብኝት አለባት ::

‎10 -ቀንድ አውጣ ለ3 አመት መተኛት ይችላል::

‎11 - አንድ ላይ የተያያዘ የሸረሪት ድር ተመሳሳይ ወፍረት ካለው አንድ ላይ ከተያያዘ የብረት ሺቦ ይጠነክራል::

‎12 -ዝሆኖች ከ3ማይል ላይ ያለ ውሀ ማሺተት ይችላሉ::

‎13 -ኦይሰትር የተባለ የዓሳ ዝርያ ከአንዱ ፆታ ወደ ሌላኛው እንዲሁም ወደ ነበረበት ለወሲብ በሚመቸው ፆታውን መቀየር ይችላል::

‎14 -በየአመቱ 1/3 የሚሆነው የአለማችን ሰብል በተባይ/ነብሳት ይወድማል::

‎15 - ለሚስቱ ታማኝ የሆነ እንስሳ ቀበሮ ብቻ ነው።

‎ስንት ቁጥር አግራሞትን ፈጠርባችሁ ??
‎የተመቸው ሼር፣ላይክ እንዲደርስ።

አንድ ሰው ነበረ እጅግ በጣም ትንሽ መሬት የነበረችው። ከመሬቷ ማነስና ከኑሮው መጉደል የተነሣ ሲቆፍር በምሬት "ወይ አዳም.. ወይ አዳም.. ወይ አዳም" ማለትን ያዘወትር ነበር። ይህን ደጋግ...
21/06/2025

አንድ ሰው ነበረ እጅግ በጣም ትንሽ መሬት የነበረችው። ከመሬቷ ማነስና ከኑሮው መጉደል የተነሣ ሲቆፍር በምሬት "ወይ አዳም.. ወይ አዳም.. ወይ አዳም" ማለትን ያዘወትር ነበር። ይህን ደጋግሞ የሰማ አንድ ባለፀጋ ለምን እንዲህ እንደሚል ሲጠይቀው "ከተዋበ ገነት በገዛ ጥፋቱ ወጥቶ ለእኛ መከራ ያተረፈ አዳም ነው፡፡ የአምላኩን ትዕዛዝ ቢሰማ ኖሮ ይህ የኑሮ ችግር በእኔ ባልደረሰ ነበር" በማለት ገለፀለት፡፡ ባለፀጋውም እኔ ብዙ ሀብት ያለኝ ብሆንም ወራሽ የለኝምና እኔ ቤት ገብተህ ውረሰኝ አለውና ወደ ቤቱ ወስዶ ያለውን ሁሉ ወርቁን፣ ብሩን፣ ከብቱንና እህሉን፣ አንዲት ጠርሙስ ስትቀር አስረከበው። ይህች የእኔ ንብረት ናትና
እንዳትነካብኝ በማለት ጠርሙሷን እንዲጠብቅለት አደራ አለው፡፡ ሰውዬውም ምን ይሆን በማለት ጉጉት አድሮበት ሳለ ያ ሰው ለጉዳዩ ከቤቱ ርቆ ሲሄድ ቶሎ ብሎ ይከፍትና ቢያያት ውስጧ ባዶ ሆኖ በማግኘቱ ተደንቆ መልሶ ዘግቶ እንደነበረች ይመልሳታል፡፡ ከመንገዱ የተመለሰው ባለፀጋውም "ንብረቴን ጠበክልኝ አልነካህም?' ሲለው በደንብ እንደጠበቀ ገለፀለት። ለካስ ይህ ባለጸጋ በሰጠው ንብረት ላይ ታማኝነቱን ይፈትነው ዘንድ ትንኝ አድርጎ ስለነበር ያ ሰው ጠርሙሱን በከፈተ ጊዜ እርሱ ሳያያት በርራ ሄዳለች፡፡ ባለጸጋውም "ዋሾ ነህ! አልታመንክም" በማለት ከሰጠው ንብረት
አባረረው፡፡ ተመልሶ ወደ ቀደመው መሬቱ ሲመለስ
"ወይ እኔ! ...ወይ እኔ! ...ወይ እኔ!" እያለ ወደ ቁፋሮው ተመለሰ፡፡
እውነት ነው፤ የምናስተውለው ነገር ነው፡፡ አብዛኛው ሰውዎች ዘንድ ደካማ ባህርያት አንዱ የራሱን ጥፋቶች (ስህተቶች) አለመቀበል ነው፤ የተወሰኑት ብርትዎች ደሞ ከዚህ በተቃራኒው ይቆማሉ "እኔ ምንድነው የተሳሳትኩት?" በማለት ራሳቸውን ይፈተሻሉ፤ መፍትሄ ፍለጋ ይኳትናሉ።
ካነበቡኩት....የተወሰደ ሸር አድርጓት

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢትዮጵያ Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share