Qajeelcha Fayyaa G/S/Oromoo የኦሮሞ ዞኑ ጤና መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Kemise
  • Qajeelcha Fayyaa G/S/Oromoo የኦሮሞ ዞኑ ጤና መምሪያ

Qajeelcha Fayyaa G/S/Oromoo የኦሮሞ ዞኑ ጤና መምሪያ Oromo Health Department Health Education and Promotion Center, main objective is disseminating update health information for the community.

Oromo zone is one of special zone in amhara region. Its capita city is Kemisse which is found 325 KM from Addis Ababa. It has tow urban and five rural worda.

ጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር በዳሰነች ወረዳ በድሮን የታገዘ የክትባት ስርጭት በይፋ ጀመረ____________የጤና ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን ...
28/12/2025

ጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር በዳሰነች ወረዳ በድሮን የታገዘ የክትባት ስርጭት በይፋ ጀመረ
____________

የጤና ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) ጋር በመተባበር፣ የማርበርግ ቫይረስ ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች የህይወት አድን መድኃኒቶችንና ክትባቶችን በድሮን የማድረስ ስራ ዛሬ በይፋ ጀምሯል።

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የወረርሽኙን ስርጭት ለመግታትና ራቅ ያሉ አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ በወሰደው የፈጣን ምላሽ እርምጃ፣ ዛሬ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዳሰነች ወረዳ በድሮን የታገዘ የክትባት ስርጭት በስኬት ተከናውኗል።

የዳሰነች ወረዳ ካለው ራቅ ያለ መልክዓ ምድር አኳያ በመኪና ለማጓጓዝ ረጅም ሰዓታት ይወስድ የነበረውን ጉዞ፣ በድሮን በመታገዝ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ክትባቱን በ –80°C ቅዝቃዜ ጠበቆ በማድረስ ለአካባቢው ማህበረሰብ ክትባቱን መስጠት ጀምሯል።

ይህም ተግባር የጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅርቦት አገልግሎት (EPSS) የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም ወረርሽኞችን ቀድሞ የመከላከልና የመቆጣጠር አቅሙን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገሩን በተግባር ያሳየበት ነው።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ወረርሽኞችን ለመመከት የራሷን የውስጥ አቅም እና የቴክኖሎጂ ውጤቶች መጠቀም መጀመሯን የሚያሳይ ትልቅ ማሳያ ሲሆን፣ በቀጣይም ይህ በድሮን መድኃኒት የማድረስ አገልግሎት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

የሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ በሽታ__________የሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ በሽታ በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት ሲሆን ይህ ቫይረስ አጣዳፊ ወይም ሥር የሰደደ የጉበት ኢንፌክሽን ያመጣል።ሄፓታይተስ ቢ...
09/12/2025

የሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ በሽታ
__________

የሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ በሽታ በቫይረስ አማካኝነት የሚከሰት ሲሆን ይህ ቫይረስ አጣዳፊ ወይም ሥር የሰደደ የጉበት ኢንፌክሽን ያመጣል።

ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ በሽታ በአብዛኛው የሚተላለፈው በተበከለ ደም ወይም ከሰዉነት በሚወጣ ፈሳሽ አማካኝነት ነው።

በኢትዮጵያ ከአጠቃላይ ሕዝብ ውስጥ ከ8-12% የሚገመተው ለሄፖታይተስ ቢ ቫይረስ በሽታ ተጋላጭ ነው።

በሄፖታይተስ ቢ ቫይረስ በሽታ ከተያዙ እናቶች የተወለዱ ሕፃናት በሄፐታይተስ ቢ ኢሚዩን ግሎቡሊን (HBIG) ካልታከሙ እና ከተወለዱ በኋላ ወዲያውኑ ክትባት ካልተሰጣቸው በወሊድ ጊዜ በበሽታው የመያዝ ዕድላቸው እስከ 90% ይደርሳል።

ከሁሉም አጣዳፊ ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ኢንፌክሽን ካለባቸው ታካሚዎች ከ5 እስከ 10% የሚሆኑት ሥር የሰደደ ሄፓታይተስ ቢ በሽታ ይይዛቸዋል። አጣዳፊ ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ኢንፌክሽን የሚከሰትበት ዕድሜ በወጣትነት ጊዜ ከሆነ፣ ሥር የሰደደ ሄፓታይተስ ቢ የመያዝ እድሉ ከፍ ያለ ነው።

ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ በሽታ ሥር የሰደደ ከሆነ፣ የጉበት ጠባሳ ሊፈጠር ይችላል፣ እና በመጨረሻም የጉበት ካንሰር ሊከሰት ይችላል።

▪የሄፖታይተስ ቢ ቫይረስ መተላለፊያ መንገዶች

• ከእናት ወደ ልጅ በወሊድ ጊዜ በሚኖር ንክኪ
• በተሰነጠቀ እና በቆሰለ ቆዳ በንክኪ የሚተላለፍ
• ጥንቃቄ የጎደለው የግብረስጋ ግንኙነት
• ንጽህናቸው ያልተጠበቁ ስለታማ ነገሮችን በጋራ መጠቀም

▪የሄፖታይተስ ቢ ቫይረስ ምልክቶች

ምልክቶቹ ብዙውን ጊዜ ቀላል ናቸው ወይም ጨርሶ ላይታዩ ይችላሉ። ኢንፌክሽኑ በደም ምርመራ ሊረጋገጥ ይችላል።

አብዛኛዎቹ ታካሚዎች የተለመዱ የቫይረስ ሄፓታይተስ ምልክቶች ይታይባቸዋል፣ ይህም፡

• የምግብ ፍላጎት ማጣት፣ ድካም ስሜት
• የሰውነት ምቾት ማጣት፣
• ትኩሳት፣
• ማቅለሽለሽ እና ማስታወክ፣
• በመቀጠልም ጃንዲስ (የቆዳ ቢጫ መሆን)ትኩሳት፣
• የመገጣጠሚያ እና የጡንቻ ሕመም
• የሽንት መጥቆር ያካትታል
ምልክቶቹ ከጥቂት ሳምንታት እስከ 6 ወራት ሊቆዩ ይችላሉ።

▪የሄፖታይተስ ቢ ቫይረስ ምርመራ

ሄፖታይተስ ቢ ቫይረስ በሽታን ለመመርመር እና የጉበት ሥራን ለመከታተል የደም ምርመራዎች ይደረጋሉ ። የጉበት አልትራሳውንድ ወይም ባዮፕሲም(ከጉበት ላይ ቅንጣት በመዉሰድ የሚደረግ ምርመራ ) ሊያስፈልግ ይችላል።

▪ሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ በሽታ ሕክምና

እረፍት እና ጤናማ የአኗኗር ዘይቤ በተጨማሪ ይመከራል።
ከባድ የጉበት እብጠት (fulminant hepatitis) ከተከሰተ፣ በአፍ የሚወሰዱ ፀረ-ቫይረስ መድኃኒቶችን መጠቀም የመዳን እድልን ይጨምራል። እንደ ክብደቱ እና በጉበት ላይ እንደደረሰው ጉዳት መጠን የጉበት ንቅለ ተከላ ይደረጋል።

▪የሄፖታይተስ ቢ ቫይረስ መከላከያ መንገዶች

• ክትባት፡ በጣም ውጤታማው የመከላከያ ዘዴ ህጻናት እንደተወለዱ የሚሰጠው የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባት ነው፣ በተጨማሪም 6፣ 10 እና 14 ሳምንት እድሜያቸው ላይ ይሰጣል።
• በሰለጠነ ጤና ባለሙያ በጤና ተቋም መውለድ
• ንጽህናቸው ያልተጠበቀ ስለታማ ነገሮችን በጋራ አለመጠቀም
• ጥንቃቄ ያለው የግብረስጋ ግንኙነት
• በበሽታው የተያዙ ሰዎችን ወደ ህክምና መውሰድ ናቸው። (ከጤና ሚንስቴር የተወሰደ)
#አብክመጤናቢሮ


ህዳር 30/2018ዓ.ም

ከ25 ሚሊዮን በላይ ሕፃናት ተደራሽ የሚሆኑበት የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ************************* ከ25 ሚሊዮን በላይ ሕፃናት ተደራሽ የሚሆኑበት ሀገር አቀፍ የተቀናጀ የፖሊዮ ክ...
08/12/2025

ከ25 ሚሊዮን በላይ ሕፃናት ተደራሽ የሚሆኑበት የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ
*************************

ከ25 ሚሊዮን በላይ ሕፃናት ተደራሽ የሚሆኑበት ሀገር አቀፍ የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከታኅሣሥ 3 እስከ 6/2018 ዓ.ም ሊካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

ዘመቻውን አስመልክቶ ሀገራዊ የንቅናቄ መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።

በኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የበሽታዎች ቅኝት እና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳይሬክተር አቶ እንዳለ ዘመነ ፖሊዮን ለማጥፋት የተቀናጀ ሀገር አቀፍ ክትባት ዘመቻ በመላው ሀገሪቱ ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።

ለዚህም በሁሉም ክልሎች የክትባቱ ቁሳቁስ እና ተያያዥ ግብዓት አቅርቦት ጨምሮ የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶች በበቂ ደረጃ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል።

በዘመቻው ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ሕፃናት በዋናነት ክትባት የሚሰጥ ሲሆን የቤት ለቤት የፖሊዮ ክትባት ከመስጠት ጎን ለጎን የበሽታው ምልክት ያሳዩትን ሕፃናት የመለየት ሥራ እንደሚከናወን ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል።

በጤና ሚኒስቴር የክትባት ፕሮግራም የኮሙዩኒኬሽን አማካሪ ወይዘሮ ፀጋነሽ ገድሉ እንደጠቀሱት፣ በዘመቻው መደበኛ የፖሊዮ ክትባት ያልወሰዱ ሕፃናት ይካተቱበታል።

በአራት ቀናት ውስጥ ክትባቱ በሁሉም ክልሎች እንደሚሰጥ ገልጸው፣ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ትብብር እና ማድረግ እንደሚኖርባቸውም አሳስበዋል።

በአባዲ ወይናይ

08/12/2025
07/12/2025

Guyyaa 28/2018
👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍
Jiraattota Aanaa Jiillee Dhummuugaafii Bulchiinsa Magaalaa Sanbatee Jirtan Hundaaf.

Duullii talaallii pooliyoo marsaa 4ffaa Muddee 3-6/2018 irraa jalqabee daa'imman umuriin isaanii waggaa shanii gadi ta'eef manaa mana deemuudhaan waan kennamuuf hawaasni hundi daa'imman keessan talaalchisuuf qophii akka taasistan isiniin jenna. Dabalataanis, gandootni Aanaa fii Bulchiinsa Magaalaa keenyaa qophii dursaa karaa qindaa'aa ta'een taasisuun qophaa'uu qabdu. Isaanis:-
👉🏽 Koree hojicha hordofuu dhaabuun hojicha hordofuu
👉🏽Sosochii hawaasaa gaggeessuu/ergaalee duulaa karaa carraawwan jiran hundaan dabarsuu ( Manneen barnootaatti, manneen amantaa, ijaarama adda addaatti hawaasni hundumtuu daa'imman waggaa shanii gadii aanaa keessan keessa jiran harcaatii tokko malee talaalchisuuf akka qophooftan isin hubachiisna!!
***Daa'immaniifi namoota Rakkoo Hidhii Tarsa'uu (cleft lip) fi Laagaan Tarsa'uu(palate) qaban adda baasuufi galmeessuun gara tajaajila yaalaatti qunnamsiisuu,
*** Daa'imman rakkoo miilaa(Clubfoot) qaban adda baasuufi galmeessuun gara tajaajila yaalaatti qunnamsiisuu,
***Daa'imman talaallii hin jalqabne(Zero dose)fi jalqabanii adda kutan adda baasuufi talaallii eegalchiisuu
*Daa'imman Hir'ina Nyaataa Qaban Adda Baasuu...

Waajjira Fayyaa Aanaa Jiillee Dhummuugaa

የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የቅኝት ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋልአዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፦የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ...
07/12/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የቅኝት ሥራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 28/2018 (ኢዜአ)፦የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የቅኝት ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ገለፁ።

የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢንስቲትዩቱ የህብረተሰብ ጤናና አደጋ ቁጥጥር፣ የበሽታዎች ቅኝት፣ ዝግጁነትና ምላሽ የመስጠት ሥራ ያከናውናል።

የድንበር ተሻጋሪ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር፣ የላቦራቶሪ አቅም ግንባታና የህብረተሰብ ጤና ምርምር ሥራዎችን እንደሚያከናውን ገልፀዋል።

የማርበርግ ቫይረስ በሽታን የመከላከልና የመቆጣጠር፣ ንክኪ ያላቸውን ሰዎች ለይቶ የመከታተል እንዲሁም የቅኝት ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል።

በመግቢያና መውጫ ኬላዎች ላይ ለህብረተሰቡ የቅድመ ጥንቃቄ መልዕክቶችን የማስገንዘብ እንዲሁም ንክኪን የመቀነስ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ብሔራዊ ግብረ ኃይልና የክስተት አስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት እየተሰራ መሆኑን ገልፀው የቤት ለቤትና የማህበረሰብ ቅኝት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።

ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የቤት ለቤት ቅኝት መደረጉንና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመው የላቦራቶሪ የመመርመር አቅምን በማሳደግ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ህብረተሰቡ የጥንቃቄ መልዕክቶችን በመተግበር ራሱን ከማርበርግ ቫይረስ መከላከል እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ማንኛውም ሰው የበሽታውን ምልክቶች ሲያስተውል በአፋጣኝ ወደ ህክምና ተቋም ሊሄድ እንደሚገባም እንዲሁ።

#ኢዜአ

በወረዳው ለሚካሄደው 4ኛው ዙር የተቀናጀ ቤት ለቤት የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የግንዛቤ ትምህርት ተሰጠ--------------------------------ሰንበቴ:ህዳር 28/2018 ዓ.ም(ጅሌ ጥሙ...
07/12/2025

በወረዳው ለሚካሄደው 4ኛው ዙር የተቀናጀ ቤት ለቤት የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ የግንዛቤ ትምህርት ተሰጠ
--------------------------------

ሰንበቴ:ህዳር 28/2018 ዓ.ም(ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት)

የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ከታህሣስ 3-6/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 4ኛው ዙር የቀናጀ ቤት ለቤት የፖሊዮ ክትባት አስመልክቶ ለማህበረሰቡ የግንዛቤ ትምህርት ሰጥቷል።

4ኛው ዙር የፖሊዮ ክትባት ከታህሣስ 3-6/2018 ዓ.ም በሁሉም ቀበሌዎች እድሜያቸው ከ5 አመት በታች ለሆኑ ህፃናት ይሰጣል።

ክትባቱ ቤት ለቤት የሚሰጥበመሆኑ ህብረተሰቡ ከወዲሁ የክትባት መስጫ ቀናቶችን ተገንዝቦ ልጆችን እንዲያስከትብ በሰንበቴ ገበያ ላይ በመገኘት የግንዛቤ ትምህርት ተሰጥቷል።

ይህ በእንዲህ እያለ ጽ/ቤቱ በዘመቻው የተቀመጠውን እቅድ ለማሳካት ቀደም ሲል ለባለድርሻ አካላት ኦሬንቴሽን መስጠቱን እና የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ መዘገባችን ይታወሳል።

መረጃ:- ከጅሌጥሙጋ ወረዳ ጤናፅ/ቤት ከጤና ማበልፀግና ሚድያ ክፍል የተገኘ

የጤና ተቋማትን ደረጃ በማሻሻል የተሻለ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ -ዶክተር መቅደስ ዳባየጤና ተቋማትን ደረጃ በማሻሻል የተሻለ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ...
02/12/2025

የጤና ተቋማትን ደረጃ በማሻሻል የተሻለ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ -ዶክተር መቅደስ ዳባ

የጤና ተቋማትን ደረጃ በማሻሻል የተሻለ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ተናገሩ።

ሚኒስትሮችን ጨምሮ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ከሚሴ ከተማ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው።

በጉብኝቱ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትእግስት ሀሚድ እንዲሁም የክልሉና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።

የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ በወቅቱ እንደሉት የጤና ተቋማትን ደረጃ በማሻሻል የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው።

የጤና ተቋማቱ ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ በየደረጃው እየተሰሩ ያሉ ተግባራትም ውጤት እያስገኙ መሆናቸውን በጉብኝቱ መገንዘባቸውን አስረድተዋል።

የኮሪደር ልማት ግንባታም ለውበት ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰቡ ጤና መሻሻል አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል።

በአማራ ክልል የኦሮሞ ልዩ ዞን አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አህመድ አሊ በበኩላቸው እንደገለፁት በዞኑ የከሚሴ ከተማን ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተከናወኑ ነው።

ለአቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎች የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች፣ የኮሪደር ልማት፣ የከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል ማስፋፊያና ሌሎች የልማት ስራዎች እየተጎበኙ መሆኑን ገልጸዋል።

ምንጭ Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ

01/12/2025

Address

Kemise

Telephone

+251335540266

Website

https://arhb.gov.et/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Qajeelcha Fayyaa G/S/Oromoo የኦሮሞ ዞኑ ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Qajeelcha Fayyaa G/S/Oromoo የኦሮሞ ዞኑ ጤና መምሪያ:

Share