Al -Jazeera Afar press

Al -Jazeera Afar press Al Jazeerah Qafar Mediah Ayyuntih Ayti Rakaakay 🤳24 Saaqat

አንዚህ የምንመለከታቸው ወጣቶች በአፋም ወረዳ ሀዶላ የበጎ አድራጎት ማህበር ወጣቶች ናቸው በወረዳው ላይ አቅመ-ደካሞችን ፣ መሰረተ-ልማታቸው የፈረሱ ተቋማትን እንዲሁም በማንኛውም የስራ መስክ...
07/12/2025

አንዚህ የምንመለከታቸው ወጣቶች በአፋም ወረዳ ሀዶላ የበጎ አድራጎት ማህበር ወጣቶች ናቸው በወረዳው ላይ አቅመ-ደካሞችን ፣ መሰረተ-ልማታቸው የፈረሱ ተቋማትን እንዲሁም በማንኛውም የስራ መስክ ይሁን ብቻ ለማህበረሰቡ አገልግሎት የሚውል ማንኛውንም በጎ ስራ ላይ በጉልበታቸውም ይሁን በገንዘብ ደከምን ሰለቸን ሳይሉ ህብረተሰቡን በማገልገል ላይ ናቸው

🙏🙏🙏🙏🙏🙏

መንግስት በጤናው ዘርፍ ላይ ትኩረት ሰጥቶ የደሞዝ ጭማሪ እና ጥቅማጥቅም  የመሳሰሉ ስራዎች በጤናው ዘርፍ ላይ እየሰራ ባለበት በዚ ወቅት ላይ አንዳንድ የአፋር ክልል ወረዳዎች ላይ ፣ በተለይ...
03/12/2025

መንግስት በጤናው ዘርፍ ላይ ትኩረት ሰጥቶ የደሞዝ ጭማሪ እና ጥቅማጥቅም የመሳሰሉ ስራዎች በጤናው ዘርፍ ላይ እየሰራ ባለበት በዚ ወቅት ላይ አንዳንድ የአፋር ክልል ወረዳዎች ላይ ፣ በተለይም በአፋምቦ ወረዳ የጤና ባለሞያዎች የትርፍ ሰዓት ክፍያ ( ዱዩቲ) ከመጋቢት ወር / 2017 ጀምሮ እስከ አሁን ጥቅምት ወር /2018 ድረስ አጠቃላይ የስምንት (8) ወር እንዳልተከፈላቸው እና ከስር እንደምትመለከቱት ባለሞያው በፅሁፍ መልኩ ለወረዳው ጽህፈት ቤት፣ ለወረዳው ፋይናስ ቢሮ ፣ እንዲሁም ለእያንዳንዱ ቢሮ ቅሬታውን ቢያሰማም ፣ ወረዳው ከዛሬ ነገ በሚል የውሸት ቃላት በመስጠት ሰራተኞች በማሰቃየት ላይ ይገኛል ። ሆኖም የአፋር ክልል መንግስት ይሄን የጤና ባለሞያዋች ጉዳይ ትኩረት ሰቶ መፍትሄ ሊሰጥ ይገባል

ምንጭ ፦ Afar press media

የሱማሌ ክልል አመራር ፀረ-ሰላም ሀይል ነው።በሱማሌ ክልል መንግስት መሪነት በአፋር አርብቶአደሮች ላይ የተከፈተው ጦርነት ሴቶችና ህፃናት ላይ ከፈተኛ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል።በኢትዮጵያ ሱማሌ...
07/06/2024

የሱማሌ ክልል አመራር ፀረ-ሰላም ሀይል ነው።

በሱማሌ ክልል መንግስት መሪነት በአፋር አርብቶአደሮች ላይ የተከፈተው ጦርነት ሴቶችና ህፃናት ላይ ከፈተኛ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል።

በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል መንግስት መሪነት ከውጭ ሶማሊያውያን የሽብር ቡድኖች፣ ከኬኒያ እና ከጅቡቲ መንግስት ለዚህ ጦርነት ስባል ከተደራጀ ወታደራዊ ሀይሎች አንድ ላይ ጥምር ጦር በመሆን በአፋር አርብቶአደሮች ላይ በከፈቱት ጦርነት በርካታ ቁጥር ያላቸው ማህበረሰብ ከቤት-ንብረታቸው ተፈናቅለዋል። እንዲሁም በርካታ አዛውንቶች፣ ሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት የሞት ሰለባ ሆነዋል።

N.B ለአብነት ያክል ከዚህ በታች ፎቶ የለጠፍኩባቸው ህፃናትና ሴቶች በዚሁ ሽብርተኛ ቡድን ከቤታቸው ታፍነው የተወሰዱ ናቸው።😥

Office of the Prime Minister-Ethiopia
Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር
INSA- የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር

 #ከአፋርና ሱማሌ ግጭት በስተጀርባ የሚገኙ  መንግስታት....✍️ የአፋርና ኢሳ ግጭት ለዘመናት መፍትሔ አልባ ሆኖ የዘለቀ ግን ደግሞ ለአንድ አላማ የቆሙ  የውጭ ሐይሎች ጠልቃ ገብነት ለግዛ...
05/06/2024

#ከአፋርና ሱማሌ ግጭት በስተጀርባ የሚገኙ መንግስታት....✍️

የአፋርና ኢሳ ግጭት ለዘመናት መፍትሔ አልባ ሆኖ የዘለቀ ግን ደግሞ ለአንድ አላማ የቆሙ የውጭ ሐይሎች ጠልቃ ገብነት ለግዛት መስፋፋት ታቅዶና ታስቦ የተነደፈ በእቅድ የሚመራ ውስብስብ የፖለቲካ አሻጥር በጉልህ የሚስተዋልበት በአደባባይ የሚፈጸም የውጮች ወራሪ ሴራ መሆኑ ግልጽ ነው። እርግጥ ነው ኢሳና አፋር በባህልም፣ በእምነትም፣ በአኗኗርም የሚመሳሰሉ ከአንድ የዘር ሐረግ የሚመዙ ወንድማማች ህዝቦች ናቸው። ነገር ግን የራሳቸው የሩቅ ጊዜ እቅድ ያላቸው #የሱማሌና #የጅቡቲ መንግስታት የራሳቸው ተልዕኮውን ለማስፈጸም እንደመሳሪያ አርብቶ አደር የሆነው ኢሳን በመጠቀም ከአፋር ህዝብ ጋር እሳትና ጭድ ሆኖ ሁሌ መገዳደል ባህል በመሐከላቸው እንዲኖር የጥላቻ ስሜት ውስጥ ዝንተዓለም እንዲኖሩ በማድረግ ከሗላ ደጀን ሆኖው በገንዘብና በመሳሪያ በጉልበት በማገዝ የአፋር ግዛት በሂደት ግዛት ለማድረግ ላለፉት 60 አመታት ለአፍታም ያልቆመ ጦርነት በግፍ እያደረጉ እነሆ ዛሬም ጭምር ሰላም ወዳዱ ችግር እንዲፈጠር እያደረጉ ይገኛሉ። ይሄም ደግሞ ምንም እንኳን እልባት ለመአካላዊ መንግስት ስጋት እስካልሆነ ድረስ መፍትሔ ባይሰጥም ከንጉሡ ጀምሮ እስከ ኢህአዴግ ዘመነ መንግስት ድረስ የሚታወቅ ሐቅ ነው። አስረጂ ማስረጃዎችም ይሄንኑ ያረጋግጣሉ። ወያኔ ከሱማሊያ መንግስት ጋር የጀመረው ኮንትሮባንድ ለችግሩ መስፋፋት ላለፉት 27 የራሱ የሆነ ተጽዕኖ ይዞ ነው የመጣው። ይህ ችግር የጎረቤት አገራት ጠልቃ ገብነት እስካልቆመ ድረስ ግጭቱ መፍትሔ አሁንም አያገኝም። የአፋርና የኢሳ ጉዳይ የፖለቲካ እንድምታ ያለው ግን ደግሞ በችልታ ሊታለፍ የማይገባ ከአፋር አልፎ ለኢትዮጵያ በሂደት ስጋት የሆነ የመሬት ወረራ ነው። የአፋር ጠላት ኢሳ ብቻ ሳይሆን የሱማሌ ክልል፣ የሞቃዲሾና የሱማሌ ላንድ እንዲሁም የጁቡቲ መንግስት ነው።ከኢሳ ጀርባ ሆኖው የአገር ጦር እያሰለፉ አርብቶ አደር የሆነውን የአፋር ህዝብ እያስጨፈጨፉ ነው።🙌

አሁንም የብልፅግና መንግስት አፋጣኝ መፍትሔ ሊሰጥ ይገባል ችግሩ የማያበራ እልቅት ከመፍጠሩ በፊት።🙏

በዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች የተለያዩ ስልጠናዎች ተሰጡ:: ===============ሠመራ ዩኒቨርሲቲ:መጋቢት 27/2016ዓ.ምሠመራ ዩኒቨርሲ ከAmref Health Africa የKefeta ፕሮጀክት...
06/04/2024

በዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች የተለያዩ ስልጠናዎች ተሰጡ::
===============
ሠመራ ዩኒቨርሲቲ:መጋቢት 27/2016ዓ.ም

ሠመራ ዩኒቨርሲ ከAmref Health Africa የKefeta ፕሮጀክት ጋር በመተባበር 850 ለሚሆኑ ተማሪዎች የ life skills እና Effective work habits ስልጠናዎች ተሰጥተዋል።

ስልጠናዎቹ በአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚደንት ስር የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ዳይሬክቶሬት ፣ በተማሪዎች ሙያ ማሻሻያ ማዕከል አስተባባሪነት የተሰጡ ሲሆን:ከመደበኛ መማር ማስተማር ጎን ለጎን ተማሪዎችን ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማገዝ በማለም የተሰጡ መሆናቸው ተገልጿል።

ከዚህ በፊት ከ dereja.com ጋር በመተባበር ለ 950 ተመራቂ ተማሪዎች የ" Employability Skills and Job readiness ስልጠና ተሰጥቷል ሲል የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ዳይሬክቶሬት ገልጿል።

በተጨማሪም http://xn--dereja-vt0a.com/ ጋር በመተባበር በ" Fidel Tutor consult" በኩል በተመረጡ የትምህርት አይነቶች የማጠናከሪያ ትምህርት ለሚሰጡ እና በ መመረቂያ ፅሁፍ አፃፃፍ ስልጠና ለሚሰጡ 15 መምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና (TOT) መሰጠቱም ተገልጿል።
#ማህበረሰቡን እናገለግላለን!!
#ዘገባው የህዝብ ግንኙነት ስራ-አስፈጻሚ ነው::
===================
Samarâ jaamiqat barteenitih baxaabaxsa le aydakaakanitte tece.

Samarâ jaamiqat Amref Health Africak Kefeta diqsita projektî luk cattiimak 850 takke barteenitih life skills kee Effective work habits aydakaakanitte teceem timixxige.

Tama aydakaakan Samarâ jaamiqatak Akaxaamî caagiidak ciggiila prezidantih gubat raaqah yan tû barittô mexxatih maysaasah xayrektoreet barteenitik mihrat maysaasah fanteenah koo baahissol gexseenim kee madab bartiyyaa kee barsiyyak xaqut barteenit dudda gablusak dudda lee qalaltam xiqta barteenit takkuh gexseen aydakaakan kinnih tanim yescessen.

Ahaak afal dereja.com diqsitta missoynâ luk cattiimak 950 takke barteenitih " Employability Skills and Job readiness aydakaakan yontocowweh sugem kassinna.

Ossatinah http://xn--dereja-vt0a.com/ luk cattiimak " Fidel Tutor consult" kabuuk doorimteh tan barittoh qaynoota duddí maqarroosiyyi baritto yontocowwem kee dooqaysimiyyi kusaaqih warkat elle yaktubeenim xiqan gurral aydakaakan taceeh tan 15 takke barseenitih aydakaakan (TOT)yontocowwem qaddoosen.

ትክክለኛ የሠዩ ማህበራዊ ትስስር ገፆችን በመከተል ተቋማዊ መረጃ ዎችን ያግኙ:
ፌስቡክ👇
https://www.facebook.com/susamara2008/
ቴሌግራም👇 https://t.me/SamaraUniversityEthiopia
ዩትዩብ👇 https://youtube.com/channe

" ... ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣ እንመክራለን " - የአማራ ክልላዊ መንግሥት የአማራ ክልል መንግሥት ባወጣው መግለጫ ፤ " የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ለሀገሪ...
28/03/2024

" ... ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣ እንመክራለን " - የአማራ ክልላዊ መንግሥት

የአማራ ክልል መንግሥት ባወጣው መግለጫ ፤ " የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ለሀገሪቱ ቋሚ ቀውስ ምንጭ ከሚያደርጉት ተግባራት እንዲታቀብ " ሲል #አስጠነቀቀ።

የክልሉ መንግሥት ፥ በአሁን ሰዓት የወልቃይት ጠገዴ ፣ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች ህዝብ ለረጅም ዓመታት በ " ህወሓት " በኃይል ተገፍፎባቸው የነበረው የማንነትና ጥያቄና ራስን በራስ የማስተዳደር ነጻነት የተመለሰበት እንደሆነ ጠቁሟል።

ህዝቡም እንደማንኛውም የሀገሪቱ ሕዝብ ሁሉ የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚነት መብቱ ሊቀለበስ የማይችል ነው ብሏል።

" የፕሪቶሪያው የሠላም #ስምምነት ከመፈረሙ በፊት ጀምሮ የአማራ ክልል እንደሌሎቹ ዞኖችና የልማት ትሩፋቶች ሁሉ የአካባቢው ሕዝብም ተጠቃሚ እንዲሆን አድርጓል " ሲል ገልጿል።

ክልሉ ፤ እንደሌሎቹ አካባቢዎች የነዚህ አካባቢ ህፃናትም የመማር መብታቸው እንዲከበር ግዴታውን መወጣቱን ገልጿል።

የትምህርት ስርዓቱን ሰበብ በማድረግ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በአማራ ክልል ላይ ጥቃት ከመፈጸም የማይመለስ መሆኑን የሚገልጽ የጠብ አጫሪ መግለጫ እንዳወጣ ጠቁሟል።

ይህም " ካለፉት ድርብርብ ውድቀቶች ትምህርት አለመውሰድን ከማሳየት የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም " ሲል ተችቷል።

የአማራ ክልል መንግሥት ፥ " ጊዜያዊ አስተዳደሩ ሀገራችንን እና ሁለቱን ክልሎች ወደ #ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራት በመቆጠብ ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረጉ ውይይቶች ላይ እንዲያተኩር እንዲሁም አንድ ሀገር ለመገንባት ለሚፈለገው ዘላቂ ሠላምና ለሕዝቦች አንድነት መጽናት በሚበጅ ሐሳብና ተግባር ላይ እንዲያተኩር እንመክራለን " ብሏል።

ሙሉ መግለጫ ፦ 👇👇

ዩኒቨርሲቲው ለአመራሮች የገዛቸውን ሞተር ሳይክሎች የቁልፍ ርክክብ አደረገ::===============ሠመራ ዩኒቨርሲቲ:መጋቢት 16/2016ዓ.ምሠመራ ዩኒቨርሲቲ ለመካከለኛ አመራሮች በረጅም ጊዜ...
28/03/2024

ዩኒቨርሲቲው ለአመራሮች የገዛቸውን ሞተር ሳይክሎች የቁልፍ ርክክብ አደረገ::
===============
ሠመራ ዩኒቨርሲቲ:መጋቢት 16/2016ዓ.ም

ሠመራ ዩኒቨርሲቲ ለመካከለኛ አመራሮች በረጅም ጊዜ ክፍያ የሚጠናቀቁ 30 ሞተር ሳይክሎችን በውስጥ ገቢው በኩል ገዝቶ ቁልፍ አስረክቧል:: ሞተሮቹ ስራን ለማቀላጠፍ እና የትራንስፖርት ችግርን ለማቃለል ታስቦ የተገዙ መሆኑም ተገልጿል።

ኮሌጅ ዲኖች፣ዳይሬክተሮች፣ስራ አስፈጻሚዎችና የትምህርት ክፍል ሀላፊዎች የሞተር ሳይክል አገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል::

ሞተሮቹን ዶ/ር መሀመድ ኡስማን(ፕሬዚዳንት) እንዲሁም ሁሉም ምክትል ፕሬዝዳንቶች በተገኙበት ቁልፍ አስረክበዋል::
===================
The university handed over the keys of motorcycles to management members.
================
Samara University: March 25/2024

Samara University handed over the keys of 30 motorcycles to middle management members bought through its internal income generating office.

The motors aimed to facilitate work and ease transportation problems and the managers will own them via long term payment.

College deans, directors, executives and department heads have benefited from the motorcycle service.

Dr. Mohammad Usman (President) handed over the keys in the presence of all Vice Presidents.
===================
We serve the community!!
Public and International Relations Executive
com

??  _ተገደሉየመንግስታቱ ድርጅት ሰላም ማስከበር ተልዕኮም ግጭቱን ለማረጋጋት እየሰራሁ ነው ብሏልበደቡብ ሱዳን በጎሳ ግጭት የ56 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተነገረ።በምስራቃዊ የሀገሪቱ ክፍል ጆን...
28/12/2022

?? _ተገደሉ

የመንግስታቱ ድርጅት ሰላም ማስከበር ተልዕኮም ግጭቱን ለማረጋጋት እየሰራሁ ነው ብሏል
በደቡብ ሱዳን በጎሳ ግጭት የ56 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተነገረ።
በምስራቃዊ የሀገሪቱ ክፍል ጆንግሌይ ክልል በኑዌር እና ሙርሌ ጎሳ አባላት ለአራት ቀናት የዘለቀ ውጊያ መደረጉንም ነው ሬውተርስ የአይን አማኞችን ዋቢ አድርጎ ያስነበበው።
የታጠቁ የኑዌር ጎሳ አባላት ወጣቶች በሙርሌዎች ላይ በመተኮስ ግጭቱን ማስጀመራቸው ተነግሯል።
ጉምሩክ እና ሊኳንጎሌ በተባሉት ወረዳዎች ከአራት ቀናት በፊት የጀመረው ግጭት እስካሁን አልበረደም ነው ያሉት አብርሃም ኬላንግ የተባሉ የመንግስት የስራ ሃላፊ።
መንግስት ግጭቱን ለማብረድ እና ለተጎዱት ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እያደረግ ስለመሆኑም ነው ያነሱት።
በግጭቱ ህይወታቸው ካለፈው 56 ሰዎች ውስጥ 51ዱ ጥቃቱን ያስጀመሩት የኑዌር ጎሳ አባላት ስለመሆናቸውም ገልጸዋል።
በደቡብ ሱዳን የመንግስታቱ ድርጅት ሰላም ማስከበር ተልዕኮ ባለፈው ሳምንት የታጠቁ የኑዌር ጎሳ አባላት ወጣቶች በሙርሌዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ እየተንቀሳቀሱ ነው ሲል አስጠንቅቆ ነበር።
ይሁን እንጂ በ2011 ነጻነቷን ያወጀችው ሀገር ግጭቱን ማስቆም አልቻለችም።
የሰላም ማስከበር ተልዕኮው የተከሰተውን የጎሳ ግጭት ለማብረድ በተሽከርካሪዎች የሚያደርገውን ቅኝት ማጠናከሩን ገልጿል።
ደቡብ ሱዳን በተለይ ኑሯቸውን በአርብቶ አደርነት ያደረጉ ሰዎች ለከብት እና መሬት በሚያደርጓቸው ውጊያዎች በርካታ ዜጎቿን አጥታለች።
December, 28, 2022
hptt//aljezeeraafar.com

ህወሓት የታጠቃቸውን ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ለመንግስት የማስረከብ ስራ እስከ ሀሙስ ይፈጸማል- አምባሳደር ሬድዋንየጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁ...
28/12/2022

ህወሓት የታጠቃቸውን ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ለመንግስት የማስረከብ ስራ እስከ ሀሙስ ይፈጸማል- አምባሳደር ሬድዋን

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ትናንት በትዊተር ገጻው ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ በ2ኛው የናይሮቢ የሰላም ስምምነት መሠረት ህወሓት የታጠቃቸው ከባባድ የጦር መሳሪያዎችን ለመንግስት የማስረከብ ስራ እስከ ነገ ሀሙስ እንደሚከናወን አስታውቀዋል።

በተጨማሪም የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት በመቀሌ ሕገ-መንግሥታዊ ኃላፊነቱን መወጣት ይጀምራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
https://aljezeeraafar.com /

👉  #ከፀኃይ አምስት እጥፍ መሞቅ የቻለው የቻይና “ሰው ሰራሽ (አርቲፊሻል)”ፀኃይ  “EAST” የሚል መጠሪያ ያለው ‘ሰው ሰራሽ ፀኃይ ለኤሌክትሪክ ኃል ለማመንጨት ይችላል የተባለ ሲሆን፤ ይ...
28/12/2022

👉 #ከፀኃይ አምስት እጥፍ መሞቅ የቻለው የቻይና “ሰው ሰራሽ (አርቲፊሻል)”ፀኃይ

“EAST” የሚል መጠሪያ ያለው ‘ሰው ሰራሽ ፀኃይ ለኤሌክትሪክ ኃል ለማመንጨት ይችላል የተባለ ሲሆን፤ ይህ ፈጠራ ገደብ የሌለው ንጽሁ የተፈጠሮ የኃይል ምንጭ ለማግኘት የሚያስችል ነው ተብሏል።

እውነተኛውን ፀሃይ በማስመሰል የተሰራው የሰው ሰራሽ ፀሐዩ ሃይድሮጅን እና ዱተሪየም ጋዞችን እንደ ሀይል ማመኝጫ ነዳጅነት በመጠቀም ንጹህ ኢመርጂን ለማመንጨት ታስቦ ዲዛይን መደረጉ ታውቋል።

በዚህ መልኩ የተሰራው “EAST” የሚል መጠሪያ ያለው ‘ሰው ሰራሽ ፀሐይ’ በ1 ሺህ ሰከንድ ከ100 ሚሊየን ዲጊሪ ሴልሽየስ ሙቀት 1 ሚሊየን አምፒር ከረንት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማምንጨት የተያዘውን ግብ ማሳካቱን ተነግሯል።
https://aljezeeraafar.com/

"ሱዳን በወረራ በያዘችው የኢትዮጵያ መሬት ላይ ዴሞግራፊ ለመቀየር በማሰብ መሰረተ ልማት እየገነባች ነው" - አቶ ደመቀ መኮንንኢትዮጵያ ካጋጠማት ችግር ጋር ተያይዞ ሱዳን ባለችበት እንድትቆይ...
18/05/2022

"ሱዳን በወረራ በያዘችው የኢትዮጵያ መሬት ላይ ዴሞግራፊ ለመቀየር በማሰብ መሰረተ ልማት እየገነባች ነው" - አቶ ደመቀ መኮንን

ኢትዮጵያ ካጋጠማት ችግር ጋር ተያይዞ ሱዳን ባለችበት እንድትቆይ ንግግር መደረጉንና ኢትዮጵያም ይህንኑ ማድረጓን የገለጹት አቶ ደመቀ፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግን የኢትዮጵያን አቋም ከማበረታታት ባለፈ የካርቱምን ድርጊት አለማውገዙን አስታውቀዋል፡፡
https://am.al_jezeera.afar.com/

Address

Logiya
Logya
7240

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Al -Jazeera Afar press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Al -Jazeera Afar press:

Share