Firew

Firew let Advert your brand prducts here!

14/04/2026

ሃሜትን ማስወገድ ይቻላል?

ሃሜት በሰው ልጆች መካከል ጥላቻን በመዝራት ለዓመታት የዘለቀን ጓደኝነት የሚንድ፣ በግለሰቦች መካከል አለመግባባትን በመፍጠር በጥላቻ መንፈስ እንዲተያዩ መንገድ የሚጠርግ እና በጥቅሉ ማህበረሰቡን ለማይወጣው ማህበራዊ ቀውስ የሚዳርግ ሲሆን ይህ ማህበራዊ በሽታ በባለትዳሮች፣ በቤተሰብ፣ በጎረቤትና በጓደኝነት መካከል ያለውን መልካም ግንኙነት በማሻከር፣ የሰው ልጅ በፍቅር፣ በሰላምና በመተማመን መኖር እንዳይችል እንቅፋት ይሆናል።
ሃሜትን በግልጽ ውይይት በመፍታት ሰላማዊ ኑሮን ማስቀጠል እንደሚቻል ታውቃላችሁ?

ብዙዎች ሃሜትን እንደ ተፈጥሮአዊ ባህሪ ቆጥረው ማስወገድ እንደማይቻል ቢያምኑም፣ የአውራ አምባ ማህበረሰብ መስራች የሆነው ዙምራ ኑሩ ግን ሃሜትን በውይይት በመፍታት ሰላማዊ ኑሮን ማስቀጠል እንደሚቻል በተግባር ያስተምራል።

ዙምራ ኑሩ ይህንን ስር የሰደደ ችግር ለመቅረፍ እንደ ዋነኛ መፍትሄ የሚያስቀምጠው ነጥብ፣ ግልጽነትና እዚያው ባለበት የመነጋገር ባህልን ማዳበር ነው። አንድ ሰው ሲሳሳት ወይም ስህተት ሲሰራ ሲታይ፣ ጉዳዩን ለሌላ ሶስተኛ ወገን ወስዶ በማማት የሰውን ስም ከማጥፋት ይልቅ ለባለቤቱ እዚያው በግልጽ መናገር ይገባል። ቁጣን አስወግዶ በፍቅር እና በፈገግታ “ይህን ነገር እንዴት አየኸው?” ብሎ መጠየቅ፣ ሃሜት ሳይወለድ እዚያው እንዲቀር በማድረግ ትልቅ ሚና ይጫወታል።

ወሬን ከማመላለስ ይልቅ ግለሰቡ ስህተቱን እስኪያስተካክል ድረስ በግልጽ በመመካከር እውነትን ማምጣት የሰው ልጅ ዋነኛ ተግባር ሊሆን ይገባል። የሌላውን ሰው ሀብትና ንብረት እንደምንጠብቀው ሁሉ፣ በሃሜት ምክንያት የሚጠፋውን የሰው ስም እና ስብዕና መጠበቅም የራስን ሀብት እንደመጠበቅ ይቆጠራል።

በአጠቃላይ ሃሜት የሰውን ስም ብቻ ሳይሆን የራስን የህሊና ሰላም እና ክብር የሚያፈርስ ማህበራዊ ቀውስ በመሆኑ፣ እንደ በሽታ ተቆጥሮ ሊታከም ይገባል። ዙምራ ኑሩ እንደሚመክረው፣ እውነትን ፊት ለፊት የመናገርን መድሃኒትነት በመጠቀም የራስንና የሌላውን ሰብዕና መጠበቅ ይቻላል። ይህን የግልጽነትና የውይይት ባህል በተግባር በማዋል፣ በጥላቻና በጥርጣሬ ፋንታ ፍቅርንና መተማመንን የሰፈነበት ማህበረሰብ መገንባት የሁላችንም ድርሻ ነው።

ሙሉ ቪዲዮውን ለመከታተል https://youtu.be/Jb-RwZo5dSg

30/03/2026

"ሰርቶ ሰርቶ ሲጨርስ የሚጣለው እቃ እንጂ የሰው ልጅ አይደለም !"

በመላው አለም የሚኖሩ ዜጎች በእርጅና ወይም ደግሞ በጤና እክል ምክንያት የፈለጉትን ያክል ሳይንቀሳቀሱ፣ የጀመሩትን ውጥን ከግብ ሳያደርሱ ፣ ለወደፊት ቀጣይ ህይወታቸው መሰረት ሳይጥሉ ፣ ሰው እያለ የሚያግዛቸውና የሚረዳቸው ባለማግኘታቸው የሚበሉት ፣ የሚጠጡት ፣ የሚለብሱት አጥተው ፥ ቢታመሙ የሚታከሙበት ቸግሯቸው በየጎዳናውና በየደሳሳ መኖሪያቸው ተቀምጠው ማየት የተለመደ ጉዳይ ነው።

የአውራ አምባ ማህበረሰብ መስራች የክብር ዶክተር ዙምራ ኑሩም ይህንኑ ችግር በመገንዘብ ከአራት ዓመት እድሜው ጀምሮ ከሚያነሳቸው መሰረታዊ ሃሳቦች መካከል አንዱ " በጤና እጦትም ይሁን በእርጅና ምክንያት ተዳክመው ለስራ ብቁ ያልሆኑ አቅመ ደካሞችን መርዳት " የሚለው ይገኝበታል።

የክብር ዶክተር ዙምራ ኑሩም ሃሳቡን እንዲህ ሲል ይገልፃል " የወደቁ ደካሞች በጤናም ሆነ በእርጅና ምክንያት ከስራ ተፈናቅለው በየሜዳው ወድቀው ይበሉት ፣ ይጠጡት ፣ ይለብሱት ያጡ ሆነው አያለሁ ። ጠንካራው ከጠንካራው ጋር በልቶ ፣ ጠጥቶ ፣ ስቆ ፣ ተጫውቶ ሲወጣ አቅመ ደካሞችን የሚያስባቸው የለም ፥ እነዚህ ደካሞች እንደኛ ሰው ናቸው መብላት ፣ መጠጣት ፣ መልበስ ያስፈልጋቸዋል ያን እንዳያገኙ አቅሙ የላቸውም እኛ ጥለናቸው ከሄድን ማን ይደርስላቸዋል? እኛ ጥለናቸው ከሄድን እኛም አንድ ቀን እንወድቅ ይሆናል ። በምንወድቅ ጊዜ እሚያስበን እንፈልጋለን ። እኛ እሚያስበን እንደምንፈልግ ሁሉ ለምን እነሱን ጥለናቸው እንራመዳለን? ለሰው ደራሹ ሰው እንጂ ሌላ ማን ይመጣለታል? የሚል ጥያቄም ያነሳል።

አውራ አምባዎች ሰርቶ ሰርቶ ሲጨርስ የሚጣለው እቃ እንጂ የሰው ልጅ አይደለም ሲሉም ይደመጣሉ ። ከንግግር ባለፈም በተግባር እየኖሩት አሳይተዋል። በዚህ የአረጋዊያን ክፍል ውስጥ ደካማ ወገኖች የየራሳቸው የማረፊያ ክፍል ኖሯቸው ፣ በየሶስት ቀን የሰውነት ንፅህናቸው ተጠብቆ ፣ በየሳምንቱ ልብሳቸው እየታጠበ ፣ በየቀኑ የመኖሪያ ግቢያቸው እየተፀዳ በአረጋዊያን ተንከባካቢዎች ተገቢውን ምግብና እንክብካቤ እያገኙ በፍቅርና በደስታ እየኖሩ ይገኛሉ ።

የአውራ አምባ ማህበረሰብ "ትልቁ ሃብት ሰው ነው ፥ ሌላው ቀጥሎ የሚገኘው ገንዘብ ነው " ብሎም ያምናል ። ቀጥሎ የሚገኘው ገንዘብ ትልቁ ሃብት የሆነውን ሰውን ሰውን ለመመገብ የሚሆንና ተሰርቶ የሚገኝ ነው ይላሉ። ስለሆነም በእርጅናም ይሁን በጤና ችግር ምክንያት ሰርተው ራሳቸውን መደገፍ የማይችሉ ደካሞችን ዋስትናቸውን የሚሸፍነው ማህበረሰቡ ነው።

" ደካማ ወገንን መርዳት የእድገት መሰላል እንጂ ውድቀትን አያመጣም " የክብር ዶክተር ዙምራ ኑሩ ።

ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት https://youtu.be/R31tnZGykgk

24/03/2026

በተልካሻ ምክንያት ትዳር አይፈርስም!

‎ትዳር በመተማመን፣ በመተሳሰብና በፍቅር የደረጀ ከሆነ ባለትዳሮች የአብራክ ክፋይ የሆኑ ልጆችን አፍርተው አቅፈው ለመሳም ይበቃሉ፣ ከስራ ተመልሰው በብርሃን ወደተሞላው የፍቅር ቤታቸው ለመግባት ይጓጓሉ፣ ጊዜያቸውንም በሳቅና በጨዋታ ያሳልፋሉ፣ በጥቅሉ ያማረ፣ የሰከነና ለሌሎችም አራዓያ የሚሆን የማይነቃነቅ ምሰሶ ያለው ቤተሰብ ለማፍራት ይችላሉ።

‎ነገር ግን ትዳር በስሜታዊነት ከተመራ፣ ከኛ ለእኔ ከቀደመ፣ እኔ ያልኩት ብቻ ካልሆነ በሚል እንቢተኝነት ከታጀበ ባለትዳሮች ቤታቸው ላይ መዋል ማደር ቀርቶ ለደቂቃዎችም ቢሆን እንኳን ለመቀመጥ አይፈልጉም። ቀስ በቀስም ስላፈሯቸው የጋራ ፍሬ ልጆች ሳይጨነቁ፣ በጋራ ሆነው ስላፈሩት ሃብትና ንብረት መበተን ግድ ሳይሰጣቸው ትዳራቸውን ያፈርሳሉ።

‎በዚህ አሁን ባላንበት ዘመን የፍቺ ቁጥር ከጋብቻ መጠን ጋር እየተስተካከለ መጥቷል። ምክኒያቶቹ ምናልባትም በውይይት ሊፈቱ የሚችሉ ሲሆኑ በጥቃቅን ችግሮች ሳይቀር ትዳራቸው ሲበተን ይስተዋላል።

‎እስኪ ስንቶቻችን በውይይት በሚፈቱ ተልካሻ ምክኒያቶች ትዳራችንን በትነናል? ስንቶቻችንስ ያለ እናት ወይ ያለአባት ፍቅር አድገናል?

‎"ቀድመን ታዘልቀኛለች፣ ያዘልቀኛል ብለን ትዳርን እንመሰርታለን እንጂ በትንሽ ትልቁ ትዳር እንዲፈርስ አናደርግም" ይህ የአውራ አምባዎች መርህ ነው።

‎ልጆች ተገቢውን እንክብካቤና ፍቅር ማግኘት አለባቸው፣ መብታቸው ተጠብቆ ማደግ ይኖርባቸዋል የሚለው ሃሳብ የክብር ዶ/ር ዙምራ ኑሩ የልጅነት ጥያቄው ሆኖ ቆይቷል። ማህበረሰቡንም ከመሰረተ በኋላ በተግባር እንዲከዎን አድርጓል። ስለሆነም ልጆች የወላጆቻቸውን ንፁህ ፍቅርና እንክብካቤ ማግኘት ሲሹ ወላጆችም አቅማቸው እስከፈቀደ ልጆቻቸውን በፍቅርና በእንክብካቤ የማሳደግ ትልቅ ሃላፊነት አለባቸው።

‎ትዳር ከፈረሰ ግን ልጆች ያንን ማግኘት አይችሉም። ይባስ ብሎ ከእናት ከአባቶቻቸው ጋር ይለያያሉ፣ ወላጆችም በጋራ ሆነው ለፍተው ያጠራቀሙትን ሃብት ይበትናሉ። ስለሆነም አውራ አምባዎች ትዳርን ለማፍረስ ያስችሉናል ያሏቸውን "ሁለት" ችግሮች ብቻ እንንገራችሁ።

‎* የመጀመሪያው፡ ከባለትዳቶች መካከል የመካንነት ችግር ከተከሰተና በህክምና የተረጋገጠ ከሆነ እንዲሁም ከባለትዳሮቹ መካከል አንደኛው ልጅ የመውለድ ፍላጎት ካለው ሲሆን ተስማምተው የመኖር ፍላጎት ካላቸው ግን በግዴታ እንዲያፈርሱ አይደረጉም።
‎*ሌላኛውና ሁለተኛው፡ በህክምና ሊድን የማይችል ለግብረ-ስጋ ግንኙነት የማያበቃ ችግር ከተከሰተ ነው።

‎ከዚህ ውጭ ያሉ ችግሮች ቢከሰቱ እንኳን ተወያይቶ፣ በሃሳብ የበላይነት በመመራት ትዳርን ያስቀጥላሉ እንጂ እንዲፈርስ አያደርጉም። ችግሩ ከእነሱ አልፎ ለልጆቻቸውም ስለሚተርፍ።

ሙሉ ቪዲዮውን https://youtu.be/VcycVumEHWk

14/03/2026

እርስዎታ የአክብሮት መገለጫ አይደለም!
ከሰው ልጆች መካከል የትኛው ነው ዘመዱ የትኛውስ ነው ባዕዱ? ይህ ጥያቄ የክብር ዶ/ር ዙምራ ኑሩ የዘመናት ጥያቄ ነበረ። ዙምራ ይቀጥልናም ሰዎች በሰውነታችን የአንድ አዳም(አደም) እና ሄዋን(ሃዋ) ልጆች የአንድ ሃረግ ፍሬዎች ነን። የአዳም ዘር ሳይቀየር ባዕድነት በየት አልፎ ገባ? በማለት ጥያቄውን ሲያቀርብ ኖሯል። ታዲያ ሁሉም የሰው ልጆች ወንድሞች እና እህቶች ነን ብሎ የሚያምነው ዙምራ እና የመሰረተው ማህበረሰብ "እርስዎታ የአክብሮት መገለጫ አይደለም ይልቁንም በሰው ልጆች መካከል ባዕድነትን የፈጠረ ነው።" ሲሉ ይናገራሉ።

እርስዎታ የአክብሮት መገለጫ ቢሆን ኖሮ በመጀመሪያ ክብር ሊያገኙ የሚገባቸው እናት እና አባት ነበሩ። ነገር ግን እርስዎ(አንቱ) አይባሉም ለምን? ? ? ?

ከሰባት ትውልድ በኋላ ያለው ግን እርስዎ ይባላል። ታዲያ እርስዎታ የአክብሮት መገለጫ ወይስ የወገን (ዘመድ) መለያ መሳሪያ? ? ? እስኪ ምላሾቻችሁን አስቀምጡልን።

የማህበረሰቡ መስራች የሆነው የክብር ዶር ዙምራ ኑሩም አንቱ ብለው ለሚጠሩት ሰዎች " ወንድማችሁ ነኝና አንቱ አትበሉኝ ፣ አታርቁኝ ፣ ዘመዳችሁ ነኛና ዘምድ አድርጉኝ ይላቸዋል።"
ሙሉ ቪዲዮውን ለመከታተል ከፈለጋችሁ
https://www.youtube.com/watch?v=6O2kugQ1c2s

“ሁለም በየቤቱ በሰላም ፍለጋ ውይይት ሰላምን ይዞ ከመጣ ዓለም ሰላም ትሆናለች”
09/03/2026

“ሁለም በየቤቱ በሰላም ፍለጋ ውይይት ሰላምን ይዞ ከመጣ ዓለም ሰላም ትሆናለች”

ውይይት የችግሮች ሁሉ መፍቻ ቁልፍ መሳሪያ!

አለም በጦርነትና በግጭት በምትናጥበት በዚህ ጊዜ አውራ አምባዎች ግን ከ1964 ዓ.ም ጀምሮ በሰላምና በፍቅር እየኖሩ ይገኛሉ። “ሁለም በየቤቱ በሰላም ፍለጋ ውይይት ሰላምን ይዞ ከመጣ ዓለም ሰላም ትሆናለች” ይህ የአውራ አምባዎች ድንቅ አባባል ነው። ስለሆነም እኚህ የሰላም ተምሳሌት የሆኑ ህዝቦች በየ 15 ቀኑ “ሰላምን ፍለጋ” የተሰኘ የቤተሰብ ውይይት አላቸው።

የውይይቱ መድረክ መሪ በተወያዮቹ ቤተሰብ አባላት በጉባኤ ይመረጣል፡፡ ለመድረክ መሪነት በእጩነት የሚቀርቡት ከህፃናት እስከ አዋቂ ያሉት የቤተሰቡ አባላት በሙሉ ናቸው። በዚህ ውይይት በጉርብትና የሚቀራረቡ ከ3 እስከ 4 የሚሆኑ ቤተሰቦች አንድ ላይ በመሆን ይወያያሉ።አንድ ቤተሰብ ብቻውንም ማድረግ ይችላል።

ለቤተሰብ ውይይቱ አጀንዳ ሆነው የሚቀርቡት የስራ እቅድ ምን ደረጃ ላይ አንደደረሰ፣ መጥፍ አሰራርንና መጥፍ አነጋገርን ማስወገድ በተመለከተና ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮችንም ተመርኩዞ ይሆናል።

ተወያዮችም ባሳለፉት የሁለት ሳምንታት ቆይታ ውስጥ የነበራቸውን የፀባይ ሁኔታ፤ የስራ እቅድና መሰል ጉዳዮችን እያነሱ ይመካከራሉ። እያንዳንዱ የውይይቱ ተሳታፊም ግለሂሱን ያቀርባል፤ በሌሎች የውይይቱ ተሳታፊዎችም ሃሳብና ምክር ይቸረዋል። የተሳሳተበት ወይም ያጠፋው ጥፋት ከነበረም አስተካክሎ ለቀጣይ እንዲገኝ ይመከራል፤ ንፁህ ከሆነ ደግሞ “ጥሩ ነው ቀጥልበት” የሚል ማበረታቻ ይሰጠዋል።

በዚህ ውይይት ህፃናት ተሳታፊዎች ሲሆኑ የውይይቱ መሪ እንዲሆኑም ይደረጋል። በራስ መተማመናቸው እንዲጨምር፣ እራሳቸውን መግለፅ እንዲችሉና ፍርሃትንም አስወግደው ቤተሰቦቻቸውንም ጭምር እንዲመክሩ ያስችላቸዋል።

ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት https://youtu.be/5ZBeT-MiYIU

01/03/2026
23/02/2026

የዛሬ መልካምነት፤ የነገ የህይዎት መሰረት!!

የወጣትነት ወይም የአፍላነት የእድሜ ክልል የወደፊት የህይዎት ኑሯችን ላይ ከፍተኛ አስተዋጾ አለው።በወጣነት የተጀመረ መጥፎ ባህሪ፣ ድርጊቶችና ልማዶች ቀጥሎ በሚመጣው ህይዎት ላይ አሉታዊ የሆነ ተጽዕኖ ያሳድራሉ። በተቃራኒው ወጣትነት በመልካም እሳቤዎችና ስራዎች ከተገነባ ግን ለመጪው ህይዎት ጥሩና የማይናድ ወይም የማይፈርስ የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ ያክል ነው። ታዲያ ዛሬ ሁሌም ስለ መልካምነት መስራትና ማውራት ስለማይሰለቻቸው የአውራ አምባ ወጣቶች እንካችሁ እንበላችሁ።

የአውራ አምባ ወጣቶች ጎትጓችም ሆነ ቀስቃሽ አይፈልጉም። ምን መስራትና ማድረግ እንዳለባቸው ሌሎች እስኪነግሯቸው አይጠብቁም። እኚህ ወጣቶች ዘወትር በሳምንት አንድ ቀን መላ የማህበረሰቡን አካባቢ ያጸዳሉ፣ የአረጋዊያንን ልብስ ያጥባሉ... ሌሎችንም በርካታ ስራዎች በበጎ ፈቃደኝነት ያከናውናሉ። በተለይም ደግሞ አቅመ ደካሞች ለሚያስፈልጋቸው ነገር ሁሉ ከጎናቸው በመቆም አይዟችሁ ይሏቸዋል፣ ያግዟቸዋል። የወጣቶቹ የስራ እንቅስቃሴ በዚህ ብቻም የሚቋጭ ነገር አይደለም። ችግኞችን ይተክላሉ፣ በማህበረሰቡ ውስጥ የሚገኙ በርካታ የመሰረተ ልማት ስራዎችንም በንቃት ይከውናሉ።

ይህ ለምን የሆነ ይመስላችኋል? ምክንያቱም ዘወትር ጠዋት፣ማታ በማህበረሰቡ መስራች የክብር ዶክተር ዙምራ ኑሩ ዙምራ ኑሩ፣ በማህበረሰቡ አባላትና በቤተሰቦቻቸው ዘንድ በስነ-ምግባር ታንጸው የነገ ሃገር ተረካቢ ዜጋ እንዲሆኑ ምክር ስለሚሰጣቸውና በመካከላቸው ያለው የዕርስ በዕርስ ፍቅርም የተለየ በመሆኑ ነው። ወጣቶቹ ሰበብ ፈልገው ተገናኝተው የሚጨዋወቱበትንና ፍቅራቸውን የሚያጠነክሩበትን መንገድ ይፈጥራሉ። ስራዎቻቸውንም በሳቅ፣ በጨዋታ፣ በፍቅርና በመተጋገዝ ያከናውናሉ።

ይህ የመልካምነት ድርጊት ከአሁን በፊት በታላላቅ እህት፣ ወንድሞቻቸው የተጀመረ፤ ዛሬ ላይ የደረሰና ነገም በመጪው ተረካቢዎች ዘንድም የሚቀጥል የህይዎት ስንቅ ነው።

ታዲያ እኚህ መልካምነትን የተላበሱ ወጣቶች ለነገ ህይዎታቸው ጣፋጭ ስንቃቸውን እያዘጋጁ አይደሉምን?

https://www.youtube.com/watch?v=8cE9aLPDXag

With AWRA AMBA – I just made it onto their weekly engagement list by being one of their top engagers 🎉
19/02/2026

With AWRA AMBA – I just made it onto their weekly engagement list by being one of their top engagers 🎉

አውራ አምባወች ባለፋባቸው 54 የውጣ ውረድ አመታት ከመኖሪያ ቀያቸቸው ተፈናቅለው ለከፋ ስደት ተዳርገዋል፤ የሚበላና የሚጠጣ በሌለበት ቀናትን ገፍተዋል፤ አፈሙዝ ዞሮባቸው የእልቂት ዘመቻ ተደ...
14/02/2026

አውራ አምባወች ባለፋባቸው 54 የውጣ ውረድ አመታት ከመኖሪያ ቀያቸቸው ተፈናቅለው ለከፋ ስደት ተዳርገዋል፤ የሚበላና የሚጠጣ በሌለበት ቀናትን ገፍተዋል፤ አፈሙዝ ዞሮባቸው የእልቂት ዘመቻ ተደግሶባቸዋል፣ በሽታ ወገኖቻችን ነጥቋቸዋል ሌላም... ሌላም....።

ነገር ግን ይህ ሁሉ ውጣ ውረድ ለሰው ልጆች ሲሉ ካሰሩለት አላማ የኋሊት ጎትቶ ሊያስቀራቸው አልቻለም። ይልቁኑ በእልህና በአልሸነፍ ባይነት ጥርሳቸውን ነክሰው በመታገላቸው ለዛሬ ፍሬ በቅተዋል።

በአውራ አምባወች የታሪክ ማህደር ተሰንደው ከተቀመጡ ውስብስብ ችግሮች መካከል በአካባቢው ማህበረሰብ ጋር የነበረው ችግር ነው።

እናጠፋችኋለን ብለው ቦንብና ክላሻቸውን ይዘው ለመጡት የአከባቢው ሰወች ግን እሾህን በእሾህ ሳይሆን "ሰላም ባይሏችሁ ሰላም በሏቸው፣ ቢያኮርፏችሁ አታኩርፏቸው ባያውቁን ነው፣ ሲያውቁን ነገ ወንድሞቻችን ናቸው" በሚለው የዙምራ አስተምሮ እሳት ይዘው ለመጡት ውሀ ይዘው በመጠበቅ አሳልፈውታል።

አሁን ላይ ያ ሁሉ ጊዜ አልፎ አንድም ችግርና መጠፋፋት ሳይፈጠር ለዛሬ መልካም ግንኙነት መሠረት ሆኗል።

አውራ አምባወች ባለፋባቸው 54 የውጣ ውረድ አመታት ከመኖሪያ ቀያቸቸው ተፈናቅለው ለከፋ ስደት ተዳርገዋል፤ የሚበላና የሚጠጣ በሌለበት ቀናትን ገፍተዋል፤ አፈሙዝ ዞሮባቸው የእልቂት ዘመቻ ተደግሶባቸዋል፣ በሽታ ወገኖቻችን ነጥቋቸዋል ሌላም... ሌላም....።

ነገር ግን ይህ ሁሉ ውጣ ውረድ ለሰው ልጆች ሲሉ ካሰሩለት አላማ የኋሊት ጎትቶ ሊያስቀራቸው አልቻለም። ይልቁኑ በእልህና በአልሸነፍ ባይነት ጥርሳቸውን ነክሰው በመታገላቸው ለዛሬ ፍሬ በቅተዋል።

በአውራ አምባወች የታሪክ ማህደር ተሰንደው ከተቀመጡ ውስብስብ ችግሮች መካከል በአካባቢው ማህበረሰብ ጋር የነበረው ችግር ነው።

እናጠፋችኋለን ብለው ቦንብና ክላሻቸውን ይዘው ለመጡት የአከባቢው ሰወች ግን እሾህን በእሾህ ሳይሆን "ሰላም ባይሏችሁ ሰላም በሏቸው፣ ቢያኮርፏችሁ አታኩርፏቸው ባያውቁን ነው፣ ሲያውቁን ነገ ወንድሞቻችን ናቸው" በሚለው የዙምራ አስተምሮ እሳት ይዘው ለመጡት ውሀ ይዘው በመጠበቅ አሳልፈውታል።

አሁን ላይ ያ ሁሉ ጊዜ አልፎ አንድም ችግርና መጠፋፋት ሳይፈጠር ለዛሬ መልካም ግንኙነት መሠረት ሆኗል።
watch more
https://youtu.be/uqwliuCitQE

Address

Logya
7240

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Firew posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share