ከርታታዉ መምህር።

ከርታታዉ መምህር። የተለያዩ መረጃዎች እና መፀሀፍቶችን የሚያገኙበት ተወዳጅ ነ?

29/06/2024

Mayso Qafar Ummatahimi

Rabí rookah xaagu ***Samarâ jaamiqatak Doktoor Reedo qaadaa kee kusaaq fanteenah addat  Exhibition (aysaxaaxag)mihratlii...
06/05/2024

Rabí rookah xaagu
***
Samarâ jaamiqatak Doktoor Reedo qaadaa kee kusaaq fanteenah addat Exhibition (aysaxaaxag)mihratlii kee Qaadâ fanteena baxaa baxsa le afittet aysexeexeg ayfaaf acayuk sugeh yan kasloyti Gifta Macammad Acmadiin Caydara Qasa dirrik 28/08/2016 I.L.L amok radah kaa yibbixeh yan lakimah a manok rabah nek baxsime.

Tohuk gexaak Samarâ jaamiqatih ayyunti taamâ wakliitah suge Gifta Macammad Acmaddiin Caydarah rabi hagga ken heeh yanim aysixxiguk kaak raaqeh yan kay buxah maraay, kay kataysiisiiy, kay wadaay kee kacantoolitih inkih imaam kee sabri yaceem qaaginna iyya !
Innaa lillaahi wa innaa ileyhi raajiquun.

  ላለፉት 30 አመታት ባህሉን ታሪኩን ለትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ ሚናውን ተጫውተዋል። የአፋር ቅርፅ በመጠበቅ ትልቁን አሰተዋጽኦ ያበረከቱት የሀገር ዋርካ ዛሬ ወደአኼራ ማረፋቸውን ስሰማ ...
06/05/2024





ላለፉት 30 አመታት ባህሉን ታሪኩን ለትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ ሚናውን ተጫውተዋል። የአፋር ቅርፅ በመጠበቅ ትልቁን አሰተዋጽኦ ያበረከቱት የሀገር ዋርካ ዛሬ ወደአኼራ ማረፋቸውን ስሰማ አዝናለሁ። የቱሩዝም ባለሙያ ጋሼ አህመዲን መሀመድ ከዚህ አለም በሞቱ ተለዩን። አላህ ጀነተል ፍርዶውስ ይወፍቃቸው። ለቤተሰቡም ሶብሩን ይስታጣቸው።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡AMN-ታህሳስ 10/2016 ዓ.ምየሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 26ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ...
20/12/2023

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

AMN-ታህሳስ 10/2016 ዓ.ም

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 26ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

የ26ኛው መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች፡-

1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትን፣ ካሣ የሚከፈልበትን እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን በቀረበው ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡

መንግስት ለሕዝብ ጥቅም በሚያከናውናቸው የልማት ሥራዎች ሲባል የመሬት ይዞታ እንዲለቁ ለሚደረጉ ባለይዞታዎች ተገቢና ተመጣጣኝ ምትክ ይዞታ፣ ካሣ መስጠትና ድጋፍ ማድረግ እንዲቻል ግምት ውስጥ መግባት የሚገባቸውን መሠረታዊ መርሆዎች ለመደንገግ፣ ካሣን የመተመን፣ የመክፈል እንዲሁም ተነሺዎችን መልሶ የማቋቋም ሥልጣንና ኃላፊነት የተጣለባቸውን አካላት እና ግዴታዎቻቸውን በግልጽ መድረግ በማስፈለጉ በስራ ላይ ያለውን አዋጅ ቁጥር 1161/2011 የሚያሻሽል ረቂቅ አዋጅ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡

ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ይጸድቅ ዘንድ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየዉ የሜዳይ፣ ኒሻን እና ሽልማት ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ በልዩ ልዩ ዘርፎች የላቀ ተግባር ለፈጸሙ ዜጎች እና ግለሰቦች እዉቅና መስጠት በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ለሀገር ለሚያበረክቱት የላቀ አስተዋጽኦ ኢትዮጵያ ባለዉለታ አድርጋ እንደምታከብራቸዉ እውቅና የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ ሌሎችም የእነርሱን አርአያነት እንዲከተሉ የሚያበረታታ፣ የስራ ፈጠራ እንዲስፋፋ፣ ሁለንተናዊ እና ቀጣይነት ያለዉ ብልጽግና እንዲረጋገጥ ፋይዳው የላቀ በመሆኑ በኢፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት የተደነገገውን የሜዳይ፣ የኒሻን እና የሽልማት አሰጣጥ ስርዓት መተግበር የሚያስችል፣ ለአተገባበሩም ህጋዊ ሥርዓት የሚዘረጋ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡

ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል እንዲጸድቅ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

3. በተጨማሪም ምክር ቤቱ የሕዝብ በዓላትን፣ የዕረፍት ቀናትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቷል፡፡

የሕዝብ በዓላት እና የእረፍት ቀናት ለዜጎች ሥነ-ምግባርና ስነ-ልቦና ግንባታ እንዲሁም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦዋችው ከፍተኛ በመሆኑ ሕጋዊ እውቅና መስጠት እና በብሔራዊ ደረጃ እንዲከበሩ ማድረግ የሚገባ በመሆኑ፤ ኃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ታሪካዊ ሥርዓታቸውን ጠብቀው ሊከበሩ የሚገባ በመሆኑ፤ የዜጎችን የእርስ በእርስ መልካም ግንኙነትና መተሳሰብ የሚያጎለብቱ እንዲሆኑ የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡

ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል እንዲጽደቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

4. በመጨረሻ ምክር ቤቱ የተወያየው በአምራች ኢንዱስትሪ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ዕድገት እና መዋቅራዊ ሽግግር መሳለጥ የላቀ ሚናውን እንዲወጣ፤ ለውጪ ምንዛሪ ግኝት ለማሳደግ፣ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ፣ ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት እና ለዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጠራ መደላድል የሚሆን የፖሊሲ ማእቀፍ ሚያስፈልግ በመሆኑ፤ የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ለማሳደግና ለማበረታታት፣ የኢንዱስትሪዎች መስፋፋት በአካባቢና በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ክብካቤ መርሆዎቻችን ላይ የተመሰረተ እንዲሆን፣ ከሌሎች ዘርፎች ጋር ያለውን ትስስርና ቅንጅት ለማሳደግ የሚያስችል ረቂቅ ፖሊሲ ተዘጋጅቶ ምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡

ምክር ቤቱም በረቂቅ ፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ መወሰኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ጠፈርተኞች የምርምር ስራቸውን የሚጀምሩት በመንኮራኩሯ እና በመሬት መካክል ያለው ስበት /gravity/ ዜሮ  መግባቱን ከረጋገጡ በኃላ ነው::በመሬት  እና በመንኮራኩሯ መካክል ያለው የመሬት ...
06/09/2023

ጠፈርተኞች የምርምር ስራቸውን የሚጀምሩት በመንኮራኩሯ እና በመሬት መካክል ያለው ስበት /gravity/ ዜሮ መግባቱን ከረጋገጡ በኃላ ነው::በመሬት እና በመንኮራኩሯ መካክል ያለው የመሬት ስበት ዜሮ ሳይገባ ሰራቸውን ከጀመሩ ይከሰከሳሉ::

በተመሳሳይ አዲስ ለውጥ ለመምጣት በአሮጌው አስተሳሳብ እና በእኛ መካክል ያለው ግንኝነት ዜሮ መግባት አለበት::

አለበለዚያ ::አእምራችን ከአሮጌው አስተሳ ነፃ ሳይሆን ከላይ አዲስ አስተሳሰብ ከጨመርንበት :አሮጌም አዲስም ያልሆነ የሁለት አስተሳሰቦች ቅየጥ አስተሳሰብ ይፈጥራል::

ይህ የአሮጌና የአዲስ አስተሳሰብ ቅየጥ /ውሁድ / አስተሳሰብ አንድ እርምጃ ወደፊት ሁለት እርምጃ ወደኃላ የሚሄድ እንቅስቃሴዎች ሁሉ ለውጥ ናቸው የሚል ነውጥኛ አስተሳሰብ ነው::
ይህ አይነት አስተሳሰብ መንታ ፊት /dual face/ ያለው አደናጋሪ አስተሳሰብ ሲሆን ሂዶ ሂዶ አያስፈልግኝም ብለህ የተውከውን አሮጌው አስተሳስብ እንድትናፊቅ ያደርገሃል::
********
By ጣሃ አህመድ

ምክንየታዊ ትውልድ :ለሁለንትናዊ ብልጽግና::************************************ ምክንየታዊነት  ትውልድ ማለት ሲሜቱን መምራት ማስተዳድር :መግዛት :መንዳት የሚችል ትው...
22/08/2023

ምክንየታዊ ትውልድ :ለሁለንትናዊ ብልጽግና::
************************************
ምክንየታዊነት ትውልድ ማለት ሲሜቱን መምራት ማስተዳድር :መግዛት :መንዳት የሚችል ትውልድ ማለት ነው::

የሚነዳ ምክንያታዊ ትውልድ ::ምክንየታዊ ትውልድ ማለት እያንዳንዱ እንቅስቃሴውን ለምን?
እንዴት? መቼ? በማን? ስለምን? በምን? እያለ የሚጠየቅ :የሚያስጠየቅ :በሀሳብ ልእልና የሚያምን :የተሳሳቱ ሀሳቦችን ሀሳብን የሚያምን ነው::

ምክንያታዊ ትውልድ ያልታረሙ አንደበቶችን በታረሙ አንደበቶች ይተካል:ስሜታዊነትን በአመክንዪ ይቀየራል፤
ገረድነትንና አሽከርነትን በጌትነትና በነጻነት ይለውጣል፤ አስመሳይነትን በግልጽነት ያከስማል፤ ሀሳብ አልባነትን በዕሳቤ የበላይነት ያረጋግጣል፤ ርዕይ አልባነትን በርዕይ ባለቤትነት ይተካል፤ በኢ - ምክንያታዊነት ላይ ምክንያታዊነትን ያነግሳል፡፡

ምክንያታዊ ትውልድ ከትላንት ይማራል፤ በጎውን ከትላንት በመውሰድ ዛሬ ላይ የራሱን አሻራ ያኖራል - ለማኖርም ይተጋል:ለነገና ከነገ ወዲያ በማሰብ ትውልዳዊ መሠረትን በማይናወጥ ዕሳቤ ላይ ይጥላል፡፡ የሰው ልጅ ከምክንያታዊነት ሲርቅ ወደ ሲሜታዊነት ይቀርባል፡፡

ከምክንያታዊነት ይርቃል፡፡ አንደኛው ከሌላኛው ጋር ሕብረት የለውም፡፡ ሊኖረውም አይችልም፡፡ የአንዱ ባህሪያትና ጠባያት ለሌላኛው ባህሪያትና ጠባያት ግጣም መኾን የማይችሉ ተቃራኒ የኹነቶች መገለጫ ናቸው፡፡

ምክንያታዊ ትውልድ በምንም አይነት መንገድ መንጋ አይኾንም፡ለአመክንዮ፣ ለዕውነትና ለዕምነት ግን መንጋ ይኾናል፡፡

ምክንየታዊ ትውልድ የድርገቱን ትክክልኝነት በአድራጊው ማንነትና ምንነት ምክንያታዊ ትውልድ አንድን ድርገት ወይም ሀሳብ ለመቃውም ወይም ለመደገፍ አድራጊው ወይም የሀሳቡ ባለቤት ማነው ብሎ በመንጋ የሚቃውም ወይም የሚደግፍ ሳይሆን ድርጊቱ ወይም ሀሳቡን ከባሌቤቱ ለይቶ በሚዛናዊነትና ለአገርና ለህዝብ ያለው አዎንታዊና አሉታዊ አስተዋጽኦ አመዛዝኖ የሚቃውም ወይም የሚደገፍ ትውልድ ማለት ነው::

ምክንያታዊ ትውልድ አንድን ሀሳብ በመንጋ ሲደግፍ መንጋነቱ በምክንያቱ ላይ ካለው ዕምነት የሚመነጭ እንጂ በአድራጊው ወይም በሀሳቡ ባለቤት ባለው እምነት ወይም ከአድራጊው ወይም ከሀሳቡባለቤት ጋር ባለው ግንኝነት ወይም ዝምድና ላይ ተመርክዞ አይደለም::

ሲሜቱን የሚነዳ ምክንያታዊ ትውልድ እንኳንስ የራሱ ያለፈ ትውልድም ኾነ የሚመጣ ትውልድ አለኝታ ነው! ምክንያታዊ ትውልድ እያንዳንዱን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴውን በምክንያት በመምራት ያለፈ ትውልድ በጎ ዕሴት ጠባቂና አስጠባቂ፤ የራሱን ትውልዳዊ ኃላፊነት በመወጣት የሚቀጥለውን ትውልድ ታሳቢ ያደረገ ኹለንተናዊ እንቅስቃሴ በማድረግ የሚመጣው ትውልድ መኩሪያና አለኝታ ይኾናል፡፡
***************************
ስለ ሲሜታዊ ትውልድ በቀጣይ አቀርባለሁ -----

ምክንየታዊ ትውልድ :ለሁለንትናዊ ብልጽግና::************************************ምክንየታዊነት ትውልድ ማለት ሲሜቱን መምራት ማስተዳድር :መግዛት :መንዳት የሚችል ትውልድ ማለት ነው:: የሚነዳ ምክንያ....

የብልፅግና መአከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ   (አሊ ጃፓን)በረ/ፕ   መታሰርን አስመልክት FB ገፁ ላይ ያሰፈረው መልዕክት፦  Slide Show
17/08/2023

የብልፅግና መአከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ (አሊ ጃፓን)
በረ/ፕ መታሰርን አስመልክት FB ገፁ ላይ ያሰፈረው መልዕክት፦ Slide Show

የብልፅግና መአከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ (አሊ ጃፓን)በረ/ፕ ከሊል አሊ መታሰርን አስመልክት FB ገፁ ላይ ያሰፈረው መልዕክት፦ ***********ጠንካራ ወጣቶችን በማሰር ይሄን ጠያቂ ሀይል ....

06/08/2023

የአፋር የጥበብ ባለቤት ቀደም ሲል ካወጣቸዉ ዘፈኖች መካከል ምን አለ (በጊሌ የቆሰለ ሰዉነት በማባበል አይድንም) እኛ ህዝባችን ይቀድማል ብለን በጀመርነዉ ትግል ጓደኛዬን ላስቀድም ማለት ስህተት ነዉ ማለት ወንጀል በመሆኑ

ሁሌ ትክክል ነህ የሚሉትን ሰብስቦ ከመጓዝ ስህተታችንን በግልጽ እየተያየን እንሂድ ማለት ጥፋት ሆኖ የተወሰኑ ሰዎችን ጥቅም ብቻ ከማስከበር ለስማችን እንትረፍ ማለት ክህደት በመሆኑ አንተም በመንገደህ እኛም በመንዳችን ማለት ደሞ ሽንፈት ሆኖብህ እንደ ቀይ ምንጣፍ ልትረገጠን ስትል እንደ አየሉ ተራራ ስለከበድንህ የፖለቲካ ልዩነታችንን እንደ ተሸከምን እንለያይ ማለታችን ደሞ ስጋት ስለሆነብህ

አንድም ስለምትፈራን አንድም ደሞ ባለጊዜነትን ማንፀባረቅ በሚመስል ስሜት በራስህ ሳይሆን በስርህ ባሉ አረም ተክሎች በመመራት እና
በመመከር አገር ያወቀዉ ፀሀይ ያወቀዉ የደርግ እርምጃ ለመዉሰድ መሞከር ለታሪክም ተፅፎ የሚቀመጥ ዉጤቱ ደሞ ለሀቅ ባለቤት የሚመለስ ሲሆን ብልፅግናችን እንደ ድርጅት የአገሪቱ ህገመንግስትም እንደ ዜጋ እኩል አርጋን በድርጅቱ በህገመንግስቱ ደሞ ተጠይቀን ስለምንጓዝ ወንጀለኛዉ ና ንፁሁ ጤነኛዉና በሽተኛዉ ሀቀኛዉና ዉሸታሙ ህዝቡ እንደምያቀዉ ሁሉ የሁሉ ቁልፍ የሆነችዉ ጊዜ ደሞ ትመልስልናለች የፖለቲካ ልዩነቱን በወገኑ ደምና እስር ለመፍታት የሞከረ የመጀመሪያው የተማረና የተሳሳተ ፖለቲከኛ መባሉም መሆኑም አይቀርም።

ስኬታማ የሆኑ ሰዎች ሰኬታማ እንዲሆኑ ከሚያደርጋቸዉ ብቃት አንዱ ፅናት መኖር ነዉ፡፡ ፅናት በአንተርፕረነርሽፕ ትለቅ ስፈራ ይዞ የሚገኝ የአንተርፕረነር ባህሪ ነዉ፡፡ ዐላማ ያላቸዉ ሰዎች ፅና...
01/08/2023

ስኬታማ የሆኑ ሰዎች ሰኬታማ እንዲሆኑ ከሚያደርጋቸዉ ብቃት አንዱ ፅናት መኖር ነዉ፡፡ ፅናት በአንተርፕረነርሽፕ ትለቅ ስፈራ ይዞ የሚገኝ የአንተርፕረነር ባህሪ ነዉ፡፡

ዐላማ ያላቸዉ ሰዎች ፅናት ከሌላቸዉ ዋጋ የለዉም፡፡ በአለም ላይ ስኬታማ የሆኑ ሰዎች የፅናት ተምሳሌት ናቸዉ፡፡ ማንም ሰዉ አለማዉን ለማሳከት ፅናት ካለዉ በእርግጠኝነት ማሳካት እንደሚችል ታመኖበታል፡፡

ችግር ባይኖር ኑሮ ፅናት አያስፈልግም፡፡ ጽናት ችገሮችና መሰናክሎች እንዴት እንደሚፈቱ ያሰተምረናል፡፡ ፅናት አንድን አላማ እሰከሚሳካ ድረስ ተስፋ ሳይቆረጡ ደጋግሞ መመኮር ማለት ነዉ፡፡ ስኬታማ ሰዎች ባለ ራእይ ናቸዉ፡፡

ራእያቸዉ በረዥም ጊዜ ከፋፍለዉ ማለት በ5፡በ10፡በ15 ወዘተ የሚሳካ ብለዉ ያሰቀምጣሉ፡፡ይህንን የረዥም ጊዜ ራእይ ለማሳካት ጽናት እንደሚስፈለግቸዉ ያምናሉ፡፡

ይህም የፀጥታው ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መሄዱን፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ አስተዳደር ደካማነትን ተከትሎ ነው። መግለጫ********* የኒጀር ጦር ፕሬዝዳንቱን ከስልጣን አነሳ፣ ሩሲያ...
31/07/2023

ይህም የፀጥታው ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መሄዱን፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ አስተዳደር ደካማነትን ተከትሎ ነው።

መግለጫ
*********
የኒጀር ጦር ፕሬዝዳንቱን ከስልጣን አነሳ፣ ሩሲያን አበረታች እና የምእራቡ ዓለም አነጋጋሪ የአፍሪካ ተጽእኖን ይነፋል?

ጁላይ 27 ቀን 2023
-----------------------------
የኒጀር ፕረዚዳንት መሀመድ ባዞም የሳህልን ደጋፊ የምዕራባውያን መሪ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ከስልጣን ተወገዱ። የሀገር መከላከያ ብሄራዊ ምክር ቤት እሳቸውን በቁጥጥር ስር አውሎ ድንበሮች የተዘጋበት የሰዓት እላፊ እገዳ ጥሎ ሁሉንም ተቋማት አግዷል። መፈንቅለ መንግስቱ የሳህልን ክልል መንግስት በወሰደው እርምጃ እና በኑሮ ውድነት የተነሳ በመበሳጨቱ ሳይሆን አይቀርም። ምዕራባውያን ኃያላን በኒጀር ከፍተኛ መዋዕለ ንዋያቸውን በማፍሰስ በአካባቢው ቁልፍ አጋር አድርጓታል። ዩናይትድ ስቴትስ ባዙም በአስቸኳይ እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል ነገርግን መፈንቅለ መንግስቱ በአካባቢው የሚካሄደውን አመጽ ለመቋቋም ምዕራባውያን የሚያደርጉትን ጥረት ሊያወሳስበው ይችላል። ይህ ሁኔታ ሩሲያ በኒጀር እና በሰፊው ክልል ላይ ተጽእኖዋን ለመጨመር እድል ይሰጣል.

#ኒናር #እኛ #ሩሲያ #አሂድ #የአለም ዜና

27/07/2023

የአፍሪካ ሩስያ ጉባኤ

26/07/2023

አሹራእ ማለት:- የሙሀረም 10ኛው ቀን ሲሆን
***********************************
“ ነብዩሏህ አደም ወደ ምድር የወረዱበት ቀን
“ ነብዩሏህ ኑህ መርከባቸው የተረጋጋችበት ቀን
“ ነብዩሏህ ኢብራሂም የተወለዱበት ቀን
“ ነብዩሏህ ሙሳ ከፊርዐውን የዳኑበት ቀን
“ ነብዩሏህ አዩብ ከህመማቸው የተፈወሱበት ቀን
“ ነብዩሏህ ዩሱፍ ከጉድጓዱ የወጡበት ቀን
“ ነብዩሏህ ሱለይማን ንግስናን የተሰጡበት ቀን
“ ነብዩሏህ ዩኑስ ከአሳ ነባሪው ሆድ የወጡበት ቀን ነው።

በመሆኑም ነገ #ሐሙስ ሙሃረም 9 እና ዕለተ #ጁምዓ ሙሃረም 10 የአሹራ ፆም በመሆኑ በመፆም እንዲያሳልፉት ምኞታችንን ገለጽን::

ያልተነካው  ነዳጅን የሚያስከዳው  የኢትዮጵያ ሀብት....🇪🇹👌ፖታሽ  ኢትዮጵያ  አላት ብቻ  ሳይሆን የምድራችን ትልቁ  ያልተነካ  ፖታሽ ባለቤት ነች ።  በጥናት የተረጋገጠ  ብቻ  5 ቢሊዮ...
26/07/2023

ያልተነካው ነዳጅን የሚያስከዳው የኢትዮጵያ ሀብት....🇪🇹👌

ፖታሽ ኢትዮጵያ አላት ብቻ ሳይሆን የምድራችን ትልቁ ያልተነካ ፖታሽ ባለቤት ነች ። በጥናት የተረጋገጠ ብቻ 5 ቢሊዮን ቶን ፖታሽ በኢትዮጵያ ምድር ይገኛል በአጠቃላይ እስከ 14 ቢሊየን ቶን ይደርሳል ።

አጥኚዎች እንዳረጋገጡት ከሆነ ይህ በአፋር ደናኪል ዲፕሬሽን እየተባለ የሚጠራው ሌላ ፕላኔት በሚመስለው የኢትዮጵያ ክፍል የሚገኘው የፖታሽ ክምችት ለ 200 ዓመታቶች ቀጥ አርጎ መጥቀም የሚችል ነው።

ፖታሽ በግብርናው ዘርፍ አለም የሚጠቀምበትን የእርሻ ማዳበርያ ለማዘጋጀት የሚውል ሲሆን ፤ ከዛ ውጭ ለበርካታ አገልግሎች እጅግ ይፈለጋል ... ለባትሪ ፣ ለሳሙናና ዲተርጀንት ፣ ለእንስሳ መኖ ፣ የበረዶ ግግር ለማቅለጥ ፣ ለምግብ ማቀነባበሪያ፣ ለመድሃኒት፣ ለፋብሪካዎችና ላልጠቀስናቸው በርካታ ጉዳዮች ይፈለጋል። በአጭሩ ለመግለፅ ግን ፖታሽ ማለት በአሁን ወመን "ምግብ " እንደማለት ማለት ነው ።

አሁን ባለው የአለም ገበያ 1 ቶን ፖታሽ 266$ ዶላር ሲሆን ይህም ሲሰላ የትሪየን ዶላር ክምችት ላይ እንደተቀመጥን ያሳያል። የተፈጥሮ ጋዛችንን አውጥተን ወደ ማዳበሪያነት ስንቀይረው ደግሞ አሁን ባለው የማዳበሪያ ዋጋ መምታት ነው። ነገር ከሁሉ በላይ 40 ሚሊየን ሄክታር የሚታረስ ለም መሬት ባላት ሃገራችን ላይ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ ሲውል ምን ያክል ሀገር ሊቀይር እንደሚችል አስረጂ አይፈልግም ።
በክምችት ደረጃ ከኢትዮጵያ ያነሰ 1ቢሊየን ቶን ያላት ካናዳ የአለማችን ቁጥር አንድ የፖታሽ ኤክፖርተር ስትሆን በሱም እስከ 8 ቢሊየን ዶላር በየአመቱ ገቢ ታገኝበታለች ።

ታዲያ ይህን ሃብት እናለማለን ያሉ የተለያዩ የውጭ ኩባኒያዎች ገብተው የነበረ ሲሆን አብዛኞች በቀደሙት ዓመታት በሙስና የተመለመሉ አቅም የሌላቸው በመሆናቸው ጥቅም ላይ ሳይውል ቆይቷል።

ነገር ግን ጠ/ሚ አብይ አህመድ በቅርቡ በፓርላማ ንግግራቸው የህዳሴው ግድብ በ2024 ሲጠናቀቅ ቀጣይ የኢትዮጵያ ሙሉ ስራና ትኩረት እዚሁ የፖታሽና የማዳበሪያ ጉዳይ ላይ እንደሚሆን አረጋግጠዋል።

ኢትዮጵያን አውቀን አልሰራንባትም እንጂ ኢትዮጵያ እጅግ ሃብታም ሃገር ናት ወገን !!

ሀገር የሚቀየረው በስራ ብቻ ነው !! 🇪🇹

ኢትዮጵያዊነት Ethiopiawinet

07/07/2023
https://youtu.be/NXsHK86nhuU
28/06/2023

https://youtu.be/NXsHK86nhuU

Rashid_saalic_4_sanatak_afal_annah_iyye_sugeMelaagi yamaatuh macalteh tangicille labhak abxi reedal tanim kee gutqeenimih tan. " Giclo baahe marak wadir gac...

ብርቱካን ሚደቅሳ የስራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን አስታወቁየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአፈ ጉባኤ ጽህፈት ቤት የስራ መልቀቂያ ማስ...
26/06/2023

ብርቱካን ሚደቅሳ የስራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን አስታወቁ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአፈ ጉባኤ ጽህፈት ቤት የስራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን አስታወቁ። ለአራት ዓመታት ከስድት ወራት ምርጫ ቦርድን የመሩት ብርቱካን ከመጪው ነሐሴ 1፤ 2015 ጀምሮ ስራ ለመልቀቅ መወሰናቸውን መወሰናቸውን የገለጹት በተረጋገጠ የፌስቡክ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ነው።

ብርቱካን ከዋና ሰብሳቢነታቸው የሚለቅቁት ጤናቸውን “በሚገባ ለመጠበቅ የረጅም ጊዜ እረፍት” ስለሚያስፈልጋቸው እንደሆነ በዚሁ የፌስ ቡክ መልዕክታቸው ገልጸዋል። በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አቅራቢነት ብሔራዊ የምርጫ ቦርድን እንዲመሩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህዳር 13፤ 2011 የተሾሙት ብርቱካን፤ መልቀቂያቸውን ለፓርላማ አፈ ጉባኤ ጽህፈት ቤት ያስገቡት ሰኔ 5፤ 2015 መሆኑን በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል።

ዋና ሰብሳቢዋ ስራ ሲጀምሩ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን “ተዓማኒ እና ራሱን ችሎ ምርጫን ማከናወን የሚችል ተቋም” የማድረግ ህልም እንደነበራቸው ስንብታቸውን ይፋ ባደረጉበት አጭር ጽሁፍ ገልጸዋል። ብርቱካን የምርጫ ቦርድን ዋና ሰብሳቢነት ከተረከቡ በኋላ፤ ተቋሙ ስድስተኛውን አጠቃላይ አገራዊ ምርጫ እና በደቡብ ክልል ሶስት ህዝበ ውሳኔዎችን አካሂዷል። ብርቱካን በስንብት ጹሁፋቸው ምርጫ ቦርድን “ተዓማኒነት በማሻሻል ረገድ፣ በተቻለ አቅምም የፓለቲካ ፓርቲዎችን እንቅስቃሴዎች ለማገዝ ባደረግነው ጥረት ስኬታማ ነን ብዬ አምናለሁ” ሲሉ ጽፈዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

በአፋር ክልል የወደሙትን ትምህርት ቤቶች ጠግኖ ወደ ሥራ ለማስገባት ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።
21/06/2023

በአፋር ክልል የወደሙትን ትምህርት ቤቶች ጠግኖ ወደ ሥራ ለማስገባት ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።

በአፋር ክልል የወደሙትን ትምህርት ቤቶች ጠግኖ ወደ ሥራ ለማስገባት ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የ4ኛ ዙር አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠናን ሁሉንም የስልጠና ቀናት ሳያቆራርጡ ያጠናቀቁ ሰልጣኞች የቢዝነስ የአዋጭነት ምክረ ሀሳባቸውን እንዲያ...
21/06/2023

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የ4ኛ ዙር አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠናን ሁሉንም የስልጠና ቀናት ሳያቆራርጡ ያጠናቀቁ ሰልጣኞች የቢዝነስ የአዋጭነት ምክረ ሀሳባቸውን እንዲያስገቡ ጥሪ አቀረበ፡፡

ባንኩ ከወራት በፊት በ4ኛ ዙር የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠና 112 ሺህ ለሚሆኑ ስራ ፈጣሪዎች ስልጠና መስጠቱ ይታወሳል፡፡

ከሰልጣኞች መካከል አምስቱንም ቀናት ስልጠናውን የተከታተሉና ሰልጠነው ያጠናቀቁ ለምስክር ወረቀት ዝግጁ የሆኑ ሰልጣኖች ብቻ ወደ ባንኩ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች በመቅረብ ሪፖርት እንዲያደርጉና የቢዝነስ አዋጭነት ሀሳባቸውን እንዲያስገቡ ነው ባንኩ ያሳሰበው፡፡

ሙሉ በሙሉ ስልጠናውን ተከታትለው ለአጠናቀቁ ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት የማዘጋጀቱ ስራ እየተሰራ ሲሆን፣ የሰልጣኞችን የስራ ጊዜ በአግባቡ ለመጠቀም ሲባል ቀሪ የሌለባቸው ሰልጣኞች የቅድመ ዝግጅት ስራቸውን እንዲጀምሩ ነው ባንኩ ሁኔታዎችን ያመቻችው፡፡

ሰልጣኞች ወደ አምራች ኢንዱትሪ ዘርፍ ለመግባት ያላቸውን የስራ ተነሳሽነት ባንኩ መደገፍና ማበረታታት ስላለበት የስልጠና የምስክር ወረቀቱ እስኪሰራጭ ድረስ በልዩ ሁኔታ ማስታናገድ እንደሚገባ ስለታመነበት ነው፡፡

በዚህም መሰረት ሙሉ በሙሉ ሁሉንም የስልጠና ቀናት ሳያቆራርጡ የሰለጠኑ ሰልጣኞች እድሉን በመጠቀም ወደ ተመዘገቡባቸው የባንኩ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች በመቅረብ በተመቻቸው እድል እንዲጠቀሙ ባንኩ ጥሪ አቅርቧል፡፡

Address

Logya

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ከርታታዉ መምህር። posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category