Sheka TV

Sheka TV This is the official Sheka TV page - where you can get all the latest news in Amharic, Sheki Noono, Majang.

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ"  ሕብረተሰቡ በነፃነት ተሳትፎ ያደረገበት መሆኑ ተገለጸ ።‎ምርጫው ሠላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁን  መነሻ በማድረግ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል  የሸካ ዞን የ...
05/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ" ሕብረተሰቡ በነፃነት ተሳትፎ ያደረገበት መሆኑ ተገለጸ ።

ምርጫው ሠላማዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁን መነሻ በማድረግ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የሸካ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ውይይት አካሄዷል።

‎ምርጫው ስኬታማ እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከቱት አካላትም ምስጋና የማቅረብና በድህረ ምርጫ ዙሪያ በማሻ ከተማ ላይ የጋራ ምክር ቤቱ የውይይት መድረክ ተደርጓል ።

‎የሸካ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት በማሻ ከተማ ውይይት ያካሄደ ሲሆን ምርጫው ሠላማዊ ሆኖ መጠናቀቁ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር መስፋቱን የሚያመላክት በመሆኑ ትልቅ ስኬት ስለመሆኑ ተነስቷል።

‎የሸካ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ አስማማው አለሙ የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሂደት ዉጤታማና ለቀጣይ ተሞክሮ የተወሰደበት እንደሆነ ተናግረዋል።

‎ከቅድመ-ዝግጅት ጀምሮ የጋራ ምክር ቤቱ ምርጫው ሠላማዊ ፣ዴሞክራሲና ሁሉን አሳታፊ እንዲሆን በተደረገው ጥረት የተሻለ ስራ መሰራቱን ገልጸው ይህ ደግሞ በንግግር የሚያምን ትውልድ መፈጠሩን የሚያመለክት ስለመሆኑም ሰብሳቢው በአፅንኦት አንስተዋል።

‎ የሸካ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ አለማየሁ አለሙ በበኩላቸው 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ከዚህ ቀደም ከነበሩ የምርጫ ሂደቶች ሕብረተሰቡ በነፃነት ተሳትፎ ያደረገበት መሆኑን ተናግረዋል።

‎ የጋራ ምክር ቤቱ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ መንግስት ያስቀመጣቸውን የህግ ማዕቀፎች በመከተል የዴሞክራሲ ምህዳሩን ማስፋት የተቻለበት እና በፉክክሩም የትብብር ሚዛን እንዲጠብቅ ማድረግ የተቻለበት መሆኑን ገልፀው ይህን ልማድ ማዳበር ይገባል ብለዋል።

‎አሁን ላይ የተጀመሩ የዴሞክራሲ ግንባታ ስራዎች በቀጣይም በተሻለ ተቋማዊ ጥንካሬ ማስቀጠል እንደሚገባም ምክትል ሰብሳቢው ጠቁመዋል።

‎በምርጫዉ ዕለት በዞኑ በሚገኙ ሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ከንጋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽት ድረስ ህብረተሰቡ ለፈለገው የፖለቲካ ፓርቲ ያለማንም ተጽዕኖ ድምፅ መስጠት እንደቻለም በጋራ ምክር ቤቱ ውይይት ላይ ተገልጿል።

‎ለስኬታማነቱ ደግሞ የህዝቡ ሚና የጎላ በመሆኑ እውቅና መስጠት እንደሚገባም ተጠቁሟል።

‎በተለይ በየደረጃው የሚገኙ የጸጥታ መዋቅር የጎላ አስተዋጽኦ ማበርከት መቻላቸውም የተገለፀ ሲሆን ይህም እስከ ድህረ ምርጫ ድረስ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ተብሏል።

‎የምርጫ ውጤት ምንም ሆነ ምን የሁሉም ፓርቲዎች ትግል ኢትዮጵያን ማሻገር ብቻ በመሆኑ በድህረ ምርጫ ወቅት የምርጫ ቦርዱን ህግ ማክበርና ማስከበር ላይ ሁሉም ፓርቲ፣ ለአመራሮቹ፣ ለአባላቱና ለደጋፊው ስለድረ ምርጫ ግንዛቤን የማስጨበጥ ስራን ማጠናከር እንደሚገባም በአጽንኦት ተነስቷል።

‎የመንግስት መዋቅር ደግሞ የመሪነት ሚናውን በአግባቡ መወጣት እንደሚጠበቅበት የተገለጸ ሲሆን በተለይ የመራጩን ህዝብ ስነልቦናን መጠበቅ ላይ ትኩረት እንዲደረግም አስተያየት ተሰጥቷል ።

‎በድህረ ምርጫ ወቅት የዴሞክራሲ ስርአት የሚፈተንበት በመሆኑ ሁሉም ነገር በጥንቃቄ መመራት እንደሚባ የተገለፀ ሲሆን መንግስት ለመመስረት የሚያስችል ድምፅ የሚያገኘዉ አንድ ፓርቲ ቢሆንም በጥቅሉ አሸናፊ ኢትዮጵያ እንደሆነችና እንዲሁም የህዝቡን ድምጽ ማክበር ላይ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባም ተነስቷል።

‎የዞኑን መንግስት ጨምሮ አጠቃላይ የምርጫው ሂደት ሰላማዊና የተሳካ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሚናቸውን ለተወጡ ሁሉ ምስጋና ያቀረበው የጋራ ምክር ቤቱ ውጤቱ እስኪገለጽ ድረስ የምርጫ ቦርድ ህግ እንዲከበር ብርቱ ስራ ከሁሉም የፖለቲካ ፓርቲ እንደሚጠበቅ የጋራ ምክር ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል ።

‎ዘጋቢ: ታሪኩ ታደሰ

ሸካ ቴቪ ማሻ 28/09/2018
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማገኘት
YouTube
https://www.youtube.com/-y7q
Telegram
https://t.me/D02MpvQ_owNDE0
Instagram
t.me/D02MpvQ_owNDE0
Tiktok
tiktok.com/
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61574375731590

ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላ...
05/06/2026

ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ

ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል!

‎የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት
‎የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር።

የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል። በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክብርት ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፥ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆኑን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይሄንን ምርጫ «የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ» ሲል ሰይሞታል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ እውቅና ከተሰጣቸው 55 ድርጅቶች 65,299 የታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፥ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም።

‎አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይሄንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከእውነታው ፈጽሞ የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሰረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዴሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚልዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረጋግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን ዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር።

‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፣ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፣ ሂደቱን ለጠበቁት የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዴሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጣናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ!

‎ስለ ኢትዮጵያ ልማት
‎ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፣ ሀገራቸውን በፍጹም የዴሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል።

‎ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢፌዴሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም። ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፥ ይሄም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ይሄንን መነቃቃት መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይሄም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል።

‎እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፥ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢልዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፥ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል። የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይሄም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፣ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው።
‎የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፥ ይሄም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፥ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች የታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፥ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው።

‎ግብርና፣ አምራች ኢንደስትሪና ቴክኖሎጂ
‎በግብርናው ዘርፍ፣ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚልዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፥ ይሄም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው።

ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኙ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው። ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች። የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል። አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፥ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።

‎የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚልዮን ቶን ወደ 15 ሚልዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢልዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል። እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች።

‎በቴክኖሎጂው ዘርፍም፥ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፥ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል።

‎የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ
‎በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከትሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ።

እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው። መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያድርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል።
‎እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል።

‎በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል።

መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል።

‎በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው።


ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም!

የአከባቢ ጥበቃ፤ ለምድር ሕልውና የሚደረግ ርብርብ የሰው ልጅ የተፈጥሮ ጌታ ነው፡፡ በተፈጥሮ ላይ የሰለጠነ ብቸኛው ፍጥረትም ነው፡፡ በምድር ላይ የሚገኙ ሁሉንም ነገሮች የመጠቀምና የማጥፋት ...
05/06/2026

የአከባቢ ጥበቃ፤ ለምድር ሕልውና የሚደረግ ርብርብ

የሰው ልጅ የተፈጥሮ ጌታ ነው፡፡ በተፈጥሮ ላይ የሰለጠነ ብቸኛው ፍጥረትም ነው፡፡ በምድር ላይ የሚገኙ ሁሉንም ነገሮች የመጠቀምና የማጥፋት ስልጣኑና ውሳኔው የራሱ ነው፡፡ ነገር ግን እነዚህን ነገሮች በአግባቡ መጠቀም ካልቻለ በራሱ በሰው ልጅ የሚያስከትሉት ጉዳት እጅግ የከፋ ነው፡፡

ተፈጥሮና የሰው ልጅ እግጅ የተቆራኙ ናቸው፡፡ ተፈጥሮ ለሰው ልጅ የምትሰጠው ተዘርዝሮ የማያልቅ ሁለንተናዊ ግልጋሎት አላት፡፡ ይሁን እንጂ የሰው ልጅ በተፈጥሮ ላይ የበረታ ክንዱን በማሳረፉ ዳፋውም በዚያ ልክ እየበዛ መጥቷል፡፡

ለዚህም ይመስላል በተፈጥሮ ጥበቃ ላይ ባሳየው ቸልተኝነት ምክንያት በተለያየ ጊዜ በከባድ አውሎ ነፋስ፤ በጎርፍ፤ በሰደድ እሳት በመሳሰሉት አደጋዎች እየተቀጣ ያለው፡፡

ይህንን የተረዳው የዓለም አቀፉ ማህበረሰብም አካባቢን አለመጠበቅና አለመንከባከብ ሊያመጣ የሚችለውን ጣጣ ለመቀልበስ በማሰብ በየዓመቱ የአካባቢ ቀን እንዲከበር አውጇል፡፡

የዓለም የአካባቢ ቀን በየዓመቱ ግንቦት 28 ቀን 2018 ይከበራል። ዘንድሮም “የአየር ንብረት ለውጥን ተፅዕኖ ለመቋቋም” ወይም “Climate Action’’ በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል።

በዛሬው ዕለት ይህ ቀን በተለያዩ አካባቢዎች ችግኝ በመትከል፤ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ፤ የአካባቢ ጽዳት ስራን በመስራትና መሰል አካባቢን በሚጠብቁና የተፈጥሮን ዘላቂነትን የሚያረጋግጡ ተግባራትን በመከወን እየተከበረ ነው፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) እ.ኤ.አ.ከ1973 ጀምሮ ቀኑን የሰየመው በዓለም አቀፍ ደረጃ በብክለት፣ በደን መጨፍጨፍና በአየር ንብረት ለውጥ እየደረሰ ያለውን አደጋ ለመከላከል፣ የሕዝቦችን ግንዛቤ ለማሳደግና መንግሥታት ለአካባቢ ጥበቃ ቁርጠኛ ፖሊሲዎችን እንዲቀረጹ ለማንቃት ነው።

ዓለም አቀፍ የአካባቢ ቀንን ስናስብ ለሕይወት ዋስትና የሚሆን ለተፈጥሮ ጥሪ ምላሽ በመስጠት መሆን ይኖርበታል፡፡

አካባቢን አለመጠበቅ ለአየር ብክለት፣ ለድርቅ፣ ለበረሃማነትና ለጎርፍ አደጋዎች ያጋልጣል። በሰው ልጅ ላይም የመተንፈሻ አካላት በሽታዎችን የሚያስከትል ሲሆን፣ የግብርና ምርታማነትን በመቀነስ ለረሃብ፣ ለስደትና ለከፋ ድህነት ይዳርጋል። የተፈጥሮ ሚዛንን መጠበቅ በዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ላይ የሚፈጥረውን ሁለንተናዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ዋነኛ መሳሪያ ነውና፡፡

ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሙቀት አማቂ ጋዝ ልቀት የምታበረክተው አስተዋጽኦ ከ 0 ነጥብ 5 በመቶ በታች ቢሆንም፣ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ለሚከሰቱት ተደጋጋሚ ድርቅ፣ ጎርፍ፣ የመሬት መንሸራተት፣ የደን መመናመንና የመሬት መራቆት በእጅጉ ተጋላጭ ናት።

እነዚህ ተግዳሮቶች በዝናብ ጥገኛ በሆነው ግብርና፣ በምግብ ዋስትና፣ በውሃ ሀብታችን እና በገጠሩ ማኅበረሰብ የኑሮ ሁኔታ ላይ ቀጥተኛ ስጋት የደቀነ ሁኗል።

ኢትዮጵያ ቀደም ብላ የጀመረቻቸው የአየር ንብረት ለውጥን የሚገቱና የተፈጥሮን ሚዛን የሚጠብቁ ተግባራት ለውጥ እያስመዘገቡ ናቸው፡፡

ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ የሚከሰተውን ድርቅ እና የደን መመናመንን ለመግታት ባደረገችው ጥረት፣ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር አማካኝነት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከልና የደን ሽፋኗን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ በዓለም አቀፍ ደረጃ አርአያ መሆን ችላለች።

ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሐግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋኑን ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደግ ችላለች፡፡

በሌላ በኩል ሀገሪቱ የምታመነጨውን የኤሌክትሪክ ኃይልን ከታዳሽ የኃይል ምንጮች በማመንጨት ካርቦን-አልባ ኢኮኖሚን ለመገንባት በምታደርገው ጥረት በአፍሪካ ግንባር ቀደም ሀገር ሆናለች።

የተለያዩ የፕላስቲክ ውጤቶች በምድር ላይ፤ በውሃማ አካላት የሚያደርሱትን ብክለትና በሰው ልጅ ጤና ላይ የሚያስከትሉትን ጉዳት ለመቀነስ የፕላስቲክ ውጤቶች አጠቃቀም ላይ እገዳ በመጣል ለውጥ እንዲመጣ ጉዞም ጀምራለች፡፡

በየከተሞች እየተሰሩ ያሉ የከተማ ኮሪደር ልማቶች ከአረንጓዴ አትክልቶችና ጋር ተጣምረው መሰራታቸው፤ በአዲስ አበባ የተጀመሩ የወንዝ ዳርቻ ልማቶች የውሃማ አካላትን ብክነት በመቀነስ በኩል ፍሬያማ ስኬቶችን እያስመዘገቡ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ቀኑን አስመልክቶ በሰጠው ማብራሪያ በ2018 ዓ.ም የችግኞችን የመጽደቅ መጠን በማሻሻል፣ ዘላቂ የተፋሰስ ልማትና የረጅም ጊዜ ሥነ-ምህዳራዊ ጥቅሞችን በማረጋገጥ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚያስፈልግ አሳስበቧል፡፡

የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የአፈር ጥበቃ፣ መስኖን ማስፋፋትና የአየር ንብረት ለውጥን ወደሚቋቋሙ አሠራሮች በመሸጋገር ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ልማት መገንባት ያስፈልጋል ብሏል፡፡

ንጹህ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ስኬታችንን መሰረት በማድረግ፣ ንጹህ ኃይልን ወደ ትራንስፖርትና ኢንዱስትሪ ዘርፍ በማስፋፋት ወደ አረንጓዴ ኢነርጂ የሚደረገውን ሽግግር ማፋጠን፤ የቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ፣ የከተማ አረንጓዴ መሠረተ-ልማትን በማጠናከርና ከከተሞች የሚወጣውን የሙቀት አማቂ ጋዝ ልህቀት በመቀነስ የአካባቢ ጥበቃ ስራችንን ማሳካት ይጠበቅብናል፡፡

የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ተጽዕኖ ለመቋቋም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብርን ማጠናከር፤ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ፤ ዘላቂ የቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ ሥርዓትን መከተል፤ የተጀመረውን የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄን ማስፋት፤ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡና የሚበሰብሱ የእቃ መያዣዎችን መጠቀም ያስፈልጋል፡፡

ይህንን ስናደርግ ለሰው ልጅ የተመቹ፤ ለኑሮ ተስማሚና ለቀጣይ ትውልድም ንጹህ አካባቢን ማስረክበ እንችላለን፡፡ተፈጥሮን ወደነበረችበት መመለስ ንጹሕ አየርና ውሃ ለማግኘት፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ የአየር ንብረት መዛባትን ለመግታትና ብዝሃ-ሕይወት ለመጠበቅ ይረዳል። በኢኮኖሚ በኩልም አረንጓዴ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር ዘላቂ ልማትን ያረጋግጣል።

የአካባቢ ቀን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ እ.ኤ.አ. በ1972 ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ሰኔ 5 ቀን 1973 በይፋ መከበር እንደጀመረ መረጃዎች ያሳያሉ። ዘንደሮም በዓለም አቀፍ ደረጃ በአዘርባጃን አስተናጋጅነት እየተከበረ ነው፡፡

#ኢፕድ

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው የዜጎች ተሳትፎ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ዕድገት ያመላከተ ነው - ምሁራን ግንቦት 24 የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ የ...
05/06/2026

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው የዜጎች ተሳትፎ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ዕድገት ያመላከተ ነው - ምሁራን

ግንቦት 24 የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ የታየበት ሆኖ አልፏል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ዜጋ እና ሥነ ምግባር መምህሩ አቶ ብሩክ ደስታ በምርጫው የታየው ጠንካራ የዜጎች የፖለቲካ ተሳትፎ በሀገራችን የፖለቲካ ምህዳር እየሰፋ መምጣቱን እና የሕዝቡ የዴሞክራሲ ግንዛቤ ማደጉን የሚያሳይ ነው ብለዋል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብ አስተዳደር መምህር እና የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አየለ አዳቶ በበኩላቸው፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች በቅድመ ምርጫ ወቅት ያደረጉት ስልጡን የሐሳብ ክርክር ዜጎች በንቃት ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እንዲወጡ በማነሳሳት በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን ገልጸዋል።

በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ አሸናፊ የሚሆነው በሕዝብ አመኔታ ያገኘ ፓርቲ ነው ያሉት ምሁራኑ፣ አዲሱን መንግሥት የሚመሠርተው ፓርቲ ሕዝብ የሰጠውን አደራ ለመወጣት ዝግጁ መሆን እንዳለበትም ለኢቢሲ በሰጡት አስተያየት አንስተዋል።

በምርጫ ሂደት አሸናፊም ሆነ ተሸናፊ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሕዝብ ድምፅ ወኪሎች በመሆናቸው፣ በቀጣይ የሀገር እና የሕዝብ ፍላጎት በሆኑ ብሔራዊ አጀንዳዎች ላይ በጋራ መሥራት እንደሚገባቸውም ምሁራኑ አሳስበዋል።

በተጨማሪም የምርጫው ሂደት ሙሉ በሙሉ እስኪጠናቀቅ እና የመጨረሻው ውጤት ይፋ እስኪደረግ ድረስ ኅብረተሰቡ የጀመረውን ሰላማዊ አካሄድ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።



ሸካ ቴቪ ማሻ 28/09/2018
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማገኘት
YouTube
https://www.youtube.com/-y7q
Telegram
https://t.me/D02MpvQ_owNDE0
Instagram
t.me/D02MpvQ_owNDE0
Tiktok
tiktok.com/
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61574375731590

ክፍፍልንና አጥፊ ፉክክርን ወደ ጋራ አጋርነት መቀየር የማይክሮሶፍት ኩባንያ በአንድ ወቅት የነበረበትን የውስጥ መከፋፈል፣ እርስ በእርስ መፎካከር እና በትዕቢት የተሞላ የአስተሳሰብ ድባብ ለው...
04/06/2026

ክፍፍልንና አጥፊ ፉክክርን ወደ ጋራ አጋርነት መቀየር

የማይክሮሶፍት ኩባንያ በአንድ ወቅት የነበረበትን የውስጥ መከፋፈል፣ እርስ በእርስ መፎካከር እና በትዕቢት የተሞላ የአስተሳሰብ ድባብ ለውጦ ወደ አዲስ የልህቀት ምዕራፍ ያሸጋገረው የሳትያ ናዴላ የለውጥ አመራር በዘመናዊ የቢዝነስ ዓለም ውስጥ እንደ ድንቅ የባህል እና የስርዓት ትንሳኤ ተምሳሌት ይወሰዳል። ናዴላ ስልጣኑን ሲረከቡ የተመለከቱት ተቋም በውስጠኛው የጠላትነት ግድግዳዎች የታጠረ እና ማናቸውንም አዲስ መረጃ እንደ ስጋት የሚመለከት ሁሉን አዋቂ የተባለ የድርጅት ባህል የተጠናወተው ነበር። እርሳቸው የጀመሩት ለውጥ የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ብቻ ሳይሆን ይልቁንም የድርጅቱን የነፍስ ክፍል የሚመስለውን የአስተሳሰብ ስርዓት መሰረት በአዲስ መልክ የመቅረጽ ሂደት ነበር።

ናዴላ የኩባንያውን ባህል ከ"ሁሉን እናውቃለን" ወደ "ሁሉን ለመማር እንጓጓለን" የሚል የዕድገት አስተሳሰብ ማሸጋገር የጀመሩት ድርጅት "አዋቂ ነኝ" ብሎ ሲያምን መማር እንደሚያቆም በመገንዘብ ነበር። በአመራራቸው ስር ስህተት እንደ ውድቀት ሳይሆን እንደ ትልቅ የመማሪያ ሂደት መታየት የጀመረ ሲሆን ይህ የጉጉት ባህል በድርጅቱ ውስጥ የመጠየቅና የመማር ነጻነትን ፈጠረ። አንድ መሪ የድርጅቱን የስርዓት አቅም የሚለካው በተሰበሰበ ውጤት ብቻ ሳይሆን ሰራተኞች በስራ ቦታ ላይ የመጠየቅ ነጻነት ምን ያህል እንዳላቸው በሚገልጸው የመማሪያ ድባብ መሆኑን ናዴላ በተግባር አሳይተዋል።

ከዚህም ባሻገር እንደ ዊንዶውስ፣ ኦፊስ እና ክላውድ ያሉ የተለያዩ የኩባንያው ክፍሎች እርስ በእርስ የሚፎካከሩበትን አጥፊ ውድድር ወደ አጋርነት በመቀየር የድርጅቱን ውስጣዊ ግድግዳዎች የማፍረስ ትልቅ ስራ ሰርተዋል። "እኔ የተሻልኩ ነኝ" የሚለውን የግል ትርፍ አሳዳጅ ግብ ወደ "እኛ የተሻልን ነን" የሚል የጋራ የድርጅት ራዕይ በመቀየር ክፍሎች ለጋራ ዓላማ የሚተባበሩበት የስርዓት አሰላለፍ ፈጠሩ።

ናዴላ ቀደም ሲል ማይክሮሶፍት እንደ ተፎካካሪ ወይም እንደ ጠላት ይይዛቸው የነበሩትን እንደ ሊነክስ ያሉ ክፍት ምንጭ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ውስጥ በማካተት ኩባንያውን ከዓለም ተነጥሎ ከሚኖርበት የዝግ ስርዓት ወደ አካታች የኢኮ-ሲስተም ቀይረውታል። ይህ የርህራሄና የክፍት አመለካከት አመራር ድርጅቱ ከዓለም ጋር የሚስማማና ከአዳዲስ አመለካከቶች ጋር የሚዋሃድ መሆኑን ያረጋገጠ ስትራቴጂ ነበር። መሪው ድርጅቱን ከሌሎች አመለካከቶች ጋር ካላዋሃደ በራሱ ግድግዳ ውስጥ ተዘግቶ እንደሚቀር በመገንዘብ ሰብአዊነትንና አካታችነትን በድርጅታዊ ስትራቴጂው ውስጥ ዋና መለያ አደረጉት።

የሳቲያ ናዴላ ስኬት የሚያስተምረው እውነት መሪው የተቋሙን ነፍስ በመቀየር መማርን እንደ መሠረታዊ የስራ ሂደት መቀበል እንዳለበት ነው። የተቋምን ውስጣዊ ግድግዳ ያላፈረሰ መሪ ለወደፊት የሚመጣውን ፈጠራና ዕድገት በእነዛው የቆዩ ግድግዳዎች ውስጥ ሰባብሮ እንደሚቀረው በመገንዘብ ባህልንና አመለካከትን መሠረት ያደረገ የአመራር ለውጥ ማምጣት የዘመኑ ግዴታ ነው።

#የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ

የዞኑ ሕዝብ በምርጫው ያሳየውን ቁርጠኛ አቋም በልማት መካስ ያስፈልጋል ተባለ። በሸካ ዞን ሕዝቡ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት ያሳየው ተነሳሽነት በልማቱም እንዲደገም  መስራት እንደሚገባ ተገል...
04/06/2026

የዞኑ ሕዝብ በምርጫው ያሳየውን ቁርጠኛ አቋም በልማት መካስ ያስፈልጋል ተባለ።

በሸካ ዞን ሕዝቡ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት ያሳየው ተነሳሽነት በልማቱም እንዲደገም መስራት እንደሚገባ ተገልጿል።

በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ እስከ ምርጫው ድረስ ሂደቱ ሰላማዊ ፣ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ እንዲሆን በብልጽግና ፓርቲ በሁሉም መዋቅሮች የተሰሩ ተግባራትን በሚመለከት በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ ምክክር ተደርጓል።

በወቅቱ የመወያያ ሪፖርት ያቀረቡት የ5ቱ መዋቅር የስራ ኃላፊዎች እንደጠቆሙት ምርጫው በሰላማዊና በዴሞክራሲያዊና እሴቶችን ባሟላ መልኩ መከናወኑን ተናግረው ለቀጣይ በሕዝቡ ዘንድ በትኩረት ምላሽ የሚሹ የመሰረተ ልማት አፈጻጸም ችግሮች ልዩ ትኩረት የሚሹ ስለመሆኑም ገልፀዋል።

በ7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ምቹ የፉክክር ምህዳር ከመፍጠር ባሻገር በየደረጃው የሚገኘው መላው የዞኑ ህብረተሰብ በምርጫው ተሳታፊ እንዲሆን በተሰራው ስራ የተሻለ ተግባር መፈፀሙን ተናግረዋል ።

በዞኑ በብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቢይ ሀልቶ ያለምንም የፀጥታ ችግር ምርጫው መጠናቀቁ ትልቅ ስኬት መሆኑን ተናግረው በዞኑ ሰባት የፖለቲካ ፓርቲዎች መሳተፋቸውንም ተናግረዋል።

በከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በወቅቱ እንደገለፁት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዞኑ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ያለምንም የፀጥታ ስጋት በሰላማዊ፣በዴሞክራሲያና ፍትሐዊ መንገድ እንድጠናቀቅ የዞኑ ህብረተሰብና ባለድርሻ አካላት ላሳዩት ቁርጠኛ አቋም አድናቆት ችረዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ የነበረው የተቀናጀ ስራ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረው ለቀጣይ ትኩረት ለሚሹ የህብረተሰብ ጥያቄዎች መላሽ ለመስጠት በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

በዚህም የሕዝብን አመኔታ ይዞ ለመቀጠል መሠረታዊ የህዝብ ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ መመለስ፣ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ማፋጠን፣ የመልካም አስተዳደር ክፍተቶችን መቅረፍ የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ መሆኑን አክለዋል ።

በመድረኩ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞና የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የሁሉም መዋቅር አመራሮች ተሳትፈዋል።

ዘጋቢ:ምንታምር አስፋው

ሸካ ቴቪ ማሻ 27/09/2018
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማገኘት
YouTube
https://www.youtube.com/-y7q
Telegram
https://t.me/D02MpvQ_owNDE0
Instagram
t.me/D02MpvQ_owNDE0
Tiktok
tiktok.com/
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61574375731590

የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ እና ግልጽ በሆነ መልኩ ተካሂዷል - የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማሕበር የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ እና ግልጽ በሆነ መንገድ ተካሂዷል አለ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች...
04/06/2026

የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ እና ግልጽ በሆነ መልኩ ተካሂዷል - የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማሕበር

የምርጫ ሂደቱ ሰላማዊ እና ግልጽ በሆነ መንገድ ተካሂዷል አለ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማሕበር።

ማሕበሩ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎና ደኅንነት ለመገምገም ያከናወነውን የምልከታ ሥራ መሠረት ያደረገ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።

በዚህም በበጎ ፈቃደኝነት የተሰማሩ 60 ታዛቢዎችን በዘጠኝ ክልሎችና በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኙ 136 የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ላይ ማሰማራቱን ገልጿል።

በምርጫው ላይ የታዛቢ ቡድኑ ምልከታ ባደረገባቸው ጣቢያዎች በአብዛኛዎቹ ሰላማዊ እና ግልጽ በሆነ መልኩ የምርጫው ሂደት መጠናቀቁን አመልክቷል።

በምርጫ ጣቢያዎች የነበረው አጠቃላይ ሁኔታ ሁሉንም ያካተተና ስልታዊ የሆኑ መዋቅራዊ ጥሰቶች ያልታዩበት መሆኑንም ባወጣው መግለጫ አረጋግጧል።

በሂደቱ የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ በግልጽ የታየ በተለይም ነፍሰ ጡር እናቶች፣ የሚያጠቡ ሴቶች፣ አረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ ተሰጥቷቸው ድምፅ እንዲሰጡ የተደረጉበት አዎንታዊ አሠራር ተስተውሏል ነው ያለው።

ማሕበሩ አሁን ያወጣው ሪፖርት የመጀመሪያ ደረጃ መግለጫ መሆኑን በመጠቆም ከምርጫ በኋላ ያለውን ሁኔታ መከታተሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልና ሙሉ የመረጃ ትንተናን ያካተተ የመጨረሻ ሪፖርቱን ወደፊት ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማሕበር የኢትዮጵያ ሕዝብ መሪዎቹን ለመምረጥ ሕገ-መንግሥታዊ መብቱን ለመጠቀም ያሳየው ተነሳሽነት የሚደነቅ እንደሆነም አመልክቷል።



ሸካ ቴቪ ማሻ 27/09/2018
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማገኘት
YouTube
https://www.youtube.com/-y7q
Telegram
https://t.me/D02MpvQ_owNDE0
Instagram
t.me/D02MpvQ_owNDE0
Tiktok
tiktok.com/
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61574375731590

የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ሪፎርም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት የሀገር ውስጥና የውጭ ጠላቶች ሴራዎችን በተግባር ማክሸፉ ተገለጸ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፀ...
04/06/2026

የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ሪፎርም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት የሀገር ውስጥና የውጭ ጠላቶች ሴራዎችን በተግባር ማክሸፉ ተገለጸ

የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፀጥታና ደኅንነት አፈፃፀም ሪፖርት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መስሪያ ቤት ተገምግሟል፡፡

በገምገማ መድረኩ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል እንደገለጹት፤ የጋራ ግብረ ኃይሉ በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫው ወቅትና ከምርጫ በኋላ ያሉ ሥራዎችን እንደ ሀገር ዕቅድ አውጥቶ በቅንጅት በመመራቱ እንዲሁም የተናበበና ሰላምን ለማፅናት ጀግንነት የታየበት ተግባር በመፈፀሙ ምርጫው በሰላም ሊጠናቀቅ ችሏል፡፡

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በመንግሥት ትኩረት ተሰጥቶት በፀጥታና ደህንነት ተቋማት ላይ በተሰራው ሪፎርም አሁን ላይ በተጨባጭ ትላልቅ ተልዕኮዎችን መሸከም የሚችሉ የፀጥታ ተቋማት መፈጠራቸውን በምርጫው ላይ የተመዘገበው ውጤት ማሳያ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

የጋራ ግብረ-ኃይሉ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማደናቀፍ በሀገር ውስጥና በውጭ ጠላቶች የተቀናጀውን ከፍተኛ ሴራ ያከሸፈና የሀገርን ሉዓላዊነት ያረጋገጠ በመሆኑ የሪፎርሙ ውጤት በተግባር የተለካበት መሆኑን ኮሚሽነር ጀነራሉ አብራርተዋል፡፡

እንደ ፀጥታ ተቋም መኩራትና መመካት ያለብን በኢትዮጵያ ሕዝብ ነው ያሉት ኮሚሽነር ጀነራሉ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሀገሪቱ ላይ እየሆነ ያለውን ተረድቶ፣ ሁሉንም በሚዛን አስቀምጦ፣ በምርጫው ቀን የሀገር አንድነት እና ሉአላዊነትን ያጸና ታላቅ ሕዝብ መሆኑን ያረጋገጠበት ምርጫ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ሕዝቡ ከዚህ በኋላ መንግሥት በካርድ እንጂ በጥይት አይሆንም የሚል መልዕክት ማስተላለፉንም አክለዋል፡፡

በቀጣይም በሽብርተኞችና በፅንፈኞች ላይ የተጀመረው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይሉ አስታውቋል፡፡

የምርጫው ውጤት ታውቆ አዲስ የመንግሥት ምስረታ እስከሚከናወን እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ያሉ ሕዝባዊና መንግስታዊ ሁነቶች በስኬት እንዲጠናቀቁ የፀጥታ ሥራው ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም የጋራ ግብረ-ኃይሉ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

ሸካ ቴቪ ማሻ 27/09/2018
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማገኘት
YouTube
https://www.youtube.com/-y7q
Telegram
https://t.me/D02MpvQ_owNDE0
Instagram
t.me/D02MpvQ_owNDE0
Tiktok
tiktok.com/
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61574375731590

ምክር ቤቱ የአየር አገልግሎት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጸደቀ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ በተካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባው ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያ...
04/06/2026

ምክር ቤቱ የአየር አገልግሎት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጸደቀ

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ በተካሄደው 23ኛ መደበኛ ስብሰባው ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያደረገቻቸውን የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ አጽድቋል፡፡

የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማሕዲ (ዶ/ር) የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆችን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳቦች ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡

የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆቹ ኢንቨስትመንትን በመሳብና የአየር ትራንስፖርት መዳረሻዎችን በማስፋት ለሀገራችን የአየር ትራንስፖርትና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ያላቸው ሚና ወሳኝ መሆኑን ምክትል ሰብሳቢው አስረድተዋል፡፡

ከአየር አገልግሎት ስምምነቶቹ መካከል በኢትዮጵያ መንግሥትና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የተፈረመው አንዱ ሲሆን፣ ስምምነቱ ለአየር መንገዶች ወደ ተመረጡ መዳረሻዎች በቀጥታ ለማረፍና ምቹ የአቪዬሽን አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። ይህን የአየር አገልግሎት ረቂቅ አዋጅ ምክር ቤቱ አዋጅ ቁጥር 1417/2018 አድርጎ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል፡፡

በመቀጠል በአንጎላ ሪፐብሊክ እና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል የተፈረመው የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጅ ለምክር ቤቱ የቀረበ ሲሆን፣ ስምምነቱ በሀገራቱ መካከል ያለውን ረዥም ዘመናት ያስቆጠረ ግንኙነት ለማሳደግ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ፈትሂ ማሕዲ (ዶ/ር) አስረድተዋል፡፡

በተመሳሳይ ምክር ቤቱ ይህን ረቂቅ አዋጅ፤ አዋጅ ቁጥር 1418/2018 አድርጎ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል፡፡

በኢትዮጵያ መንግሥት እና በባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ መካከል የተደረገው የአየር አገልግሎት ስምምነት በአገራቱ መካከል እያደገ የመጣውን የአየር ትራንስፖርት ፍሰት ከግምት ያስገባ መሆኑን ምክትል ሰብሳቢው ፈትሂ ማሕዲ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

ይህም የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ፣ በንግድና ቱሪዝም እና የውጭ ምንዛሬ ለአገራችን በማስገኘት ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በተመሳሳይ ምክር ቤቱ ይህን ረቂቅ አዋጅ፤ አዋጅ ቁጥር 1419/2018 አድርጎ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል፡፡

ሌላው በምክር ቤቱ የጸደቀው የአየር አገልግሎት ረቂቅ አዋጅ፤ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት መካከል የተደረገው ስምምነት ሲሆን፣ ያለ በረራ ድግምግሞሽ ገደብ የጭነት በረራዎችን ማከናወን ጨምሮ ለበረራ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን ከጉምሩክ ቀረጥ ነፃ ማስገባትን የሚያካትት በመሆኑ የበረራ ወጪን እንደሚቀንስ ፈትሂ ማሕዲ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

በተመሳሳይ መልኩ ምክር ቤቱ ይህን ረቂቅ አዋጅ፤ አዋጅ ቁጥር 1420/2018 አድርጎ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል፡፡

በአጠቃላይ የአየር አገልግሎት ስምምነቶቹ የኢትዮጵያን ጥቅም የሚያስጠብቁና በዘርፉ በቀጠናው ያላትን ሚና በማጉላት ተጠቃሚነቷን የሚያሳድጉ እንደሆነም መጠቆሙን የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል፡፡

በሁሉም መመዘኛዎች ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ የምርጫ ሂደት ነው-የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም መመዘኛዎች ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ የምርጫ ሂደ...
04/06/2026

በሁሉም መመዘኛዎች ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ የምርጫ ሂደት ነው-የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም መመዘኛዎች ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ የምርጫ ሂደት መሆኑን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ ገለጹ።

አጠቃላይ የምርጫ ሂደቱንና የዜጎችን ተሳትፎ በተመለከተ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ የምርጫ ሂደቱ ከመጀመሪያው ጀምሮ በርካታ ፓርቲዎችን በማሳተፍ በሃሳብ ክርክር የዘለቀና ድምፅ ለመስጠትም በርካታ ዜጎች የተመዘገቡበት መሆኑን ገልጸዋል።

በድምጽ አሰጣጡም ዜጎች ዝናብ፣ብርድና ፀሃይ ሳይበግራቸው ከማለዳ እስከ ሌሊት ድምፅ የሰጡበት ታሪካዊ ክስተት መሆኑን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉንም አሳታፊ ባደረገ መልኩ በሰላም እንዲጠናቀቅ የጋራ ምክር ቤቱ በትብብር ሲሰራ መቆየቱን አንስተዋል።

በመሆኑም ምርጫው በሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሂደት ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የምርጫ ሂደቱ እንደ አጠቃላይ የተሳካ መሆኑን ገልጸው፥ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል መፎካከሩ እንዳለ ሆኖ በቀጣይ ሀገርን በመገንባት ሂደት ውስጥ በጋራ መቆም እንደሚገባም ጠቁመዋል።

Address

Sheka Zone
Masha
0000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sheka TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category