27/08/2025
ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ!
የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በመቀሌ አጥቢያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ህብረት መዘምራን በትግርኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን “ሓገር ስለዘላትኒ” [ሐገር ስላለችን] የተሰኘውን የህብረት ዝማሬ አልበም ሲያቀርብላችሁ በታላቅ ደስታ ነው።
በቤተክርስቲያን የዝማሬ ጸጋ እየበዛና እያደገ፣ በገዛ ደሙ ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅቶ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ ያደረገው ኢየሱስ በተለያዩ ቋንቋዎች ለቅዱሳን መታነጽና ለራሱ ክብር የሚሆኑ ዝማሬዎችን በሌሊት ለቅዱሳኑ እየሰጠ ስላለ እጅግ ደስ ይለናል።
እጅግ አድካሚ በሆነው የዝማሬ አልበም ስራ ውስጥ ዝማሬዎቹን ከመቀበል አንስቶ፣ በመላው ዝግጅት ውስጥ በጸጋ፣ በችሎታ እንዲሁም በጸሎትና በገንዘብ በተለያየ መንገድ የተሳተፉትን ወንድሞችና እህቶችን ሁሉ የቤተክርስቲያን አምላክ ኢየሱስ በማያልቀው በረከት እንዲባርክ ጸሎታችንም ምኞታችንም ነው።
አልበሙ በቅርብ ቀናት ውስጥ በApostolic Songs መተግበሪያ ላይ ዝግጁ የሚሆን ሲሆን ቅዱሳን ሁሉ ዝማሬዎቹን በተለያዩ የግዢ አማራጮች በማውረድ ጸጋውን፣ ቤተክርስቲያንን እና አገልግሎቱን ትደግፉ ዘንድ በኢየሱስ ፍቅር እናሳስባለን።
የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን
ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል
ነሐሴ 2017 ዓ.ም