Adoniyas Belete

Adoniyas Belete ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው፥”
— ማርቆስ 12፥29

27/08/2025

ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ!

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በመቀሌ አጥቢያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ህብረት መዘምራን በትግርኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን “ሓገር ስለዘላትኒ” [ሐገር ስላለችን] የተሰኘውን የህብረት ዝማሬ አልበም ሲያቀርብላችሁ በታላቅ ደስታ ነው።

በቤተክርስቲያን የዝማሬ ጸጋ እየበዛና እያደገ፣ በገዛ ደሙ ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅቶ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ ያደረገው ኢየሱስ በተለያዩ ቋንቋዎች ለቅዱሳን መታነጽና ለራሱ ክብር የሚሆኑ ዝማሬዎችን በሌሊት ለቅዱሳኑ እየሰጠ ስላለ እጅግ ደስ ይለናል።

እጅግ አድካሚ በሆነው የዝማሬ አልበም ስራ ውስጥ ዝማሬዎቹን ከመቀበል አንስቶ፣ በመላው ዝግጅት ውስጥ በጸጋ፣ በችሎታ እንዲሁም በጸሎትና በገንዘብ በተለያየ መንገድ የተሳተፉትን ወንድሞችና እህቶችን ሁሉ የቤተክርስቲያን አምላክ ኢየሱስ በማያልቀው በረከት እንዲባርክ ጸሎታችንም ምኞታችንም ነው።

አልበሙ በቅርብ ቀናት ውስጥ በApostolic Songs መተግበሪያ ላይ ዝግጁ የሚሆን ሲሆን ቅዱሳን ሁሉ ዝማሬዎቹን በተለያዩ የግዢ አማራጮች በማውረድ ጸጋውን፣ ቤተክርስቲያንን እና አገልግሎቱን ትደግፉ ዘንድ በኢየሱስ ፍቅር እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን
ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል
ነሐሴ 2017 ዓ.ም

ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው::🖍 መክብብ 3:-11
07/08/2025

ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው::
🖍 መክብብ 3:-11

Can't wait
12/06/2025

Can't wait

ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ!

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በዘማሪ አቤንኤዘር ፈቃዱ የተዘጋጀውን ቁ. 2 [እጠጋለሁ ወዳንተ] የዝማሬ አልበም ሲያቀርብላችሁ በታላቅ ደስታ ነው።

እግዚአብሔር በቤተክርስቲያን በኩል ለራሱ ክብር እና ለቅዱሳን መታነጽ በሚሆኑ የዝማሬ ጸጋን ጨምሮ በተለያየ ጸጋ እየባረከ ስላለ እጅግ ደስ ይለናል።

በዚህ አድካሚ የዝማሬ አልበም መዝሙሮቹን ተቀብሎ በስጦታ ለቤተክርስቲያን ያበረከተውን ዘማሪ አቤንኤዘር ፈቃዱን ጨምሮ በተለያየ መንገድ የተሳተፉትን ሁሉ የቤተክርስቲያን አምላክ ኢየሱስ በማያልቀው በረከት እንዲባርክ ጸሎታችንም ምኞታችንም ነው።

አልበሙ በቅርብ ቀናት ውስጥ በApostolic Songs መተግበሪያ ላይ ዝግጁ የሚሆን ሲሆን ቅዱሳን ሁሉ ዝማሬዎቹን በተለያዩ የግዢ አማራጮች በማውረድ ጸጋውን፣ ቤተክርስቲያንን እና አገልግሎቱን ትደግፉ ዘንድ በኢየሱስ ፍቅር እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን
ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል
ሰኔ 2017 ዓ.ም

◉ ከፍ ካለው ነገራችን የሚልቀውና  የሚበልጠው የሁሉ አለቃ የሆነው አንዱ ኢየሱስ አለ። ◎    ✍በኑሮአችን ና በምናሳልፍቸው ጊዜያት የእያንዳንዳችንን የሆነ እኛ የማንችለው ነገር ሊኖር ይች...
06/06/2025

◉ ከፍ ካለው ነገራችን የሚልቀውና የሚበልጠው የሁሉ አለቃ የሆነው አንዱ ኢየሱስ አለ። ◎

✍በኑሮአችን ና በምናሳልፍቸው ጊዜያት የእያንዳንዳችንን የሆነ እኛ የማንችለው ነገር ሊኖር ይችላል፣ ነገር ግን አንድ ማስተዋል ያለብን ነገር ግን ቢኖር የኛን የመኖራችን ተስፍን ሰንቆ ይዞ ያለውን ኢየሱስን ደግመን ሁልግዜ ተስፍ ስናደርገው እርሱ አያሳፍርም ። ከፍ ካለው ነገራችን የሚልቀውና የሚበልጠው የሁሉ አለቃ የሆነው አንዱ ኢየሱስ አለ።🙏 እግዚአብሔር በጊዜው ከፍ ያደርገናል።

✉️ Adoni

ኦሪት ዘዳግም 3:3 አምላካችን እግዚአብሔርም ደግሞ የባሳንን ንጉሥ ዐግን ሕዝቡንም ሁሉ በእጃችን አሳልፎ ሰጠን፤ ....አንድ ሰው እንኳ አምልጦ አልቀረለትም።👏 ክብር ሁሉ ለኢየሱስ ይሁን!!...
19/05/2025

ኦሪት ዘዳግም 3:3
አምላካችን እግዚአብሔርም ደግሞ የባሳንን ንጉሥ ዐግን ሕዝቡንም ሁሉ በእጃችን አሳልፎ ሰጠን፤ ....አንድ ሰው እንኳ አምልጦ አልቀረለትም።👏 ክብር ሁሉ ለኢየሱስ ይሁን!!
Apostolic church

Address

Mekelle

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Adoniyas Belete posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share