Mizan Media Network - MMN

Mizan Media Network - MMN Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mizan Media Network - MMN, Media/News Company, Mizan Teferi.
(1)

ቤተሰብ ይሁኑ የሀገራችንን መልካ ምድር እንወቅ እናሳውቅ መልካምነት ለራስ ነውና።

በፈጣንና ወቅታዊ መረጃ የበለጸገ ማህብረሰብ እንፈጥራለን!!! #𝗠𝗠𝗡
ሚዛን ሚዲያ ኔትዎርክ
𝐌𝐢𝐳𝐚𝐧 𝕞𝕖𝕕𝕚𝕒 𝗻𝗲𝘁𝘄𝗼𝗿𝗸

ቴሌግራም ይቀላቀሉን
https://t.me/Mizanmedianetwork

የኤልሳቤጥ ደስታ ጉዞ የጽናት፣ የክብር፣ እና የማይደበዝዝ የኢትዮጵያ ውበት አስደናቂ ታሪክ ነው።በተፈጥሯዊ ውብ ቆዳዋ፣ በልዩ ግርማዋ እና በራስ መተማመኗ፣ ኤልሳቤጥ የአዲሱን ትውልድ የኢትዮ...
31/07/2026

የኤልሳቤጥ ደስታ ጉዞ የጽናት፣ የክብር፣ እና የማይደበዝዝ የኢትዮጵያ ውበት አስደናቂ ታሪክ ነው።

በተፈጥሯዊ ውብ ቆዳዋ፣ በልዩ ግርማዋ እና በራስ መተማመኗ፣ ኤልሳቤጥ የአዲሱን ትውልድ የኢትዮጵያ ሞዴሎች በኩራት ትወክላለች። በሁሉም የምትሳተፍባቸው የብራንድ ዘመቻዎች የኢትዮጵያን ባህል፣ ልዩነት እና ልቀት ለዓለም ታስተዋውቃለች፣ በስራዋም ብዙዎችን ታነሳሳለች።

ኤልሳቤጥ በBN Advertising & Talent Management Company ብቸኛ አስተዳደር ስር ያለች ተሰጥኦ ሲሆን፣ በታዋቂው በጎ አድራጊ ማስተር አብነት ከበደ ጋር በመተባበር ይህ ፕሮጀክት ተከናውኗል።

የግብይት አማካሪ: ናትናኤል ዘሪሁን | NZ Communications
ፎቶግራፍ: Miki Photo (Fitle Picture) 📸
ሜካፕ: Marzel 💄
ስታይሊስት እና አርት ዳይሬክተር: Hemen ✨

ውበትን ከዓላማ ጋር፣ ተሰጥኦን ከራዕይ ጋር፣ ኢትዮጵያንም በኩራት እናክብር። 🇪🇹❤️

የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች የተማሩበትን ዩኒቨርሲቲ ለመጎብኘት ማቀዳቸውን ገለጹ።በቅርቡ በአዲስ አበባ የተገናኙ የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች የተማሩበትን ዩኒቨርሲቲ ...
31/07/2026

የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች የተማሩበትን ዩኒቨርሲቲ ለመጎብኘት ማቀዳቸውን ገለጹ።

በቅርቡ በአዲስ አበባ የተገናኙ የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች የተማሩበትን ዩኒቨርሲቲ ለመጎብኘት ማቀዳቸውን ገለጹ።

በተለያዩ ስራዎች የተሰማሩት እነዚህ 40 የቀድሞ የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አዲስ አበባ በሜራደን የባህል አዳራሽ ''እኛ የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፍሬዎች ነን '' ሲሉ የተገናኙ ሲሆን የዚህም ፕሮግራም ዋና አላማ በመረጡት ቦታ በመገናኘት የቀድሞ የዩኒቨርስቲ የማይረሳ ገጠመኞቻቸውን ማንሳት ፣ የተለያዩ አዝናኝ የሆኑ ስነጽሁፎችን በማቅረብ ከመዝናናት ባለፈ በዋናነት ለዚህ ደረጃ በእውቀትና በስነምግባር አንጾ ላበቃቸው የተማሩበት ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ እንዲሁም አቃፊ የሆነውን የአካባቢው ማህበረሰብ በማስታወስ ምስጋና ማቅረብ መሆኑን የዚሁ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ የህግ ባለሙያው ጠበቃ ኢዮብ ጎሽሜ ገልጾልናል።

ኢዮብ ጎሽሜ እንደገለጸልን የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲና የአካባቢው ማህበረሰብ የምንጊዜም ባለውለታቸው ስለመሆኑ ጠቁሞ ወደፊት በአካል ተገኝተው ለመጎብኘተ እንዲያስችላቸው ከወዲሁ አንድ አስተባባሪ ኮሚቴ መቋቋሙን ገልጿል።

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በዚህ አጋጣሚ የተማሪዎቹ የተሰባሰቡበት ዋና አላማን እያደነቀ ሌሎቹም በርካታ በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎቹ ከነዚህ የቀድሞ ተማሪዎች ተሞክሮ በመውሰድ እነሱም የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ አምባሳደርነት ሚናቸውን እንዲወጡ ይገልጻል።

የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ስራ

31/07/2026

የጠመንጃን ቋንቋ በውይይት እንተካለን | የደቡብ ምዕራቡ የሀገር ሽማግሌ እና የሶማሌው አርብቶ አደር ታሪካዊ የምክክር ምስክሮች

በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ለመጀመሪያ ጊዜ አንዲት እናት 6.4 ኪ.ግ የምትመዝን ህጻን በሰላም ተገላገለች።በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ለመጀመሪያ ጊዜ አንዲት...
30/07/2026

በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ለመጀመሪያ ጊዜ አንዲት እናት 6.4 ኪ.ግ የምትመዝን ህጻን በሰላም ተገላገለች።

በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ለመጀመሪያ ጊዜ አንዲት እናት 6.4 ኪ.ግ የምትመዝን ህጻን በሰላም ተገላገለች።

የህጻኗ እናት የስኳር ህመምተኛ መሆኗ ጉዳዩን ከባድ ቢያደርገውም ቀድሞ በመታወቁ ክትትል በማድረግ በእናቷና ህጻንዋ ላይ ምንም ጉዳት ሳይደርስ ቀኑ ሲደርስ በኦፕሬሽን ማገላገል መቻሉን የህክምና ቡድኑን የመሩት የማህጸንና ጽንስ ስፔሻሊስቱ ዶ/ር ቹቹ አረጋ ገልጸዋል።

የአማን ሻሸቃ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ሳይሉሽ ባህሩ ከ6 ዓመት በፊት 2ኛ ልጇን ስትወልድ 5 ኪ.ግ መሆኑንና በኦፕሬሽን እንደተገላገለች ገልጻለች።

ወ/ሮ ሳይሉሽ ከክትትል ጀምሮ ሳይለይ ነፍሴን አትርፎልኛል ሲሉም የማህጸንና ጽንስ ስፔሻሊስቱን ዶ/ር ቹቹ አረጋን አመስግነዋል።

መረጃው የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የሕዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ ነው።

የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ!የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነ...
30/07/2026

የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ!

የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።

"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።

ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።

ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።

የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።

ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።

እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።

በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።

ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።

ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።

ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖልና ከማላዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ አድነው ባሻው ውዳሞን በቁጥጥር ሥር አዋለየኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል እና ከ...
30/07/2026

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖልና ከማላዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ አድነው ባሻው ውዳሞን በቁጥጥር ሥር አዋለ

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል እና ከማላዊ ፖሊስ ጋር በመተባበር በበርካታ የሀገራችን ወጣቶች ላይ ከባድ ኢሰብአዊ ድርጊት ሲፈጽም የቆየውን አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ አድነው ባሻው ውዳሞን በማላዊ ሀገር በቁጥጥር ሥር እንዲውል በማድረግ በሕግ ተጠያቂ እንዲሆን ወደ ሀገራችን እንዲመጣ አድርጓል።

አድነው ባሻው ውዳሞ በቁጥጥር ሥር ሊውል የቻለው ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተለይም ከሀድያ እና ከንባታ ዞኖች በርካታ ወጣቶችን ሕይወት እንደሚያሻሽል በመሐላና በአጉል ተስፋ በማታለል በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያዘዋውር መቆየቱን ፖሊስ በሰውና በሰነድ ማስረጃ አረጋግጧል።

ተጠርጣሪው ከእያንዳንዱ ተጓዥ ከ600 ሺህ እስከ 800 ሺህ ብር የሚጠይቅ ሲሆን፤ በቅድመ ክፍያ ኢትዮጵያ ውስጥ 100 ሺህ ብር እና ከዚያ በላይ ሲቀበል መቆየቱንም የምርመራ መዝገቡ አመላክቷል።

ተጓዦችን በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ በማሻገርም በጋንቦ ጫካ ውስጥ በድብቅ በማስቀመጥ በየ 24 ሰዓት ትንሽ ሩዝ ከቁራጭ ዳቦ ጋር ብቻ በመስጠት፣ በከፍተኛ ረሃብና የውሃ ጥም እንዲሰቃዩ ከማድረጉም በላይ በሞተርና በእግር ሴሎ በረሃን ጭምር እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል ሲል ፖሊስ ገልጿል።

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተጎዦችን በሕገ-ወጥ መንገድ ናይሮቢ ከተማ ካደረሳቸውም በኋላ በአንድ ክፍል ውስጥ በማጎር፣ ተጨማሪ ገንዘብ ከቤተሰቦቻቸው እንዲያስልኩ በማስገደድ ከፍተኛ ግፍ መፈጸሙን ፖሊስ በሰውና በሰነድ ማረጃ ደርሼበታለሁ ብሏል።

ከቤተሰብ ገንዘብ ማስላክ ያልቻሉትን ተጓዦችን በዱላ በመደብደብና "እዚሁ ትሞታላችሁ" እያለ በማስፈራራት እንዲሁም በኤሌክትሪክ ንዝረት በማሰቃየት ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት በመፈጸም ተጨማሪ አንድ መቶ ሺህ ብር እና ከዚያ በላይ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ግብረ አበሮቹ በኩል በባንክ እንዲከፈለው አድርጓል ብሏል ፖሊስ።

ከዚህም ባለፈ ተጓዦቹን ከናይሮቢ ወደ ሞምባሳ፣ ከዚያም ወደ ታንዛኒያ በዕቃ መጫኛ ኮንቴነሮች፣ በተሳቢና ከኋላ ክፍት በሆኑና በሸራ በተሸፈኑ መኪኖች ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ተጓዦች በመጫን ታንዛኒያ በሚገኝ ጫካ ውስጥ ጥሎ በመጥፋት ለአሰቃቂ አደጋ ዳርጓቸዋል ሲል ፖሊስ ገልጿል።

አብዛኞቹ ወጣቶች ደቡብ አፍሪካ ሳይደርሱ በተለያዩ ሀገራት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለው በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር በመግባታቸው እስከ ሦስት ዓመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጡና እስራቱን ሲጨርሱም እስከ 170 ሺህ ብር ከፍለው ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን የፖሊስ ምርመራ መዝገብ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ባደረገው ከፍተኛ ክትትል በበርካታ የሀገራችን ወጣቶች ላይ ኢሰብዓዊ ድርጊት ሲፈጽምና የኢኮኖሚ ጉዳት ሲያደርስ የቆየውን አድነው ባሻው ውዳሞን የማላዊ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ለኢትዮጵያ አሳልፎ መስጠቱን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከሌሎች ሀገራት የፖሊስ ተቋማት ጋር በመተባበር በተመሳሳይ ወንጀል ላይ የተሰማሩትን አድኖ ለሕግ የማቅረብ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል እየገለፀ ኅብረተሰቡ በEFPApp፣ በ991 እና በSPS መረጃ በመስጠት እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።

በሐዋሳ በጣለው ከባድ ዝናብና ንፋስ የሰው ሕይወት ማለፉና የንብረት ጉዳት መድረሱ ተገለጸ
30/07/2026

በሐዋሳ በጣለው ከባድ ዝናብና ንፋስ የሰው ሕይወት ማለፉና የንብረት ጉዳት መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሚዛን አማን ወደ አዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ወደ ሚዛን አማን መደበኛ በረራ ሊጀምር መሆኑ ተገለጸ​የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ የሙከራ በረራውን በስኬት እ...
29/07/2026

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሚዛን አማን ወደ አዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ወደ ሚዛን አማን መደበኛ በረራ ሊጀምር መሆኑ ተገለጸ

​የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ የሙከራ በረራውን በስኬት እንዳጠናቀቀ ያስታወቀ ሲሆን፣ በመጪው አርብ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም (ጁላይ 31 ቀን 2026) ጀምሮ በመደበኛነት የበረራ አገልግሎቱን በይፋ እንደሚጀምር አስታውቋል።

​ይህ አዲስ የበረራ መስመር በየቀኑ በሚዛን እና በአዲስ አበባ መካከል የሚከናወን ሲሆን፣ ይህም በክልሉ የሚስተዋለውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ የአካባቢውን ኢኮኖሚ ለማነቃቃት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ይጠበቃል።

በመሆኑም ተጓዦች ትኬት መቁረጥና አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑ ተገልጿል።

29/07/2026

የሙከራ በረራውን በስኬት ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአርብ ጀምሮ መደበኛ በረራውን ከሚዛን ወደ አዲስ አበባ ፣ ከአዲስ አበባ ወደ ሚዛን ይጀምራል ፡፡
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ !!

4 የአንድ ቤተሰብ አባላት በትራፊክ አደጋ ሕይወት አለፈ‼ዛሬ ​በኦሮሚያ ክልል አለልቱ አካባቢ በደረሰ አሳዛኝ የትራፊክ አደጋ የአራት አንድ ቤተሰብ አባላት ሕይወት ወዲያውኑ ማለፉ ተገለጸ‼​...
28/07/2026

4 የአንድ ቤተሰብ አባላት በትራፊክ አደጋ ሕይወት አለፈ‼

ዛሬ ​በኦሮሚያ ክልል አለልቱ አካባቢ በደረሰ አሳዛኝ የትራፊክ አደጋ የአራት አንድ ቤተሰብ አባላት ሕይወት ወዲያውኑ ማለፉ ተገለጸ‼

​አደጋው የደረሰው አንድ ጠጠር የጫነ ሲኖትራክ ከባድ ተሽከርካሪ ከፋብሪካ ከሚወጣ ሚኒባስ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው ተብሏል።

​በሚኒባስ ተሽከርካሪው ውስጥ ይጓዙ የነበሩት ሰዎች የአንድ ቤተሰብ አባላት ሲሆኑ፣ በዚሁ አደጋ የሹፌሩ ባለቤት፣ አባቱ፣ እናቱ እና አንድ የቅርብ ዘመዳቸው ሕይወታቸው ማለፍ ተገልጿል።

ሰይፉ ኒውስ እንደዘገበው ​በሹፌሩ እና ሁለት ህፃናት ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ስለደረሰበቸው በህክምና ላይ ይገኛሉ።
ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን እመኛለሁ።

©Wasu Mohammed - Mereja

Address

Mizan Teferi

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mizan Media Network - MMN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share